en
Feedback
Shien ekawuch

Shien ekawuch

Open in Telegram
869
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1230 days
Posts Archive
በአማራ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር የሚያባብሱ እና የተለያዩ የጥፋት ተግባራትን የሚከውኑ አካላት በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው‼️ 🗣የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከትናንት ምሽት ጀምሮ በአማራ ክል
በአማራ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር የሚያባብሱ እና የተለያዩ የጥፋት ተግባራትን የሚከውኑ አካላት በቁጥጥር ሾር እየዋሉ ነው‼️ 🗣የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከትናንት ምሽት ጀምሮ በአማራ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር የሚያባብሱ እና የተለያዩ የጥፋት ተግባራትን የሚከውኑ አካላት በአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ እዝ በቁጥጥር ሾር እየዋሉ መሆኑን የኢፌዲሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ አስታወቁ። የኢፌዲሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥቷል።  የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በዋናነት በአማራ ክልል ላይ የሚተገበር ቢሆንም በየትኛው የሀገሪቱ ክፍል መንግስት የሚያደርገውን የህግ ማስከበር ተግባር ለማስተጓጎል የሚደረጉ እንቅስቃሴ ላይ እርምጃ ይወሰዳል ብሏል መግለጫው። መንግስት አሁንም ለሰላም አማራጭ ቁርጠኛ መሆኑ ያነሱት ሚኒስትሩ፣ ቡድኑ ለሰላም ምንም አይነት ፍላጎት ስለሌለው ነው የአስቸኳይ ጊዜ እንዲታወጅ ያስፈለገው። ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 https://t.me/Esattvnews

#ሰበር_ዜና! የነበልባሎ ክፍለጦር አዛዥ የነበረው ሻለቃ ጌታሁን መኮነን የሰሜን አቸፈር ወረዳ መቀመጫ የሆነችውን ሊበን ከተማን ተቆጣጠረ! ሻለቃ ጌታሁን በሁመራ ግምባር፣ ሸረሪና ላይ የነበልባሉን ክ
+2
#ሰበር_ዜና! የነበልባሎ ክፍለጦር አዛዥ የነበረው ሻለቃ ጌታሁን መኮነን የሰሜን አቸፈር ወረዳ መቀመጫ የሆነችውን ሊበን ከተማን ተቆጣጠረ! ሻለቃ ጌታሁን በሁመራ ግምባር፣ ሸረሪና ላይ የነበልባሉን ክፍለጦር እየመራ ከሕወሓት ጋር ሲዋጋ እንደነበር ይታወቃል። ቆስሎ ህክምና ላይ ቢሆንም ከሥርዓቱ ጋር አልተባበርም በማለት ዛሬ ማለዳ የሰሜን አቸፈር ወረዳን ከተማ ተቆጣጥሯል። ሻለቃ ጌታሁን የሚመራው ፋኖ በጀግናው አርበኛ አያሌው መኮነን ስም "አያሌው ብርጌድ" የሚል ስም ተሰጥቶታል። በአሁኑ ሰዓት በሊበን ከተማ ከህዝቡ ጋር በመወያየት የፋኖ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሟል። (ታደለ ጥበቡ) የቪዲዮ መረጃ በቴሌግራም ገፃችን ይመልከቱ!👇 https://t.me/Esattvnews

መረጃ ሞጣ! በሞጣ የአማራ ህዝባዊ ኃይል እና በመከላከያ መካከል አሁን በዚህ ሰዓት ከፍተኛ ውጊያ እየተካሄደ ነው። የወይን ውሃ ፋኖዎች ወደ ሞጣ በመዝለቅ እገዛ እያደረጉ ነው። በሞጣ የሚገኘው የመከላከያ ካምፕ ውስጥ ያሉ የገዥው ቡድን ሰራዊቶች ከባድ መሳሪያ ወደ ማህበረሰቡ እየተኮሱ ነው። ይሄን ኃይል ለማገዝ ከአዲስ አበባ የጠላት ጦር እየመጣ ነው። የደብረወርቅና የግንደወይን ህዝብ መንገድ እንዲዘጉላቸው ጥሪ አስተላልፈዋል። ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 https://t.me/Esattvnews

ሰበር ዜና! መከላከያ ሰራዊት በአርበኛ ዘመነ ካሴ ላይ ተኩስ ከፍቷል። በአጎራባች ወረዳዎች ያላችሁ ፋኖዎችና አካባቢ ወጣቶች ለአርበኛው እገዛ አድርጉ። ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከ
ሰበር ዜና! መከላከያ ሰራዊት በአርበኛ ዘመነ ካሴ ላይ ተኩስ  ከፍቷል። በአጎራባች ወረዳዎች ያላችሁ ፋኖዎችና አካባቢ ወጣቶች ለአርበኛው እገዛ አድርጉ። ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 *Facebook groups፦https://facebook.com/groups/610101051110031/ *ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews

ባህርዳር ..! ባህርዳር ሁሉንም የንግድ ሱቆቿን ዘጋግታለች። መንገዶቿን እየዘጋጋች ነው። ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 https://t.me/Esattvnews
ባህርዳር ..! ባህርዳር ሁሉንም የንግድ ሱቆቿን ዘጋግታለች። መንገዶቿን እየዘጋጋች ነው። ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 https://t.me/Esattvnews

በአማራ ክልል በመከላከያና በታጣቂ ሚሊሻዎች፣ ፋኖ የተነሳው ግጭት መባባሱን ተከትሎ የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ቅድሚያ መስጠት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች
በአማራ ክልል በመከላከያና በታጣቂ ሚሊሻዎች፣ ፋኖ የተነሳው ግጭት መባባሱን ተከትሎ የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ቅድሚያ መስጠት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ። መንግሥት በሚወስዳቸው እርምጃዎች ነዋሪዎች ለበለጠ ጉዳት እንዳይጋለጡ ጥንቃቄ እንዲደረግ ኢሰመኮ ሐምሌ 28/2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አሳስቧል “በአማራ ክልል ሰላም እና ደኅነነት ለማረጋገጥ መንግሥት በሚወስዳቸው እርምጃዎች ለሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ነዋሪዎች እንዳይዳረጉ ጥንቃቄ እንዲያደርግም” ኢሰመኮ ጥሪ አቅርቧል። SHARE SHARE ለሁሉም ይዳረስ🙏🙏🙏🙋‍♂️ @Esattvnews            @Esattvnews @Esattvnews            @Esattvnews

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ያለው ኹኔታ እንዳሳሰባቸው ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ጋር ትናንት ማምሻውን ባደረጉት የስልክ ውይይት ላይ መግለጣቸውን መስሪያ ቤታቸው አስታውቋል። ብሊንከን፣ የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሃት የደረሱበት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸሙ ያሳየውን እድገት በውይይቱ ላይ እንዳነሱ ተገልጧል። ብሊንከንና ጠንካራ ቁጥጥር የተዘረጋበት የምግብ ዕርዳታ ሥርጭት ሥርዓት በኢትዮጵያ በመዘርጋት አስፈላጊነት ዙሪያ ከዐቢይ ጋር ተወያይተዋል። SHARE SHARE ለሁሉም ይዳረስ🙏🙏🙏🙋‍♂️ @Esattvnews            @Esattvnews @Esattvnews            @Esattvnews

31 አመት ሙሉ በየቀኑ በየሰአቱ በየወሩ በያመቱ የተገፋ ህዝብ ፣ ከ31 አመቱ ላይ 5 አመት ሙሉ በላዮ ላይ ዕሳት የቀላቀለ በረዶ የወረደበት ህዝብ በየ መድረኩ የተሰደበ ህዝብ፣ በሚኖርበት አገሩ እ
31 አመት ሙሉ በየቀኑ በየሰአቱ በየወሩ በያመቱ የተገፋ ህዝብ ፣ ከ31 አመቱ ላይ 5 አመት ሙሉ በላዮ ላይ ዕሳት የቀላቀለ በረዶ የወረደበት ህዝብ በየ መድረኩ የተሰደበ ህዝብ፣ በሚኖርበት አገሩ እንደበግ በየቀኑ የሚታረድ ህዝብ፣ ንበረቱን ማንነቱን የተቀማ ህዝብ፣ በየ አገሩ የተላኩ አምባሳደሮች ሳይቀር በማንነቱ የገፉት ብቸኛው የ31 አመት መከራ አንጋቢ አምሓራ ብቻ ነው። ይሄ ህዝብ 30 አመት ታገሶ በ31ኛ አመቱ መገደል መገፋት መታለል መሰደብ ማንነቴን በሀይል መቀየር በቃኝ አለ እንጅ እስካሁን ድረስ የወረረው ክልል፣ የቀየረው እምነት የወረረ ብሄር የለም ለገባው የአማራ ጥያቄዎች እጅግ ቀላል ናቸው። ጦርነት አይጠቅመንም የሚሻለው ችግሮችን በሰላም መፍታት ነው። SHARE SHARE ለሁሉም ይዳረስ🙏🙏🙏🙋‍♂️ @Esattvnews @Esattvnews @Esattvnews @Esattvnews

#Amhara ዛሬ አርብ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ላይ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እና በፋኖ የታጠቁ ኃይሎች መካከል ግጭቶች ሲደረጉ መዋሉን እንዲሁም በተለያዩ ከተሞች ውጥረት መኖሩን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል። ዛሬ ጥዋት ጎንደር ላይ ተኩስ እንደነበር ፤ ፍኖተ ሰላምና ጅጋ ላይ ከፍ ያለ ግጭት እንደነበር ፤ በተለያዩ ቦታዎች ላይም የተኩስ ድምፅ ይሰማ እንደነበር፣ ተመላክቷል። በብዙ ቦታዎች አሁንም ችግሮች እንዳሉ ነዋሪዎች አመልክተዋል። ደብረታቦር፣ ወልድያ እንዲሁም ቆቦ ላይ መረጋጋት ያለ ቢሆንም አሁንም ውጥረት እንዳለ ተገልጿል። በክልሉ መዲና ' ባህር ዳር ' ላይ የተሻለ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንደነበር ፤ ገበያዎችም ተከፍተው አገልግሎት ሲሰጡ እንደነበር ያመለከተው የሬድዮ ጣቢያው ዘገባ ከባህር ዳር ከተማ ወደ ሌሎች ከተሞች ወይም ከሌሎች ከተሞች ወደ ባህር ዳር የሚያስገቡት መንገዶች በመዘጋታቸው እንቅስቃሴ የለም ብሏል። ዛሬ ፈተናቸውን የጨረሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመሄድ መንገድ በማጣታቸው በጣም መቸገራቸው ተገልጿል። ተማሪዎቹ ስልክ ስላልያዙ ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት የተቸገሩ ሲሆን በቅርብ ቤተሰብ ያላቸው አንዳንድ ተማሪዎች ቤተሰቦቻቸው ስማቸውን እያስጠሩ እየወሰዷቸው እንደነበር ተነግሯል። ዩኒቨርሲቲው የመኝታም ሆነ የምግብ አቅርቦት እነድማያቋርጥ ለተማሪዎቹ አሳውቋል። በሌላ በኩል ፤ በዛው በባህር ዳር ከተማ ሁለት ቦታ ቦምብ መፈንዳቱ የተነገረ ሲሆን ስለደረሰው ጉዳት ዝርዝር መረጃ አልወጣም ሲል ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በተመለከተ ቃላቸውን ለሬድዮ ጣቢያው የሰጡ ነዋሪዎች የተለያየ አመለካከት ያላቸው ሲሆን አንዳንዶቹ " ችግሩን የሚያባብስ ውሳኔ ነው " የሚል አቋም አላቸው ፤ ሌሎች በበኩላቸው ውሳኔው " ችግሩን ሊቀንሰው ይችላል "  ሲሉ ገልጸዋል። ከዚህ ባለፈ ግን በርካታ አስተያየት ሰጪዎች አዋጁን ከማወጅ ይልቅ የክልሉ መንግሥት እና ፌዴራል መንግሥት መሳሪያ ታጥቀው ከሚዋጉ ኃይሎች ጋር ችግሩን በንግግር እና በድርድር መፍታት አለባቸው የሚል አቋም እንዳላቸው ለሬድዮ ጣቢያው አጋርተዋል። በአማራ ክልል በርካታ አካባቢዎች የኢንተርኔት ግኙነት እንደተቋረጠ ነው። SHARE SHARE ለሁሉም ይዳረስ🙏🙏🙏🙋‍♂️ @Esattvnews            @Esattvnews @Esattvnews            @Esattvnews

#በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሚታዩ የፀጥታ ችግሮች አሳሳቢ እየሆኑ መጥተዋል "አሉ፦አቶ ደመቀ መኮንን!!! @ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ማምሻውን ይህንን መልዕክት በጽሁፍ አሰራጭተዋል። "በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሚታዩ የፀጥታ ችግሮች አሳሳቢ እየሆኑ መጥተዋል:: በመሰረቱ ብዙ ምላሽ ያላገኙ ጥያቄዎች ይኖራሉ፡፡ @እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ግን ጠቃሚው መንገድ ሰላማዊና የውይይት አግባብ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ያለው አካሄድ 1. የጥያቄዎችን መፍቻ መንገድ የሚያደናቅፍ 2. ያለንን የሚያሳጣ 3. በዘላቂነት ሊታዩ ይገባቸዋል የምንላቸውን ጉዳዮች እንዳይፈቱ የሚያወሳስብ አካሄድ ነው፡፡ @ሰላም ከሌለህ ሁሉን ታጣለህ' የሚባለውን እውነታ ከልብ በማጤን በአስተውሎት መጓዝ በሚገባን ታሪካዊ ወቅት ላይ እንገኛለን፡፡ @በየዘመኑ ብዙ ፈተናዎች እና ችግሮች ሲገጥሙ በጥበብ ተሻግረው ያሻገሩንን የአባቶቻችን ጥበብና አስተውሎት ማጥበቅ ይጠይቃል፡፡ የሀገር ሽማግሌ የጠፋበት፣ ታላቅ የሌለበት፣ መካሪ የሃይማኖት አባት የታጣበት ይመስል ሁላችንንም የሚያባላና የሚበላ አካሄድ ይስተዋላል፡፡ @የዚህ መጨረሻ በግራም በቀኝም ከውጭም ከውስጥም ላሰፈሰፉ ኃይሎች ሰርግና ምላሽ ሆኖ አቅም የሚያሳጣ፣ ክብራችንን የሚጎዳ፣ ተጋላጭነታችንን የሚያሰፋ በአጠቃላይ ሁሉንም የሚያሳጣ እንዳይሆን ያሰጋል፡፡"ከለውጡ ብዙ የጠበቅናቸው ግን ደግሞ ምላሽ ያላገኘንባቸው ያላረኩንና ሌሎች ችግሮችና ስሜቶች ይኖራሉ፡፡ @ለእነዚህ ጉዳዮች ቆም ብለን በማሰብ በሰላሙ መንገድ ዘላቂ መፍተሄ እንዲያገኙ ማድረግ ተገቢ ነው ለዚህም የሁሉም ዋስትና የሆነውን ህግና ሥርዓት በተሟላ መልኩ ማክበርና ማስከበር ይገባል፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+1

photo content

#ኤርትራ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳን ያካለለ ርዕደ-መሬት ከትናንት ማክሰኞ ማታ ጀምሮ በተደጋጋሚ መከሰቱ ተነገረ!!! @የጀርመኑ GFZ እና ቮሎካኖ ዲስከቨሪ የተባለ ድረገፅ፤ ዛሬ በተቀራራቢ ሰዓት ሁለት ርዕደ-መሬቶች መከሰታቸውን አመላክቷል። @የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ ትናንት ማታ ሁለት ሰዓት ከ15 ደቂቃ ላይ የተከሰተው ትልቅ መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ሬክተር መለኪያ 5.6 መሆኑንና ማዕከሉም (epicenter) በኤርትራ ከምፅዋ 43 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መሆኑን ገልጿል። @የርዕደ-መሬቱ ንዝረት ትናንት ማታ በኢትዮጵያ፣ ትግራይ ክልል በርዕሰ ከተማዋ መቐለ ጨምሮ በሽረ፣ ዓዲግራት፣ አክሱም፣ ዓድዋ እና ሌሎች ከተሞች ተሰምቷል። በርዕደ-መሬቱ ምክንያት በትግራይ የደረሰ አደጋ ይሩር አይኑር እስካሁን የተባለ ነገር የለም። @ያነጋገርናቸው የመቐለ ነዋሪዎች በንዝረቱ በተለይም ዕቃዎች ሲንቀሳቀሱ እና ሲወድቁ መመልከታቸው ጠቁመውናል። ትናንት ማታ ሰዓት ሰዓት ከ15 ደቂቃ ከተሰማው ርዕደ-መሬት በተጨማሪ ዛሬ ጠዋት 12 እና 2 ሰዓት አካባቢም መስተዋሉ ተነግሯል። @የስነምድር ተማራማሪዎች የአፍሪካ ቀንድ ለርዕደ-መሬት ተጋላጭ ከሚባሉ አካባቢዎች መካከል መሆኑ ይጠቁማሉ። የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር በበኩሉ ዛሬ ባወጣው መረጃ ባለፉት 24 ሰዓታት እስከ በሬክተር መለኪያ 5.6 የሚሆን ተደጋጋሚ ርዕደ-መሬት መከሰቱን እና በቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን አስታውቋል። @ርዕደ-መሬቱ ትናንትና ማክሰኞ ማታ 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ላይ እንዲሁም ዛሬ ረቡዕ ደግሞ ንጋት ላይ በተደጋጋሚ፥ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ማዕከል አድርጎ መከሰቱንም ጠቁሟል። በዚህም በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ በመግለጽ፥ በሰንዓፈ ግን አምስት ቤቶች መፍረሳቸውን አመልክቷል። @ከአንድ ወር በፊትም እንዲሁ በሬክተር መለኪያ 4.2 የሚሆን ርዕደ-መሬት መከሰቱን እና ንዝረቱም በኤርትራ እና ትግራይ አካባቢዎች መሰማቱ ይታወሳል። የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ በትናንትናው ዕለት ብቻ በመላው ዓለም 51 ርዕደ-መሬቶች መከሰታቸው መመዝቡን በድረገፁ አስታውቋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#መከላከያ ሰራዊቱ የጀመረውን ይቀጥላል እናንተ ግን መሳሪያ አስቀምጡና እንነጋገር'' ፦ዶ/ር ይልቃል ከፋለ!!! @ትንሽ ተስፋ ነበረኝ ይህ ሰውዬ በመጨረሻው ሰዓት ወደ ህሊናው ይወድቃል የሚል ቅንጣቢ ተስፋ 'እናንተን ሊገድል የዘመተው ሰራዊት የጀመረውን ይቀጥላል። @እናንተ እየተገደላችሁም ቢሆን የተረፋችሁት ከእኛ ጋር እንነጋገር' የሚለው የዚህ ሰው የዛሬ መግለጫ የክልሉም ሆነ የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት ሰላም ለመፍጠር ምንም ዓይነት ፍላጎት እንደሌላቸው የሚያሳይ ነው። @የዛሬው መግለጫ ለታሪክ ተሰንዶ መቀመጥ አለበት ነገ የፍትህ ቀን ሲመጣ ትልቅ ትርጉም አለው የአማራ ህዝብ እያደረገ ያለው ተጋድሎ ፍትሃዊና ህጋዊ መሆኑ ከምን ጊዜውም በላይ ግልጽ እየሆነ መጥቷል። @የትላንቱ የመከላከያ ሚኒስቴር መግለጫ እብሪትና ቅጥፈት የተሞላው መሆኑን ላስተዋለ ሰዎቹ ግዙፍ እልቂት ለማምጣት ቅንጣት ታክል ርህራሄ እንደሌላቸው የሚያረጋግጥ ነው። @እንግዲህ ምርጫ የለም "ወደ ኋላ የቀረ ነገር አይታይም "ከፊት ግን ነጻነት አለ!! *ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ከተናገረው *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የሁለት ልጆች "እናት በችሎት ፊት "ዳኛና "ፓሊስ" ባለበት በባሏ በስለት ተወግታ መገሏ ተሰማ!!! @በምስራቅ ሐረርጌ የበደኖ ወረዳ ፍርድ ቤት ያለፈው አርብ ሐምሌ 21/2015 በወ/ሮ ትዕግስት ልኬለው እና በባለቤታቸው አቶ ደረጀ ሰይፉ መካከል ከፍቺ በኋላ በተፈጠረው የንብረት ክፍፍል ጉዳይ ውሳኔ ለመስጠት ችሎት ተሰይሟል። @ዳኛው ውሳኔውን በንባብ ካሰሙ በኋላ ነው ያልተጠበቀውና የብዙዎችን ልብ የሰበረው ክስተት የተፈጠረው። @ወ/ሮ ትዕግስት ከቀድሞ ባላቸው ሁለት የ21 እና 17 አመት ወጣት ወንዶች ልጆችንና ንብረት ያፈሩ ሲሆን ፤ የቀድሞ ባለቤታቸውን ህልፈተ ህይወት ተከትሎ ለሁለተኛ ግዜ በመሰረቱት ትዳር ከአቶ ደረጀ ሰይፉ ጋር መኖር ቢጀምሩም በትዳራቸው ውስጥ የነበሩ አለመግባባቶች እየጠነከሩ ሄደው ለፍቺ ያደርሳቸዋል። @ይሁን እንጂ የፍቺ ሂደቱ እንዳሰቡት ሳይሆን ይቀርና በንብረት ክፍፍል ዙሪያ ፍትህ ለማግኘት በምስራቅ ሐረርጌ ዞን በደኖ ወረዳ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ። ጉዳዩን ሲመረምር የቆየው ፍርድ ቤትም ባለፈው አርብ ሀምሌ 25/2015 ለወ/ሮ ትዕግስት ይፈርድላቸዋል። @በዚህን ወቅት ነበር ያልታሰበው የሆነው፤ አቶ ደረጀ ደብቀው የያዙትን ሴንጢ በማውጣት ችሎት ውስጥ ወ/ሮ ትዕግስትን ደረታቸውን ከዛም ጀርባቸውን ደጋግመው ከወጉ በኋላ፤ ለእርዳታ በመጡት ዳኛም ላይም ሴንጢውን ወርውረው ስተዋቸዋል።ፖሊስም ደርሶም ዳኘውን ከተጨማሪ ጥቃት ታድጓቸዋል። @ወ/ሮ ትዕግስት ወደ ህክምና ቢወሰዱም እርዳታ ከማግኘታቸው በፊት ህይወታቸው አልፏል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#የፀጥታ አካላት በክልሉ ህግን ለማስከበር በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ሁሉ "ህዝቡ ድጋፍ በማድረግ የተለመደ ትብብሩን እንዲያሳይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር "ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ጥሪ ማቅረባቸው ተነገረ!!! @ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ላይ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) በመግለጫቸው ላይ እንዳሉት÷ ህግ የማስከበር ሥራ የመንግስት ሃላፊነት ነው። @በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ሰላማዊውን ህዝብ በማወክና መንገድ በመዝጋት ችግር የሚፈጥሩ አካላት የክልሉን ልማትና የህዝቡን አንድነት እየጎዱ በመሆናቸው ከእዚህ ድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ብለዋል። @የሀገር መከላከያ ሠራዊት ህግን ለማስከበር ወደ ተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ሲንቀሳቀስ የሚደረግ ትንኮሳ መቆም እንዳለበት የገለጹት ይልቃል (ዶ/ር)÷ መላው የክልሉ ህዝብም ለሠራዊቱ ድጋፍ በማድረግ የተለመደ ትብብሩን እንዲያሳይ ጥሪ አቅርበዋል። @በተለይ የሁሉም የአገሪቱ ህዝቦች ልጅ የሆነውን የመከካከያ ሠራዊት ስም ማጥፋት ተገቢነት የሌለው መሆኑን መላው ህዝብ ሊገነዘብ እንደሚገባ ተናግረዋል። @"የሀገር መከላከያ ሠራዊት የአገር ሉአላዊነትን የሚያስጠብቅ የህዝብ መከታ ነው" ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ÷ የሠራዊቱን እንቅስቃሴ ለመገደብ የሚደረጉ ጥረቶች መቆም አለባቸው ብለዋል። @በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች እየተስተዋለ ያለው ችግር ከመባባሱ በፊት ነፍጥ ማንገብ መቆም አለበት ነው ያሉት፡፡ @በየአካባቢው በሚካሄዱ የውይይት መድረኮች በመሳተፍ ሀሳብን መሞገትና ልዩነቶችን በውይይት መፍታት እንደሚገባ ማስገንዘባቸውንም ኢዜአ ዘግቧል፡፡ @የክልሉ መንግስት ከዚህ ቀደምም ችግሮችን በውይይት ለመፍታት ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰው÷ አሁንም ሰላምን ለማጠናከር በየአካባቢው ከህዝቡ ጋር እየተወያየ መሆኑን ገልጸዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#በጦርነት የሚፈታ ነገር እንደሌለ መማር ያልቻለ "መንግስት!!! @ያሳዝናል! *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group
+1
#በጦርነት የሚፈታ ነገር እንደሌለ መማር ያልቻለ "መንግስት!!! @ያሳዝናል! *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb