en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ማስጠንቀቂያ ! የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ የግንባታ ሳይቶች ከሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል ግንባታቸው ተጠናቆ ቁልፍ እንዲወሰዱ የተነገራቸው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕድለኞች ባለመምጣታቸው፣ á‰ á‰€áŠ“á‰ľ ውስጥ ቁልፍ እንዲወስዱ ማስጠንቀቂያ ሰጠ፡፡  ኮርፖሬሽኑ ቁልፍ ላልተወሰደባቸው ቤቶች የሚያደርገውን ጥበቃ እንደሚያነሳ አስታውቋል፡፡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚገኙባቸው ፕሮጀክት ሳይቶች በሙሉ የተለጠፈው የኮርፖሬሽኑ ማስጠንቀቂያ፣ የሕንፃና የቤት ቁልፍ ርክክብ ከተጀመረ ብዙ ወራት ቢቆጠሩም ነዋሪው ቤቱን ተረክቦ እያደሰና እየገባ አለመሆኑን ይገልፃል። በዚህም ምክንያት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቶች ለተለያዩ ችግሮች እየተዳረጉ በመሆናቸው፣ ነዋሪዎች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስከ የካቲት 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ መጥተው ቁልፍ እንዲረከቡ ያሳስባል፡፡  ያንብቡ : https://telegra.ph/Reporter-01-30 ምንጭ፦ ሪፖርተር

#Save_the_Children በኦሮሚያ፣ ደቡብ እና ሲዳማ ክልሎች የህፃናት አድን ድርጅት (Save the Children) በ136 ትምህርት ቤቶች ላይ የምገባ ፕሮግራም እየሰጠ መሆኑን ለኢትዮጵያ ትም
+2
#Save_the_Children በኦሮሚያ፣ ደቡብ እና ሲዳማ ክልሎች የህፃናት አድን ድርጅት (Save the Children) በ136 ትምህርት ቤቶች ላይ የምገባ ፕሮግራም እየሰጠ መሆኑን ለኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን አሳውቋል። ለ90 ሺህ ተማሪዎች በ136 ትምህርት ቤቶች ላይ በኦሮሚያ ፣ ደቡብ እና ሲዳማ ክልሎች በ4 ወረዳዎች GPE ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት በተገኘ ድጋፍ የምገባ ፕሮግራም ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የኢትየጵያ ደቡባዊ አካባቢ ማናጀር የሆኑት ዶክተር ሀይሉ ተስፋዬ ገልፀዋል። በዚህ የትምህርት ቤት የምገባ ፕሮግራም ምክንያት በርካታ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ማድረጉንና በተማሪዎች ትምህርት ውጤት እና የትምህርት ጥራት ላይ ከፍተኛ መሻሻል እንዲመጣ ማድርጉን ማናጀሩ ጨምረው ገልፀዋል። ዶክተር ሀይሉ ተስፋዬ በቀጣይ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር Save the Children ዋነኛ አላማ ያደረገው የህፃናትን ትምህርትንና የምገባ ፕሮግራም የሚደረስና ጥራቱን የመጠበቅ ተግባር እንቀጥላለን ብለዋል። ትምህርት ሚኒስቴር ስራው እንዲሳካ ለሚያደርገው ደግፍ ምስጋና አቅርበዋል። ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን @tikvahethiopia

#DireDawaUniversity የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት የሕክምና ሳይንስ ተማሪ የነበረው ታሪኩ ሶሪ ሐሙስ ጥር 19/2014 ዓ.ም እኩለ ቀን አካባቢ ራሱን ማጥፉቱን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል
#DireDawaUniversity የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት የሕክምና ሳይንስ ተማሪ የነበረው ታሪኩ ሶሪ ሐሙስ ጥር 19/2014 ዓ.ም እኩለ ቀን አካባቢ ራሱን ማጥፉቱን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። የተማሪውን ህልፈት ምክንያት ለማጣራት ከጸጥታ አካላት ጋር እየሰራ እንደሚገኝ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። የተማሪው አስክሬን ወደ አዲስ አበባ ጳውሎስ ሆስፒታል ተልኮ ምርመራ እንደተደረገበት የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የዓለም ዐቀፍና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ደቻሳ ጋንፉሬ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲው የምርመራው ውጤቱ እንደደረሰው ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ እንደሚያደርግ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። " ተማሪ ታሪኩ ታንቆ ራሱን እንዳጠፋ ነው የምናቀው " ያሉት ዳይሬክተሩ፤ "ከህልፈቱ ጋር እየተነሱ ያሉ ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ምርመራ እየተደረገ ነው" ብለዋል። የተማሪው አስክሬን ትላንት ቤተሰቦቹ ወደሚገኙበት ወለጋ ዞን ሆሩ ጉዱሩ መላኩን ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ገልጸዋል። More : @tikvahuniversity @tikvahethiopia

" ... ተለጥፎ የነበረው መልዕክት ከእውቅናዬ ውጭ ነው ፤ የምክር ቤቱንም አቋም አይወክልም " - ፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከሰዓታት በፊት በተረጋገጠ የፌስቡክ ገፁ ላይ ስለተለጠፈ
" ... ተለጥፎ የነበረው መልዕክት ከእውቅናዬ ውጭ ነው ፤ የምክር ቤቱንም አቋም አይወክልም " - ፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከሰዓታት በፊት በተረጋገጠ የፌስቡክ ገፁ ላይ ስለተለጠፈው መልዕክት አጭር መልዕክት አስተላልፏል። ምክር ቤቱ በገፁ ላይ ተለጥፎ የነበረው መልእክት ከምክር ቤቱ እውቅና ውጪ የተለጠፈ መሆኑን ገልጿል። እንዲሁም መልዕክቱ የምክር ቤቱን አቋም እንደማይወክል አሳውቋል። ም/ቤቱ በተረጋገጠ ገፁ ላይ መልዕክቱን ማን እንዳጋራውና እንዴት ሊጋራ እንደቻለ፣ ለዚህ ሚጠየቅ አካል ይኖር እንደሆነ የሰጠው ማብራሪያ የለም። @tikvahethiopia

" ... እንስሳት የሚበሉትን አጥተው አብዛኛዎቹ አልቀዋል፤ ከእንስሳትም አልፎ ለሰው ህይወትም እየሰጋን ነው " - አቶ ጎዳና ሎራ #NakorMelkaVoA በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የድሬ ነዋሪ የሆ
" ... እንስሳት የሚበሉትን አጥተው አብዛኛዎቹ አልቀዋል፤ ከእንስሳትም አልፎ ለሰው ህይወትም እየሰጋን ነው " - አቶ ጎዳና ሎራ #NakorMelkaVoA በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የድሬ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጎዳና ሎራ ባለፈው ዓመት መዝነብ የነበረበት የመኸር እና ክረምት ዝናብ ባለመዝነቡ በሰዎች እና በእንስሳት ላይ ጉዳት መድረሱን ገልፀው ፤ ተጨማሪ ጉዳት ለመከላከል ርብርብ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል። አቶ ጎዳና ሎራ ፦ " ከዝናብ እጥረት የተነሳ ድርቅ አጋጥሞናል። ክረትም የዘራነው ዘር ሳይበቅል ነው የቀረው። እንስሳትም የሚበሉትን አጥተው አብዛኛዎቹ አልቀዋል፤ ከእንስሳትም አልፎ ለሰው ህይወትም እየሰጋን ነው። ለምሳሌ እኔ 30 ከብቶችን አጥቻለው 80 የሚሆኑ ከብቶች ያለቁበትም አለ። ባለንበት ቀበሌ በድርቅ ምክንያት ከ10 በላይ ሰዎች ታመው ሰውነታቸው አብጧል። የቦረና የኑሮ መሰረት የከብት እርባታ ነው። ድርቁ እያሳደረሰው ካለው ጉዳት አንፃር በእዚህ የሚቀጥል ከሆነ የባሰ አደጋ ያጋጥመናል። መንግስታዊ የሆኑና ያልሆኑም ድርጅቶች እንዲሁም ህዝቡ ድርቁ ሊያመጣ የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ ሊረባረቡ ይገባል " @tikvahethiopia

#ATTENTION የኦሮሚያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር እና ልማት ተነሺዎች ኮሚሽን በደቡብ ምሥራቅ ኦሮሚያ በ7 ዞኖች ድርቅ መከሰቱን አሳውቋል። በድርቁ ከ800 ሺህ በላይ ሰዎች ተጎጂ መሆናቸውን
+1
#ATTENTION የኦሮሚያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር እና ልማት ተነሺዎች ኮሚሽን በደቡብ ምሥራቅ ኦሮሚያ በ7 ዞኖች ድርቅ መከሰቱን አሳውቋል። በድርቁ ከ800 ሺህ በላይ ሰዎች ተጎጂ መሆናቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል። የኦሮሚያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር እና ልማት ተነሺዎች ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙስጠፋ ከድር ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፥ " በቦረና ፣ ምስራቅ ጉጂ እና ባሌ ውስጥ ድርቁ በከፍተኛ ሁኔታ ተስተውሏል። በምዕራብ ጉጂ ፣ ምዕራብ ባሌ እና በምዕራብ እና ምስራቅ ሀረርጌ በአጠቃላይ በደቡብ ምስራቅ ኦሮሚያ ድርቁ ተከስቷል ፤ ይህ የሆነው ባለፈው አመት የመኸር እና የክረምት ዝናብ ሳይዘብ በመቅረቱ ነው " ብለዋል። ዝናብ ሳይዘንብ በመቅረቱ ሳር አለመብቀሉን፣ ምንጮችም መድረቃቸውን አቶ ሙስጠፋ ተናግረዋል። በአጠቃላይ 800,244 ሰዎች እርዳታ ለመጠበቅ መገደዳቸውንም አክለው ገልፀዋል። በድርቅ ሳቢያ በእስሳት ላይ ስለደረሰው ጉዳት በተመለከተ ፥ " በ7ቱ ዞኖች በድርቁ የተጎዱ እንስሳት ቁጥር ከ188 ሺህ በላይ ሆኗል። አብዛኛዎቹ በሰው ድጋፍ ነው ከመሬት የሚነሱት። ቦረና ውስጥ ከ6 ሚሊዮን በላይ የቁም እንስሳት እንዳለ ነው የሚታወቀው በእነዚህ ላይ ጉዳት እየደረሰ ነው " ብለዋል። ኮሚሽነሩ መንግስት በድርቅ የተጎዱ ወገኖችን ለመደገፍ እና ለእንስሳት መኖ በማቅረብ ጉዳት ለመቀነስ እየሰራ ነው ብለው ፤ ነገር ግን በቂ አንዳልሆነ አስገንዝበዋል፤ መንግስታዊ የሆኑ እና መንግስታዊ ያልሆኑ እንዲሁም የግል ድርጅቶች፣ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ያሉ ሰዎች እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል። አቶ ሙስጠፋ ከድር እስካሁን በድርቁ የሰው ህይወት አለማለፉን ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል። @tikvahethiopia

#UAE የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዩኤኢ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካን ቡድናቸው ለይፋዊ የስራ ጉብኝት በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ አቡ ዳቢ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ
+3
#UAE የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዩኤኢ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካን ቡድናቸው ለይፋዊ የስራ ጉብኝት በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ አቡ ዳቢ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር የጋራ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። ምንጭ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት @tikvahethiopia

አጭር ማስታወሻ ፦ 1ኛ. በአዲስ አበባ በጊዜያዊነት ታግዶ የነበረው መሬት ነክ አገልግሎት አሁን ላይ እግዱ ተነስቶ አገልግሎቱ በየክፍለ ከተማው እየተሰጠ ነው። ታግደው ከነበሩ አገልግሎቶች መካከል ጊ
አጭር ማስታወሻ ፦ 1ኛ. በአዲስ አበባ በጊዜያዊነት ታግዶ የነበረው መሬት ነክ አገልግሎት አሁን ላይ እግዱ ተነስቶ አገልግሎቱ በየክፍለ ከተማው እየተሰጠ ነው። ታግደው ከነበሩ አገልግሎቶች መካከል ጊዜያዊ እግድ የተነሳላቸው አገልግሎቶች ዝርዝር በዚህ ይመልከቱ : https://t.me/tikvahethiopia/66990?single 2ኛ. ተቋርጦ የቆየው የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሽያጭ ሆነ በስጦታ የማስተላለፍ ውል ከሰኞ ጥር 23/ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ይጀምራል። አገልግሎቱን ለማግኘትና የጉዳይ መከታተያ ቁጥር በኦንላን ለማግኘት www.dars.gov.et ይጠቀሙ። 3ኛ. ዩኤኢ (UAE) ኢትዮጵያና ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ላይ ጥላው የነበረው የጉዞ እገዳ ከዛሬ ቅዳሜ ጀምሮ ተነስቷል። በተያያዘ ማስታወሻ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዛሬ ጀምሮ የዱባይ በረራውን ይቀጥላል። 4ኛ. በወሰን ማስከበር ምክንያት ሳይጠናቀቅ የቆየው የገርጂ ሮባ ዳቦ -መብራት ኃይል (አዲስ አበባ) አስፓልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቆ ሙሉ ለሙሉ ለትራፊክ ክፍት ሆኗል። 5ኛ. በአዲስ አበባ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ማስክ ያላደረጉ አሽከርካሪዎች እና ረዳቶች ከተገኙ ብር 1 ሺህ ይቀጣሉ ፤ ማስክ ያላደረጉ ተሳፋሪ በሚጭኑበት ወቅት ደግሞ በአንድ ሰው 500 ብር ይቀጣሉ። 6ኛ. የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ የመታሰቢያ ሀዉልት ነገ እሁድ በሆሳዕና ከተማ ይመረቃል። @tikvahethiopia

#Hossana የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ መታሰቢያ ሀዉልት ነገ እሁድ በሆሳዕና ከተማ ይመረቃል። ለዚህ የምረቃ ስነስርዓት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ወደ ሆሳዕና ከተማ ይገባሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው።
+2
#Hossana የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ መታሰቢያ ሀዉልት ነገ እሁድ በሆሳዕና ከተማ ይመረቃል። ለዚህ የምረቃ ስነስርዓት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ወደ ሆሳዕና ከተማ ይገባሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። የሀዲያ ዞን አስተዳደር ወደ ከተማው የተጋበዙትን እንግዶች በሠላማዊ መንገድ ለመቀበልና ለማስጎብኘት እንዲያስችል መላዉ የዞኑና የከተማዉ ነዋሪዎች የአካባቢዉን ሠላምና ፀጥታ በመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ተጠይቋል። በሌላ በኩል የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስን ጀግንነት የሚዘክር የፎቶ ኤግዚቢሽን ዛሬ በሆሳዕና ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። መረጃው ከሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የተገኘ ነው። @tikvahethiopia

#Woldia የወልድያ ከተማ አስተዳደር ለኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን እና ለአማራ ክልል መንግሥት ጥያቄዎችን ማቅረቡን ገልጿል። ከተማ አስተዳደሩ ቀደም ሲል የተጀመረውና ኅብረተሰቡ ለጤና እክልና ለ
+1
#Woldia የወልድያ ከተማ አስተዳደር ለኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን እና ለአማራ ክልል መንግሥት ጥያቄዎችን ማቅረቡን ገልጿል። ከተማ አስተዳደሩ ቀደም ሲል የተጀመረውና ኅብረተሰቡ ለጤና እክልና ለተለያዩ ችግሮች እያደረገ ያለው የከተማዋ የአስፋልት መንገድ ግንባታ በፍጥነት ወደ ሥራ የሚገባበትን መንገድ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለ ስልጣን አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጠው ጥያቄውን አቅርቧል። በተመሳሳይ ሁኔታ የኅብረተሰቡን የመልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በተገቢው መንገድ ምላሽ ለመስጠት ወቅቱን የሚዋጅ አደረጃጀት መፍጠር የሚያስችለውን የከተማዋን የሪጅዮ ፖሊታንት መዋቅር ጥያቄ ለክልሉ መንግሥት በድጋሜ በጽሑፍ አቅርቧል። ከተማ አስተዳደሩ ለከተማዋ መልማት ከፍተኛ ሚና ያላቸውን ተገቢ ጥያቄዎች የከተማዋን እድገት የሚመኝ ሁሉ ጉዳዮቹን አጀንዳ በማድረግ ጥረት እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረቡን ከወልዲያ ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል። @tikvahethiopia

#Update የወልድያ ከተማና አካባቢያው ዳግም ኤሌክትሪክ አገኘ። ከደሴ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ወልድያ ማከፋፋያ ጣቢያ በተዘረጋው የ66 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ም
+1
#Update የወልድያ ከተማና አካባቢያው ዳግም ኤሌክትሪክ አገኘ። ከደሴ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ወልድያ ማከፋፋያ ጣቢያ በተዘረጋው የ66 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በደረሰ ቃጠሎ የተነሳ የተቋረጠው ኤሌክትሪክ የወልዲያ ከተማና አካባቢው ዳግም ኤሌክትሪክ ማግኘቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል። ትናንት የደረሰውን የኤሌክትሪክ ምሰሶ ቃጠሎ በሌላ በመተካት ወልድያ፣ መርሳ፣ ውጫሌ እና አካባቢያቸ ዳግም ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ርብርብ ሲደረግ ቆይቶ ወልዲያ ከደቂቃዎች በፊት ኤሌክትሪክ ማግኘት ችላለች። በየደረጃው ሌሎች ከተሞችም ኤሌክትሪክ እንደሚያገኙ ተገልጿል። @tikvahethiopia

#AddisAbaba የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በጋራ በመቀናጀት ባደረጉት ኦፕሬሽን አንድ ስናይፐር ጠብመንጃ ፣ ከ20ሺ በላይ የክላሽ እና 260 የብሬን ጥይት ከእ
+2
#AddisAbaba የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በጋራ በመቀናጀት ባደረጉት ኦፕሬሽን አንድ ስናይፐር ጠብመንጃ ፣ ከ20ሺ በላይ የክላሽ እና 260 የብሬን ጥይት ከእነ ተጠርጣሪዎቹ መያዛቸውን አስታወቁ፡፡ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 አ/አ 62651 በሆነ ኤፍ ኤስ አር አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ አካል ላይ መሸሸጊያ (ሻግ) በማሰራት ከወሊሶ ወደ አዲስ አበባ ሲጓጓዝ የነበረ አንድ ስናይፐር ጠበመንጃ፣ 20 ሺህ 630 የክላሽን -ኮቭ ጠበመንጃ እና 260 የብሬን ጥይት ጥር 20 ቀን 2014 ዓ/ም በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው እህል በረንዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተይዟል። ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ የመኪናው ሾፌርና የጦር መሳሪያውን ያስጫነው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። @tikvahethiopia

#AddisAbaba ከ 4 ኪሎ በሽሮ ሜዳ በቁስቋም አድርጎ እንጦጦ ማርያም የሚደርስ የአንበሳ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት የጉዞ መስመር በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡ የተከፈተው
#AddisAbaba ከ 4 ኪሎ በሽሮ ሜዳ በቁስቋም አድርጎ እንጦጦ ማርያም የሚደርስ የአንበሳ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት የጉዞ መስመር በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡ የተከፈተው አዲሱ መስመር ‹‹መስመር ቁጥር 122 ልዩ ›› የሚል መጠርያ ሲኖርው 10.3 ገደማ ኪ.ሜ ርቀት የሚገመትና እና የ 4 ብር ታሪፍ ተመን የተደረገለት መሆኑን አንበሳየ ከተማ አውቶብስ ድርጅት አስታውቋል። በ6 አውቶብሶች አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ መስመር በተለመደው የአውቶብስ አገልግሎት ሰዓት ተሳፋሪዎችን የሚያስተናግድ ይሆናል። @tikvahethiopia

#ማሳሰቢያ በአዲስ አበባ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመግታት በትራንስፖርት ዘርፍ የወጡ የመከላከያ መንገዶች በአግባቡ እንዲተገበሩ የአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ቢሮ አሳስቧል። ቢሮው ዛሬ በትራንስፖ
#ማሳሰቢያ በአዲስ አበባ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመግታት በትራንስፖርት ዘርፍ የወጡ የመከላከያ መንገዶች በአግባቡ እንዲተገበሩ የአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ቢሮ አሳስቧል። ቢሮው ዛሬ በትራንስፖርት ዘርፍ የኮቪድ 19 ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የቫረሱን ስርጭት ለመቀነስ በትራንስፖርት ዘርፍ የተቀመጠውን መመሪያ ተግባራዊ በማያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ ከዛሬ ጀምሮ ቁጥጥር እንደሚደረግ ተገልጿል። የትራንስፖርት አገልግሎት በሚሰጥበት ወቅት፦ - የተሽከርካሪዎችን ንጽህና መጠበቅ፣ - አሽከርካሪዎችና ረዳቶች ማስክ መጠቀም - ማስክ ያላደረጉ ተሳፋሪዎች አገልግሎት እንዳያገኙ ማድረግ እንደሚገባም ተብራርቷል፡፡ የኮቪድ ስርጭት ለመግታት በወጣው መመሪያ መሰረት ማስክ ያላደረጉ አሽከርካሪዎች እና ረዳቶች ከተገኙ ብር 1 ሺህ የሚያስቀጣ ሲሆን፥ ማስክ ያላደረጉ ተሳፋሪ በሚጭኑበት ወቅት በአንድ ሰው 500 ብር የሚያስቀጣ ይሆናል፡፡ ምንጭ፦ የአ/አ ትራንስፖርት ቢሮ @tikvahethiopia

" ለጋሾች ርዳታ ለማድረስ በእግር መጓዝ ጀምረዋል " - UN OCHA በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ እና ሊተነበይ የማይችል መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ
+1
" ለጋሾች ርዳታ ለማድረስ በእግር መጓዝ ጀምረዋል " - UN OCHA በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ እና ሊተነበይ የማይችል መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት (UNOCHA) ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል። በአፋር በኩል በመጋሌ፣ ኢረብቲ፣ በራህሌ፣ ዳሎል እና አባላ ግጭት መኖሩን ፤ በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር በኩል፣ በዋግ ኽምራ እና ሰሜን ወሎ ዞኖች ከትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት መኖሩን ሪፖርት አድርጓል። በተቀረው የአማራ ክልል ሁኔታው ​​የተረጋጋ እና ለሰብአዊ ምላሽ ተደራሽ መሆኑን ገልጿል። UNOCHA በትግራይ ክልል ባለው የነዳጅ እጥረት ሳቢያ የውጭ ሃገራት ርዳታ ድርጅቶች በምግብ እጦት የተጎዱ ሴቶች እና ህጻናትን ለመርዳት በእግራቸው መጓዝ ጀምረዋል ሲል አሳውቋል። UNOCHA ፤ የሰሜን ኢትዮጵያ የሰብአዊ አቅርቦት ወቅታዊ ሁኔታ በሚመለከት ባወጣው ሪፖርቱ በትግራይ ክልል ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የርዳታ ድርጅቶች በአጠቃላይ ካለፉት አራት ቀናት አንስቶ ነዳጃቸው መሟጠጡን ገልጿል። ያም ቢሆን ግን ድርጅቶቹ " ሠራተኞቻቸው የቀሯቸውን ጥቂት የርዳታ አቅርቦቶች ለማዳረስ እስከ ቻሉት ድረስ በእግር መጓዝ ጀምረዋል " ብሏል። UN OCHA ትግራይ ክልል ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ሀገር በቀል የርዳታ ድርጅቶችም ቢሆኑ በነዳጅ እጥረት " ሙሉ ለሙሉ እንቅስቃሴያቸውን የማቆም ስጋት " ተጋርጦባቸዋል ብሏል። ከነዳጁ በተጨማሪ የገንዘብ እጥረት መከሰቱም ተገልጿል። ሙሉ ሪፖርት : https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/ @tikvahethiopia

" ለ36 ሺ 800 ተማሪዎች ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል " - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ፤ በ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በፀጥታ ችግር የ12ኛ ክፍል ሀገር
" ለ36 ሺ 800 ተማሪዎች ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል " - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ፤ በ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በፀጥታ ችግር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያልተፈተኑ ተማሪዎችን በሙሉ እንደሚያስፈትን አሳውቋል። ክልሉ አሁንም ድረስ በሰሜን ጎንደር እና በዋግኽምራ ብሔረሰብ ዞን አንዳንድ ስፍራዎች አሳሳቢ የፀጥታ ስጋት ቢኖርም ከዞኖቹ ማስፈተን አንችልም የሚል ሪፖርት ስላልደረሰው ለ36 ሺ 800 ተማሪዎች ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅት ማድረጉን ገልጿል። ከጥቅምት 29 እስከ ህዳር 2 በተሰጠው የብሔራዊ ፈተና በክልሉ 133 ትምህርት ቤቶች በፀጥታ ችግር ማስፈተን አልቻሉም። አሁን ላይ ምን አልባት እንኳን ነገሮች ከአቅም በላይ የሚሆኑበት አጋጣሚ ከተፈጠረ እንኳን ተማሪዎችን ሰላማዊ ወደ ሆኑ ሌሎች ዞኖች በመውሰድ ፈተናው እንደሚሰጥ ቢሮው ገልጿል። በመጀመሪያው ዙር ፈተናውን ለመውሰድ በክልሉ ከ127 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ተመዝገበው ነበር። የሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከጥር 24 እስከ 27 ለተከታታይ አራት ቀናት ይሰጣል፡፡ መረጃ ምንጭ አሐዱ ቴሌቪዥን ነው። @tikvahethiopia

#Biyo ቢዮ ኃ.የተ.የግል ማህበር በተለያዩ ጊዜያት የመጣቸውን ለመስኖ ውሃ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዮ አይነት የውሃ ፓንፕ (Gate valve) መሸጥ እንደሚፈልግ ገልጿል። መግዛት የምትፈልጉ ከታ
#Biyo ቢዮ ኃ.የተ.የግል ማህበር በተለያዩ ጊዜያት የመጣቸውን ለመስኖ ውሃ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዮ አይነት የውሃ ፓንፕ (Gate valve) መሸጥ እንደሚፈልግ ገልጿል። መግዛት የምትፈልጉ ከታች በተገለጹት አድራሻ ስለ ሽያጩ ዝርዝር መጠየቅ ይቻላል። አድራሸ፡- ስልክ ቁጥር 0970-72-34-66 ወይም 0116-63-01-60 መገናኛ ቢሮ ኢሜል፡- info@beyo-plc.com.et

#Woldia ከደሴ ወደ ወልድያ ከተማ የሚገባው የኤሌክትሪኮ ኃይል እክል እንዳጋጠመው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ማስታወቁን የወልዲያ ኮሚኒኬሽን ገልጿል። ተቋሙ ከደሴ ወልድያ ከተማ የሚገባው 6
+1
#Woldia ከደሴ ወደ ወልድያ ከተማ የሚገባው የኤሌክትሪኮ ኃይል እክል እንዳጋጠመው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ማስታወቁን የወልዲያ ኮሚኒኬሽን ገልጿል። ተቋሙ ከደሴ ወልድያ ከተማ የሚገባው 66 ኬቪኤ የትራንስሚሽን መስመር ባልታወቀ ምክንያት በሀብሩ ወረዳ ቀበሌ " ቀርጨም በር " አካባቢ ባለ 4 ቋሚ ምሰሶ በእሳት በመቃጠሉ ምክንያትና የደረሰውንም ጉዳት የአካባቢው ነዋሪ (ማኅበረሰብ) አደጋው መድረሱን ለሚመለከታቸው አካላት ባለማሳወቁ በፍላጋ ማግኘቱን አስታውቋል። ተቋሙ የደረሰውን ጉዳት በመጠገን አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ መሆኑን አስታውቆ ኅብረተሰቡ በትእግስት እንዲጠብቅ አሳስቧል። ምንጭ ፦ የወልዲያ ከተማ ኮሚኒኬሽን @tikvahethiopia

#France #Ethiopia በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያ በፈረንሳይ መንግስት የተለገሰ 6.7 ሚሊዮን የኮቪድ-19 ክትባት ዶዝ በኮቫክስ አማካኝነት መረከቧን በአዲስ አበባ የሚገኘው የፈረንሳይ ኤምባሲ ዛሬ
#France #Ethiopia በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያ በፈረንሳይ መንግስት የተለገሰ 6.7 ሚሊዮን የኮቪድ-19 ክትባት ዶዝ በኮቫክስ አማካኝነት መረከቧን በአዲስ አበባ የሚገኘው የፈረንሳይ ኤምባሲ ዛሬ አሳውቋል። ኤምባሲው፤ ኢትዮጵያን ከፈረንሳይ ለአፍሪካ በክትባት ልገሳ ቀዳሚ ኢትዮጵያን ተጠቃሚ አድርጓታል ብሏል። ይህ አቅርቦት ከዴንማርክ፣ ፊንላንድ፣ ግሪክ፣ ጣሊያንና ስዊድን ጋር በዩኒሴፍ ድጋፍ 13 ሚሊዮን የክትባቶች ዓለም አቀፍ ልገሳ አካል መሆኑ ተገልጿል። በአዲስ አበባ የፈረንሳይ ኤምባሲ ፥ " እንደ ቡድን አውሮፓ በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች ቦታዎች ለውጥ ማምጣት እንችላለን " ብሏል። @tikvahethiopia

ፎቶ : ዛሬ በፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት ሹመት ከተሰጣቸው መካከል ጄነራል ባጫ ደበሌ፣ ጄነራል ሀሰን ኢብራሂም ፣ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ፣ አቶ ደሴ ዳልኬ እና አ
+4
ፎቶ : ዛሬ በፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት ሹመት ከተሰጣቸው መካከል ጄነራል ባጫ ደበሌ፣ ጄነራል ሀሰን ኢብራሂም ፣ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ፣ አቶ ደሴ ዳልኬ እና አቶ ተፈራ ደርበው ይገኙበታል። @tikvahethiopia