en
Feedback
Afar Communication Bureau

Afar Communication Bureau

Open in Telegram

Rakaakayak Doolat Angaarawih Biiro

Show more
872
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+1230 days
Posts Archive
በአፋር ክልል እየተካሄደ የሚገኘው አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ የህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ የታየበት ነው- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘውን አ
+1
በአፋር ክልል እየተካሄደ የሚገኘው አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ የህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ የታየበት ነው- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘውን አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር አይሮሪት መሃመድ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወክለው የመጡ ተሳታፊዎች ንቁ ተሳትፎ ያደረጉበት፤ በተለየ ሁኔታ ደግሞ የሴቶች ተሳትፎ ጎልቶ የወጣበት ሆኖ አግኝተነዋል ብለዋል። የክልሉ መንግስትም በተለያየ መንገድ ድጋፍ ማድረጉን ያደነቁት ኮሚሽነሯ ለሂደቱ መሳካት አስተዋፅኦ ያደረጉ አካላትን በሙሉ አመስግነዋል። በቀጣይ ቀናት ስለሚኖሩ ቀሪ መርሃግብሮች የተናገሩት ኮሚሽነር ብሌን ገብረመድህን በበኩላቸው፤ ከቅዳሜ መስከረም 25 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በወረዳ ደረጃ በተደረገው ውይይት የተመረጡ ተወካዮችና ባለድርሻ አካላት በአምስት ቡድኖች ተከፍለው በመወያየት አጀንዳዎችን እንደሚያዘጋጁ ገልፀዋል። አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፉ ቀጥሎ እስከ ሰኞ በሚኖረው ጊዜ እንደ አፋር ክልል በአገር ደረጃ ለሚደረገው ምክክር የሚቀርቡ አጀንዳዎች እና ተወካዮች ተመርጠው እንደሚጠናቀቅ ተናግረዋል።

photo content
+1

የሁለቱን ክልሎች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን እና የጋራ ሰላም ለማጠናከር በቁርጠኝነት መስራት ይገባል ተባለ ። በአፋር እና ትግራይ ክልል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እና የጋራ ስላምን ለማጠናከር በትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራ ሉዑክ ሰመራ ከተማ ገብቷል ። በትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራው የሉዑካን ቡድን ሰመራ ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፈሬ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የአፋር ክልል ር/መስተዳድር ሀጂ አወል አርባ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል ። በትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር በፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ የተመራው ሉዑካን ቡድን የክልሉን የፀጥታ እና የዞን አመራሮችን ያካተተ መሆኑ ታውቋል ። የአፋር ክልል ር/መስተዳድር ሀጂ አወል አርባ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እና ከፍተኛ አመራርን ላካተተዉ ሉዑካን እንደገለፁት ጎረቤት በሆኑ የአፋር እና ትግራይ ህዝቦች መካከል የሰላምና ፀጥታ ችግሮችን በመፍታት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን ለማጠናከር በሁለቱ ክልሎች መካከል ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ብሎም የትግራይ ክልል ሰላም ለክልላችን ሰላም ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ በክልሉ መረጋጋትን ለመፍጠር የሁሉንም ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ ለክልሉ ሰላም እና መረጋገት የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል። የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በውይይቱ ወቅት ባደረጉት ንግግር በአፋር እና ትግራይ ህዝቦች መካከል የቆየ ወንድማማችነት እና የመደጋገፍ ታሪክ ያላቸው መሆኑን በማንሳት ሁለቱ ክልሎች በትብብር ሊያሳኳቸው የሚገቡ በርካታ ተግባራት የሚጠበቅባቸው መሆኑን በማዉሳት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን እስከ ታችኛዉ መዋቅር ድረስ በማውረድ በግጭቶች የተፈናቀሉ ህዝቦችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን በመግለፅ ግንኙነቱን በህዝብ ለህዝብ ደረጃ ለማካሄድ በቀጣይ ግዜያቶች መድረኮች መፈጠር እንዳለባቸው ገልፀዋል ። በውይይት መድረኩ በሁለት ህዝቦች መካከል ያለው ግኙነት ለማጠናከር የህዝብ ለህዝብ ኮንፈረንሶችን ማካሄድ ፤ የሁለቱ ህዝቦች የባህላዊ የግጭት አፈታት ባህሎችን በጋራ በመጠቀም የሚከሰቱ ችግሮችን መፍታትና በሁለቱ ክልሎች መካከል ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በጋራ የሚሰሩ ስራዎችን ላይ ለመወያየት እንዲሁም አልፎ አልፎ በሁለቱም በኩል የሚነሱ ግጭቶችን በፍጥነት ለመፍታት እና የተፈናቀሉ ማህበረሰቦችን ወደ ቀያቸዉ ለመመለስ በጋራ በሚሰራባቸው ጉዳዮች ላይ በመድረኩ ላይ ውይይት ተካሄዷል። የዛሬዉ የመሪዎች ዉይይት ለቀጣይ ግንኝነቶች በር ከፋች መሆኑ ተገልጿል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 39ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 39ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው ብሔራዊ የመካከለኛ ዘመን 2017-2020 የገቢ ስትራቴጂ ላይ ነው፡፡ ስትራቴጂው የታክስ ሥርዓቱን ለማዘመን እና ለግል ኢንቨስትመንቱ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የታለመ ሲሆን አጠቃላይ የታክስ ፖሊሲዎችን እና አስተዳደራዊ ሪፎርሞችን እንዲሁም ማሻሻያዎችን ለመተግበር የሚያስችል ነው፡፡ ሰትራቴጂው ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ተደርጎ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በስትራቴጂው ላይ በዝርዝር ከተወያየበት በኋላ በምክር ቤቱ ውሳኔ ካገኘበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ከማልታ ሪፐብሊክ መንግስት እና ከቻድ ሪፐብሊክ መንግስት ጋር የተፈረማቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነቶችን ለማጽደቅ የቀረቡ 2 ረቂቅ አዋጆች ላይ ነው፡፡ ስምምነቶቹ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ማንኛውም የማልታ ከተማ እና ወደ እንጃሜና ከተማ በ3ኛና 4ኛ ትራፊክ መብት የመንገደኛ እና የጭነት የበረራ ምልልስ ለማድረግ፣ ተወካይ አየር መንገዶችን በሽርክና ለማሰራት፣ በ5ኛ ትራፊክ መብት ወደ ተመረጡ መዳረሻዎች በረራ ለማድረግ የሚያስችል እና አገራችን ከሁለቱ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር፣ ለንግድና ኢንቨስትመንት፣ ለወጪ ንግድ፣ ለቱሪዝም፣ ለስራ እድል ፈጠራ እና ለውጭ ምንዛሪ ግኝት ትልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው ስምምነቶች ናቸው፡፡ ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጆቹ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ ወስኗል፡፡ 3. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የፓሪስ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት ኮንቬንሽን ለማጽደቅ በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የፓሪስ ኢንዱስትሪያዊ ንብረት ኮንቬንሽን በአባል አገራት መካከል ሕብረት በመፍጠር የኢንዱስትሪ ንብረትን ለመጠበቅ፣ የፈጠራ ባለቤትነት፣ የግልጋሎት ሞዴሎች፣ የኢንዱስትሪ ንድፎች፣ የንግድ ምልክቶች፣ የአገልግሎት ምልክቶች፣ የንግድ ስሞች፣ የምርቶች ምንጭ አመልካች ምልክቶች ለመጠበቅ እንዲሁም ተገቢ ያልሆነ ውድድር ለመከላከል እና ለግብርና እና ሁሉንም የተመረቱ ወይም ተፈጥሯዊ ምርቶች የሚያካትት ነው፡፡ የኮንቬንሽኑ መጽደቅ ሀገራችን ለምታደርገው የአለም ንግድ ድርጅት አባልነት ጥያቄ ድጋፍ የሚሆን ሲሆን ከአባል ሀገራቱ ለሚነሱ የኢንዱስትሪያዊ ንብረት ጥበቃን ለሚመለከቱ ጥያቄዎች አዎንታዊ መልስ ለመስጠት ያስችላል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የዓለም አቀፍ ምልክቶችን ከሚመለከተው የማድሪድ ስምምነት ጋር የተዛመደውን ፕሮቶኮል ለማጽደቅ በወጣ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ፕሮቶኮሉ የንግድ እና የአገልግሎት ምልክቶች በአገር ውስጥ ሕግ ከሚደረግላቸው ጥበቃ አልፈው በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥበቃ እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል ከመሆኑም በተጨማሪ ምርቶች እና አገልግሎቶች ያላግባብ ለሌሎች ጥቅም እንዳይውሉ በቂ ጥበቃ የሚደረግበትን ሁኔታ የሚፈጥር፣ ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና አገልግሎቶች እንዲኖሩና የሀብት ምንጭ እንዲሆኑ ትልቅ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ምክር ቤቱ በፕሮቶኮሉ ላይ ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡ 5. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ደንብ እና የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ደንብ ላይ ነው፡፡ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር እና ሀላፊነት ለመወጣት፤ የተቀላጠፈ አገልግሎት ለደንበኞች ለመስጠት እንዲሁም ከፓስፖርት የቆይታ ጊዜ ጋር በተያያዘ ያሉ ጥቄዎችን መፍታት እንዲችል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ በተጨማሪም የጀመረውን ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ፣ ሪፎርሙ በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ለማስቻል የአገልግሎቱን ልዩ ባህሪይ ከግምት ውስጥ ያስገባ ሰራተኞች መተዳደሪያ ደንብ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቦቹ ላይ በዝርዝር ከተወያየባቸው በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረጉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ Office of the Prime Minister-Ethiopia

photo content
+4

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአፋር ክልል የሚያካሂደው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ በሰመራ ከተማ ተጀምሯል። በመድረኩ ላይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሃጂ አወል አርባና የሀገራዊ ምክክር ኮሚሺን ኮሚሺነር አምባሳደር አይሮሪት መሀመድን (ዶ/ር )ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካሎች ተገኝተዋል:: ለ6ቀናት በሚቆየው የውይይት መድረክ ተሳታፊዎቹ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገበል ያሏቸውን ነጥቦችን ጨምሮ በሀገር አቀፍ ጉባኤው ላይ የሚወክሏቸውን ተወካዮች በመምረጥ አንደሚጠናቀቅም ይጠበቃል ። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር አይሮሪት መሐመድ (ዶ/ር)፤ ኮሚሽኑ በሀገራችን ውስጥ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚስተዋሉ የሀሳብ ልዩነቶችን በሰለጠነ እና ሰላማዊ በሆነ መልኩ በምክክር እንዲፈቱ ትልቅ ዓላማን ሰንቆ በመስራት ላይ ይገኛል ብለዋል። ኮሚሽኑ ይህንን ቁልፍ ተግባር ሲያከናውን የየክልሉን ዓውድ መሰረት ያደረጉ አሰራሮችን ተከትሏል ያሉት ኮሚሽነሯ፤ በዚህ ረገድ በየአካባቢው ያሉ የሀገር በቀል ዕውቀቶች የኮሚሽኑን ስራ ለማቀላጠፍ በእጅጉ ማገዛቸውን ገልጸዋል። የሀሳብ ልዩነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችን ለችግሮቻችን ለዘለቄታው የሚበጁ መፍትሔዎችን ለማስቀመጥ እንደሚያግዝም ተናግረዋል። ዛሬ መስከረም 21/2017 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው የአፋር ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክር መድረክ ለተከታታይ 6 ቀናት የሚካሄድ ይሆናል። በዚህ መድረክ የመጀመሪያዎቹ 3 ቀናት የወረዳ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ተሳታፊዎች በቡድን ተወያይተው አጀንዳዎቻቸውን ያደራጃሉ፡፡ በቀጣዮቹ ቀናት ደግሞ የተለያዩ ማኅበራትንና ተቋማትን የሚወክሉ ባለድርሻ አካላት ከወረዳ ተሳታፊዎች ጋር በመኾን የአፋር ክልልን የሀገራዊ ምክክር አጀንዳዎች ለኮሚሽኑ ያስረክባሉ፡፡ በአፋር ክልል በሚከናወነው በዚህ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ ከአንድ ሺህ አምስት መቶ በላይ ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

photo content
+8

Ajenxa Gaaboyso kee Mabbalow gudgud Samarâ magaalal qimbisen. Itiyoppiyak Agat Mabbaloowih Komishiin Qafar Rakaakayal Ajenxa Gaaboyso kee Mabbalow Gudgud Samarâ Magaalal Qimbise. Tama Gudgudul Rakaakayak Naharsi Saqal Massakaxxa le Cajji Awwal Qarbaay, Agatak Mabbaloow Komishiinik Komishineer Ambaasaxxer Dr Ayroorit Macammad Edde Anuk Baxaabxsa le Ummattah Awlaytiit kee Ayyunt Exxaaxi Edde Angaluk Geytinta. Mabbalow Gudgud Asaakuuk Abbaxuk Ciggilta 6 Ayroora fan Gexsitak Sugelem kee Baaxoh Caddol Gexsittu waytah tan Agat Mabbaloowih Walalat Tangalu Waytah tan Qafar Ummattah Awylaytit edde Doorimele Axcuk Qambaalan.

Karmâ buqre- Carri rasuk Dawwê daqaara Dawwe Daqaarak Doolat Angaarawih caagidah maktaba
+5
Karmâ buqre- Carri rasuk Dawwê daqaara Dawwe Daqaarak Doolat Angaarawih caagidah maktaba

Weeqí Qawwalaylah Tekkaawissoh

Maysaxxaga! Qafar Rakakayih Poolisih adoyta akkuk Qafar ummattah saalam kee nagaynah solteh tan Qafar Poolisit tangaleemih fa
Maysaxxaga! Qafar Rakakayih Poolisih adoyta akkuk Qafar ummattah saalam kee nagaynah solteh tan Qafar Poolisit tangaleemih fayxi le agat xaylo ruffaha xaagu. Qafar Rakakayak Poolis Komishin qusba Poolis adoytit samlisak Qafar Poolisit tangalem faxxa agat xaylo meexak geytima. Toh kinnuk Qafar Poolisit tangalem faxxa agat xaylok edde nan Ximolik 29 fan siinil xayyowinnaan Poolis fanteenal tankuttubeenim sin naysixxige. Qafar Rakakayak Poolis Komishin

ነሐሴ 17 በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን በጋራ ለመትከል 3 ቀን ቀረን !
ነሐሴ 17 በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን በጋራ ለመትከል 3 ቀን ቀረን !

Uwwayti iro baaxoh sarfi sinnim (Franco-valuta) baaxo fan culsaanam idniseenim qadaagâ xakak le. Irô Baaxoh sarfi Mekla sinnim, Uwwayti baaxo fan culsaanam edde xiqqimtah tan gexsit (Franco- valuta) fidseenih geytiman. Doolat xayi udduurih addat dudda leh tan Makro-Ikonomik Riformi afâ baaxô lakqoh sarfi qadaagâ gitaak madqimtuh abbinoosak geytimam kee tah Itiyoppiyak Agat Banki Abbinoosak geytimam tamixxigeh. Tama maysaasak ugutak, culenti kabxa bisoh hayoonuh, addah Baaxô fan culsaanam madqal waaso elle heenih sugeenimik sansi Automobiil kee amni Kee saay silaacittek iroh tan uwwaytitte, Irô baaxoh lakqoh sarfi mekla maleh (Franco Valuta) akah culan Innah doolat madqeh. Kabxaa kee Dariifah Fantaaxaw Malaak elle tescessennal Uwwayti Farnko Valuutal baaxô fan akah culusan innah idniseenih yaniinim awayih uddur geytimta qadaaga kee tellemmoh angagoyyitte qaadih fan gacseleemih taagah qadaaga sabhalaltuh naba doori le. -------------------------------------------------- Qafar Agatih Rakaakayak Angaaraw Biirok Ayyuntiinô ratteemah doorititte: ⇆ Facebook: www.fb.com/afarcom1 ⇇ Twitter (X) : www.twitter.com/afarcom1 ⇆ Telegram: www.t.me/afarcom ⇆ Instagram: www.instagram.com/afarcom1 ⇆ Tiktok: https:www.tiktok.com/@afarcom ⇆ Youtube: https://www.youtube.com/@afarcom

Algeen Raat Yamaate Horah! 5 Ayro Raqte Ximolik 17 -2016 I.l.l. አረንጓዴ አሻራ ለነገዉ ትዉልድ 5 ቀን ቀረው! ነሀሴ 17 አረንጓዴ አሻራችንን እናሳርፋለን! #አ
Algeen Raat Yamaate Horah! 5 Ayro Raqte Ximolik 17 -2016 I.l.l. አረንጓዴ አሻራ ለነገዉ ትዉልድ 5 ቀን ቀረው! ነሀሴ 17 አረንጓዴ አሻራችንን እናሳርፋለን! #አረንጓዴ_አሻራ #600_ሚሊዮን_ችግኝ

አረንጓዴ አሻራ ለነገዉ ትዉልድ 6️⃣ ቀን ቀረው! ነሀሴ 17 አረንጓዴ አሻራችንን እናሳርፋለን! #አረንጓዴ_አሻራ #600_ሚሊዮን_ችግኝ
አረንጓዴ አሻራ ለነገዉ ትዉልድ 6️⃣ ቀን ቀረው! ነሀሴ 17 አረንጓዴ አሻራችንን እናሳርፋለን! #አረንጓዴ_አሻራ #600_ሚሊዮን_ችግኝ

Weeqi Qawwalaylah Bohoyih Takkaawisso!!!! ^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^ Ciggiltah tan ayroorah addat sissik weeqi qawwalayla bohoy yaniimih taagah ambad leh tan Takkaawisso faxximta !!! Itiyoppiyak Silayti Luddal Faxxiima Cubbi Abaanam Faxximtam Itiyoppiyak Mitro loojih Inistitiyuut Kassisse. Taham kesem karawwadih leeh caddo wagsiisak sissik Takkaawisso leeh caddo fayya tem wayih udder 1.98 mitir addah teemiik, Gexxaamah robti cayla Kee Weeqi dufih meysi tanim Itiyoppiyak Mitroloojih Instituut Qaddoyse. Tohih taagah, inki inki leeh exxaaxil tanih tan dariifak, kesem karawwad leek, yemmeggeemik amakkaquk sissik weeqayti dariifal yan ayyunta fayya le aroocal akah tayyaaqen innah wagsiisa xagarak. Kassiisih:- Baxsaluk Qammi baxaay, Dulellaasaay, Awash fanti qaleey, Carrukaay, Gawwaaniiy, Buuri moodaytuu; kee Galaqli Daqoorit weeqi bohoy le deraafil geytima miraaciini ummattah faxxiima oytitte tabisak bohoy daggoowuh faxxiima uguugus kee macal faxxiimam kinnuk kulli mari isil tan binaadamiyyo dirkik nawqay!!! QARD Qawwalaylah Osodih Makkaabiyyô Komishiin

photo content
+2