cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

#KALTUBE

ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተሞልቶ በእኛ አደረ። ዩሐ1÷ 14 " Daily Spiritual Feeding" በዚህ ያገኙናል👉 @Kaltube_bot ●የዩቲዩብ ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ👇 https://www.youtube.com/kaltubeOfficial?sub_Confirmation=1 ●ስድስተኛ ቃልኛ ዲጂታል መፅሔታችን👇 https://t.me/KALTUBE/7576

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
20 061Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Show all...
የጸጋውን ቁርበት - Eyerusalem Negiya || track 03, volume 3 || 2021

የጸጋውን ቁርበት ግጥምና ዜማ - ኢየሩሳሌም ነጊያ ሙዚቃ ቅንብር - አማኑኤል ፍቃዱ ሞሽን ግራፊክስ - ቲራጎ ታደሰ

https://www.youtube.com/channel/UCW_nqpVEorBEgj1KHEc5X-Q

#Addis_Ababa #Eyerusalem_Negiya #Volume_3

ግራ ና ቀኝ 💐ተከታታይ ልብወለድ ክፍል ፲፮ ስነዳ ከመፍጠኔ የተነሳ ላበረው ይመስላል ትራፊክ እያየሁ እንኳን ፍጥነቴን አልቀነስኩም ጭራሽ የትራፊክ መብራት ጥሼ አለፍኩ ከሆላዬ እየተከተለኝ መሆኑን ያስተዋልኩት ከስንት ደቂቃ በሗላ ነው መኪናውን እንዳቆም ምልክት ሰጠኝ አቆምኩ በሞተር ነበር የመጣው እየተጠጋኝ ብስጭት ባለ ንግግር ከመኪናው ውረጂ አለኝ ወረድኩ መንጃፍቃድሽን አምጪ እሺ ብዬ አሳየሁት በጣም በፍጥነት እየነዳሽ መሆኑን ታውቆሻል በዛ ላይ የትራፊክ መብራት ጥሰሽ ነው ያለፍሽው ሰው ላይ ንብረት ላይ እና እራስሽ ላይ አደጋ ብታደርሺ ኖሮስ ደሞ ጠጥተሻል እንዴ ብሎ የትንፋሽ መመርመሪያውን አወጣ አረ በፍፁም አልኩት እንግዲ እሱን የምናይ ይሆናል ብሎ መረመረኝ ና አለመጠጣቴን አረጋገጠ ይቅርታ ጌታዬ አስቸኳይ ነገር አጋጥሞኝ ነው ቢተባበሩኝ እና በይቅርታ ቢያልፉኝ ደስ ይለኛል እባኮትን ብዬ ተቅለሰለስኩ እሱ ግን ወይ ፍንክች ይሄ በይቅርታ አይታለፍም ቅጣት ያስፈልጋል እኔ ህጉን ነው የምከተለው አለና ደረሰኝ አውጥቶ ፃፈብኝ ሌላ እዳ ውስጥ ገባሁ ገና ሄጄ ቅጣቴን መክፈል አለብኝ እስከዛ መኪናዬን መጠቀም አልችልም አልቅሽ አልቅሽ አለኝ ሌላ አማራጭ ሳጣ ለየአብ ደወልኩለት በጣም እንደደበረኝ ነግሬው ላግኝህ አልኩት ከድምጴ የመከፋት ስሜት ስለሚስተዋልብኝ ምንም ሳያቅማማ መጣሁ ጠብቂኝ አለኝ እዛው ከቆምኩበት መቶ ወሰደኝ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደሄድንበት ወደዛ ቆንጆ ባህላዊ ምግብ ቤት በድጋሚ ሄድን ፋሌቅ ደና አደለሽም ሁኔታሽ ያስታውቃል ደብሮኝ ብቻ ነው ብለሽ አታሞኚኝ ህፃን ልጅ አደለሁም አሁን በይንገሪኝ ምንድነው የሆንሽው ብሎ አተኮረብኝ ከአይኑ መሸሽ አልቻልኩም ሙሉ እውነታውን ባልነግረውም ጥቂቱን ነገርኩት ከእህቴ ጋር ተጣላን ከቤት ልብሶን ይዛ ወጣች 3 ቀን ሆናት ዛሬ ላናግራት ሱቅ ሄጄ ነበር ግን ልንግባባ አልቻልንም በሱ ተናድጄ በፍጥነት ሳሽከረክር ትራፊክ ያዘኝ እና ተቀጣሁ የማረገው ግራ ግብት ሲለኝ ደወልኩልክ በቃ ይሄነው የተፈጠረው ብዬ ተነፈስኩ በጣም ያሳዝናል ግን ለምን ተጣላችሁ ይሄን ያህል ምን ቢፈጠር ነው ከባድ ነገር መሆን አለበት ሲለኝ ምክንያቱን አትጠይቀኝ ላብራራልክ የማልችለው ነገሮች አሉኝ እባክክ ብዬ አንገቴን ወደጠረጴዛው ደፍቼ የምግብ ዝርዝር የያዘውን ደብተር ማገላበጥ ጀመርኩ እሺ ግን ለምን ከኔ የሚደበቅ ትልቅ ነገር ሆኖ ነው ደሞ ከፈለግሽ እህትሽን እኔ ላናግራት እችላለሁ ብሎ ሳይጨርስ አ አይ አያስፈልግም የግል ጉዳይ ነው ብዬ ኮስተር አልኩኝ በፊቴ መቀያየር ደንግጦ ዝም አለ መልሼ ደሞ በንግግሬ አፈርኩ የአብ ይቅርታ ስለተጨነቅኩ ነው በቃ እኔ አንተ የማታቃቸው ብዙ ችግሮች አሉብኝ አሁን እሱን ለመናገር ጊዜውም ቦታውም አደለም እግዚአብሔር ከፈቀደ እና ብርታቱን ካገኘሁ አንድ ቀን እነግርሀለሁ እስከዛ በምታምነው ይሁንብህ ምንም ጥያቄ አትጠይቀኝ ©በያኔት ማስረሻ ...........ይቀጥላል........... Share💚Share💚Share💚 @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE
Show all...
የእግዚአብሔር ቃል ልክ እንደ ጠዋት ፀሀይ ነው። የጠዋት ፀሀይ ደካማ አጥንቶችን ያጠነክራል ፤ ቅዱሱ ቃልም መንፈሳዊ ሰላላነታችንን በብርታት ይቀይራል። የጠዋት ፀሀይ ንቃትን እና ትኩረትን ይጨምራል ፤ ህያው ቃሉም ከዚህች ደሊላ ዓለም ነቅትን በትኩረት እንድንኖር ያደርገናል። የጠዋት ፀሀይ የጡንቻ ህመምን እና ቁስለትን ያስታግሳል ፤ የእግዚአብሔር ቃልም ስለ ክርስቶስ በዚህች ምድር ያለብንን መከራ እስከ ፍጻሜ እንድንታገስ ይረዳናል። የጠዋት ፀሀይ የተከማቸ ስብን ያቃጥላል ፤  ቅዱሱ ቃልም ፈጥኖ የሚከብበንን የኀጢአት ሸክም እንድናራግፍ ያደርገናል። የጠዋት ፀሀይ ለፀጉር እድገት ይጠቅማል ፤ ህያው ቃሉም እግዚአብሔር የሰጠንን ራዕይ አሳድጎ ለፍሬ ያበቃል።  የጠዋት ፀሀይ ለምሽቱ የእንቅልፍ ጊዜያችን ይረዳናል ፤ የእግዚአብሔር ቃልም የጉብዝና ወራቶቻችን አልፈው ስንደክም ስንቅ ይሆነናል። የጠዋት ፀሀይ እይታችንን ያስተካክላል ፤ ቅዱሱ ቃልም የህይወታችንን እይታ ይለውጣል። “ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው።”      መዝሙረ ዳዊት 119፥105 ተፃፈ በቦዔዝ ታምሬ ጥቅምት-25-2013 ዓ.ም በተወዳጁ ቻናል | KALTUBE "Daily Spiritual Feeding" 👇💐👇💐👇💐👇💐👇💐 @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE
Show all...
                           የአለም መንፈስ               THE SPIRIT OF THE WORLD #ያንብቡት!! #ነፃ አውጪ ትንቢታዊ ትምህርት #በመናፍስት ላይ የበላይነት የአማኞች ስልጣን ነው ●መጽሐፍቅዱሳችን በአጠቃላይ ስለ ሁለት የመንፈስ አይነት ያስተምረናል። የመጀመሪያው  የእግዚአብሔር መንፈስ ሲሆን  ሁለተኛው ደግሞ የአለም መንፈስ ነው። የእግዚአብሔር መንፈስ ሰዎችን በፅድቅና በቅድስና ይኖሩ ዘንድ በጎ ተፅዕኖ የሚያሳድር ቅዱስ መንፈስ ነው። እንደሚታወቀው መንፈስ ቅዱስ ወደ ምድር የወረደው አለማዊያንን በመውቀስ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ ለመመለስ እንዲሁም ቅዱሳንን ለማስተማር፣ለመምራት፣ ለማፅናናትና መለኮታዊ ኃይል ለመስጠት ነው። መንፈስ ቅዱስ ሰዎችን ወደ እግዚአብሔር አብ ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ የሚመልስ እና አለምን በፅድቅ ተፅዕኖ የሚያደርግ መንፈስ ነው። ● በተቃራኒው ደግሞ የአለም መንፈስ አለ። ይህ የአለም መንፈስ ከእግዚአብሔር ያልሆነ መንፈስ ሲሆን በአየር ላይ የሚሰራ የክርስቶስ ኢየሱስ ተቃዋሚ መንፈስ (ANTICHRIST SPIRIT) ነው። ተግባሩ ደግሞ የማይታዘዙትን ሰዎች በአየር ላይ ሆኖ በበላይነት መቆጣጠርና አለማዊ ተፅዕኖ ውስጥ መዝፈቅ ነው። ይህ የአለም መንፈስ የአጋንንት መንፈስ ነው።ዋናው ስራው አለመታዘዝን መስበክና የማይታዘዙትን ወይም በክርስቶስ ኢየሱስ ያላመኑትን ሰዎች ጨቁኖ ማስተዳደር ነው። ● አለም ላይ ብዙ ሰዎች በማያውቁት ኃይል እየተገፉ የማይፈልጉትን ከባባድ ወንጀል ይፈፅማሉ።የራሳቸውን ሳይሆን የመንፈሱን ፈቃድ ሳይወዱ በግዳቸው እንዲፈጽሙ ይገደዳሉ። ለምሳሌ የሚወዱትን ሰው ይገድላሉ፤ ስንት አመት ያካበቱትን ሃብትና ቅሪት በእሳት ያቃጥላሉ። ወዘተ ከዛ መጨረሻ ላይ ለምን እንዲህ እንዳደረጉ ሲጠየቁ እኔ የማውቀው ነገር የለም ወይም ምን እንደገፋፋኝ አላቅም የሚል ምላሽ ይሰጣሉ። ● ይህ ሁሉ የአለም መንፈስ የበስተጀርባ ተፅዕኖ ነው።የአለም መንፈስ የሰዎችን አዕምሮና ስሜት በመቆጣጠር የማይገባቸውን እንዲያደርጉ ግፊት ያደርጋል።የአለም መንፈስ እራሱን በስነልቦና ቀውሶች ውስጥ በመደበቅ ትልልቅ ጥፋት እያስከተለ ይገኛል። ይህ የአለም መንፈስ በዋነኝነት የስራ አድራሻውን በአየር ላይ አድርጎ የሚንቀሳቀስ መንፈስ ነው። በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም፥ በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው #በአየር ላይ ሥልጣን- እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው።ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2 : 1-2 ●ነገር ግን የአለም መንፈስ በክርስቶስ ኢየሱስ ባመኑ የእግዚአብሔር መንፈስ ባደረባቸው ቅዱሳን ላይ ምንም አይነት ስልጣን የለውም።ሃሌሉያ!   እያንዳንዱ አማኝ በክርስቶስ ኢየሱስ በመታዘዝ ካመነበት ቅፅበት አንስቶ አየር ላይ ባለው ገዢ መንፈስ ላይ የበላይ ገዢ ሆኗል።ይህ የሆነው በመታዘዝ ነው።      ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና። 1ኛ የሐ 4 : 4 ● አየር ላይ ያለው መንፈስ ቀድሞ በእኛ ላይ  ህጋዊ መብት ያገኘው ባለመታዘዛችን ነበር። አሁን ግን ለጌታ በመታዘዝ ስልጣኑ ሁሉ ከእኛ ተገፏል።የአለም መንፈስ/አየር ላይ ያለው መንፈስ/ ትልቁ አቅሙ  የሰዎች ለጌታ አለመታዘዝ ነው። አለመታዘዝ ደግሞ ኃጢአት ነው። ሰይጣን በራስ መተማመኑ የሚጨምረው ሰዎች ለጌታ ሳይታዘዙ ሲቀሩ ነው።ያኔ ባለ በሌለ ጉልበቱ ያለመታዘዝን እድል ተጠቅሞ ሰዎችን ይዘርፋል፣ይገድላል፣ ያጠፋል።       ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።  የዮሐ 10 : 10 ●እንደ አማኝ ይህን የአለም መንፈስ በክርስቶስ ኢየሱስ ስንገስፀው ሰዎችን ለቆ ይሄዳል። ለዛ ነው ላላመኑ ሰዎች መፀለይ ያለብን። እኛ ካልፀለይን ምንም ለውጥ አይመጣም። ለዛ ነው በክርስቶስ ኢየሱስ የአለም ብርሃን የተደረግነው። ተነስተን የምናበራበትና ወንጌል ለትውልድ በማወጅ ብዙዎችን ነፃ ለማውጣት ተጠርተናል።ለቤተሰብ፣ለጓደኛ ሁሉ ወንጌል መመስከር ያለብን ሰአት አሁን ነው። ያኔ አየር ላይ ያለው መንፈስ ግራ ይጋባል። ብዙዎች ካለመታዘዝ ወደ መታዘዝ ወዘር ይላሉ። ●አሁኑኑ ተነሱና በፀሎት ያላመኑ ቤተሰቦቻችሁን አስለቅቁ።ከዛ መስክሩላቸው። የአለም መንፈስ የሚዋረደው አሁን ነው። እናንተ ገዢዎች ናችሁ። እናንተ ራስ እንጂ ጅራት አይደላችሁም። ሃሌሉያ! ✍ነቢይ መሳይ አለማየሁ 👇👇👇👇👇👇👇👇 @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE
Show all...
ግራ ና ቀኝ 💐ተከታታይ ልብወለድ ክፍል ፲፭ እንደ ቀልድ መሽቶ እየነጋ እህቴ ከቤት ከወጣች 3 ቀን ሞላት እቤቱ ሊበላኝ ነው ብቸኝነቱን ከዚ በላይ መቋቋም ከበደኝ እስካሁን ትመለሳለች በኔ አትጨክንም ብዬ ነው በትዕግስት የጠበቅኳት ከዚ በላይ ግን አልችልም ሱቅ መኖሯ ስለማይቀር እዛው ሄጄ አናግራታለሁ። ሱቅ እንደደረስኩ ከደምበኛ ጋር እየተነጋገረች ነው እስክትጨርስ በሩ ጋር ቆሜ ጠበቅኳት ምን እንደምላት በውስጤ እያብሰለሰልኩ ድንገት ምን ፈለግሽ ብላ ከሰመመኔ አባነነቺኝ ላወራሽ ነዋ እቤት እንድትመጪ ልጠይቅሽ ካላንቺ እዛ ቤት ውስጥ መኖር አልቻልኩም ብቸኝነቱ ከብዶኛል ከምንም ነገር በላይ ደሞ ናፍቀሽኛል እባክሽ ተመለሽ ብዬ እግሯ ላይ ተደፋሁ ተነሽ ምን እየሆንሽ ነው በዚ መንገድ መቼም ይቅር አልልሽም አሁን ሰው ቢመጣስ እባክሽ ግር ግር አትፍጠሪ ብላ አስነሳቺኝ እሺ በምን መንገድ ይቅር ትይኛለሽ ምን እንዳረግ ነው የምትፈልጊው እኔ የፈለግሽውን ለማረግ ዝግጅ ነኝ መቼም ቢሆን እደጅ አላድርም አምሽቼም አልገባም ብቻ ይቅርታ አድርጊልኝ እ ማሃዬ ብዬ ከአፏ የእሺታ ምላሽ መጠባበቅ ጀመርኩ እሷ ግን ያልጠበቅኩትን ምላሽ ሰጠቺን እኔ ይቅር የምልሽ ወደቤትም የምመለሰው እደጁ ማምሸቱን ማደሩን ስትተይ ብቻ ሳይሆን እስከነ ጭራሹ ሱስሽን እርግፍ አርገሽ ስትተይ ያኔ ወዳንቺ እመጣለሁ ካለዛ ግን ይቅርታን እንዳታስቢው አለች የምር እውነት አልመሰለኝም እየቀለድሽ ነው አልኳት የምን ቀልድ ጨዋታ የያዝኩ ይመስልሻል በሂወት ቀልድ የለም አሁን ገንዘብ ካስፈለገሽ ልስጥሽ እና ሂጂ ባልኩሽ ነገር ላይም አስቢበት እና መልስ እፈልጋለሁ ለነ አባዬም ቢሆን ሁሉን ነገር ከመናገሬ በፊት በውሳኔሽ ላይ በደምብ ደግመሽ ደጋግመሽ አስቢበት ብላ ከቦርሳዋ ውስጥ ገንዘብ አውጥታ ወደኔ ዘረጋችልኝ (ያሁኑ ይባስ ለነ አባዬ ከነገረቻቸው ሁሉ ነገር ያበቃል ከቤት ወጥቼ ስራ ገቢ የምኖርበት ሳይኖረኝ ምንልሆን ነው) ወደዘረጋችልኝ እጆቿ እያየሁ አይ ብር አለኝ አልፈልግም አልኳት እና ለደቂቃዎች በማህላችን ዝምታ ነገሰ የቀረ የምናወራው ነገር አለ ብላ ዝምታውን ሰበረችው ሂጂልኝ ማለቷ እንደሆነ ገባኝ ኧረ የለም ምን ቀረ ብዬ እንደ እብድ ሳቅኩ አንጀቴ እያረረ ሳቄ ግን አሸነፈኝ ለምን እንደሳቅኩ ግን አላውቅም አሀሀሀሀሀሀ አለቀልኝ በይኛ እህህህህህህ ጓዳና ልወጣነው ክክክክክ ወይ መጨረሻዬ እህህ(በረጅሙ ተነፈስኩ ሳቄን እምባ ወረሰው) አንቺም ጨከንሽብኝ እሺ ብዬ ወጣሁ በሁኔታዬ ግራ ተጋብታለች ልትጠጋኝ ብላ ደሞ ተመለሰች ከሱቅ ከወጣሁ በሗላ ከአይኖ እስክሰወር ድረስ ቁማ ስታየኝ ነበር አሁን ይበልጥ ባዶነት ተሰማኝ ቆይ ምን ላረግ ነው ሁሉን ነገር እንደቀልድ መተው እኳ ከባድ ነው እንዴት እችላለሁ በማይመጣው መጣችብኝ ደካማ ጎኔን ተጠቅማ በጭንቀት አሰረቺኝ ምንም ባስብ ልለውጠው አልቻልኩም ብቻ መኪናዬን እራሴን ወደምደብቅበት መጠጥቤት በፍጥነት እቸጋለብኩ ነዳሁት ©በያኔት ማስረሻ ...........ይቀጥላል........... Share💚Share💚Share💚 @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE
Show all...
                   እውነታዎች (Realities) ሰሞኑን ወደ አዕምሮ የተለያዩ ጥሩ ጥሩ ሐሳቦች ይፈሱ ነበር።ከዛ ሐሳቦቹን በሙሉ ሰብሰብ አድርጌ በአጫጭር ፅሑፍ ላካፍላችሁ ወደድሁ። ✦ሰይጣን ወደ ኢየሱስ መጥቶ ድንጋዮቹን ዳቦ እንዲያደርግ ሲፈትነው ያላወቀው ነገር ቢኖር ሰይጣንን እራሱን ወደ ዳቦነት መቀየር እንደሚችል ነበር። ✦ሁሌም ሚዛናዊ አመለካከትን አዳብር። ሚዛናዊነት ያለው አስተሳሰብ፣ንግግር እና ምልከታ ማዳበር መልካም ነው። ✦በአሉባልታ ብቻ ነገሮችን መወሰን የብዙ የህይወት ችግሮች መንስዔ ነውና ነገሮችን ከመወሰንህ በፊት ቢያንስ ሶስት ጊዜ ተዘጋጅበት።      አንደኛ ፀልይበት፣ሁለተኛ አስብበት፣ሶስተኛ ተማከርበት ✦ለአላማህ መሳካት ከማያስፈልጉ ሰዎች በራቅህ ቁጥር አላማህን በቀላሉ ወደማሳካት ትመጣለህ። ✦ አንድ እርምጃ ወደፊት እንትድሄድ ከሚረዱህ ጋር እንጂ ወደኋላ ከሚያስቀሩህ ሰዎች ጋር ጉዞ አትጀምር። ✦ስላንተ ትኩረት ከሌላቸው ሰዎች ጋር ብዙ ለመስራት አትታገል። ✦ሰውን ሁሉ ለማስደስት ስትሞክር አቋም የለሽ ሆነህ እንዳትገኝ በመልካም አቋምህ ፅና። ✦ትናንትን መማርያ መጽሐፍ አድርገው።ዛሬን ደግሞ የተማርከውን መተግበሪያ አድርገው። ✦ጠንካራ አስተሳሰብና ስሜትን እየገነባህ ስትመጣ የማንም መንደርተኛ ንግግርና አሉባልታ ህይወትህን ማነቃነቅ አይችልም። ✦ያላረከውን አድርገሃል ተብለህ ስትከሰስ ጠበቃው ኢየሱስ በስራ ላይ ስለሆነ አትፍራ።ጠበቃው በነፃ ያሰናብትሃል። እንኳንስ ንፁህ ሆነህ ወንጀለኛም ሆነህ ምህረቱ ካንተ ጋር ነውና። ✦በአሉታዊ አስተሳሰቦች ከተሞሉ ሰዎች ጋር በጥበብና በጥንቃቄ ካልተመላለስክ አንተም የነሱ ቡድን አባል መሆንህ አይቀርም። ✦ከምታደርገው ድርጊት በስተጀርባ ሰብአዊነትና መንፈሳዊነት ሲኖር በሰው ፊት ምስጉን በእግዚአብሔር ፊት ደግሞ ብሩክ ትሆናለህ። ✦ሁሌም ህይወትህ በነዚህ ሶስት አይነት ሰዎች ሲታጀብ ያማረ ነው። 1ኛ እንደኛ የምተከተላቸው ሰዎች( 2ኛ አብረህ የምትጓዛቸው እኩዮች ፣ 3ኛ የምታስከትላቸው ወይም አንተ አርአያ የሆንክላቸው ሰዎች፣ ✦ክፉ ሰዎች መልካም ሰዎችን እንዳታይና እንዳታመሰግን ልብህን እንዳያሻክሩት ተጠንቀቅ። ✦ቂም መያዝ ረጅም መንገድ ለመጓዝ አስበህ መንገድ ላይ ዘግይቶ እንደመቅረት ነው። ቂም ሰዎች ከህይወት ፍፃሜያቸው ጋር እንዳይገናኙ እንቅፋት ይሆናል። ✦እውነተኛ ባለ ራዕይ ብዙዎችን ይቅር እያለ ወደፊት የሚሄድ ሰው ነው። ✦በቀን 490 ጊዜ ባለንጀራህን ይቅር በል ያለው ጌታ በቀን ስንት ጊዜ ይሆን እኛን ይቅር የሚለን?! ✦ጨለማ ውስጥ መልክ የለም።ጨለማ ውስጥ ሁሉም ነገር ጥቁር ነው። ጨለማ ውስጥ ልዩነት የሚያመጣው ብርሃን ብቻ ነው።በክርስቶስ የአለም ብርሃን ነን ተነስተን ስናበራ ጨለማ ያበቃለታል። ✦ስኬት ብዙ ሰዎች የተስማሙበት ብቻ ሳይሆን ብዙ ሰዎች የተቃወሙትም ሊሆን ይችላል።ስለ ስኬት ያለህ መረዳት የስኬትህ ጅማሬ ነው። ✦ፀሎት የእግዚአብሔርን ሐሳብ ማስቀየርያ ሳይሆን ማስፈፀሚያ መንገድ ነው። ✦ስትሞገስ በርታ፣ስትነቀፍ ደግሞ በጣም በርታ። ✦እግዚአብሔር በአንተ አልፎ ሲሰራ ሁሌም ሶስት አይነት ሰዎች አሉ፤         1ኛ ተሳታፊዎች  2ኛ ታዛቢዎች  3ኛ ተቃዋሚዎች ✦እግዚአብሔር ዘላለማዊ እንጂ ዘመናዊ ሐሳብ የለውም። ✦የፈሰሰ ውሀ የማይታፈሰው በምድራዊ ስርዓት እንጂ በመለኮታዊ ስርዓት ውስጥ አይደለም። ✦በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት የሚያስገኝልን የድርጊታችን ሁኔታ ሳይሆን የልባችን ሁኔታ ነው። ✦የእምነትህ መጠን የሚለካው በይዘት ሳይሆን በስራ ነው። የእምነትህ ታላቅነት የሚለካው በእምነት በምታደርጋቸው ታላላቅ ስራዎች ነው። ✦ሰይጣን መቼም ቢሆን ትክክለኛውን የህይወትህን ክብደት አይነግርህም። ወይ  በትዕቢት እንድትነፋ ኪሎህን ጨምሮ ይነግርሃል አሊያም ደግሞ  የበታችነት እንዲሰማህ ከኪሎ በታች እንደሆንክ ይነግርሃል።ለመሆኑ እንደ አማኝ እራስህን ለመመዘን ወዴት ይሆን የምትሄደው? ✍በነቢይ መሳይ አለማየሁ  👇👇👇👇👇👇👇👇 @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE
Show all...
Bereket Tesfaye -ክርሰቲያን ነኝ 👌 https://www.youtube.com/watch?v=k99PuyLT3gY
Show all...
በረከት ተስፋዬ Chirstian Neng By Bereket Tesfaye ክርስቲያን ነኝ

Do not Forget to susbscribe to my channel Note: Unauthorized distribution and re-upload of this content is strictly prohibited Get Bereket Tesfaye Latest Album,

https://itunes.apple.com/us/artist/be​...

https://play.google.com/music/listen?​...

Subscribe to

https://www.youtube.com/channel/UCD7n​...

https://www.facebook.com/BereketMusic/​

telegram

https://t.me/bereketesfaye?fbclid=IwA​...

Instagram

https://www.instagram.com/singerberek...

የሱስን በማመኔ የሞተዉ መንፈሴ ነቃ ህይወት የሰጠኝ ጌታ ለየኝ ከነገድ ከቋንቋ በወንድ ፈቃድ ስይሆን መወለድና እድገቴ በልጁ የወለደኝ የሰማዩ አባቴ ከአብ ተወልጃለዉ አይደለዉ ምድራዊ ዘሬ ሰማያዊ ከነገድ ከቋንቋ እስሬን የፈታ ኢየሱስ የኔ ጌታ አብ የናቀዉን አላከብር አልገኝ ዘር ቆጠራ ሰፈር ጌታ ሰዉን እንደሚያይ አያለዉ ብሄሩን ሳላይ ሰዉን ወዳላዉ ከአብ ተወልጃለዉ አይደለዉ ምድራዊ ዘሬ ሰማያዊ ከነገድ ከቋንቋ እስሬን የፈታ ኢየሱስ የኔ ጌታ የዘር መርገም ነበረ ከላዬ ሰብሮት እንጂ ኢየሱስ ጌታዬ ከአዳም ዘር ፈልቅቆ አዉጥቶ የራሱ ዘር አርጎኛል ዋጅቶ በቃሉ ፃድቅ ብሎኛል የፍቅር እጁ ተዘርግቶልኛል የማይገባኝ ለመቆም ፊቱ ልጁ አደረገኝ ሸሎሞ ቤቱ ዘማሪት አይዳ ክርስቲያን የ ብሄር የብለይ…

ግራ ና ቀኝ 💐ተከታታይ ልብወለድ ክፍል ፲፬ ምን ቀን ነው የአብቃልን ያወቅኩት በሱ ምክንያት የሂወት መስመሬ እየተንገዳገደ ነው ያለፈ ማንነቴን ሁሌ አስታውሰዋለሁ መርሳት ብፈልግም እሱ አካባቢ በሄድኩ ቁጥር ይበልጥ አስታውሰዋለሁ መፍትሔውስ ለሚለው ጥያቄ መልሱ የሚሆነው መጋፈጥ ካልቻልኩ መሸሽ ነው አይምሮዬ ይሄን ያስባል ልቤ ግን ሌላ ነው ሌላው ቢቀር ውሸታምነቴን ሲያቅ ምን እንደሚለኝ ሳስብ እፈራለሁ የመጠጥ የሀሺሽ ሱስ ያለባትን ሴት ለሚስትነት ማን ይመኛታል እንኳን በመንፈሳዊ ህይወቱ የበረታ ወንድ ቀርቶ ድርዬ ወንድ እንኳን ሱሰኛ ሚስት አይፈልግም አንዳንዴ ምናለ በሌላ አጋጣሚ ተዋውቀን በሆነ ብዬ እመኛለሁ ደሞኮ የማውቀው እኔ እሱን እንደምወደው እንጂ እሱ ስለኔ የሚያስበውን አደለም ግራ ግብት ያለ ነገር ... በሂወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ውጪ አደርኩ ንጋት ላይ አንድ አስተናጋጅ ከእንቅልፌ ቀስቅሶ ከቤት ቤቱ ሊዘጋ መሆኑን ነግር እንድወጣ ጠየቀኝ በምን ጊዜ እንቅልፍ እንደወሰደኝ ባላውቅም ብርጭቆውን በጄ እንደያዝኩ ጠረቤዛው ላይ በግንባሬ ተደፍቻለሁ ልክ እንደቀሰቀሰኝ አይኖቼን እያሻሸሁ በስካር በዛለ ሰውነቴ ወደዚ ወደዛ እየተምታታሁ ወደ ቤት ለመሄድ ተነሳሁ ግን ያስጨነቀኝ ነገር ቢኖር የእህቴ አይን ማየት ነው የፈለገ ባመሽ አንግቼ ግን አላቅም ይሄኔ ስንቱን እያሰበች ይሆናል ወይ ደሞ በንዴት ጦፋ እየተንጎዳጎደች እስክመጣ እየጠበቀቺኝ ይሆናል አዎ እንዳሠብኩት ሶፋ ላይ ጋቢ ለብሳ ተቀምጣለች ገና በሩን ከፍቼ ከመግባቴ ተስፈንጥራ ተነሳች ምን ሆነሽ ነው ስደውል አታነሺም ምን ተፈጥሮ ነው ብላ በጥያቄ አጣደፈችኝ አይ ምንም እንቅልፍ ወስዶኝ ነው ምንም ሆኜ አደለም ብዬ አስተባበልኩ ግን ነገሩ በዚ አላበቃም ማታ እዚ እንደምታድሪ ነግረሺኝ ክፍልሽ ገባሽ ከዛ እኔን ካስተኛሽ በሗላ ወድያው ወጣሽ ላስቆምሽ እንኳን አልቻልኩም በጣም ፈጠንሽ ይባስ ብለሽ ንጋት 12:00 ላይ መጣሽ እኔ ለሊቱን በጭንቀት እንዴት እንዳሳለፍኩ ታውቅያለሽ የሆነነር ሆነሽ ቢሆንስ ተመተሽ ወይም ፆታዊ ጥቃት ደርሶብሽ ሆኖ ቢሆን ሰው የምሆን ይመስልሻል (እያለቀሰች) ይበቃኛል የእስከዛሬው ትዕግስቴ ከዛሬ ነገ ትሻሻያለሽ ብዬ መገመቴ ሞኝነት ነው አሁን አንቺን የማላይበት ቤቱን ለቅቄ እወጣልሻለሁ ያኔ እንደፈለግሽ ትሆኚበታለሽ ብላ ጥላኝ ሄደች ማሂ ማሂ ብላትም ዘጋቺኝ እዛው በቆምኩበት ተንሸራትቼ ወደቅኩ በጣም ስቅስቅ ብዬ ነው ያለቀስኩት ለምን ለምን ለምን ሂወቴ ለምን እንደዚ ሆነ ለምን በኔ ምክንያት ሰው ይጎዳል ለምን አልሞትም እእህ ማሂ ሻንጣዋን ይዛ መጣች ከምር አምርራለች ሳግ እየተናነቀኝ የት ልትሄጂ ነው ቆይ እኔስ ብቻዬን ምን እሆናለሁ አላሳዝነሽም አልኳት እሱን ማሰብ የነበረብሽ ቀድመሽ ነበር አሁን አደለም ከፊቴ ዘር በይ ብላ አምባረቀችብኝ በምንም ላስቀራት አልቻልኩም ሻንጣዋን እየጎተተች ወጣች ©በያኔት ማስረሻ ...........ይቀጥላል........... Share💚Share💚Share💚 @KALTUBE @KALTUBE @KALTUBE
Show all...
የእየሩሳሌም ነጊያ አዲስ አልበም በብዙ ትጋት የተሰራ አልበም ነው። እባካችሁ እንዲሁ በቀላሉ በቴሌግራም ቻናል መልቀቅ ምን ማለት ነው ቢያንስ እንኳን ሁሉም Track YouTube ላይ Upload ተደርጎ እስኪያልቅ ድረስ ታገሱ ። የለቀቃችሁ ብዙ ቻናሎች አላችሁ ከዚህ ተግባራችሁ ብትቆጠቡ መልካም ነው። የእየሩሳሌም ነጊያ አዲስ አልበም ከመዝሙር መሸጫዎች ሲዲውን በመግዛት ወይም በእነዚህ ሊንክ አውርዱ❤️❤️ Spotify https://open.spotify.com/album/6aljuxGNs90ZXATRfhavpw Apple Music https://music.apple.com/us/album/yetsegawin-quribet-vol-3/1570016382 Youtube https://www.youtube.com/channel/UCfDm9KT5NCiY9X_scwSqP_A Telegram @JerriNegiya 💐@KALTUBE 💐@KALTUBE
Show all...
Yetsegawin Quribet, Vol. 3

Eyerusalem Negiya · Album · 2021 · 14 songs.

ክርስቲያን ሆይ ዓለም ብታሳድደን የምትገፋን ወደ መንግሥተ ሰማያት ነውና በዚህ እውነት ደስ ይበለን። ቦዔዝ ታምሬ S.P Quote - Friday/Sunday sнαяє💐ѕнαяє💐ѕнαяє💐 ©ቃል-ቲዩብ @KALTUBE @KALTUBE
Show all...