en
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Top Mereja

Channel Top Mereja (@topmereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 338 subscribers, ranking 10 174 in the News & Media category and 1 514 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 338 subscribers.

According to the latest data from 04 October, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -234 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 October, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 338
Subscribers
No data24 hours
-547 days
-23430 days
Posts Archive
#international news ሄቦላህ ከእስራኤል ጋር ለመደራደር በጋዛ ተኩስ አቁም መደረግ አለበት በሚል አስቀምጦት የነበረውን ቅድመ ሁኔታ እንደተወው ተነግሯል፡፡ ቡድኑ ከባለፈው አመት ጥቅምት ሰ
+1
#international news ሄቦላህ ከእስራኤል ጋር ለመደራደር በጋዛ ተኩስ አቁም መደረግ አለበት በሚል አስቀምጦት የነበረውን ቅድመ ሁኔታ እንደተወው ተነግሯል፡፡ ቡድኑ ከባለፈው አመት ጥቅምት ሰባት ማግስት ጀምሮ ከሀማስ ጋር በመወገን በእስራኤል የሮኬት እና የሚሳኤል ጥቃት ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ባለፈው አንድ አመት የጋዛ ጥቃት እስካልቆመ እና የተኩስ አቁም ስምምነት እስካልደተደረሰ ድረስ በቴልአቪቭ ላይ የሚፈጽመውን ጥቃት እንደሚቀጥል ሄዝቦላህ ሲዝት መቆየቱ ይታወቃል፡፡ የሄዝቦላህ ምክትል መሪ ናይም ቃሲም በትላንትናው እለት በቴሌቪዥን ባስተላለፉት መልዕክት ከሀማስ እና ከፍልስጤማውያን ጎን መቆማችንን ብንቀጥልም የሊባኖስ ፓርላማ አፈ ጉባኤ ከእስራኤል ጋር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለድርድር እንድንቀርብ ያቀረቡትን ሀሳብ እንቅበላለን ብለዋል፡፡ምክትል መሪው ናይም ቃሲም “የፓርላማው አፈጉባኤው ናቢህ ቤሪ ያቀረቡትን የተኩስ አቁም ሀሳብ ጠላታችን እስራኤል የምትቀበል ከሆነ ለመደራደር ዝግጁ ነን። በጦርነቱ የመቀጠል ፍላጎት ካላት ግን የውጊያ ውጤቶች ቀጣዩን ሁኔታ ይወስናሉ” ነው ያሉት፡፡  አፈ ጉባኤው ከሌሎች የሊባኖስ ፖለቲከኞች እና ከምእራባውያን ጋር በመነጋገር የተኩስ አቁም ተፈጻሚ እንዲሆን በቅርቡ የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ከሁለት ቀናት በፊት ሌሎች መካከለኛ የሄዝቦላህ አመራሮች በተመሳሳይ ቡድኑ ከእስራኤል ጋር ያለቅድመ ሁኔታ የመደራደር ፍላጎት እንዳለው መግለጻቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ቡድኑ ሙሉ ለሙሉ የአቋም ለውጥ አድርጎ ይሆን የሚለው ሀሳብ በአካባቢው ከሚያመጣው የስትራቴጂ ለውጥ አንጻር ምላሽ የሚያሻው ትልቅ ጥያቄ ነው፡፡  @topmereja

#ኢትዮጵያ ጀነራል አበባው ታደሰ የፊቤላ ኢንዱስትሪያል የመኪና መገጣጠሚያን ጎበኙ የጦር ሃይሎች ም/ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል አበባው ታደሰ በደብረ ብርሃን ከተማ የፊቤላ ኢንዱስትሪያል ኃ/የተ/የግ/ማ የመኪና መገጣጠሚያን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም ተገጣጥመው ለሥራ ዝግጁ የሆኑ ተሽከርካሪዎችን እና አጠቃላይ የኢንዱስትሪውን የሥራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌ/ጀ ሹማ አብደታና የአማራ ክልል የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊን ጨምሮ የክልሉና የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች በጉብኝቱ መሳተፋቸውን የመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ መረጃ ያመላክታል፡፡ @topmereja

#Accident በትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት አለፈ አደጋው ከዮራ ሻሾ ቀበሌ በቆሎ ጭኖ ወደ አመያ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ ጨበራ ሻሾ ቀበሌ ላይ በመገልበጡ ነው የደረሰው፡፡ በዚህም የ2 ሰ
#Accident በትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት አለፈ አደጋው ከዮራ ሻሾ ቀበሌ በቆሎ ጭኖ ወደ አመያ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ ጨበራ ሻሾ ቀበሌ ላይ በመገልበጡ ነው የደረሰው፡፡ በዚህም የ2 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን÷በ5 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን የአመያ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር በቀለ በለጠ ተናግረዋል፡፡ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ እንደሚገኝ መጠቆማቸውንም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡ @topmereja

ለአሻም ሚዲያ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ! የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ለአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ባለስልጣኑ የቴሌቪዥን ጣቢያው ከዚህ ቀደም ባሰ
+1
ለአሻም ሚዲያ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ! የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ለአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ባለስልጣኑ የቴሌቪዥን ጣቢያው ከዚህ ቀደም ባሰራጨው ግጭት ተኮር እና ሚዛናዊነት የጎደለው ዘገባ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ በተደጋጋሚ የጽሁፍና የቃል ማሳሰቢያ መስጠቱን አስታውቋል፡፡ ጣቢያው ባለስልጣኑ የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ወደ ጎን በመተው ያልተረጋገጡ መረጃዎችን በማህበራዊ ሚዲያና በመደበኛው ሚዲያ በማምጣት ህብረተሰቡን ለማደናገር ጥረት ሲያደርግ በመስተዋሉ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱም ተገልጿል።      #topmereja

Ultrapro የሚባል ልክ እንደ Binance Exchage በ App መጥቶላችኋል 👌 አዲስ እንደመሆናቸው መጠን ለአዲስ ተመዝጋቢ በነፃ 25$ እየሰጡ ነው 🥳 ይህን Giveaway መካፈል የምትችሉት እስከ ለሊቱ 6 ሰአት ብቻ ነው so ቤተሰብ ይህ እድል እንዲያመልጣችሁ አልፈልግም የዚህ App ስም Ultrapro exchange " ይባላል ከ playstore ላይ ታገኙታላችው  ነገር ግን አፑ እኛ አገር ስለማይሰራ በ VPN ተጠቅማችሁ አውርዱት 👌 ነገር ግን የ USA Address አትጠቀሙ ቀጥሎ የምታደርጉት sign up በማድረግ በ Email regester አድርጉ Refferal code ከጠየቃችሁ ይሄን አስገቡ  👉 UTX75636199 Withdraw ማድረግ የሚጀምረው እንደተናገሩት ከሆነ ከነገ ጀምሮ ነው  ነገር ግን KYC ነገ መጠየቅ ስለሚጀምሩ  ግዴታ ነው KYC ከጨረሳችሁ ገንዘባችሁን ወደፈለጋችሁት ማውጣት ትችላላችው ነገ Appu launch ስለሚደረግ በቻላችሁት መጠን ፍጠኑ APP LINK  https://play.google.com/store/apps/details?id=com.application.ultrapro Web link https://www.ultraproex.com/register/?refCode=UTX75636199

Sirutt endayameltachu👍

ኢትዮጵያን ከኤርትራ የሚያገናኘው የስልክ መስመር ተቋረጠ ኢትዮጵያ እና ኤርትራን የሚያገናኘው የስልክ መስመር ተቋረጠ። በቅርቡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ የሚያደርገው በረራ ማቋረጡ ይታወሳ
ኢትዮጵያን ከኤርትራ የሚያገናኘው የስልክ መስመር ተቋረጠ ኢትዮጵያ እና ኤርትራን የሚያገናኘው የስልክ መስመር ተቋረጠ። በቅርቡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ የሚያደርገው በረራ ማቋረጡ ይታወሳል። ምንጭ- የኔታ ቲዩብ @topmereja

Ultrapro የሚባል ልክ እንደ Binance Exchage በ App መጥቶላችኋል 👌 አዲስ እንደመሆናቸው መጠን ለአዲስ ተመዝጋቢ በነፃ 25$ እየሰጡ ነው 🥳 ይህን Giveaway መካፈል የምትችሉት እስከ ለሊቱ 6 ሰአት ብቻ ነው so ቤተሰብ ይህ እድል እንዲያመልጣችሁ አልፈልግም የዚህ App ስም Ultrapro exchange " ይባላል ከ playstore ላይ ታገኙታላችው  ነገር ግን አፑ እኛ አገር ስለማይሰራ በ VPN ተጠቅማችሁ አውርዱት 👌 ነገር ግን የ USA Address አትጠቀሙ ቀጥሎ የምታደርጉት sign up በማድረግ በ Email regester አድርጉ Refferal code ከጠየቃችሁ ይሄን አስገቡ  👉 UTX75636199 Withdraw ማድረግ የሚጀምረው እንደተናገሩት ከሆነ ከነገ ጀምሮ ነው  ነገር ግን KYC ነገ መጠየቅ ስለሚጀምሩ  ግዴታ ነው KYC ከጨረሳችሁ ገንዘባችሁን ወደፈለጋችሁት ማውጣት ትችላላችው ነገ Appu launch ስለሚደረግ በቻላችሁት መጠን ፍጠኑ APP LINK  https://play.google.com/store/apps/details?id=com.application.ultrapro Web link https://www.ultraproex.com/register/?refCode=UTX75636199

Ultrapro የሚባል ልክ እንደ Binance Exchage በ App መጥቶላችኋል 👌 አዲስ እንደመሆናቸው መጠን ለአዲስ ተመዝጋቢ በነፃ 25$ እየሰጡ ነው 🥳 ይህን Giveaway መካፈል የምትችሉት እስከ ለሊቱ 6 ሰአት ብቻ ነው so ቤተሰብ ይህ እድል እንዲያመልጣችሁ አልፈልግም የዚህ App ስም Ultrapro exchange " ይባላል ከ playstore ላይ ታገኙታላችው  ነገር ግን አፑ እኛ አገር ስለማይሰራ በ VPN ተጠቅማችሁ አውርዱት 👌 ነገር ግን የ USA Address አትጠቀሙ ቀጥሎ የምታደርጉት sign up በማድረግ በ Email regester አድርጉ Refferal code ከጠየቃችሁ ይሄን አስገቡ  👉 UTX75636199 Withdraw ማድረግ የሚጀምረው እንደተናገሩት ከሆነ ከነገ ጀምሮ ነው  ነገር ግን KYC ነገ መጠየቅ ስለሚጀምሩ  ግዴታ ነው KYC ከጨረሳችሁ ገንዘባችሁን ወደፈለጋችሁት ማውጣት ትችላላችው ነገ Appu launch ስለሚደረግ በቻላችሁት መጠን ፍጠኑ APP LINK  https://play.google.com/store/apps/details?id=com.application.ultrapro Web link https://www.ultraproex.com/register/?refCode=UTX75636199

በ ‘ሃሪኬን ሚልተን’ እየተመታች ያለችው ፍሎሪዳ ነዋሪዎች ከቀያቸው እየወጡ ነው በአሜሪካዋ ግዛት ፍሎሪዳ የተከሰተው ዝናብ የቀላቀለ አውሎ ነፋስ (ሃሪኬን ሚልተን) በሚሊየን የሚቆጠሩ ነዋሪዎች አካባ
+2
በ ‘ሃሪኬን ሚልተን’ እየተመታች ያለችው ፍሎሪዳ ነዋሪዎች ከቀያቸው እየወጡ ነው በአሜሪካዋ ግዛት ፍሎሪዳ የተከሰተው ዝናብ የቀላቀለ አውሎ ነፋስ (ሃሪኬን ሚልተን) በሚሊየን የሚቆጠሩ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ ማስገደዱ ተሰምቷል፡፡ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ከተከሰተው በይበልጥ በቀጣዮቹ ቀናት ፍሎሪዳ ዝናብ በቀላቀለ አውሎ ነፋስ ልትመታ እንደመትችል እና በዚህም 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች በአደጋው ሊጎዱ ስለሚችሉ ከአካባቢው እንዲወጡ አዝዘዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱን ማስጠንቀቂያ ተከትሎ በሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎች አካባቢውን ለቀው መውጣታቸው እና በቀጣይም በሚሊየን የሚቆጠሩ ነዋሪዎች እንደሚወጡ ይጠበቃል ተብሏል፡፡ በፍሎሪዳ የሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትም በተከሰተው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ቀደም ብለው መዘጋታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ሰሞኑን በጆርጂያ፣ ፍሎሪዳ፣ ደቡብ ካሮላይና፣ ቴነሲ፣ ቨርጂኒያ እና ሰሜን ካሮላይና የተከሰተው ‘ሄለን ሃሪ ኬን’ የ225 ሰዎችን ሕይወት ሲቀጥፍ በርካቶችን ከቀያቸው አፈናቅሏል @topmereja

ቴክኖ ከሆሊውዱ ታዋቂ ፊልም ትራንስፎርመርስ ጋር በመሆን አዲሱን ስፓርክ 30 ስልክ ይፋ አድርጓል! ይህ ስልክ ከፊልሙ የተወሰዱ ገፅ በህሪያትን በዲዛይን ያካተተ ሲሆን ቴክኖ ኢትዮጵያ ከሴንቸሪ ሲኒማ
ቴክኖ ከሆሊውዱ ታዋቂ ፊልም ትራንስፎርመርስ ጋር በመሆን አዲሱን ስፓርክ 30 ስልክ ይፋ አድርጓል! ይህ ስልክ ከፊልሙ የተወሰዱ ገፅ በህሪያትን በዲዛይን ያካተተ ሲሆን ቴክኖ ኢትዮጵያ ከሴንቸሪ ሲኒማ ጋር በመተባበር የቴክኖ አዲሱን ስፓርክ 30 ስልክ በቅርበት እንዲሁም ትራንስፎርመር ፊልምን ከቤተሶት ጋር በነፃ እንዲያዩ ጋብዟል፡፡ እሁድ ጥቅምት 3 ልጆቾን እና ቤተሰቦን ይዘው ሴንቸሪ ሲኒማ ብቅ ይበሉ በተለያዩ ስጦታዎች እና ጨዋታዎች እየተንበሸበሹ፣ አዲሱን ስፓርክ 30 ስልክ በቅርበት እያዩ ፊልሞትን ይኮምኩሙ፡፡ @tecno_et @tecno_et @topmereja

#MoE #Placement በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የ
+1
#MoE #Placement በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ መሙላት እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ የሚሹ ተማሪዎች ማመልከቻቸውን በ https://student.ethernet.edu.et በኩል ብቻ እንዲልኩ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

#MoE በ2017 የትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም (Remedial Program) ለመከታተል የመቁረጫ ነጥብ ተወስኗል። በዚህም በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የወ
+1
#MoE በ2017 የትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም (Remedial Program) ለመከታተል የመቁረጫ ነጥብ ተወስኗል። በዚህም በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የወሰዱና እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 31% ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎች በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የሪሚዲያል ፕሮግራም መከታተል ይችላሉ ተብሏል። በመንግስት ተቋማት ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ የሪሚዲያል ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል። #topmereja

#international news ሂዝቦላህ ወደ ሃይፋ ከተማ ከ100 በላይ ሮኬቶችን አስወነጨፈ ከተማዋ እንዲህ አይነት ጥቃት ሲያጋጥማት ከ18 ዓመታት በኋላ እንደሆነ ተገልጿል። እስራኤል በሊባኖስ ውስ
+1
#international news ሂዝቦላህ ወደ ሃይፋ ከተማ ከ100 በላይ ሮኬቶችን አስወነጨፈ ከተማዋ እንዲህ አይነት ጥቃት ሲያጋጥማት ከ18 ዓመታት በኋላ እንደሆነ ተገልጿል። እስራኤል በሊባኖስ ውስጥ በአየርና በእግረኛ ጦር አማካኝነት ለምትፈጽመው ጥቃት አጸፋ እየመለሰ ያለው ሂዝቦላህ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል እያስወነጨፈ ስለመሆኑ ቢቢሲ ዘግቧል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የሊባኖስ መዲና የሆነችው ቤይሩት ባለስልጣናት በከተማዋ ከስጋት ነጻ የሆነ ስፍራ የለም ሲሉ ተናግረዋል። እስራኤል በበኩሏ የሂዝቦላህ ይዞታዎችን ዒላማ ያደረገ ጥቃት እየፈጸመች እንደሆነ ገልጻ፤ በጥቃቷ የተገደሉትን የሂዝቦላህ መሪ ሀሰን ነስላህን በመተካት የቡድኑ ሃላፊ ሊሆን ይችላል የተባለው ግለሰብ ባለፈው ሳምንት ሳይገደል እንዳልቀረ አስታውቃለች። የእግረኛ ጦሯ በደቡብ ምዕራብ ሊባኖስ በተሰጠው ስምሪት በድንበር አካባቢ ተልዕኮውን እየተወጣ ስለመሆኑም አመልክታለች። @topmereja

የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ። ከመስከረም 28/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በሥራ ላይ የሚቆይ የሁሉም የነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉ ተሰምቷል። በዚህ መሰረት፦ ➡️ ቤንዚን - ብር 91.14 በሊትር ➡️ ነጭ ናፍጣ - ብር 90.28 በሊትር ➡️ ኬሮሲን - ብር 90.28 በሊትር ➡️ ቀላል ጥቁር ናፍጣ - ብር 100.20 በሊትር ➡️ ከባድ ጥቁር ናፍጣ - ብር 97.67 በሊትር  ➡️ የአውሮፕላን ነዳጅ በሊት 77.76 ብር ሆኗል። @topmereja

#amhara በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን አማኑኤል ከተማና በምዕራብ ጎጃም ዞን ፈረስ ቤት ከተማና አካባቢው በፋኖ ታጣቂዎችና በመንግስት የመከላከያ ሰራዊት መካከል ከትናንት ጀምሮ ውጊያ እየተካሄ
+1
#amhara በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን አማኑኤል ከተማና በምዕራብ ጎጃም ዞን ፈረስ ቤት ከተማና አካባቢው በፋኖ ታጣቂዎችና በመንግስት የመከላከያ ሰራዊት መካከል ከትናንት ጀምሮ ውጊያ እየተካሄደ እንደሆነ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በሌላ በኩል ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ውጊያ ሲካሄድባት የነበረችው የደንበጫ ከተማ የተኩስ ድምፅ ባይሰማም ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ በከተማዋ ውስጥ እንንደማይታይ አንድ የአይን እማኝ ገልጠዋል፡፡ ከትናንት ጀምሮ እስከዛሬ ጠዋት ድረስ በምዕራብ ጎጃም ዞን ፈረስ ቤት ከተማና በዙሪያው ጦርነቶች እንደነበሩና ዛሬ ረፋድ ላይ ተኩሱ በተወሰነ ደረጃ መቀነሱን አንድ ነዋሪ ቀን ቀትር ላይ ነግረውናል፡፡ “ከሁለት ሰዓት ጀምሮ ከባድ ውጊያ ነበር አሁን (ቀትር) በረድ ብሏል፡፡” ብለዋል፡፡ ትናንትና ወደ ገጠሩ አካባቢ ሙሉ ቀን ጦርነት እንደነበር የጠቀሱት አስተያየት ሰጪው፣ በተለይ “አቅላት” በሚባል አካባቢ ውጊያ እንደነበርና ዛሬ ደግሞ በከተማው ዙሪያ፣ በተለይም “ሻንጊ” በተባለ ቦታ ላይ ከባድ ውጊያ ቀትሎ ማርፈዱን ገልጠዋል፡፡ “ ነዋሪው ነፍስ ግቢ፣ ነፍስ ውጪ ላይ ነው፣ ሰው ተቸግሯል” ሲሉ ነው ያከሉት፡፡ ሌላ የአካባቢው ነዋሪ በበኩላቸው ጦርነቱ በሁለቱ ኃይሎች መካከል የተጀመረው ከመስከረም 21/2017 ጀምሮ መሆኑን አመልክተው፣ አሁንም በአራቱም አቅጣጫ ውጊያ መኖሩን ዛሬ ቀትር ላይ ተናግረዋል፡፡ @topmereja

#Amhara በአማራ ክልል ግጭቶች ተባብሰው መቀጠላቸውን ነዋሪዎች ገለፁ በፋኖ ታጣቂ ቡድን ላይ ከፍተኛ ጥቃት ሊፈጽም መሆኑን መንግስት ባወጀበት ወቅት በተለያዩ የአማራ ክልል አካባቢዎች እየተካሄደ
#Amhara በአማራ ክልል ግጭቶች ተባብሰው መቀጠላቸውን ነዋሪዎች ገለፁ በፋኖ ታጣቂ ቡድን ላይ ከፍተኛ ጥቃት ሊፈጽም መሆኑን መንግስት ባወጀበት ወቅት በተለያዩ የአማራ ክልል አካባቢዎች እየተካሄደ ያለው ውጊያ ተባብሶ መቀጠሉን በምዕራብና ምስራቅ ጎጃም ዞኖች ያሉ ነዋሪዎች ገለጹ። የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው በምዕራብ ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ወረዳ የፈረስ ቤት ከተማ እንዲሁም በምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ቀራኒዮ ከተማ ዙሪያ ያሉ ነዋሪዎች ከከተሞቹ ዳርቻ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ ማርፈዱን ጨምረው አመልክተዋል:: በሌላ በኩል በአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህርዳር ከተማ ባለፈው ሳምንት የአድቬንቲስት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጨምሮ በተለያዩ ቦታዎች የደረሱ የቦምብ ፍንዳታዎች ከፍተኛ ስጋት እንዳሳደሩባቸው የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ገልፀዋል:: ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ በሰጡት መግለጫ “ሁሉም አካላት” በሰላማዊ ሰዎች እና በሲቪል ተቋማት ላይ ከማነጣጠር እንዲቆጠቡ ሲሉ ጥሪ አሰምተዋል። በመንግስት ሰራተኞች፣ በፖለቲካ ፓርቲ አባላት፣ በጋዜጠኞች እና በሲቪል ማህበረሰብ አባላት ላይ እየተፈጸሙ ያሉትን የዘፈቀደ እስሮች ጉዳይ ኮምሽኑ እየተከታተለ አመልክተዋል። @topmereja

#tigray የደብረፂዩን አንጃ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሊቀመንበርና ሌሎች ሹማምንትን ከሀላፊነታቸው የማንሳት ስልጣን እንደሌለውና በጉዳዩም ላይ እስከ ሰኞ ማምሻውን ድረስ ከፌደራሉ መንግስት ጋር
+1
#tigray የደብረፂዩን አንጃ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ሊቀመንበርና ሌሎች ሹማምንትን ከሀላፊነታቸው የማንሳት ስልጣን እንደሌለውና በጉዳዩም ላይ እስከ ሰኞ ማምሻውን ድረስ ከፌደራሉ መንግስት ጋር የተደረገ ውይይት አለመኖሩን የፌደራሉ መንግስት ባለስልጣን ለዋዜማ ነግረዋል። ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ፣ ጌታቸው ረዳን ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሥልጣን ማንሳቱን ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ቡድኑ፣ ጌታቸውን ማን ሊተካቸው እንደሚገባ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር በመነጋገር ላይ እንደሚገኝም አስታውቋል፡፡ የደብረጺዮን የሕወሓት ቡድን፣ 13 የካቢኔ አባላትን፣ የቢሮ ሃላፊዎችንና የዞኖች አስተዳዳሪዎችን ከሃላፊነት ማውረዱን ጠቅሶ፣ በምትካቸው ሌሎች አመራሮችን መመደቡንና ከሃላፊነታቸው የተነሱት ሰዎች ከትናንት ጀምሮ የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር መምራት እንደማይችሉ አመልክቷል። ቡድኑ፣ ከሃላፊነታቸው አንስቻቸዋለኹ ባላቸው አመራሮች ምትክ የመደባቸውን ሃላፊዎች ዝርዝር ይፋ አድርጓል። በካቢኔ ሹመት ላይ ተመድበዋል ከተባሉት መካከል፣ ምርጫ ቦርድ እውቅና የነፈገው የፓርቲው ጉባኤ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ የመረጣቸው አማኑኤል አሠፋ እንዲኹም አብርሃም ተከስተ ይገኙበታል። በሌላ በኩል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት. ክንፍ “መፈንቅለ መንግስት አውጆብኛል” በማለት ባወጣው መግለጫ ከሷል። ቡድኑ ሥርዓት አልበኝነትን ለማስፋፋትና ትርምስ ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ያለው አስተዳደሩ፣ በዚህ ቡድን አመራር ላይ “ሕጋዊ ርምጃ” መውሰድ እንደሚጀምርና በሂደቱ ለሚደርስ ማናቸውም ጉዳት ይኼው ቡድን እና አመራሮቹ ብቻ ተጠያቂ እንደኾኑ ሕዝቡ እንዲረዳ አሳስቧል። @topmereja

#International news ከእስራኤል ጋር በነበረው የአውሮፓውያኑ 2006 የመጨረሻ ጦርነት ወቅት የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት አገራቸውን አለም አቀፉ ማህበረሰብ እንደረሳት ለቢቢሲ ተናገ
#International news ከእስራኤል ጋር በነበረው የአውሮፓውያኑ 2006 የመጨረሻ ጦርነት ወቅት የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት አገራቸውን አለም አቀፉ ማህበረሰብ እንደረሳት ለቢቢሲ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ፉአድ ሲኖራ ሊባኖስ እንድትንኮታኮት መደረጓ ተቀባይነት እንደሌለው እና በአገሪቱ ሰላምን ለማስፈን ተነሳሽነት የለም ሲሉ ወቅሰዋል። “በአሁኑ ወቅት የአገር ውስጥ፣ የአረቡ ዓለም እና በአለም አቀፍ ደረጃ እውነተኛ ጥረት የሚሻ ከባድ ፈተና ውስጥ እንገኛለን” ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። “ሁኔታዎች ምን ሊያስከትሉ እንደሚችሉ በቅጡ ሳይረዱ ወደ ውድቀት አፋፍ እንዲሁም ወደ ቀውስ ውስጥ ሊገባ ይችላል” ያሉት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አገራቸው በዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ ያለችው የአሜሪካ አስተዳደር በራሱ ምርጫ በተጠመደበት ወቅት መሆኑን አስታውሰዋል። “አገራችን ፕሬዚዳንት መምረጥ አልቻለችም ምክንያቱም በአገሪቱ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ቡድኖች በተለይም ሄዝቦላህ ከጀርባው የማይወጋው ፕሬዚዳንት አንፈልግም የሚል አቋም በጽኑ በመያዛቸው ምርጫ እንዳይካሄድ እንቅፋት ሆኗል” ሲሉ አስረድተዋል። ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት የተደረገው የእስራኤል እና የሊባኖስ የመጨረሻ ጦርነት የተጀመረው የሄዝቦላህ ተዋጊዎች ድንበር ጥሰው የእስራኤል ወታደሮች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ተከትሎ ነው። በዚህም ጥቃት ሶስት ወታደሮች ሲገደሉ፣ ሁለት ወታደሮች ታግተው ለወር ወደዘለቀ ግጭት አገራቱን መርቷቸው ነበር። @topmereja

#Amhara የተባበሩት መንግሥታት በአማራ ክልል የሚያደርገውን የሰብዓዊ ድጋፍ፣ የምግብ እርዳታን ጨምሮ ለማቋረጥ እያሰበ ሲሆን፣ ይህ ዕቅዱ ተቃውሞ ገጥሞታል። ሮይተርስ የዜና ወኪል የተመለከተው ረቂ
#Amhara የተባበሩት መንግሥታት በአማራ ክልል የሚያደርገውን የሰብዓዊ ድጋፍ፣ የምግብ እርዳታን ጨምሮ ለማቋረጥ እያሰበ ሲሆን፣ ይህ ዕቅዱ ተቃውሞ ገጥሞታል። ሮይተርስ የዜና ወኪል የተመለከተው ረቂቅ ምክረ ሃሳብ በክልሉ የሰብዓዊ እርዳታ ሠራተኞች ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ የተባበሩት መንግሥታት በክልሉ የሚያካሄደውን የሰብዓዊ እርዳታ ለማቋረጥ ሃሳብ እንዳለው አመልክቷል። የመንግሥታቱ ድርጅት ነሐሴ ወር ላይ ያዘጋጀው ይህ ረቂቅ ምክረ ሃሳብ ባለፈው ዓመት ከጥር ወር ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ብቻ 10 የሰብዓዊ እርዳታ ድርጅት ሠራተኞች አካላዊ ጥቃት ሲደርስባቸው 11 ደግሞ ባልታወቁ ወንጀለኛ ቡድኖች መታገታቸው በሰነዱ ላይ ተመልክቷል። የመንግሥታቱ ድርጅት ያዘጋጀው ባለሦስት ገጽ ሰነድ “በክልሉ የሚያካሄደውን የሰብዓዊ እርዳታ ለጊዜው ማቆም” ማሰቡን አስፍሯል። በርካታ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ለጋሽ አካላት በምክረ ሃሳቡ ላይ የቀረበውን በክልሉ የሚካሄደውን የረድኤት ሥራ የማቋረጥ ሃሳብን መቃወማቸው ተገልጿል። ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም ምግብ ፕሮግራም በአምስት ወራት ውስጥ 50 የረድዔት ሠራተኞች በኢትዮጵያ በሰብዓዊ ተግባራት ላይ ተሰማርተው እያሉ ሕይወታቸውን እንዳጡ አስታውቆ ነበር። የዓለም ምግብ ፕሮግራም ኢትዮጵያን አስመልክቶ ሰኔ 9/2016 ዓ.ም. ባወጣው ሪፖርቱ የፀጥታ ችግር በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በሚያደርገው ሰብዓዊ እንቅስቃሴ ላይ ጫና እያሳደረ መሆኑን ገልጿል። የዓለም የምግብ ፕሮግራም አጋር የሆነው ሜዲካል ቲምስ ኢንተርናሸናል የተሰኘው የረድዔት ድርጅት አሽከርካሪ በአማራ ክልል እንደተገደለ በዚህ ሪፖርት ላይ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ይህም ሕይወታቸው የጠፋ የእርዳታ ሠራተኞች ቁጥር ሃምሳ ማድረሱንም አክሏል።