en
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Top Mereja

Channel Top Mereja (@topmereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 338 subscribers, ranking 10 174 in the News & Media category and 1 514 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 338 subscribers.

According to the latest data from 04 October, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -234 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 October, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 338
Subscribers
No data24 hours
-547 days
-23430 days
Posts Archive
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዕለታዊ ምንዛሬ‼️
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዕለታዊ ምንዛሬ‼️

5ኛው የሳይበር ደኅንነት ወር በሳይንስ ሙዚየም ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል ሀገር አቀፉ የሳይበር ደኅንነት ወር "የቁልፍ መሠረተ-ልማት ደኅንነት ለዲጂታል ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ
+1
5ኛው የሳይበር ደኅንነት ወር በሳይንስ ሙዚየም ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል ሀገር አቀፉ የሳይበር ደኅንነት ወር "የቁልፍ መሠረተ-ልማት ደኅንነት ለዲጂታል ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ወር እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡ የሳይበር ደኅንነት ወርን ማካሄድ ያስፈለገው ተቋማትና ዜጎች በዘርፉ ያላቸውን ንቃተ-ህሊና ለማሳደግ ነው ተብሏል፡፡ በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ ውጤታማ የሆነ ቅንጅት በመፍጠር የሳይበር ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የወሩ መከበር እግዛ እንደሚያደርግም ተገልጿል፡፡ ወሩ ሲከበር በዘርፉ የሚደረጉ ውይይቶችና ምክክሮች፣ የተማሪዎች ውድድሮች፣ የ5 ሚሊየን የኮደርስ ኢኒሼቲቭ ለሳይበር ደኅንነት የሚጫወተው ሚና በሚል የሚዘጋጁ ፕሮግራሞች እንደሚኖሩም ተመላክቷል፡፡ @topmereja

#ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ በታሪኳ በቡና ምርት ከፍተኛውን ገቢ ማግኘቷ ተገለፀ! በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ ነው የተባለለት 1.43 ቢሊየን ዶላር የቡና የውጭ ምንዛሬ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣ
+1
#ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ በታሪኳ በቡና ምርት ከፍተኛውን ገቢ ማግኘቷ ተገለፀ! በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ ነው የተባለለት 1.43 ቢሊየን ዶላር የቡና የውጭ ምንዛሬ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። ባለፈው ዓመት 3 መቶ ሺህ ቶን የሚጠጋ ቡና ለዓለም ገበያ ቀርቦ ከ1.4 ቢሊየን ዶላር በላይ መገኘቱን የተጠቆመ ሲሆን በቡና ምርት ከብራዚል እና ቬትናም ቀጥላ በዓለም 3ኛ የሆነችውን ኢትዮጵያን ከቬትናም ጋር እኩል ለማድረግ ምርት ማሳደግ ላይ በትኩረት እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡ ኢትዮጵያ በዓለም ገበያ 1 ኪሎ ግራም ቡናን በ103 ሺህ ብር መሸጥ መቻሉ ይታወሳል፡፡ @topmereja

#MoE በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በ 'Remedial' ፕሮግራም ለመከታተል
#MoE በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በ 'Remedial' ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ ሞልተው እንዲጨርሱ መገለጹ ይታወሳል። ይሁን እንጂ " አንዳንድ ትምህርት ቤቶች በሲስተም ችግር ምክንያት የተማሪዎቻችንን የትምህርት መስክ እና የዩኒቨርስቲ ምርጫ መሙላት ተቸግረናል " ባሉት መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር የምርጫ መሙያ ጊዜውን እስከ ረቡዕ ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል። @topmereja

# Addis ግንባታ ከማከናወናቸው አስቀድመው ቤት የሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች፤ ከደንበኞቻቸውን የሚሰበስቡትን ገንዘብ በዝግ የባንክ አካውንት እንዲያስቀምጡ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች
# Addis ግንባታ ከማከናወናቸው አስቀድመው ቤት የሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች፤ ከደንበኞቻቸውን የሚሰበስቡትን ገንዘብ በዝግ የባንክ አካውንት እንዲያስቀምጡ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ። አዲሱ ረቂቅ አዋጅ፤ ቤት ለመገንባት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ያላገኙ የሪል ስቴት አልሚዎች ደንበኞችን እንዳይመዘግቡ እና ቅድመ ክፍያ እንዳይሰበስቡም ይከለክላል። “የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ” የተሰኘው ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ዛሬ ሐሙስ መስከረም 30/2017 ዓ.ም. በተደረገው የፓርላማው አራተኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመጀመሪያ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው። በዛሬው ስብሰባ ላይ ከቀረቡት አራት ረቂቅ ሕጎች መካከል የሆነው ይህ አዋጅ፤ ከዚህ ቀደም ራሱን የቻለ ሕግ ላልነበረው የሪል ስቴት ቤቶች የግንባታ እና ግብይት ሂደት አዲስ እና አሳሪ አሠራሮችን ያስተዋወቀ ነው። እንደ ሕንጻ ያሉ የማይንቀሳቀስ ንብረቶች ያላቸው ዋጋ በመንግሥት እንዲሁም በግል ባለሙያዎች የሚገመትበትን እንዲሁም ግመታው አገልግሎት ላይ የሚውልበት አሠራርም በረቂቅ አዋጁ ላይ ተቀምጧል። አዲሱ ሕግ፤ ገንዘቡ የሚቀመጥበት ዝግ የባንክ አካውንት የሚከፈተው “አግባብ ባለው አካል ፈቃድ መሠረት” እንደሆነም ያስረዳል። በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ ከረቂቅ አዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚወጣ ደንብ እንደሚወሰንም ተጠቅሷል። አዲሱ ሕግ፤ ገንዘቡ የሚቀመጥበት ዝግ የባንክ አካውንት የሚከፈተው “አግባብ ባለው አካል ፈቃድ መሠረት” እንደሆነም ያስረዳል። በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ ከረቂቅ አዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚወጣ ደንብ እንደሚወሰንም ተጠቅሷል። @topmereja

በሳዑዲ ሞት የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን መንግሥት ሕይወታቸውን እንዲያተርፍ ተማጸኑ!!! በደቡባዊ ሳዑዲ አረቢያ ናጅራን እስር ቤት የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የኢትዮጵያ መንግ
በሳዑዲ ሞት የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን መንግሥት ሕይወታቸውን እንዲያተርፍ ተማጸኑ!!! በደቡባዊ ሳዑዲ አረቢያ ናጅራን እስር ቤት የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የኢትዮጵያ መንግሥት ጣልቃ ገብቶ ሕይወታቸውን እንዲያተርፍ ተማጸኑ። በእስር ቤቱ እስካሁን ሁለት ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ ኃይሎች እንደተገደሉ እና ሌሎቹም ሞታቸውን እየተጠባበቁ መሆኑን የሞት የተፈረደባቸው ሁለት ስደተኞች ለቢቢሲ ገልጸዋል። እነዚህ በእስር ላይ ያሉ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ 47 እንደሚሆኑ እነኚሁ ስደተኞች ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት የስልክ ቆይታ አስረድተዋል። “መቼ እንደምንሞት ባናውቅም ሞት ተፈርዶብናል። ዛሬ ልንገደል እንችላለን ወይም ነገ፤ አናውቅም። በጣም ፈርተናል። ለምን ሞት እንደተፈረደብኝ አላውቅም። ድንበር በሕገ ወጥ መንገድ አልፈሃል ነው የተባልኩት። ከታሰርኩ አምስት ዓመት ከአምስት ወር ሆነኝ” ሲሉ እኚህ ስደተኛ ለቢቢሲ ያደረባቸውን ከፍተኛ ፍርሃት በስልክ ገልጸዋል። የሞት ፍርድ ሲፈረድባቸው እውነት ይሆናል ብለው እንዳላሰቡ ለቢቢሲ የተናገሩት ኢትዮጵያዊው ስደተኛ እስረኛ ባለፈው ሳምንት ሁለት ኢትዮጵያውያን እስረኞች መገደላቸውን ተከትሎ “የእኛም ዕእጣ ፈንታ ሞት እንደሆነ አወቅን” ይላሉ። “በሞት እና በሕይወት መካከል ነው ያለነው። ሌሎቹ ከተገደሉ በኋላ መተኛት አልቻልንም” ሲሉ ተናግረው “መንግሥታችን ጉዳዩን እንዲሰማልን እንፈልጋለን” ሲሉ ተማጽነዋል። አክለውም በእስር ላይ ስላሉት ኢትዮጵያውያን ባሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው “ኤምባሲ መጥቶ ጠይቆን አያውቅም” ሲሉ ተናግረዋል። @topmereja

#ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁኔታ!! መንግሥት ከዚህ በፊት በተለያዩ አገራት ለችግር የተዳረጉ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ያቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ቀዳሚ ትኩረቱን እዚህ ላይ ማድረጉ
+1
#ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁኔታ!! መንግሥት ከዚህ በፊት በተለያዩ አገራት ለችግር የተዳረጉ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ያቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ቀዳሚ ትኩረቱን እዚህ ላይ ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። በዚያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤትም ዜጎችን ከችግር ለማስወጣት ምዝገባ መጀመሩን ይፋ አድርጓል። ፖለቲካየመካከለኛው ምሥራቅ በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁኔታ ሰለሞን ሙጬ ከ 18 ሰዓታት በፊትከ 18 ሰዓታት በፊት መንግሥት ከዚህ በፊት በተለያዩ አገራት ለችግር የተዳረጉ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ያቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ቀዳሚ ትኩረቱን እዚህ ላይ ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። በዚያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤትም ዜጎችን ከችግር ለማስወጣት ምዝገባ መጀመሩን ይፋ አድርጓል። በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ቤይሩት ሊባኖስ ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ የተባሉ 51 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ቤይሩት ሊባኖስ ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ የተባሉ 51 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት በአፋጣኝ እንዲያስወጣቸው ጥሪ እያደረጉ ነው። በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ቤይሩት ሊባኖስ ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ የተባሉ 51 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

#ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁኔታ!! መንግሥት ከዚህ በፊት በተለያዩ አገራት ለችግር የተዳረጉ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ያቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ቀዳሚ ትኩረቱን እዚህ ላይ ማድረጉ
+1
#ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁኔታ!! መንግሥት ከዚህ በፊት በተለያዩ አገራት ለችግር የተዳረጉ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ያቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ቀዳሚ ትኩረቱን እዚህ ላይ ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። በዚያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤትም ዜጎችን ከችግር ለማስወጣት ምዝገባ መጀመሩን ይፋ አድርጓል። ፖለቲካየመካከለኛው ምሥራቅ በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁኔታ ሰለሞን ሙጬ ከ 18 ሰዓታት በፊትከ 18 ሰዓታት በፊት መንግሥት ከዚህ በፊት በተለያዩ አገራት ለችግር የተዳረጉ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ያቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ቀዳሚ ትኩረቱን እዚህ ላይ ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። በዚያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤትም ዜጎችን ከችግር ለማስወጣት ምዝገባ መጀመሩን ይፋ አድርጓል። https://p.dw.com/p/4lZz3 በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ቤይሩት ሊባኖስ ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ የተባሉ 51 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ቤይሩት ሊባኖስ ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ የተባሉ 51 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋልምስል MOHAMMAD ABOU AL AINAIN/AFP ማስታወቂያ በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት በአፋጣኝ እንዲያስወጣቸው ጥሪ እያደረጉ ነው። 03:13 በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ቤይሩት ሊባኖስ ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ይኖሩ የነበሩ የተባሉ 51 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። @topmereja

#Update የሶማሊያና ኤርትራ መሪዎች 'በሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት' ዙርያ ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ ቀጠናዊ ውጥረት ባየለበት ወቅት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ እና የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ 'በሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት' ዙርያ በ #አስመራ ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ። ሁለቱ መሪዎች “በሁለትዮሽ፣ ቀጠናዊ እና አለም አቀፋዊ ጉዳዮች እንዲሁም በዋነኝነት በሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ላይ ያተኮረ ውይይት” በትናንትናው ዕለት ማድረጋቸውን የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል አስታውቀዋል። መሪዎቹ “አስተማማኝ የመከላከያ እና የጸጥታ መዋቅርን ጨምሮ ጠንካራ እና ሉዓላዊ ተቋማትን መገንባት” አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል ተብሏል።     @topmereja

የአሜሪካዋ ፍሎሪዳ "ሀሪኬን ሚልተን" በተባለ ከባድ አውሎ ነፋስ ተመታች! የአሜሪካዋ ፍሎሪዳ ግዛት ምዕራባዊ የባህር ዳርቻ አስፈሪ በተባለለት ሀሪኬን ሚልተን በተባለ ከባድ ማእበል መመታቷ ተነግሯል።
+2
የአሜሪካዋ ፍሎሪዳ "ሀሪኬን ሚልተን" በተባለ ከባድ አውሎ ነፋስ ተመታች! የአሜሪካዋ ፍሎሪዳ ግዛት ምዕራባዊ የባህር ዳርቻ አስፈሪ በተባለለት ሀሪኬን ሚልተን በተባለ ከባድ ማእበል መመታቷ ተነግሯል። ሀሪኬን ሚልተን ማዕበል ነፋስና ነጎድጓዳማ ዝናብ ያዘለ በመሆኑ ጉዳቱን ከባድ እንዳደረገው ነው የተገለጸው። በግዛቲቱ የሚገኙ 3 ሚሊዮን መኖርያ እና ንግድ ቤቶችም በዚሁ ምክንያት የኤሌክትሪክ ሀይል ኢንዲቋረጥባቸው ሆኗል። በተለይም በሃርዲ ካውንቲ ውስጥ ከ97 በመቶ በላይ ቤቶች ኤሌክትሪክ እንደሌላቸው ሪፖርት ተደርጓል። የአሜሪካ ብሔራዊ አውሎ ነፋስ ማዕከል (ኤን.ኤች.ሲ) በሰጠው መግለጫ ሀሪኬን ሚልተን በፍሎሪዳ ምስራቃዊ የባህር ጠረፍ በሰዓት በ90 ማይል (150 ኪ.ሜ.) የሚጓዝ መሆኑን አስታውቋል። ይህም ጠንካራ ማእበል ነው ያለው ማእከሉ በከተሞች መሰረተ ልማትን እና ዛፎች እንዲወድቁ ምክንያት መሆኑን ነው የገለጸው። የአሜሪካ የአደጋ ጊዜ አገልግሎት ማዕበሉ በቀጣይ ቀናትም ከባድ ዝናብ፣ ጎርፍ እና አውዳሚ ነፋስ ሊያስከትል እንደሚችል አስጠንቅቋል። እንደ ታምፓ ቤይ ታይምስ ዘገባ ከሆነ አሁን ላይ በማዕበሉ የተጎዱ ሰዎችን ለመርዳት በፍሎሪዳ ግዛት የሚገኙ ሁለገብ ስታዲየሞች ለብሔራዊ ጠባቂዎች እና ለኤሌክትሪክ ሰራተኞች እንደ ማረፊያ ቦታ እያገለገሉ ይገኛሉ። በሀሪከን ሚልተን የተነሳ ብዙዎች ቤት ንብረታቸውን ሲያጡ ቁጥራቸው በውል ያልተለዩት ደግሞ ህይወታቸው ሳያልፍ እንዳልቀረ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሀን ጠቅሶ ዶቼቬሌ ዘግቧል።   @topmereja

በመሬት ናዳ የ10 ሰዎች ህይወት አለፈ። በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጉባ ቆርቻ እና ሻናን ዱንጎ ወረዳዎች ትላንት ማክሰኞ በጣለው ከባድ ዝናብ የተነሣ በተከሠተው የመሬት መናድ፣ 10 ሰዎች መሞታቸውን ወረ
+2
በመሬት ናዳ የ10 ሰዎች ህይወት አለፈ። በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጉባ ቆርቻ እና ሻናን ዱንጎ ወረዳዎች ትላንት ማክሰኞ በጣለው ከባድ ዝናብ የተነሣ በተከሠተው የመሬት መናድ፣ 10 ሰዎች መሞታቸውን ወረዳዎቹ አሳውቀዋል። የጉባ ቆርቻ ወረዳ አስተዳዳር ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጠው ቃል መስከረም 28 ቀን 2017 ዓ/ም በጃርጃታ ቀበሌ ውስጥ በተከሰተው የመሬት መናድ ምክንያት 4 ሰዎች ሲሞቱ በሌላ ቀበሌ በደረሰው አደጋ ደግሞ አንድ ሰው ሞቷል። በሻናን ዱንጎ ወረዳ በሌሊስቱ ቀበሌ በዚሁ ቀን በተከሰተው ሌላ የመሬት መናድ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት ማለፉን የወረዳው አስተዳዳር ለሬድዮ ጣቢያው ገልጿል። ነፍስ ይማር ! @topmereja

#Updated የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ለአሻም ቲቪ የሰጠው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ አንድም በተጨባጭ የተረጋጋጠ ማስረጃ የሌለው ነው  ሲል አሻም ቲቪ አስታወቀ! "የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዛሬ መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም ለአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር በጻፈው ደብዳቤ ‹‹ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ›› ሰጥቷል፡፡ ባለስልጣኑ ለእዚህ ውሳኔ ያበቃው ‹‹ ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን፣ ግጭት አባባሽ ዘገባዎችን፣ የሕዝብን አብሮነት የሚሸረሸሩ፣ የአገርና ብሔራዊ ጥቅም የሚጎዱ መረጃዎችን በቂ ማጣራትና ምክንያታዊ ጥረት ሳያደርግ በተደጋጋሚ ማሰራጨቱን በይዘት ክትትል በማረጋገጤ ነው ›› ብሏል፡፡ ይሁንና በደብዳቤው አንድም ቦታ በማስረጃ የተደገፈ የይዘት ክትትል አላቀረበም፡፡ ይህ ለአሻም የተሰጣት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ሲቀጥል ‹‹ ከዚህ ቀደም ባሰራጨው ግጭት ተኮር እና ሚዛናዊነት የጎደለው ዘገባ ከደርጊቱ እንዲቆጠብ በተደጋጋሚ በባለስልጣኑ የጽሁፍና የቃል ማሳሰቢያ ሲሰጠው መቆየቱን ›› አስታውሶ ‹‹ ጣቢያው ግን የባለስልጣኑን ማሳሰቢያ ባለማክበር የሀገሪቱን ህጎች የሚጥሱ ይዘቶችን በማሰራጨት ላይ ይገኛል ›› ሲል ወንጅሏል፡፡ በተመሳሳይ ለእዚህ ከፍተኛ ውንጀላ በአሻም ምክንያት የተፈጠረ ግጭት መኖሩን፣ የህዝብን አብሮነት የሚሸረሽሩ፣ ብሔራዊ ጥቅምን የሚጎዱ መረጃዎች ስለማቅረቧ አንድም ተጨባጭ ማስረጃ አላቀረበም፡፡ ባለስልጣኑ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ አሻም በምትሰራቸው ሚዛናዊ ዘገባዎች ላይ ኢ-አሰማኝ የሆኑ የማሳሰቢያ ደብዳቤዎችን ሲጽፍ ሰንብቷል፤ የሥራ ኃላፊዎችም በቃል ሲያስጠነቅቁ ከርመዋል፡፡ ይሁን እንጂ አሻም ለሁሉም ደብዳቤዎች ተገቢ ምላሾችን ከነማስረጃዎቹ በመጥቀስ ምላሽ ስትሰጥ ከርማለች፡፡ አንድም ጊዜ ግን አሻም የሰጣቻቸው የጽሁፍ ምላሾች ስህተት ስለመሆናቸው አልያም ውድቅ ስለመደረጋቸው ባለስልጣኑ የመልስ-መልስ ደብዳቤ ጽፎ አያውቅም፡፡ አሻም ቲቪ የባለስልጣኑን ማሳሰቢያን ጨምሮ ከተለያዩ ተቋማትና ግለሰቦች እጅግ የበረታ ዛቻ፣ ማስፈራሪያ፣ የጋዜጠኞች እስር ሲደርስባት ቢቆይም ሁሉንም ተቋቁማ ለሙያ ታምና፣ ለህዝብ ደምጽ በመሆን እስካዘሬ ዘልቃለች፡፡ በቀጣይ ጊዜያት እንደ አስፈላጊነቱ የአሻም ቲቪ የሥራ ኃላፊዎች ዝርዝር መግለጫን የሚሰጡ ይሆናል፡፡ እስካዛሬ አብራችሁን ለቆየችሁ እና ወደፊትም ለምትዘልቁ የአሻም ተከታታዮች ምስጋናችንን ከልብ የመነጨ ነው" ሲል አሻም አሳውቋል:: (Via አሻም ቲቪ) @topmereja

#Updated የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ለአሻም ቲቪ የሰጠው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ አንድም በተጨባጭ የተረጋጋጠ ማስረጃ የሌለው ነው  ሲል አሻም ቲቪ አስታወቀ! "የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዛሬ መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም ለአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር በጻፈው ደብዳቤ ‹‹ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ›› ሰጥቷል፡፡ ባለስልጣኑ ለእዚህ ውሳኔ ያበቃው ‹‹ ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን፣ ግጭት አባባሽ ዘገባዎችን፣ የሕዝብን አብሮነት የሚሸረሸሩ፣ የአገርና ብሔራዊ ጥቅም የሚጎዱ መረጃዎችን በቂ ማጣራትና ምክንያታዊ ጥረት ሳያደርግ በተደጋጋሚ ማሰራጨቱን በይዘት ክትትል በማረጋገጤ ነው ›› ብሏል፡፡ ይሁንና በደብዳቤው አንድም ቦታ በማስረጃ የተደገፈ የይዘት ክትትል አላቀረበም፡፡ ይህ ለአሻም የተሰጣት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ሲቀጥል ‹‹ ከዚህ ቀደም ባሰራጨው ግጭት ተኮር እና ሚዛናዊነት የጎደለው ዘገባ ከደርጊቱ እንዲቆጠብ በተደጋጋሚ በባለስልጣኑ የጽሁፍና የቃል ማሳሰቢያ ሲሰጠው መቆየቱን ›› አስታውሶ ‹‹ ጣቢያው ግን የባለስልጣኑን ማሳሰቢያ ባለማክበር የሀገሪቱን ህጎች የሚጥሱ ይዘቶችን በማሰራጨት ላይ ይገኛል ›› ሲል ወንጅሏል፡፡ በተመሳሳይ ለእዚህ ከፍተኛ ውንጀላ በአሻም ምክንያት የተፈጠረ ግጭት መኖሩን፣ የህዝብን አብሮነት የሚሸረሽሩ፣ ብሔራዊ ጥቅምን የሚጎዱ መረጃዎች ስለማቅረቧ አንድም ተጨባጭ ማስረጃ አላቀረበም፡፡ ባለስልጣኑ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ አሻም በምትሰራቸው ሚዛናዊ ዘገባዎች ላይ ኢ-አሰማኝ የሆኑ የማሳሰቢያ ደብዳቤዎችን ሲጽፍ ሰንብቷል፤ የሥራ ኃላፊዎችም በቃል ሲያስጠነቅቁ ከርመዋል፡፡ ይሁን እንጂ አሻም ለሁሉም ደብዳቤዎች ተገቢ ምላሾችን ከነማስረጃዎቹ በመጥቀስ ምላሽ ስትሰጥ ከርማለች፡፡ አንድም ጊዜ ግን አሻም የሰጣቻቸው የጽሁፍ ምላሾች ስህተት ስለመሆናቸው አልያም ውድቅ ስለመደረጋቸው ባለስልጣኑ የመልስ-መልስ ደብዳቤ ጽፎ አያውቅም፡፡ አሻም ቲቪ የባለስልጣኑን ማሳሰቢያን ጨምሮ ከተለያዩ ተቋማትና ግለሰቦች እጅግ የበረታ ዛቻ፣ ማስፈራሪያ፣ የጋዜጠኞች እስር ሲደርስባት ቢቆይም ሁሉንም ተቋቁማ ለሙያ ታምና፣ ለህዝብ ደምጽ በመሆን እስካዘሬ ዘልቃለች፡፡ በቀጣይ ጊዜያት እንደ አስፈላጊነቱ የአሻም ቲቪ የሥራ ኃላፊዎች ዝርዝር መግለጫን የሚሰጡ ይሆናል፡፡ እስካዛሬ አብራችሁን ለቆየችሁ እና ወደፊትም ለምትዘልቁ የአሻም ተከታታዮች ምስጋናችንን ከልብ የመነጨ ነው" ሲል አሻም አሳውቋል:: (Via አሻም ቲቪ)      @topmereja

#accident የቱርክ አየር መንገድ ፓይለት አውሮፕላን እያበረረ ህይወቱ አለፈ የቱርክ አየር መንገድ አብራሪ ከአሜሪካ ሲያትል ተነስቶ ወደ ቱርክ ኢስታንቡል የሚጓዝ አውሮፕላን በማብረር ላይ እያለ
+1
#accident የቱርክ አየር መንገድ ፓይለት አውሮፕላን እያበረረ ህይወቱ አለፈ የቱርክ አየር መንገድ አብራሪ ከአሜሪካ ሲያትል ተነስቶ ወደ ቱርክ ኢስታንቡል የሚጓዝ አውሮፕላን በማብረር ላይ እያለ ህይወቱ ማለፉ ተነገረ፡፡ የ59 ዓመቱ አውሮፕላን አብራሪ ኢልሴሂን ፔሊቫን በበረራ ላይ እያለ በህመም በመውደቁ ረዳት አብራሪው አውሮፕላኑን ያለምንም ችግር ማሳረፉን የቱርክ አየር መንገድ ቃል አቀባይ ያህያ ኡስቱን በኤክስ ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ ለአብራሪው የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ በማድረግ ለተሻለ ህክምና እንዲደርስ የተደረገው ጥረት ሳይሳካ መቅረቱ ተገልጿል። ረዳት አብራሪው አውሮፕላኑን በፍጥነት በማሳረፍ ለዋና አብራሪው እርዳታ ለማድረግ ቢሞከርም ህይወቱን ማትረፍ እንዳልተቻለ ቃል አቀባዩ ገልጸዋል። ወደ ኢስታንቡል በመብረር ላይ የነበረው ኤርባስ350 አውሮፕላን ባጋጠመው የአብራሪው ድንገተኛ ህመም የተነሳ በኒውዮርክ ማረፉን ተናግረዋል። በቱርክ አየር መንገድ ውስጥ ከ2007 ጀምሮ በአብራሪነት ሲሰራ የቆየው አብራሪው ባለፈው መጋቢት ወር ባደረገው የጤና ምርመራ ስራውን ለመስራት የሚከለክል የጤና እክል እንደሌለበት መረጋገጡንም ጠቅሰዋል። ፔሊቫንን ለሞት ያበቃው የጤና ችግር እስካሁን ምን እንደሆነ አለመታወቁን ቢቢሲ ዘግቧል። ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ አደጋ ያጋጠመው በፈረንጆቹ 2015 ሲሆን፤ ዕድሜው 57 የሆነ አብራሪ ከፎኒክስ ወደ ቦስተን በማብራር ላይ ሳለ ህይወቱ ማለፉ ይታወሳል። @topmereja

" አደጋው እጅግ አሰቃቂ ነበር " - ፖሊስ በአዲስ አበባ ዛሬ ረፋድ 4 :00 ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አልፏል። ከጎሮ ወደ ኮዬ እየተጓዘ የነበረ ኮድ 3-69867 ቱርቦ የሆነ
+1
" አደጋው እጅግ አሰቃቂ ነበር " - ፖሊስ በአዲስ አበባ ዛሬ ረፋድ 4 :00 ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አልፏል። ከጎሮ ወደ ኮዬ እየተጓዘ የነበረ ኮድ 3-69867 ቱርቦ የሆነ የጭነት ተሽከርካሪ  ከከተማ አውቶቢስ ጋር ተጋጭቶ ነው አደጋ የደረሰው። በዚህም የ4 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 7 ሰዎች ላይ ቀላል እና ከባድ ጉዳት ደርሷል። በአደጋው የሞቱት ሁሉም ሴቶች ናቸው። ዕድሜያቸውም ከ20 እስከ 52 የሚገመቱ ናቸው። 3ቱ ሴቶች የአውቶቢስ ትኬት በመቁረጥ ላይ እያሉ ነው አደጋው የደረሰባቸው። በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በቤጂንግ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው። የአዲስ አበባ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ " አደጋው እጅግ አሰቃቂ ነበር " ብለዋል። የአደጋው ምክንያት እየተጣራ ነው ሲሉ ገልጸዋል። @topmereja

#Afar በአፋር ክልል ፣ ዱለቻ ወረዳ ሳጋንቶ ቀበሌ በመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ የፈለቀውን ፍል ውኃ ጥናት ሳይደረግበት ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም ማሳሰቢያ ተላለፈ። ማሳሰቢያውን ያስተላለፈው የሰመራ ዩኒ
#Afar በአፋር ክልል ፣ ዱለቻ ወረዳ ሳጋንቶ ቀበሌ በመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ የፈለቀውን ፍል ውኃ ጥናት ሳይደረግበት ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም ማሳሰቢያ ተላለፈ። ማሳሰቢያውን ያስተላለፈው የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ነው። ዩኒቨርሲቲው " በክልሉ በቅርቡ በተከሰተው እና ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ ከተማ ድረስ በተሰማው ርዕደ መሬት ሳቢያ በአካባቢው ከተፈጠረ የመሬት ስንጥቅ ውስጥ ፍል ውኃ መፍለቅ ጀምሯል " ሲል ገልጿል። ይህንን ፍል ውኃ ጥናት ሳይደረግበት ሰዎችም ሆኑ እንስሳት እንዳይጠቀሙት ማሳሰቢያ አስተላልፏል። በሬክተር ስኬል 4.9 በተመዘገበው ርዕደ መሬት የተሰነጠቀው መሬት 1.5 ሜትር ስፋት ያለው ስለመሆኑ አመልክቷል። ካለፉት ሁለት ሳምንታት ወዲህ በአፋር ክልል የተከሰተው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ በአንዳንድ አካባቢዎች የመሬት መሰጠንቅ፣ መኖሪያ ቤቶች ላይ መፍረስና መሰንጠቅ እንዲሁም እስሳት ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ እና መጠነኛ ጉዳት ስለማስከተሉ ዩኒቨርሲቲው አስረድቷል። ህብተረተሰቡ በተፈጥሮ አደጋው ከተሰነጠቁ አካባቢዎች፣ ድልድዮች እና ተራራዎች እንዲርቅ ጥሪ ቀርቧል። #ኢቢሲ @topmereja

መንጃ ፍቃድ❗️ ከአዲስ መንጃ ፈቃድ ውጭ ያሉ ሁሉም መንጃ ፈቃዶች ከነገ ጀምሮ በየአራት ዓመቱ እንደሚታደሱ ተገለፀ! ከአዲስ መንጃ ፈቃድ እና ዕድሜያቸው ከ55 በላይ ከሆኑ ግለሰቦች ውጭ ያሉ ሁሉም
መንጃ ፍቃድ❗️ ከአዲስ መንጃ ፈቃድ ውጭ ያሉ ሁሉም መንጃ ፈቃዶች ከነገ ጀምሮ በየአራት ዓመቱ እንደሚታደሱ ተገለፀ! ከአዲስ መንጃ ፈቃድ እና ዕድሜያቸው ከ55 በላይ ከሆኑ ግለሰቦች ውጭ ያሉ ሁሉም መንጃ ፈቃዶች ከነገ ጀምሮ በየአራት ዓመቱ እንደሚታደሱ የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡ ባለሥልጣኑ ባለፉት 6 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፍትኃዊነት ጥያቄን ሲያስነሳ የነበረው የሁለት ዓመት እና የአራት ዓመት የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት ጥያቄ ምላሽ ማግኘቱን ገልጿል። በዚህም ከአዲስ መንጃ ፈቃድ እና ዕድሜያቸው ከ55 በላይ ከሆኑ ግለሰቦች ውጭ ያሉ ሁሉም መንጃ ፈቃዶች ከነገ መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በየአራት ዓመቱ እንደሚታደስ አስታውቋል፡፡ አዲስ መንጃ ፈቃድም ከሁለት ዓመት ሙከራ በኋላ፣ ባለው አሰራር መሠረት በየአራት ዓመቱ እንደሚታደስ ከባለስልጣኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ዕድሜያቸው ከ55 ዓመት በላይ ለሆኑ ግለሰቦች በየሁለት ዓመት የሚታደስ ሆኖ ክፍያው የአራት ዓመቱ ክፍያ ግማሽ (50%) እንደሚሆንም ተመላክቷል።     @topmereja

🇪🇹 🇪🇷 📞 ተቋርጧል በቅርቡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ያቋረጠ ሲሆን ! አሁን ደሞ ሁለቱ ሀገራት የሚያደርጉት የስልክ መስመር ተቋርጧል:: @TopMereja
🇪🇹 🇪🇷 📞 ተቋርጧል በቅርቡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ያቋረጠ ሲሆን ! አሁን ደሞ ሁለቱ ሀገራት የሚያደርጉት የስልክ መስመር ተቋርጧል:: @TopMereja

#international news ኢላን መስክ ብራዚል ውስጥ ተዘግቶ የነበረውን ኤክስ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍሎ አስከፈተ!!! የብራዚል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞው ትዊተር የአሁኑ ኤክስ ላይ ጥሎት የነበ
#international news ኢላን መስክ ብራዚል ውስጥ ተዘግቶ የነበረውን ኤክስ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍሎ አስከፈተ!!! የብራዚል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞው ትዊተር የአሁኑ ኤክስ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ማንሳቱን አስታውቋል። ዳኛ ኤክሳንደር ዴ ሞራየስ ውሳኔያቸውን ሲያነቡ ማኅበራዊ ሚድያው ላይ የተጣለው ዕግድ የተነሳው ቅጣቱን ስለከፈለ እና የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጩ ገፆችን ስለዘጋ ነው ብለዋል። በመግለጫው መሠረት የኢላን መስክ ንብረት የሆነው ኤክስ 5.1 ሚሊዮን ዶላር ከፍሏል። ኩባንያው በሀገሪቱ ሕግ መሠረት ብራዚል ውስጥ ተወካይ ለመቅጠርም ተስማምቷል። ዳኛው የኢላን መስክ ማኅበራዊ ሚድያ ብራዚል ውስጥ እንዲታገድ ወስነው የነበረው መንግሥት የተሳሳተ መረጃ ያሰራጫሉ ያላቸውን ገፆች ባለመዝጋቱ ነው። በተለይ አንዳንድ ገፆች በ2022 የነበረውን የብራዚል ምርጫ ለማደናቀፍ የተሳሳተ መረጃ አሰራጭተዋል ተብለው ይጠረጠራሉ። የብራዚል ኔትዎርክ አቅራቢ ድርጅቶች ተቆጣጣሪ የሆነው አናቴል በሚቀጥሉት 24 ሰዓታት ውስጥ ኤክስን ለተጠቃሚዎች ክፍት እንዲያደርግ ተነግሮታል። የቀድሞው ትዊተር የአሁኑ ኤክስ ብራዚል ውስጥ 24 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች እንዳሉት ይነገራል።

#Update በተለያዩ የወለጋ ወረዳዎች በቀጠለ ግጭት ቢያንስ ስድስት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ በምዕራብ ወለጋ ዞን በሚገኙት ቤጊ እና ቆንዳላ ወረዳዎች፣ እንደዚሁም በቄለም ወለጋ ዞን፣ ሳጆ ወላሊ ወ
+1
#Update በተለያዩ የወለጋ ወረዳዎች በቀጠለ ግጭት ቢያንስ ስድስት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ በምዕራብ ወለጋ ዞን በሚገኙት ቤጊ እና ቆንዳላ ወረዳዎች፣ እንደዚሁም በቄለም ወለጋ ዞን፣ ሳጆ ወላሊ ወረዳ በመንግሥት ታጣቂዎች እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል፣ ባገረሸው ግጭት፣ “ባለፉት ሦስት ቀናት ቢያንስ ስድሰት ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል” ሲሉ ነዋሪዎች ተናግረዋል። “ሰዎቹ የተገደሉት የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች ካፈገፈጉ በኋላ የመንግሥት ኀይሎች በወሰዱት እርርምጃ ነው “ያሉት ነዋሪዎቹ ድርጊቱን ኮንነዋል። በጉዳዩ ላይ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግስትና በየደረጃው ካሉ ባለስልጣናት ምላሽ ለማገኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም። ከዚህ በፊት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኀይሉ አዱኛ ለተመሳሳይ ውንጀላ በሰጡት ምላሽ፣ “የመንግሥት ኀይሎች ሲቪል ሰዎችን ዒላማ አያደርጉም፤” በማለት አስተባብለዋል። “ለታጣቂው ቡድን የሎጅስቲክስ ድጋፍ የሚያደርጉና መረጃ የሚሰጡ ሰዎች ይያዛሉ” ሲሉ አክለው የገለጹት አቶ ኀይሉ፣ ጉዳያቸው የሚጣራው “ሕግን በተከተለ መንገድ” መኾኑን ተናግረዋል።