en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
ከአቢሲንያ ባንክ ሁለት ቅርንጫፎች በሌላ ሰው የሂሳብ ቁጥር 30 ሺ ብር አጭበርብሮ እንደወሰደ የተጠረጠረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የጭሮ ከተማ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የጭሮ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ
+1
ከአቢሲንያ ባንክ ሁለት ቅርንጫፎች በሌላ ሰው የሂሳብ ቁጥር 30 ሺ ብር አጭበርብሮ እንደወሰደ የተጠረጠረ ግለሰብ በቁጥጥር ሾር ማዋሉን የጭሮ ከተማ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የጭሮ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ግለሰቡ áŒˆáŠ•á‹˜á‰ĄáŠ•  áŠ áŒ¨á‰Ľáˆ­á‰ĽáˆŽ ከወሰደባቸው  áˆ˜áŠŤáŠ¨áˆ 15 ሺህ ብር ከባንኩ ጭሮ ቅርንጫፍ ነው። ግለሰቡ በዚህ ቅርንጫፍ የካቲት 10/2014 ዓ.ም የገንዘብ  áˆ›á‹áŒŤ ማዘዣ ላይ የራሱ አስመስሎ ገዛኸኝ ከተማ የሚለውን ስም በመጻፍ ለገንዘብ ከፋዩ በመስጠት ነው ያጨበረበረው ፡፡ በዚህም ገንዘቡን ከከፋዩ ከወሰደ  á‰ áŠ‹áˆ‹   á‰ ááŒĽáŠá‰ľ ከእይታ ለመሰወር ቢሞክርም  áˆ˜áˆ¨áŒƒá‹ የደረሳቸው የባንኩ ጥበቃ ሰራተኛ ከማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ፓትሮልና ሚሊሻዎች ጋር በመተባበር በቁጥጥር ሾር ውሏል። ግለሰቡ ሳሳን ባንተ ነኝ ብሎ ራሱን ቢገልጽም  á‰ľáŠ­áŠ­áˆˆáŠ› ማንነቱና አድራሻው  áŠĽá‹¨á‰°áŒŁáˆŤ ነው። በተመሳሳይ ሰሞኑን በሂርና ከተማ ከሚገኘው የአቢሲንያ ባንክ ጡሎ ቅርንጫፍ 15 ሺህ ብር ያወጣ መሆኑ ተረጋግጧል። በተደረገው ፍተሻ 7 የተለያዩ ሰዎች መታወቂያዎች ይዞ ተገኝቷል። #ENA @tikvahethiopia

#ችሎት እነ አቶ አብዲ ኢሌ ተቃውሞ አሰሙ። ዛሬ ፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የፀረ-ሽብር እና የህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የቀረቡት የቀድሞ የሱማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አብዲ áˆ˜áˆ€áˆ˜á‹ľ ኡመር (አብዲ ኢሌ) ጨምሮ 17 ተከሳሾች ተቃውሞ አሰምተዋል። እነ አቶ አብዲ ኢሌ ከኛ ጋር ታስረው የነበሩት እስረኞች ተፈተው እኛ የምንታሰርበት ምክንያት የለም ሲሉ ነው ተቃውሞ ያሰሙት። አቶ አብዲ መሀመድ እጃቸውን በማንሳት ይህን ተናግረዋል ፦ " ከዚህ በኋላ ፍርድ ቤት አንቀርብም እኛ áŠ¨áˆľáˆ­ ከተፈቱ ግለሰቦች የተለየ ምንም ወንጀል አልፈጸምንም። ስለዚህ ሌሎች ዕስረኞች ተፈተው እኛ ታስረን ፍርድ ቤት የምንቀርብበት ምክንያት የለም። ከአማራ፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፣ ከትግራይ áŠĽáŠ“ ከሌሎችም ከተፈጸመው ወንጀል የኛ በምን ይለያል ? ግድያ በተፈጸመበት ሁኔታ áˆŒáˆŽá‰˝ ሳይጠየቁ እኛ ብቻ የምንታሰርበት ጉዳይ የለም። ስለዚህ ከዛሬ ጀምሮ እኛ ፍርድ ቤት አንቀርብም። ፍርድ ቤቱ የራሱን ውሳኔ ይስጥበት " ከሳሽ አቃቤ ህግ ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ አስተያየት ይስጥበት እና ክርክሩ ይቀጥል ሲል ችሎቱን ጠይቋል። ፍርድ ቤቱ ከእስር የተፈቱ እስረኞችን ክስ ያቋረጠው ፍትህ ሚኒስቴር መሆኑን ገልጿል። አስተያየታቸዎውን ለፍትህ ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚችሉ የገለጸው ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ መርምሮ ተገቢውን ትዛዝ ለመስጠት ለፊታችን ሀሙስ የካቲት 3ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል። (የመረጃ ባለቤት ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ) ያንብቡ : https://telegra.ph/Abdi-Muhamud-Omer-02-08

#MoE ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ (የትምህርት ሚኒስትር) ፦ • የፈተና መሰረቅ ከግለሰብ ይልቅ ተቋማዊ እየሆነ በመምጣቱ ፤ በአጠቃላይ የደረሰብን የሞራል ክስረት ከፍተኛ ነው። • የእኔ ክልል ተማሪዎች
+1
#MoE ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ (የትምህርት ሚኒስትር) ፦ • የፈተና መሰረቅ ከግለሰብ ይልቅ ተቋማዊ እየሆነ በመምጣቱ ፤ በአጠቃላይ የደረሰብን የሞራል ክስረት ከፍተኛ ነው። • የእኔ ክልል ተማሪዎች ማለፍ አለባቸው በሚል በተቋም ደረጃ የፈተና ወረቀቶችን በመስረቅና መልስ በመስጠት ጭምር ተባባሪ የሆኑ አመራሮች መኖራቸው የትምህርት ሲስተሙ ጥራት ተዓማኒነት ከፍተኛ ጥያቄ ዉስጥ ገብቷል። • ግማሹ ለፍቶ ጥሮ ዉጤት እየያዘ ፣ ሌላዉ ደግሞ ከድግሪ ፋብሪካዎች ድግሪ እየተቀበለ የሚያልፍበት ሁኔታ ካለ ችግሩ የተወሰኑ ሰዎች ማለፍ ሳይሆን ፣ ችግሩ የትምህርት ጥራቱ ላይ ነዉ። • ፈተና የሰዎችን ክህሎት እና ታታሪነት መለኪያ መሆኑ ቀርቶ ተሰርቆ ና መልስ ተሰጥቶ የሚመጣ ዉጤት ምዘና አያሟላም፣ ተዓማኒነት አይኖረዉም። • የትምህርት ተቋማት ምዘና ተደርጎባቸዉ ሰርተፊኬት ይስጡ በሚባልበት ሁኔታ በተለይ ለግል ትምህርት ቤቶች የስራ ሰርተፊኬት የሚሰጠዉ በችሎታቸዉ ሳይሆን በጉቦ ከሆነ ሲስተሙ ፈርሷል ይህንንም ሁላችንም ነው የምናዉቀዉ ነገርግን ፊትለፊት ስለማንነጋገርበት ስር የሰደደ መፍትሄ ልንፈልግለት ያልቻልነዉ ጉዳይ ነዉ። • የትምህርት ስርዓቱን ተዓማኒነት ጥያቄ ዉስጥ የሚከት አካሄድ በጣም ተንሰራፍቷል። • የትምህርት ስርዓቱን ለማሻሻል እንደዚህ ያሉ አሰራሮችን ማስቆም እና የሲስተሙን ተዓማኒነት ችግር ዉስጥ የሚከቱ ጉዳዮችን ከስር መሰረታቸዉ መፍታት አለብን። [ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ለህዝብ ተዋካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ነው ] - ከኢትዮ ኤፍ ኤም @tikvahethiopia

ስለ አሚና መሐመድ የአማራ እና የትግራይ ክልል ጉብኝት ምን ተባለ ? የተባበሩት መንግሥታቱ ድርጅት ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሐመድ በጦርነቱ የተጎዱ የአማራና የትግራይ ክልል ከተሞችን ጎብኝተዋል። እንዲሁም ከክልል አመራሮች ጋር ተገናኝተዋል። አሚና ባለፈው እሁድ በአማራ ክልል ኮምቦልቻን የጎበኙ ሲሆን ጦርነቱ በሕዝቡ በተለይ በሴቶችና በህፃናት ላይ ያደረሰውን አስከፊ ጉዳት ማየታቸውን ተመድ አስታውቋል። በሆስፒታሎች፣ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በገበያ ስፍራዎች እና በሌሎች አካባቢዎች ላይ የደረሰውን ዘረፋና ውድመት የተመለከቱ ሲሆን የአማራ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ሌሎችንም ባለሥልጣናትን አግኝተዋል። ከኮምቦልቻ ጉብኝታቸው በኋላ ጦርነቱ ብዙ ያስከፈለ መሆኑን ገልጸው ሰላም ብቸኛ አማራጭ እንደሆነ ተናግረዋል "የኢትዮጵያን ሕዝብ ሰላም እንዲያገኝ መርዳት አለብን" ሲሉም ተናግረዋል። ከኮምቦልቻ ቀጥለቅ ወደ ትግራይ ክልል፣ መቐለ ያቀኑት አሚና በጦርነቱ በሴቶችና በህፃናት ላይ ያደረሰውን አስከፊ ገፅታ ተመልክተዋል። ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና ለኢትዮጵያውን የሚያመጣውን እፎይታን በተመለከተ ከዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር መወያየታቸው ንተመድ ገልጿል። አሚና በተመድ የሚደገፈውንና ከወሲባዊ ጥቃት የተረፉ ሴቶችን ጨምሮ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ የሚያደርገውን የአይደር ሆስፒታልን ጎብኝተዋል። " በግጭት ውስጥ አሸናፊዎች እንደሌሉ " በመጥቀስ ወሲባዊ ጥቃት የተረፉ ሴቶቹ ታሪኮች ሊነገሩ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። በሁለቱ ክልሎች ከሴቶች እንዲሁም ከተማሪዎች ጋር ባደረጉት ቆይታ የተመድ ወሲባዊ እንዲሁም ፆታን መሰረት ላደረጉ ጥቃቶችን እንደማይታገስ አፅንኦት በመስጠት ተናግረዋል። አሚና ወሲባዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች አጋርነታቸውን ገልፀዋል። በጦርነቱ ምክንያት በሴቶች ላይ የደረሰውን ግፍ እና በደል እንዲሁም አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ለማቃለል ተመድ መፍትሄ በማፈላለግ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ሴቶች ካለባቸው ህመም እንዲፈወሱ በተሃድሶ እና በመልሶ ማቋቋም ሥራዎች ውስጥ እንዲካተቱም አመራሮቹን አሳስበዋል። በተጨማሪ ተመድ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገውን የሰላም ጥረትም ይደግፋል ብለዋል። #UnitedNations @tikvahethiopia

#Update ኦባሳንጆ ኮምቦልቻ ገብተዋል። የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕከተኛ ኦሊሴንጎን አባሳንጆ ዛሬ ኮምቦልቻ ገብተዋል። በትላንትናው ዕለት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት ኮሚሽነር አ
#Update ኦባሳንጆ ኮምቦልቻ ገብተዋል። የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕከተኛ ኦሊሴንጎን አባሳንጆ ዛሬ ኮምቦልቻ ገብተዋል። በትላንትናው ዕለት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዴኦዬ ፤ የአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ቀውስ በሰላማዊ መንገድ እንዲቋጭ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ መቀጠሉን በመግለፅ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በአማራ እና በአፋር ክልሎች በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች ጉብኝት እንደሚያደርጉ ማሳወቃቸው አይዘነጋም። ዛሬ ኮምቦልቻ የገቡት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ በከተማው ያለ የጅምላ መቃብር ስፍራ እና የወደሙ ተቋማትን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። @tikvahethiopia

#Egypt #Djibouti ኢማኤል ኦመር ጌሌ ግብፅ ገብተዋል። የጅቡቲ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ በተደረገላቸው ግብዣ ለሁለት ቀን የስራ ጉብኝት ትላንት ለሊት
+2
#Egypt #Djibouti ኢማኤል ኦመር ጌሌ ግብፅ ገብተዋል። የጅቡቲ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ በተደረገላቸው ግብዣ ለሁለት ቀን የስራ ጉብኝት ትላንት ለሊት ግብፅ ገብተዋል። ፕሬዜዳንቱ ካይሮ ኤርፖርት ሲደርሱ አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ናቸው የተቀበሏቸው። በዛው ዕለት ሁለቱ መሪዎች ስብሰባ የሚኖራቸው ሲሆን በሁለትዮሽ ጉዳዮቻቸውና በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራሉ ተብሏል። ፎቶ፦ የጅቡቲ ፕሬዜዳንት (ኢሳማኤል ኦመር ጌሌ) @tikvahethiopia

#AU2022Summit ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለትም እንግዶቿን እየሸኘች ነው። የሴኔጋል ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበር ማኪ ሳልን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋ
#AU2022Summit ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለትም እንግዶቿን እየሸኘች ነው። የሴኔጋል ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበር ማኪ ሳልን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። @tikvahethiopi

#EOTC ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፖትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋ እና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የስተርሊንግ ፋውንዴሽን ዋና ሥራ
+1
#EOTC ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፖትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋ እና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የስተርሊንግ ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና የዩታ ግዛት አስተዳደር የንግድ ቢሮ ኃላፊ የሆኑትን ሚስተር ኤድዋርድን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ብፁዕነታቸው መቀመጫውን በአሜሪካ ዩታ ግዛት ያደረገው የስተርሊንግ ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና የዩታ ግዛት አስተዳደር የንግድ ቢሮ (Edward, CEO of the US-based Sterling Foundation and CEO of the Utah State Business Bureau) ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ሚስተር ኢድዋርድ የሚመራ ልዑክ ባነጋገሩበት ወቅት ሊ/ት ቀሲስ ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ዋና ጸሐፊ ተገኝተው ነበር። የልዑካን ቡድኑ ወደ #ኢትዮጵያ የመጣበትን ጉዳይ በማንሣት ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በተለይም የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤን በሠላም ግንባታ እንዲሁም በአብሮነት እሴት ሥራ ላይ ተቋሙ በሀገሪቱ የሚሰራውን ሥራ ለማገዝ ያላቸውን ፍላጎት መግለጻቸውን ከኢ/ኦ/ተ/ቤ ውጭ ግንኙነት መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። @tikvahethiopia

ፎቶ : ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫን ተረክባለች። ሴኔጋል የአፍሪካን ዋንጫ ካነሱ ሀገራት መካከል ስሟን አስመዝግባለች። ዋንጫውን ይዛ ወደ ሀገሯ ስትገባ ደግሞ እጅግ ደማቅ የሆነ አቀባበል እንደሚደረግላት
+4
ፎቶ : ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫን ተረክባለች። ሴኔጋል የአፍሪካን ዋንጫ ካነሱ ሀገራት መካከል ስሟን አስመዝግባለች። ዋንጫውን ይዛ ወደ ሀገሯ ስትገባ ደግሞ እጅግ ደማቅ የሆነ አቀባበል እንደሚደረግላት ይጠበቃል። 🇸🇳 C H A M P I O N S O F A F R I C A 🏆 #AFCON2021 በዚህ ተደምድሟል። @tikvahethiopia

PHOTO : የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ ዳራሮ በዓል የመዝግያ ፕሮግራም በደማቅ ስነ-ስርዓት በዲላ ሁለገብ እስቴድየም ዛሬ ተካሂዷል። Photo Credit : የዲላ ከተማ ሚኒኬሽን @tikvahethi
+4
PHOTO : የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ ዳራሮ በዓል የመዝግያ ፕሮግራም በደማቅ ስነ-ስርዓት በዲላ ሁለገብ እስቴድየም ዛሬ ተካሂዷል። Photo Credit : የዲላ ከተማ ሚኒኬሽን @tikvahethiopia

#AU2021 ህብረቱ በዝግ እየመከረ ነው። 35ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ ከሰዓት #በዝግ በተለያዩ ጉዳዮች እየመከረ ይገኛል፡፡ በአህጉሪቱ ሰላምና ደህንነት እንዲሁም የኮቪድ-19 ወረር
+1
#AU2021 ህብረቱ በዝግ እየመከረ ነው። 35ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ ከሰዓት #በዝግ በተለያዩ ጉዳዮች እየመከረ ይገኛል፡፡ በአህጉሪቱ ሰላምና ደህንነት እንዲሁም የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመቆጣጠር በተከናወኑ ስራዎችና በተገኙ ውጤቶች ዙሪያ ነው በዝግ እየመከረ የሚገኘው። ዛሬ ምሽት ላይ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ዶ/ር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለአፍርካ ሀገራት መሪዎች የእራት ግብዣ እንደሚያደርጉ ኢብኮ ዘግቧል። @tikvahethiopia

የአፋር ተፈናቃዮች ቁጥር ከ300 ሺህ አለፈ። የአፋር ክልል ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህወሓት እንደአዲስ በከፈተው ጦርነት ተቆጣጥሮ በሚገኝባቸው አካባቢዎች ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሷል ሲል አመል
የአፋር ተፈናቃዮች ቁጥር ከ300 ሺህ አለፈ። የአፋር ክልል ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህወሓት እንደአዲስ በከፈተው ጦርነት ተቆጣጥሮ በሚገኝባቸው አካባቢዎች ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሷል ሲል አመልክቷል። በአካባቢዎቹ ዝርፊያ እንዲሁም ውድመት ደርሷል የሚለው የአፋር ክልል መንግስት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን ገልጿል። ጦርነቱ ከወር በላይ እንደሆነው የተገለፀ ሲሆን አሁንም ድረስ ተባብሶ መቀጠሉ ታውቋል። @tikvahethiopia

#Update በአፋር ክልል ጦርነቱ ተባብሶ መቀጠሉ ተሰምቷል። የአፋር ክልል መንግስት ዛሬ ቅዳሜ ባወጣው መግለጫ ህወሓት ሰርዶን ለመቆጣጠር እንደ አዲስ በኪልበቲ ረሱ ዞን የከፈተውን ከባድ ጦርነት አ
#Update በአፋር ክልል ጦርነቱ ተባብሶ መቀጠሉ ተሰምቷል። የአፋር ክልል መንግስት ዛሬ ቅዳሜ ባወጣው መግለጫ ህወሓት ሰርዶን ለመቆጣጠር እንደ አዲስ በኪልበቲ ረሱ ዞን የከፈተውን ከባድ ጦርነት አጠናክሮ ቀጥሏል ብሏል። የክልሉ መንግስት ህወሓት ከታህሳስ 10 ቀን 2014 ጀምሮ እንደ አዲስ በአፋር በኩል ጦርነት መክፈቱን አስታውሷል። በኪልበቲ ረሱ ዞን የተለያዩ 5 ወረዳዎችና አንድ ከተማ መስተዳድር ማለትም ፦ አብአላ ከተማ አስተዳደር ፣ በአብአላ ወረዳ፣ በመጋሌ ወረዳ፣ በኤረብቲ፣ በኮነባ እና በራህሌ ወረዳዎች በተደጋጋሚ ጦርነት በመክፈት ሰርዶን ለመያዝ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጿል። ቡድኑ ሰርዶን መያዝ የፈለገው የኢትዮ-ጂቡቲን መስመር ለመቆጣጠርና አፋርን እንደ መደራደሪያ ለመጠቀም መሆኑን የገለፀው የአፋር ክልል በፊት ሚሌን ለመቆጣጠር ያደረገውን ትግል በጠነከረ መልኩ ውጊያ በማካሄድ በራህሌ እና ኮነባን በቁጥጥሩ ስር ማዋሉን ገልጿል። የአፋር ክልል በመግለጫው " የአፋር አናብስቶች አሸባሪው ህወሓት ከተቆጣጠራቸው አብአላ ከተማ አስተዳድር፣ አብአላ ወረዳ ፣ መጋሌ ወረዳ እና ኤረብቲ ወረዳዎች እንዲሁም ከባድ ጦርነት ከከፈተባቸው በበራህሌ እና ኮነባ ተጨማሪ ማስፋፋት እንዳያደርግ ከባድ ፊልሚያ አድርገዋል " ሲል ገልጿል። ነገር ግን ህወሓት ይዞት በመጣው ሜካናይዝድ ጦር በከባድ መሳሪያ በመታገዝ በራህሌና ኮነባ ወረዳን በመቆጣጠር የተለመደውን ጅምላ ግድያና ዘረፋ እያካሄደ ነው ብሏል። አሁንም ህወሓት የኢትዮ - ጂቡቲ መተላለፊያ ኮሪደር ዋና መስመርን ለመቁረጥ ያለ የሌለ ኃይሉን በመጠቀም ትልቅ ሜካናይዝድ የሆነ ውጊያ እያካሄደ መሆኑንና ጦርነቱን አጠናክሮ መቀጠሉን የአፋር ክልል አሳውቋል። @tikvahethiopia

#AU2021 " ከ40 ሺህ በላይ የፀጥታ አካላት ተሰማርተዋል " - የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ባስቀመጠው አቅድ መሰረት የአፍሪካ ህብረት የመሪ
+1
#AU2021 " ከ40 ሺህ በላይ የፀጥታ አካላት ተሰማርተዋል " - የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ባስቀመጠው አቅድ መሰረት የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ሰላማዊ ሂደቱን ጠብቆ እየተካሄደ መሆኑን የጋራ ግብረ ኃይሉ አሰተባባሪ ኮሚቴ አስታውቋል። የጋራ ግብረ-ኃይሉ ለጉባኤው ሰላማዊነት ከ40 ሺህ በላይ የጸጥታ አካላት በአዲስ አበባ መሰማራታቸውን የገለፀ ሲሆን ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ አገልግሎት ላይ ያልዋሉ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ጉባኤው በሰላም እንዲካሄድ ቀን ከሌት እየሰራ መሆኑንም ገልጿል። መሪዎች ባረፉባቸው እንዲሁም በሚያርፉባቸው አካባቢዎች የተጠናከረ ጥበቃ እየተከናወነ ይገኛል። የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለጉባኤው ሰላማዊነት እያደረጉት ያለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ የጋራ ግብረ-ኃይሉ ጥሪ አቅርቧል። መንግስት የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ በሰላም ለማካሄድ ቀደም ብሎ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ፣ የሪፐብሊካን ጥበቃ፣ ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ የአዲስ አበባ ፖሊስና የኦሮሚያ ፖሊስን ያካተተ የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል። ፎቶ ፦ ፋይል @tikvahethiopia

" ሶስተኛ ዙር ፈተና የለም " - አቶ ተፈራ ፈይሳ ዛሬ የ2ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መጠናቀቁ ይታወቃል። የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ ፥ ፈ
+1
" ሶስተኛ ዙር ፈተና የለም " - አቶ ተፈራ ፈይሳ ዛሬ የ2ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መጠናቀቁ ይታወቃል። የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ ፥ ፈተናው በአማራ፣ ኦሮሚያ ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ያለምንም ችግር መጠናቀቁን ለ @tikvahuniversity ተናግረዋል። ፈተናውን ከ58 ሺ እስከ 59 ሺህ ተማሪዎች እንደወሰዱ ይጠበቃል ብለዋል። ከተፈታኞቹ ከፍተኛው ቁጥር በአማራ ክልል ሲሆን ከ37 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ ተመዝግበው ነበር። በጸጥታ ችግር ምክንያት ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች ''ሁሉም በሚባል ደረጃ '' በሁለተኛው ዙር ለፈተናው የተቀመጡ በመሆኑ ሥሦተኛ ዙር ፈተና እንደማይኖር ም/ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። @tikvahethiopia

#Tigray , #Mekelle 📍 10ኛው የካርጎ በረራ ዛሬ ወደ ትግራይ ክልል ተደርጓል። ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ወደ ትግራይ ክልል በአስር ቀናት ውስጥ አስረኛውን የካርጎ አይሮፕላን በረራ
#Tigray , #Mekelle 📍 10ኛው የካርጎ በረራ ዛሬ ወደ ትግራይ ክልል ተደርጓል። ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ወደ ትግራይ ክልል በአስር ቀናት ውስጥ አስረኛውን የካርጎ አይሮፕላን በረራ አስፈላጊ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችን በመጫን አድርጓል። በበረራዎቹ እንደ ኢንሱሊን ፣ ሄሞዳያሊስስ ፣ ኦክሲቶሲን ፣ ቴታነስ ቶክሳይድ ፣ ጓንት ፣ የቀዶ ጥገና ቁሳቁሶችን እና አስፈላጊ መድሃኒቶችን ለጤና ተቋማት ማድረስ ተችሏል። በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጤና ሚኒስቴር እና በዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አማካኝነት የቀረቡት እነዚህ የህክምና ቁሳቁሶች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን አፋጣኝ የህክምና ፍላጎቶች ለመሸፈን ይረዳሉ ተብሏል። የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፥ የመጀመሪያው በረራ በሚመለከታቸው አካላት ድጋፍ እኤአ ረቡዕ ጥር 26 መደረጉን አስታውሶ አቅርቦቱ በመደበኝነት እንደሚቀጥል አሳውቋል። ለሚቀጥለው ሳምንትም 5 ተጨማሪ በረራዎችን ለማድረግ አስቀድሞ መታቀዱንም ገልጿል። @TikvahEthiopia

#ዝናቧ_ገብረፃዲቅ የመምህርት ዝናቧ ገ/ፃዲቅ ግድያን አስመልክቶ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ። በጅሁር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ በመምህርነት ስታገለግል የነበረችው መምህርት ዝናቧ ገ/ፃዲቅ ግድያን አ
+3
#ዝናቧ_ገብረፃዲቅ የመምህርት ዝናቧ ገ/ፃዲቅ ግድያን አስመልክቶ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ። በጅሁር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ በመምህርነት ስታገለግል የነበረችው መምህርት ዝናቧ ገ/ፃዲቅ ግድያን አስመልክቶ ዛሬ ሰላማዊ ሰልፍ መደረጉ ተሰምቷል። የእነዋሪ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራን ፣ ተማሪዎችና የከተማ ነዋሪዎች በአንድነት ሆነው ከጅሁር ከተማ ከመጡ ሰልፈኞች ጋር በመጣመር የመምህርቷን አሰቃቂ ሞት በአደባባይ አውግዘዋል፡፡ ሰልፈኞቹ በእነዋሪ ከተማ አደባባይ እና በጅሩ ሁለገብ ስቴዲዬም የተለያዬ መፈክሮችን ይዘው ድርጊቱን በእጅጉ ኮንነዋል፡፡ ሰልፈኞች ከያዙት መፈክር መካከል ፦ " በግፍ ለተገደለችው እህታችን መ/ርት ዝናቧ ገ/ፃዲቅ ህጋዊ ፍትህ ይሰጣት " " እኛ መምህራን የትውልድ እናት እና አባት እንጂ ሰይፍን የማስተናገድ አቅም የለንም " " ትክክለኛ ፍርድ ይፈረድ " " መምህርን መግደል ትውልድን መግደል ነው " " እኛ መምህራን የህፃንታ እናት እና አባት በመሆናችን በተከራየንበት ቤት በግፍ ተገድለን መገኘት የለብን " የሚሉ ይገኙበታል። መምህርት ዝናቧ ገ/ፃዲቅ ለሶስት ወር ጠፍታ ስትፈልግ ከቆየ በኃላ በመጨረሻ ተከራይታ በምትኖርበት ቤት ተቀብራ ተገኝታለች። ፎቶ ፦ ሞረትና ጅሩ ወረዳ @tikvahethiopia

#ዝናቧ_ገብረፃዲቅ መምህሯ የተከራየችበት ግቢ ውስጥ ተቀብራ ተገኘች። በሰሜን ሸዋ ዞን በሞረትና ጅሩ ወረዳ በጅሁር ንዑስ ወረዳ ለ3 ወራት ጠፍታ የነበረችው መምህርት በተከራየችበት ግቢ ውስጥ ተቀብራ
+1
#ዝናቧ_ገብረፃዲቅ መምህሯ የተከራየችበት ግቢ ውስጥ ተቀብራ ተገኘች። በሰሜን ሸዋ ዞን በሞረትና ጅሩ ወረዳ በጅሁር ንዑስ ወረዳ ለ3 ወራት ጠፍታ የነበረችው መምህርት በተከራየችበት ግቢ ውስጥ ተቀብራ ተገኘች፡፡ የጅሁር ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ዝናቧ ገ/ፃዲቅ ጥቅምት 25/02/2014ዓ/ም በግምት ከቀኑ 10 ሰዓት አካባቢ የጠፋች መሆኑን ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት የፀጥታ መዋቅሩና የፍትሕ አካሉ እንዲሁም የጅሁር ከተማ ማህብረሰብ እና ቤተሰቦቿ ጭምር በጋራ በተደረገው ስራ በተከራየችበት ግቢ ጓሮ ውስጥ ተቀብራ መገኘቷን ገልጿል። ዋና አዛዥ ኮማንደር ዘነበ ሰሙንጉስ ፥ " በወረዳችን የዚህ አይነት አፀያፊ ተግባር መፈፀሙ እጅግ አሳዛኝ ነው " ብለዋል። የመምህርት ዝናቧ አከራይ በግቢያቸው ወንጀሉ ተፈጽሞ በመገኘቱ ሙሉ ቤተሰቡን በመያዝ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ተገልጿል። ኮማንደር ዘነበ "ድርጊቱ እጅግ የሚያሳዝንና የጅሩን ህዝብ የማይወክል አረመኔያዊ ተግባር በመሆኑ መላ ህዝባችን ሊያወግዘው ይገባል " ሲሉም ተናግረዋል። ምርመራው አሁንም እየተጣራ በመሆኑ ትክክለኛ ውሳኔ እንዳረፈበት ለህዝባ እንደሚገለፅ ፖሊስ አሳውቋል። @tikvahethiopia

#Update የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ለሁለተኛ ዙር ሲሰጥ የነበረው የ2013 ዓ.ም አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን አሳውቋል። የኤጀንሲው ምክት
#Update የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ለሁለተኛ ዙር ሲሰጥ የነበረው የ2013 ዓ.ም አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን አሳውቋል። የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ፈይሳ ፦ - በኦሮሚያ፣ - በአማራ፣ - በአፋር እና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በ189 የፈተና መስጫ ጣቢያዎች ፈተናው መሰጠቱን ገልፀው የመልቀቂያ ፈተናው ካለምንም እንከን በሰላም ተጠናቋል ሲሉ ገልፀዋል። @tikvahethiopia

አስተያየት ስጡበት ! የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ህዝቡ አስተያየት እንዲሰጥባቸው ምክር ቤቱ ዝርዝራቸውን ዛሬ ይፋ አድርጓል። በተለያዩ አግባቦች በተጠቆሙት 42 የኢትዮጵ
+1
አስተያየት ስጡበት ! የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ህዝቡ አስተያየት እንዲሰጥባቸው ምክር ቤቱ ዝርዝራቸውን ዛሬ ይፋ አድርጓል። በተለያዩ አግባቦች በተጠቆሙት 42 የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን እጩ ኮሚሽነሮች ላይ ከዛሬ ጀምሮ የህዝብ አስተያየት ይሰበሰባል። ይህን 👉http://www.hopr.gov.et/am/web/guest/dialog-candidate ማስፈንጠሪያ በመጫን አስተያየት መስጠት እንደሚቻል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳውቋል። #ሼር #Share @tikvahethiopia