en
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Top Mereja

Channel Top Mereja (@topmereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 338 subscribers, ranking 10 174 in the News & Media category and 1 514 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 338 subscribers.

According to the latest data from 04 October, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -234 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 October, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 338
Subscribers
No data24 hours
-547 days
-23430 days
Posts Archive
ጥቆማ ‼️ በአማራ ክልል ወቅታዊ የጦርነት መረጃዎች በፍጥነት የምታገኙበት የመረጃ ገፅ ➘ Join በማለት ተቀላቀሉ 👇 https://t.me/+9O_tmq0LF9RiZjk0 https://t.me/+9O_tmq0LF9RiZjk0

የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል የሚያቀናጅ ኮማንድ ፖስት ተቋቋመ ! ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም. (August 6, 2023) ከአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተሠጠ አስቸኳይ መግለጫ የአማራ ሕዝብ ላለፉት ረጅም ዓመታት እንደ ሕዝብ ሲደርስበት የነበረውን መስፈሪያ-የለሽ መከራ፣ አገርና ሕዝብን ለማቆየት ሲል ስቃዩን ችሎ ሰላማዊ የለውጥ ሁኔታ ይፈጠራል በሚል ሲታገስ ቆይቷል። ትዕግሥቱን ፍርሃት፣ ዝምታውን የተሸናፊነት፣ መንግሥት ማክበሩን እንደ አላዋቂነት ተወስዶ በመከራ ላይ መከራ ሲደራረብበት ቆይቷል። ይህ ሁሉ የአማራው ታጋሽነት የአገርን ሕልውና ከአደጋ ለመጠበቅ፣ የንጹሃን እልቂትን ለማስቀረትና በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ መፍትሄ ይገኛል ከሚል ፍጹም ስልጡንነት ነበር። ሆኖም የአብይ አህመድ የኦሮሙማ የፓለቲካ አይድዮሎጂን ተከትሎ፣ የአማራውን ሕህዝብ፣ ከክርስትናና ከሙስሊም እምነት ተከታዮች ጋራ አጥፍቶ፣ በምስራቅ አፍሪካ የኩሽ ግዛት ለመፍጠር የጀመረው የፋሺዝም የዘር ማፅዳትና የመስፋፋት ፓሊሲ ከኢትዮጵያም አልፎ በመላው አፍሪካ ቀንድ አገሮች ላይ ታላቅ የፀጥታ ችግር ፈጥሮ፣ ቀጠናውን የኃያላን ጦር አውድማ ሳያደርገው ኢንተርናሽናል ኮሚኒቲው አስፈላጊውን ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ይህ የጉግማንጉግ ሰው-በላ የአራዊት አገዛዝ ለሠላም የተዘረጋውን የሕዝባችንን እጅ ለመቁረጥ ምሳሩን መዞ እልቂትን አውጇል። ዐማራው ህልውናውን ለመከላከል ያለው ብቸኛ አማራጭ ኃይል ብቻ በመሆኑ ሳይወድ በግድ በጠላቶቹ ጋባዥነት ወደ ለየለት ጦርነት ውስጥ ገብቷል። የአማራ ሕዝብ በአሁኑ ወቅት የአብይ አህመድ የኦሮሙማ-ኦህዴድ-ኦነግ አገዛዝን ወረራ ለመመከት በበርካታ ግንባሮች እየተፋለመ ይገኛል። ሕዝባችን እየተፈጸመበት ያለውን መረን-የለሽ ጭፍጨፉ፣ አፈናና ግድያ ዝም ብሎ ከመመልከት ወደ ሁለገብ የተከላካይነት ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተጋድሎው ግለትና የጦር ግንባሩ ስፋት አማራው የሚያደርገውን ትግል በበለጠ ውጤታማና አሸናፊ እንዲሆን የተቀናጀ አመራር የሚሰጥ አካል ማዋቀር አስፈልጓል። ይህንንም የሚያቀናጅ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሟል። የአማራው የተለያዩ ክፍላተ አገሮች፣ በሥራቸው የፋኖ ብርጌዶች ያሏቸው ኮማንድ ፖስቶች ሲኖሯቸው፣ እነዚህንም በበላይነት የሚያስተባብረው ጀግናው አርበኛ ሉቴናንት ኮረኔል ፉንታሁን ሙሃባ ነው። የኮማንድ ፖስቱ ዓላማዎች፡- * ክልሉን ሙሉ በሙሉ ከጠላት ለማፅዳት የተባበረና የተቀነባበረ ትግል እንዲካሄድ ማድረግ፤ * ነፃ የወጡ ከተሞችን ጥበቃ እንዲኖራቸውና ሕዝባዊ አስተዳደር በማዋቀር የአገልግሎት ተቋማት ስራቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ፤ * ትግሉን ለመቀላቀል የሚፈልጉ ኃይሎችን ማሰልጠን፣ ማስታጠቅና ለትግል ማሰማራት፤ * የሎጅስቲክስ አቅርቦትን ለማሳለጥና፣ ጉዳት የደረሰባቸውን በመንከባከብ እርዳታ እንዲያገኙ ማመቻቸት፤ * የጠላት ምርኮኞችንም ዓለም ዓቀፍ ህግ በሚፈቅደው መሠረት መጠብቅ፣ ተጸጽትውና ይቅርታ ጠይቀው ከወገን ጦር እንዲቀላቀሉ መሞከር፣ ወይም ወደፊት ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ። ይህንንም ሕዝባዊ ዓላማ ለማሳካት የተቋቋሙት ኮማንድ ፖስቶችና ብርጌዶች የሚከተሉት ናቸው፡ ኮረኔል ፉንታሁን ሙሃባ አጠቃላይ የኮማንድ ፖስቶቹ የበላይ አስተባባሪ ከመሆኑም በተጨማሪ የወሎን ብርጌዶች ኮማንድ ፖስት ይመራል፡፡ ብርጌዶቹ:- * አንደኛ ብርጌድ * ሁለተኛ ብርጌድ * አሳምነው ብርጌድ-ላሊበላ እንዲሁም ይህ ኮማንድ ፖስት ከምስራቅ አማራ ፋኖ ዋና አዛዥ አርበኛ ምሬ ወዳጆ ጋር በመመካከር ተናቦ እንዲታገል ተዋቅሯል፤ በጎንደር ያሉ ብርጌዶች ኮማንድ ፖስት በጊዜያዊነት በሻለቃ አንተነህ ይመራል፡፡ ብርጌዶቹ፦ * ምኒልክ ብርጌድ * ቆስቁስ ብርጌድ * ደቡብ በጌምድር ብርጌድ * ቋረኛው ብርጌድ የሽዋ ኮማንድ ፖስትን የሚመራው በሻለቃ መከታው ሲሆን በእዙ ሥር አራት ብርጌዶች ይኖራሉ፡፡ የጎጃም ኮማንድ ፖስት፦ * ብርጌዶቹ * የበረኸኛ ብርጌድ ኮማንድ ፖስቶቹ የዓማራ ሕዝባዊ ኃይሎች ባሉበት ቦታ ሁሉ ተናበውና ተባብረው ይሠራሉ። ሌሎችም ብርጌዶች በሂደት ወደፊት ይካተቱበታል። እንዲሁም በውይይት ላይ ያሉ በተለያየ የፋኖ አደረጃጀት የተዋቀሩ የቁርጥ ቀን ልጆች በሚያደርጉት ትግል፣ ሁሉም ተቀናጅቶ በአንድ ሠፊ ግንባር እንዲዋቀሩ መሬት የረገጠ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። ለጊዜው ከተፈጠረው አጣዳፊ ሁኔታ አኳያ ከላይ የተዘረዘሩት የፋኖ ብርጌዶች በአንድ ዕዝ ሥር ተናበውና ተደጋግፈው ለመታገል የጋራ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ለሕዝብ ስናሳውቅ በታላቅ ኩራት ነው። በዚህ ኮማንድ ፖስት የተካተቱትንም ሆነ በየአካባቢው ከጠላት ጋር የሚፋለሙትን ሁሉ፣ ወገናችን በሚችለውና ባለው አቅሙ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው አደራ እንላለን። በመጨረሻም በአገር መከላከያ ሥር ተሰልፈህ አገር ለመጠበቅ አደራ የተቀበልክ ሠራዊት፣ ጦርነቱ በሕዝብና በጥቂት አንባገነንና ጨፍጫፊ የብልጽግና ፋሽስታዊና ዘረኛ መሪዎች መካከል መሆኑን አውቀህ ከሕዝባዊ ፋኖዎች ጋራ እንድትቀላቀል፣ ወይም በብልጽግና መሪዎች ላይ አፈሙዝህን እንድታዞር ታሪካዊ ጥሪ ቀርቦልሃል። በዚህ ጦርነት ግፉና መስዋዕትነቱ የከፋ ቢሆንም፣ የአብይ አህመድ ፋሺስታዊው የኦሮሙማ ሰው-በላ አገዛዝ ፈጽሞ አገር የመምራት እድል ከእንግዲህ ወዲያ አይኖረውም። ከግብረ-አበሮቹም ጋራ ለፍርድ የሚቅርብበት ጊዜ ሩቅ አደለም። ስለሆነም በተለያየ የመንግሥት ሃላፊነት ላይ ያላችሁ ባለስልጣናት፣ በውጭ የዲፕሎማሲ ስራ የተሰማራችሁ፣ አገዛዙን በተለያየ መንገድ የምታገለግሉ፣ ከዚህ ሕዝብ ጨፍጫፊ ሥርዐት እራሳችሁን በጊዜ እንድታገሉ ሞራላዊና ሕሊናዊ ግዴታ አለባችሁ። ለለውጥ የተነሳው ሕዝብ እየደረሰበት ያለውን መከራ ችላ ብላችሁ ከአራጁ አገዛዝ ጋር ከቀጠላችሁ ሕዝባችን በእናንተ ላይ ሊያደርሰው የሚችለውን የበቀል እርምጃ ማስቆም የሚችል ኃይል አይኖርም። ለሃያ ሰባት ዓመታት የሕወሃት/ኢህአዴግን፣ እንደዚሁም ላለፉት አምስት ዓመታት የኦህዴድ ኦነግ/ብልጽግናን የግፍ ጽዋ የቀመሳችሁ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሆይ! የአማራ ሕዝብ ለህልውናው ብሎም ኢትዮጵያ እንደአገር እንድትቀጥል ለሚከፍለው ከፍተኛ መስዋእትነት የድርሻችሁን እንድትወጡ ወገናዊ ጥሪ ቀርቦላችኋል። የአማራ ሕዝብ በልጆቹ መስዋዕትነት ያሸንፋል! መነሻችን የአማራ ሕልውና፣ መዳረሻችን የኢትዮጵያ አንድነት! የአማራ ሕዝባዊ ግንባር! @topMereja

ሰበር ዜና!! ሆቴሎች ተመቱ! ዉጊያዉ ቀጥሏል | ፋኖ ዋና ከተማዋን ተቆጣጠረ ተረጋገጠ | ማረሚያ ቤቱ ተቃጠለ! አነደዱት https://youtu.be/AD_I6fWghsA

ከአዲስ አበባ ከተማ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ የተሰጠ መግለጫ ! በአዲስ አበባ ከተማ የማህበረሰቡን እሴቶች፤ ሃይማኖታዊና ባሕላዊ ትውፊቶች እንዲሁም ስነ-ልቦና የሚጎዱ እና በማህበረሰባችን ዘን
ከአዲስ አበባ ከተማ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ የተሰጠ መግለጫ ! በአዲስ አበባ ከተማ የማህበረሰቡን እሴቶች፤ ሃይማኖታዊና ባሕላዊ ትውፊቶች እንዲሁም ስነ-ልቦና የሚጎዱ እና በማህበረሰባችን ዘንድ ያልተለመዱ መጤ ልምምዶች እየታዩ ይገኛል ያለው ቢሮው፣ በአንዳንድ ሆቴሎች የግብረ-ሰዶም እንቅስቃሴዎች እንዳሉ ለቢሮው የደረሱ የጥቆማ መረጃዎች ያሳያሉ ብሏል። ቢሮው ባወጣው መግለጫ፣ በከተማችን ያሉ ሆቴሎች እና ሬስቶራንቶች በአጠቃላይ የቱሪስት አገልግሎት መስጫ ተቋማት የሀገራችንን ባህል፣ እሴት እና እምነት አክብረው እና የአገሪቱን የቱሪዝም ሥነ-ምግባር ደንብ ጠብቀው እንዲሰሩ ይገደዳሉም ብሏል። ተቋሙ የማህበረሰባችንን እሴቶች እና ሃይማኖታዊ ትውፊቶች የሚሸረሽሩ ሥነ-ልቦናን እና ሞራልን የሚጎዱ አሉታዊ ተግባር ላይ ተሰማርቷል በሚል ከህብረተሰቡም ሆነ ከባለድርሻ አካላት በኩል የሚቀርብ ጥቆማ ካለ ተጨባጭነቱን በማረጋገጥ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣንና ሀላፊነት መሰረት ተገቢውን ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ የገለፀ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ከዚህ ፀያፍ ተግባር ጋር በተገናኘ ማንኛውንም መረጃ በአቅራቢያው በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ጥቆማ እንዲያቀርብ ጠይቋል። @topMereja

ሰበር ዜና!!👇👇 https://youtu.be/uSY8FajqBVc

ሰበር ዜና!! ጉድ ተሰማ ሙሉ መረጃ👇👇 https://youtu.be/GD6uTB2KmZ0

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ያለው ኹኔታ እንዳሳሰባቸው ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ጋር ትናንት ማምሻውን ባደረጉት የስልክ ውይይት ላይ መግለጣቸውን መስሪያ ቤታቸው አስታውቋል። ብሊንከን፣ የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሃት የደረሱበት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸሙ ያሳየውን እድገት በውይይቱ ላይ እንዳነሱ ተገልጧል። ብሊንከንና ጠንካራ ቁጥጥር የተዘረጋበት የምግብ ዕርዳታ ሥርጭት ሥርዓት በኢትዮጵያ በመዘርጋት አስፈላጊነት ዙሪያ ከዐቢይ ጋር ተወያይተዋል። @topmereja

ሰበር ዜና!! https://youtu.be/3NxjChIYyP0

" እንደአስፈላጊነቱ #በየትኛዉም የሃገሪቱ አካባቢ ተፈፃሚነት ይኖረዋል " - የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6 /2015 አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በዋነኝነት በ " አማራ ክልል " ተፈፃሚ ቢሆንም እንደ አስ
+1
" እንደአስፈላጊነቱ #በየትኛዉም የሃገሪቱ አካባቢ ተፈፃሚነት ይኖረዋል "  - የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6 /2015 አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በዋነኝነት በ " አማራ ክልል " ተፈፃሚ ቢሆንም እንደ አስፈላጊነቱ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ላይ ተፈፃሚ ይሆናል ተብሏል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6 / 2015 በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደር እንዲሁም በክልሉ አስተዳደር የሕዝብን ሠላም እና ፀጥታ ለማስከበር የሚወሰድ እርምጃን ፣ በክልሉ ወይም በሃገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የፀጥታ ችግር የሚያባብስ ማንኛውንም እንቅስቃሴ ወይም ሁኔታን በሚመለከት እንደ አስፈላጊነቱ በየትኛዉም የሃገሪቱ አካባቢ ተፈፃሚነት እንደሚኖረው ተገልጿል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ ለስድስት (6) ወራት የፀና እንደሚሆን የተገለፀ ሲሆን የስድስት (6) ወር ጊዜ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአዋጁ ተፈፀሚነት ቀሪ የሚሆንበትን ጊዜ ሊወስን ይችላል ተብሏል። @topmereja

ሰበር ዜና! ዋናዉ የጦር መሪ ተገደሉ! | ፋኖ ሌላ ትልቅ ከተማ ያዘ | ጎጃም ጎንደር ወሎ ሰበር መረጃዎች👇👇 ሙሉ ዝርዝሩን ሊንኩን በመጫን ይመልከቱ https://youtu.be/mtfcEs-IEfk
ሰበር ዜና! ዋናዉ የጦር መሪ ተገደሉ! | ፋኖ ሌላ ትልቅ ከተማ ያዘ | ጎጃም ጎንደር ወሎ ሰበር መረጃዎች👇👇 ሙሉ  ዝርዝሩን ሊንኩን በመጫን ይመልከቱ https://youtu.be/mtfcEs-IEfk

አማራ ክልል ራያ ቆቦ የሞባይል ዳታ ኢንተርኔት ተለቋል @topmereja

ሰበር ሰበር ሰበር👇👇 ሊንኩን በመጫን ይመልከቱ👇👇 https://youtu.be/bjX8nAP-hNE
ሰበር ሰበር ሰበር👇👇 ሊንኩን በመጫን ይመልከቱ👇👇 https://youtu.be/bjX8nAP-hNE

ሰበር ዜና! ባለስልጣኑ በፋኖ ተገደሉ! | ጦርነቱ ቀጠለ ጎንደር ቀዉጢ ሆነ | ፋኖ 4 ከተማ ተቆጣጠረ https://youtu.be/GfxgHjA7jLI
ሰበር ዜና! ባለስልጣኑ በፋኖ ተገደሉ! | ጦርነቱ ቀጠለ ጎንደር ቀዉጢ ሆነ | ፋኖ 4 ከተማ ተቆጣጠረ https://youtu.be/GfxgHjA7jLI

ሰበር ዜና ‼️ ቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ ክህደት ባደረጉ እና ሕገወጥ ሢመት የፈጸሙ ጳጳሳትን ከቤተክርስቲያን አንድነት አውግዞ ለየ ! ቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣ
ሰበር ዜና ‼️ ቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ ክህደት ባደረጉ እና ሕገወጥ ሢመት የፈጸሙ ጳጳሳትን ከቤተክርስቲያን አንድነት አውግዞ ለየ ! ቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ ክህደት የፈጸሙ ጳጳሳት ተግባራቸው ምንፍቅና በመሆኑ በሕይወታቸውም ሆነ በሞታቸው የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት እንዳያገኙ በመወሰን ከቤተ ክርስቲያን አንድነት አውግዞ ለየ። የተወገዙት የቀድሞ ጳጳሳት "አባ" ኢሳይያስ "አባ" መቃርዮስ "አባ" መርሐክርስቶስ "አባ" ጴጥሮስ ሲሆኑ ተሹመናል የሚሉ መነኮሳትን አውግዞ መለየቱን በአሁኑ ሰዓት እየሰጠ ከሚገኘው መግለጫ ለመረዳት ተችሏል። @topMereja

በሰፈሩት ቁና አይቀርም ፓለቲካ እና ጭካኔወቹ !! ሌሎች ሊማሩበት የሚገባ እንድሁም አለምን ያሳዘነ ፎቶ!! ይህ ከዚህ በታች በፎቶ የምትመለከቱት ሰው ኮሌኒየል ኢብራሂም ሸምሰዲን ይባላል።ድሮ የሱዳን
+2
በሰፈሩት ቁና አይቀርም ፓለቲካ እና ጭካኔወቹ !! ሌሎች ሊማሩበት የሚገባ እንድሁም አለምን ያሳዘነ ፎቶ!! ይህ ከዚህ በታች በፎቶ የምትመለከቱት ሰው ኮሌኒየል ኢብራሂም ሸምሰዲን ይባላል።ድሮ የሱዳን መከላከያ ሚኒስቴር የነበረ ሰው ነበር ። በ1995 በሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኡመር ሀሰን አልበሺር ሴራ ተከሶ ዘብጥያ ወረደ።የሱዳን ፕሬዝዳንት ኡመር አልበሽርም የህብረተሰቡ ጥያቄ ኮሌኑየሉ የት ገባ የሚል ጥያቄ በየቀኑ ማስተናገድ ጀመሩ ውትወታ የበዛባቸው ኡመር አልበሽርም ለህዝቡ እንዲህ በማለት መለሱ! ! "በ 2008 በተከሰከሰች የአውሮፕላን አደጋ ምከንያት የኢብራሂም ሸምሰዲን ህይወቱ አልፏል በማለት ለህዝቡ አወጁ። ነገር ግን በገሀድ የነበረው እውነት ሌላ ነገር ነበር።የመከላከያው ሚኒስተር ኮሌኒየል ኢብራሂም ሸምሰዲን አልሞተም!! ኡመር ሀሰን አልበሺር ከመሬት በታች በሆነ ድብቅ እስር ቤት አስሮት ከአለም ህዝብ ተገልሎ በጠባብየ ትንሽ መቃብር ኮሌነየሉ ህይወቱን ገፋ። ብዙ ስቃዬችን እና መከራወችን አስተናገዴ ፣በመጨረሻም ኡመር አልበሽር ከስልጣን መንበሩ ሲለቅ ኮሌኒየል ኢብራሂም በህይወት እንዳለ አለም አወቀ። ፖለቲከኞች የዚህን ያህል ጨካኝ ናቸው።ኡመር ሀሰን አልበሺር እንደዚህ አድርጓል።እሱም፡በተራው ዛሬ ዘብጥያ ወርዷል። በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም የእኛም ሀገር መንግስት ጨቋኝ ካድሬ በሰፈሩት ቁና መስፈር አይቀርም እና ከጨቋኙ ኡመር አልበሽር ተማሩ! ! @topMereja

ከ55 ሺሕ በላይ የትግራይ ሰራዊት አባላት ከሰራዊት አባልነታቸው መሰናበታቸው ተገለጸ ከ55 ሺሕ በላይ የትግራይ ሰራዊት አባላት ከሰራዊት አባልነታቸው መሰናበታቸው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል
ከ55 ሺሕ በላይ የትግራይ ሰራዊት አባላት ከሰራዊት አባልነታቸው መሰናበታቸው ተገለጸ ከ55 ሺሕ በላይ የትግራይ ሰራዊት አባላት ከሰራዊት አባልነታቸው መሰናበታቸው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት እና የሰላምና ደህንነት ካብኔ ሰክሬተርያት ታደሰ ወረደ ገለጹ፡፡ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕሬዝደንት በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፤ “ሽኝት እየተደረገላቸው ያሉት የትግራይ ሰራዊት አባላት የትግራይ ህዝብ ህልውና እና ደህንነት ለማስጠበቅ መክፈል ያለባቸው መስዋእነት የከፈሉ ክብር የሚገባቸው ጀግኖች ናቸው” ብለዋል፡፡ በዚህም መሰረት ከ55 ሺሕ በላይ የትግራይ ሰራዊት አባላት የስንብት መርሀ ግብር ተደርጎላቸው ወደየ አካባቢያቸው ሽኝት እንደተደረገላቸው እና ደማቅ አቀባበል እየተደረገላቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ሲል ድምፀ ወያኔ ዘግቧል፡፡ _

ሰበር ዜና ! መከላከያ ተመታ / ለአዲስ አበባ አዲስ ከንቲባ ሙሉ መረጃዉን ሊንኩን በመንካት ይመልከቱ https://youtu.be/adLvJSS3HXA https://youtu.be/adLvJSS3HXA
ሰበር ዜና ! መከላከያ ተመታ / ለአዲስ አበባ አዲስ ከንቲባ ሙሉ መረጃዉን ሊንኩን በመንካት ይመልከቱ https://youtu.be/adLvJSS3HXA https://youtu.be/adLvJSS3HXA

ሰበር ዜና! ከምሽቱ 3:30 ጀምሮ በወልድያ ከተማ የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች ገልፀዋል። በከተማዋ በተለይ ፒያሳ ዳቦ ቤቱ አከባቢ የተጀመረው የተኩስ ልውውጥ አድማሱን እያሰ
ሰበር ዜና! ከምሽቱ 3:30 ጀምሮ በወልድያ ከተማ የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች ገልፀዋል። በከተማዋ በተለይ ፒያሳ ዳቦ ቤቱ አከባቢ የተጀመረው የተኩስ ልውውጥ አድማሱን እያሰፋ በአሬሮ፣ በመናኸሪያው ጀርባ፣ በቲንፋዝ እና በማረሚያ ቤቱ አከባቢ ከባድ የሆነ የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ መሆኑን ነው የአማራ ድምፅ ሚድያ የከተማዋ ነዋሪዎችን በማነጋገር ለማረጋገጥ የቻለው። ምንጮቻችን አክለውም የተኩስ ልውውጡ በቡድን መሣሪያዎችም ጭምር የታገዘ ነው ያሉ ሲሆን፤ ነገር ግን ተኩሱ በማን እና በማን መካከል እንደሆነ ማረጋገጥ አልቻልንም ብለዋል። ዘገባው የአማራ ድምፅ ሚዲያ ነው!

አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ ! አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ 400 በላይ ተማሪዎችንም አሰመርቋል። የምርቃት ስነ
+3
አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ ! አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ 400 በላይ ተማሪዎችንም አሰመርቋል። የምርቃት ስነ-ስርዓቱ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትርና የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበልን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልሉ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሶስተኛ ዲግሪ ከ1ሺህ 400 በላይ ተማሪዎችን እያስመረቀ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 234 የሚሆኑት ሴቶች ናቸው ተብሏል። @topMereja

ማህበራዊ ሚዲያዎች ያለ VPN መስራት ጀመሩ ! ለወራት ያህል በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ ተነስቷል። #ቴሌግራም ፣ ዩትዩብ ፣ ፌስቡክ ፣ ቲክቶክ መሰል የማህበራዊ ሚዲያዎ
+1
ማህበራዊ ሚዲያዎች ያለ VPN መስራት ጀመሩ ! ለወራት ያህል በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ ተነስቷል። #ቴሌግራም ፣ ዩትዩብ ፣ ፌስቡክ ፣ ቲክቶክ መሰል የማህበራዊ ሚዲያዎች ከወራት በፊት (የካቲት ወር 2015 ዓ/ም) በተጣለባቸው ገደብ ያለ VPN መስራት እንዳቆሙ ይታወቃል። ዛሬ ሰኞ ከሰዓታት በፊት ግን እነዚህ የማህበራዊ ሚዲያዎች #ያለ_VPN_እየሰሩ እንደሚገኙ እና ገደቡም መነሳቱን #ማረጋገጥ ችለናል። @topMereja