en
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Top Mereja

Channel Top Mereja (@topmereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 338 subscribers, ranking 10 174 in the News & Media category and 1 514 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 338 subscribers.

According to the latest data from 04 October, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -234 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 October, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 338
Subscribers
No data24 hours
-547 days
-23430 days
Posts Archive
#ዶላር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዶላር ዋጋ አሽቆለቆለ። ባለፉት በርካታ ቀናት በንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር በ112 ብር ከ3957 ሳንቲም እየተገዛ በ123 ብር ከ6353 ሳንቲም ሲሸጥ ነበር።
#ዶላር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዶላር ዋጋ አሽቆለቆለ። ባለፉት በርካታ ቀናት በንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር በ112 ብር ከ3957 ሳንቲም እየተገዛ በ123 ብር ከ6353 ሳንቲም ሲሸጥ ነበር። ዛሬ ባንኩ ይፋ ባደረገው የዕለታዊ የምንዛሬ ተመን አንዱን የአሜሪካ ዶላር የሚገዛበትን ዋጋ ወደ 113 ብር ከ1308 ሳንቲም አሳድጎ መሸጫውን ወደ 115 ብር ከ3934 ሳንቲም አውርዶታል። እንደ ዛሬው የምንዛሬ ተመን ባንኩ ዶላር መግዣውን በ1 ብር ከፍ ያደረገው ሲሆን መሸጫው ላይ ካለፉት ቀናት የ8 ብር ቅናሽ አድርጎበታል። @topmereja

#Addis Abeba እነ ጆን ዳንኤል የክስ መቃወሚያ አቀረቡ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል በመንቀሳቀስ የተከሰሱ ስድስት ግለሰቦች ክሱ እንዲሻሻል የመጀመሪያ ደረጃ የክስ መ
#Addis Abeba እነ ጆን ዳንኤል የክስ መቃወሚያ አቀረቡ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል በመንቀሳቀስ የተከሰሱ ስድስት ግለሰቦች ክሱ እንዲሻሻል የመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያ አቀረቡ። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የህገ መንግስትና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የቀረበውን የክስ መቃወሚያ መርምሮ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በዛሬው ቀጠሮ የክስ መቃወሚያቸውን በጠበቆቻቸው አማካኝነት ያቀረቡት ተከሳሾቹ ዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል)፣ አማኑኤል መውጫ፣ ናትናኤል ወንድወሰን፣ ኤልያስ ድሪባ፣ ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው። የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በነ ዮሃንስ ዳንኤል መዝገብ በስድስት ተከሳሾች ላይ አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣ የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ ወንጀል ክስ በተጨማሪም በ1ኛ ተከሳሽ ብቻ ደግሞ የአየር መንገዱን መልካም ስም ለሚያጎድፍ በተንቀሳቃሽ ምስል በኮምፒዩተር ስርዓት አማካኝነት ማሰራጨት ወንጀል የሚል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል። ተከሳሾቹ የክሱ ዝርዝር ከደረሳቸው በኋላ ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ በተሰጠ ትዕዛዝ መሰረት ዛሬ ከማረሚያ ቤት ቀርበው ጉዳያቸውን ተከታትለዋል። በዚህም የተከሳሽ ጠበቆች የክስ ዝርዝሩ እንዲሻሻል የመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያ በጽሁፍ አቅርበዋል። ፍርድ ቤቱ በተከሳሾች በኩል በቀረበው የክስ መቃወሚያን በሚመለከት ዐቃቤ ሕግ ከቀጠሮ በፊት መልሱን (አስተያየቱን) በሬጅስትራር በኩል እንዲያቀርብ በማለት በአጠቃላይ በመቃወሚያው ላይ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም ተቀጥሯል። @topmereja

#ህገመንግስት አንቀጽ 3: የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ 🇪🇹 1. የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከላይ አረንጓዴ፣ ከመሐል ቢጫ፣ ከታች ቀይ ሆኖበመሐሉ ብሔራዊ ዓርማ ይኖረዋል፡፡ ሦስቱም ቀለማት እኩል ሆነው
+1
#ህገመንግስት አንቀጽ 3: የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ 🇪🇹 1. የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከላይ አረንጓዴ፣ ከመሐል ቢጫ፣ ከታች ቀይ ሆኖበመሐሉ ብሔራዊ ዓርማ ይኖረዋል፡፡ ሦስቱም ቀለማት እኩል ሆነው በአግድም ይቀመጣሉ፡፡ 2. ከሰንደቅ ዓላማው ላይ የሚቀመጠው ብሔራዊ ዓርማ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ ሕዝቦች እና ሃይማኖቶች በእኩልነትና በአንድነት ለመኖር ያላቸውን ተስፋ የሚያንጸባርቅ ይሆናል፡፡ 3. የፌዴራሉ አባሎች የየራሳቸው ሰንደቅ ዓላማና ዓርማ ሊኖራቸው ይችላል፡፡ ዝርዝሩን በየራሳቸው ምክር ቤት ይወስናሉ፡፡ 17 ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በኢትዮጵያ ተከብሮ ውሏል። @topmereja

#incident እናት እና አባቷን ለገንዘብ ስትል ገድላ ቤታቸው ውስጥ ለዓመታት የደበቀቸው ልጅ ተፈረደባት!!! በዩናይትድ ኪንግደም ኤሴክስ በተባለው ግዛት ውስጥ ጡረተኛ እናት እና አባቷን ለገንዘብ
+1
#incident እናት እና አባቷን ለገንዘብ ስትል ገድላ ቤታቸው ውስጥ ለዓመታት የደበቀቸው ልጅ ተፈረደባት!!! በዩናይትድ ኪንግደም ኤሴክስ በተባለው ግዛት ውስጥ ጡረተኛ እናት እና አባቷን ለገንዘብ ስትል በመግደል ለአራት ዓመታት በቤታቸው ውስጥ የደበቀቸው ልጅ የዕድሜ ልክ እስር ተፈረደባት። የ36 ዓመቷ ቨርጂኒያ ማካሉህ ጡረተኛ እናት እና አባቷ የሚያገኙትን የጡረታ ገንዘብ እና ሌሎች ገቢዎችን ለመጠቀም ስትል የፈጸመችው ግድያ ለአራት ዓመታት ያህል ሳይታወቅ ቆይቷል። ለጎረቤት እና ለዘመድ አዛውንቶቹ ወላጆቿ ለእረፍት ወደ ባሕር ዳርቻ አካባቢ መሄዳቸውን በመንገር ማንም ጥርጣሬ እንዳይገባው ያደረገችው ልጅ፤ ከዓመታት በኋላ የተፈጠረን ጥርጣሬ መሠረት በማድረግ ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ግለሰቦቹ በልጃቸው መገደላቸውን አረጋግጧል። የዩኒቨርስቲ መምህር የነበሩት የ70 ዓመቱ አባት ጆን ማክሉህ ተመርዘው መገደላቸው ሲታወቅ፣ የ71 ዓመቷ እናት ሉዊስ ደግሞ በስለት እና በጠንካራ ነገር ተመትተው ተገድለው ሁለቱም እዚያው ቤታቸው ውስጥ አስከሬናቸው ተደብቶ ቆይቷል። ይህ ዘግናኛ የግድያ ወንጀል ሊጋለጥ የቻለው በኢሴክስ አውራጃ የሚገኝ የአዛውንቶች ደኅንነትን የሚከታተል ቡድን ለፖሊስ በሰጠው ጥቆማ ምክንያት ነበር። የሁለቱን አዛውንቶች ጤንነት በየጊዜው የሚከታተል የሕክምና ባለሙያ ጥንዶቹን ለረጅም ጊዜ እንዳላያቸው በመግለጽ ምን እንዳጋጠማቸው አሳውቆ ነበር። ልጃቸው ወላጆቿ ከሐኪም ጋር ላላቸው ቀጠሮ መገኘት ያልቻሉበትን የተለያዩ ምክንያቶች ስታቀርብ ቆይታለች። በተጨማሪም የኮቪድ ወረርሽን ተከስቶ የእንቅስቃሴ ገደብ መጣሉ የአዛውንቶቹ መጨረሻ በጊዜ እንዳይታወቅ አድርጎ ቆይቶ ነበር። Source. BBC @topmereja

#international news ኢራን ባለፈው ሳምንት ለፈጸመችው የሚሳዔል ጥቃት እስራኤል የአጸፋ እርምጃ መውሰዷ አይቀሬ ሲሆን፣ የእስራኤል የበቀል ጥቃት ጊዜ እየቀረበ ነው። ኢራን ጥቃቱን የፈጸመች
+1
#international news ኢራን ባለፈው ሳምንት ለፈጸመችው የሚሳዔል ጥቃት እስራኤል የአጸፋ እርምጃ መውሰዷ አይቀሬ ሲሆን፣ የእስራኤል የበቀል ጥቃት ጊዜ እየቀረበ ነው። ኢራን ጥቃቱን የፈጸመችው ዋነኛ ወዳጆቿ የሄዝቦላህ መሪ ሐሳን ናስራላህ እና የሐማስ የፖለቲካ መሪ ኢስማኢል ሃኒያህ በእስራኤል የተፈጸሙ ናቸው በተባሉ ጥቃቶች በመገደላቸው መሆኑን ጠቅሳለች። የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ረቡዕ ዕለት እንደተናገሩት ከሆነ የእስራኤል የበቀል እርምጃ “ዒላማውን የጠበቀ እና ገዳይ” ይሆናል። አጸፋው ኢራን የማትጥብቀው ዓይነት መሆኑንም አክለዋል። ከእስራኤል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው የባሕረ ሰላጤው አረብ አገራት የአየር ክልላቸውን ለማንኛውም ጥቃት እንዳይፈቅዱ ኢራን አስጠንቅቃለች። ኢራን እንድትጠቃ እስራኤልን የሚረዳ ማንኛውም አገርም የኢራን ዒላማ እንደሚሆንም ገልጻለች። የእስራኤልን የበቀል እርምጃ በተመለከተ ዋሽንግተን እና ቴል አቪቭ መክረዋል። የኢራን ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል? የሚለው ከግምት ውስጥ ከሚገቡት ነገሮች መካከል ናቸው። በኢራን የኑክሌር ጣቢያዎች ላይ የሚደረግን ማንኛውንም እርምጃ እንደምትቃወም አሜሪካ ከወዲሁ ይፋ አድርጋለች። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ከአራት ሳምንታት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ይካሄዳል። ዋሽንግተን በነዳጅ ተቋማት ላይ በሚደርስ ጥቃት ምክንያት የዋጋ ጭማሪ መከሰቱን አትቀበልም። ወደ ሌላ የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ተጎትታ የመግባትም ፍላጎት የላትም። አብዛኛው ስሌት የኢራንን ምላሽ መለየት እና እንዴት ጉዳቱን መቀነስ ይቻላል የሚለውን ያካትታል። ኢራን በእስራኤል ላይ ያስወነጨፈቻቸው ሚሳዔሎች ወታደራዊ ተቋማትን ዒላማ ማድረጋቸውን እና ለቀደመው ጥቃት ምላሽ ተሰጥቷል የሚል ሐሳብ ነው በኢራን በኩል የተያዘው አቋም።

የአራዳ መጠጥ ምርቶች አቅራቢ የሆነው ኮማሪ ቤቭሬጅ ለሃይኒከን መሸጡ ተሰማ፡፡ በአጭር ጊዜ በተጠቃሚዎች ከፍተኛ ተቀባይነት ያገኘው የአራዳ መጠጦች አምራች ኮማሪ ፋብሪካውን ለሃይኒከን ለመሸጥ ሲያደር
+1
የአራዳ መጠጥ ምርቶች አቅራቢ የሆነው ኮማሪ ቤቭሬጅ ለሃይኒከን መሸጡ ተሰማ፡፡ በአጭር ጊዜ በተጠቃሚዎች ከፍተኛ ተቀባይነት ያገኘው የአራዳ መጠጦች አምራች ኮማሪ ፋብሪካውን ለሃይኒከን ለመሸጥ ሲያደርግ የነበረው ድርድር ከሳምንት በፊት መጠናቀቁን ነው ካፒታል ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች የሰማችው፡፡ የሽያጩ ድርድር ለበርካታ ወራት ሲደረግ የነበረ መሆኑን የገለጹት ምንጮች ሁለቱ ወገኖች በሀምሌ ወር ወደ መጨረሻ የድርድር ምእራፍ ተሸጋግረው የነበረ ቢሆንም ሀምሌ 22 ቀን 2016 ዓም ወደ ትግበራ የገባውን የምንዛሬ ገበያ ለውጥ ተከትሎ ድርድሩ በድጋሚ ሲደረግ እንደነበር ነው የተጠቀሰው፡፡ የሽያጩ ዋጋ በዚህ ወር መጨረሻ በይፋ ይገለጻል ያሉት ምንጮች ሁለቱ ወገኖች በዚሁ ወቅት በይፋ ፋብሪካውን እንደሚረካከቡ ነው የጠቀሱት፡፡ ኮማሪ ከአዲስ አበባ በሰሜን ምስራቅ 96 ኪሜ ርቀት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጨኬ አካባቢ በገነባው ፋብሪካ በሰዐት 27 ሺ ጠርሙስ የተለያዩ የአራዳ መጠጥ ምርቶችን ያመርታል፡፡ ከሶስት አመት በፊት ወደስራ የገባው እና በኢትዮጵያ ባለሃብቶች የተቋቋመው ፋብሪካው ከ29 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ የተደረገበት ነው፡፡ እኤአ በ2011 ሀረር እና በደሌ ቢራ ፋብሪካዎችን ከመንግስት በ163 ሚሊየን ዶላር በመግዛት ወደ ኢትዮጵያ የመጠጥ ገበያ የተቀላቀለው በአለም ታዋቂ የሆነው የቢራ አምራች ሃይኒከን እኤአ በ2015 ቂሊንጦ ላይ በ310 ሚሊየን ዩሮ ባስገነባው ዘመናዊ የቢራ መጥመቂያ ታዋቂውን አለም አቀፍ ብራንዱን ጨምሮ የተለያዩ የቢራ ምርቶችን እያመረተ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ @topmereja

#Update ዛሬ ጠዋት በአዋሽ እንዲሁም በመተሀራ አከባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። በኢትዮጵያ ከሳምንት በፊት 4.9 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በአዋሽ ፣ መተሀራ ፈንታሌ ተራራ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ መድረሱን ሪፖርት መደረጉ ይታወሳል። በዛሬው ዕለት ደግሞ ላይ ከጠዋቱ 1:40 አከባቢ በድጋሜ ተመሳሳይ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን በአከባቢው ያለ የቲክቫህ ቤተሰብ አረጋግጦልናል። ሳቡሬ የሚባል አከባቢ እንዳለ የገለጸልን ቤተሰባችን "ከጠዋቱ 11:00 ጀምሮ ንዝረት ይሰማ ነበር ልክ 1:40 አከባቢ ሲሆን ከባለፈው የበለጠ የመሬት መንቀጥቀጥ ለሰከንዶች ተሰምቶናል" ሲል ነግሮናል። እሱ ከሚገኝበት ቦታ በቅርብ ርቀት የፈንታሌ ተራራ መኖሩን የጠቆመው ይኸው ቤተሰባችን፥ "በእኛ በኩል ባለው ፈንታሌ ተራራ የመሰንጠቅ ነገር አለ ተብሎ ሰዎች ሊያጣሩ ሄደዋል የተፈጠረውን ነገር ግን እስካሁን አላወቅንም" ሲል ተናግሯል። ላለፉት አንድ ወራት በዚሁ አይነት ሁኔታ መቆየታቸውን ገልጾ " በተደጋጋሚ ሪፖርት እናደርጋለን አሁን ግን እየተላመድነው መጥተናል" ሲል ያለውን ሁኔታ ገልጾልናል። በተመሳሳይ የመሬት መንቀጥቀጥን የሚከታተሉ ድረ-ገጾችም እንዲሁ በዛሬው ዕለት 4.6 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በደቡባዊ አፋር ክልል መከሰቱን አስቀምጠዋል። በተጨማሪም መነሻው ከመተሀራ በቅርብ ርቀት ላይ መከሰቱን የሚገልጹ እና የመሬት መንቀጥቀጡም በሬክተር ስኬል 5.1 መሆኑን የሚገልጹ መረጃዎች ወጥተዋል። @topmereja

#Update የስም ቀይሩ ውሳኔው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለአሻም ከላክው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ጋር የሚገናኝ አለመሆኑን የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ገልጿል። የፍርድ ቤት ትእዛዙ የወጣው
#Update የስም ቀይሩ ውሳኔው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለአሻም ከላክው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ጋር የሚገናኝ አለመሆኑን የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ገልጿል። የፍርድ ቤት ትእዛዙ የወጣው በብስራት ራድዮ ሲተላለፍ ከነበረው አሻም አፍሪካ የተሰኘ ፕሮግራም አዘጋጆች ተቋሙ ላይ ባቀረቡት ክስ መሰረት መሆኑን  የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ፈቃድ፣ ምዝገባና እውቅና ዴስክ ሃላፊ አቶ ደሴ ከፍያለው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። የስሙ ጉዳይ ቆየት ያለ ክስ እንደነበር ገልጸው ይግባኝ ተጠይቆበት እስከ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የደረሰ እና ለፕሮግራሙ አዘጋጆች ተፈርዶ ውሳኔ የተሰጠበት ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ፍርድ ቤቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ውሳኔውን እንዲያስከብር በጠየቀው መሰረት ደብዳቤ ለአሻም ቴሌቪዥን መጻፉን ገልጸዋል። አሻም ቴሌቪዥን በአዲስ የስም ስያሜ እና  በተጨማሪ አዳዲስ ዝግጅቶች ወደ ተመልካቾች እንደሚደርስ ከመግለፅ ውጪ ስለውሳኔው ያለው ነገር የለም። @topmereja

#accident በሸገር ከተማ አሸዋ ሜዳ በአንድ ሆቴል በተከሰተ የእሳት አደጋ በሆቴሉ አልጋ ይዞ የነበረ ግለሰብ ህይወቱ አለፈ ትላንት ዓርብ ምሽት 3:02 ሰዓት ላይ በሸገር ከተማ አሸዋ ሜዳ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በአንድ ሆቴል ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ የአንድ ሰዉ ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።በእሳት አደጋዉ በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት የደረሰ ሲሆን እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ሲያደርጉ ከነበሩት መካከል ሁለት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ጉዳት ከደረሰባቸዉ መካከል አንዱ የእሳት አደጋ ሰራተኛ መሆኑም ተነግሯል።ህይወቱ ያለፈዉ ግለሰብ እድሜዉ 38 ዓመት የተገመተ ሲሆን በሆቴሉ አልጋ ተከራይቶ የነበረ ነዉ።የእሳት አደጋዉ ተስፋፍቶ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተችሏል።በሌላ በኩል በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሶስት ሚሊኒየም አዳራሽ ጀርባ ለህንጻ ግንባታ ስራ ተቆፍሮ ክፍቱን የተተወና ዉሀ ባቆረ ጉድጓድ ዉስጥ ዕድሜዉ 35 ዓመት የተገመተ ሰዉ ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል። ግለሰቡን ለሞት ያበቃዉ በጥልቅ ጉድጓድ ዉስጥ የተጠራቀመዉን ዉሀ በፓምፕ ለማዉጣት ሲሞክሩ የነበሩ ሰራተኞችን ለማገዝ ወደ ዉሃ ዉስጥ ገብቶ በመስጠሙ መሆኑን አቶ ንጋቱ ጨምረው ነግረውናል።ሟቹ ግለሰብ በአካባቢዉ ባለ ድርጅት ዉስጥ በጥበቃ ስራ ላይ የተሰማራ ነዉም ተብሏል። @topmereja

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ዳታ የዋጋ ቅናሽ አደረገ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በ2022 ሥራ ከጀመረ ወዲህ በሀገሪቱ የሞባይል ዳታ አገልግሎት ዋጋ እስከ 70 በመቶ መቀነሱን አስታዉቋል። በዩናይትድ ኪንግደ
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ዳታ የዋጋ ቅናሽ አደረገ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በ2022 ሥራ ከጀመረ ወዲህ በሀገሪቱ የሞባይል ዳታ አገልግሎት ዋጋ እስከ 70 በመቶ መቀነሱን አስታዉቋል። በዩናይትድ ኪንግደም የሚደገፍ የሞባይል ኔትወርክ ኦፕሬተር በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በመላ አገሪቱ እጅግ በጣም ፈጣን የ4ጂ ሞባይል ኢንተርኔት እንዲያገኙ አስችሏል። በሌላ በኩል መንግስታዊ የቴሌኮም አቅራቢ ድርጅት የሆነዉ ኢትዮቴሌኮም ድግሞ በቅርቡ የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን ዳጉ ጆርናል መዘገቡ ይታወሳል። ኢትዮ ቴሌኮም በፈረንጆቹ 2018 ላይ ሰፊ የሆነ ከ40 እስከ 50 በመቶ የሚሆን ከፍተኛ የታሪፍ ቅናሽ አድርጎ ነበር። ተቋሙ የታሪፍ ቅናሽ አድርጎ የነበረው የደንበኞቹንና የማህበረሰቡን የመክፈል አቅም ያገናዘበ መሆን ይገባል” በሚል እንደሆነ በወቅቱ ገልፆ እንደነበር ይታወሳል። @toomereja

photo content
+1

photo content

images.webp0.06 KB

photo content

#Passport የፖስፖርት የግዜ ቆይታ ከ5 ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ እንደሚል ተገልጿል። የኢሚግሬሽን ዜግነትና አገልግሎት የፖስፖርት የግዜ ቆይታ ከ5 ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ እንደሚል ገልጿል።
+1
#Passport የፖስፖርት የግዜ ቆይታ ከ5 ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ እንደሚል ተገልጿል። የኢሚግሬሽን ዜግነትና አገልግሎት የፖስፖርት የግዜ ቆይታ ከ5 ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ እንደሚል ገልጿል። ፖስፖርት ለማደስ 5 ዓመት ይጠበቅ የነበረ ሲሆን ከአንድ ወር በኃላ ወደ ሥራ በሚገባው አሰራር መሰረት ግን ከ25 ዓመት በላይ ለሆናቸው ዜጎች በየ10 ዓመቱ እንደሚታደስ አገልግሎቱ ገልጿል። @topmereja

#Federal የፌደራል ፍርድ ቤቶች የ2017 ዓ/ም የዳኝነት የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በ6 ኪሎ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተካሂዷል። ፍርድ ቤቶች ከነሀሴ 1/ 2016 ዓ/ም ጀምሮ እስከ መከረም 30/ 2017 ዓ/ም ለሁለት ወራት በከፊል ዝግ ሆነው የቆዩ ሲሆን ዛሬ ጥቅምት 1 በይፋ መከፈታቸው ተበስሯል። #topmereja

#እንድታውቁት እሁድ ጥቅምት 3/2017 ከማለዳዉ 12፡00 እስከ ምሽት 12፡00 ሰዓት ድረስ በጥገና ሥራ ምክንያት በድሬዳዋ ከተማና ዙሪያዋ ፤በሐረር ከተማና ዙሪያዋ ፣ ፊቅ፣ ጅጅጋና ደገሀቡር የመብ
+1
#እንድታውቁት እሁድ ጥቅምት 3/2017 ከማለዳዉ 12፡00 እስከ ምሽት 12፡00 ሰዓት ድረስ በጥገና ሥራ ምክንያት በድሬዳዋ ከተማና ዙሪያዋ ፤በሐረር ከተማና ዙሪያዋ ፣ ፊቅ፣ ጅጅጋና ደገሀቡር የመብራት አገልግሎት ይቋረጣል ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስራቅ ሪጅን 1 ትራንስሚሽን ስብስቴሽን ኦፕሬሽን መምሪያ አስታውቋል። @topmereja

#update የኢትዮ ቴሌኮም 10% ድርሻ ሽያጭ ጥቅምት 6 በሚደረግ ዝግጅት ይፋ እንደሚያደርግ ተሰምቷል። ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (Ethiopian Securities Exchang
#update የኢትዮ ቴሌኮም 10% ድርሻ ሽያጭ ጥቅምት 6 በሚደረግ ዝግጅት ይፋ እንደሚያደርግ ተሰምቷል። ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (Ethiopian Securities Exchange) አማካይነት 10% ድርሻውን ለኢትዮጵያውያን እንደሚሸጥ በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል። @topmereja

#erteria #somali የግብጹ ፕሬዝዳንት ከሶማሊያና ኤርትራ መሪዎች ጋር የሶስትዮሽ ጉባዔ ለማድረግ አስመራ ገቡ የግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታ አልሲሲ ከሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ ሞሃመድ እና ከኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈውርቂ ጋር የሶስትዮሽ ጉባኤ ለማድረግ አስመራ ገቡ። በትላንትናው ዕለት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ ሞሃመድ ኢርትራ መግባታቸው እና ‘በሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት’ ዙርያ ከኢሳያስ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል። የኤርትራ የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገ/መስቀል የግብጽ እና የኤርትራ መሪዎች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በማሻሻል እና ሌሎች የጋራ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩ ገልጸዋል። ይህንንም ተከትሎ የግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታ አልሲሲ፣ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ ሞሃመድ እና ከኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈውርቂ የሶስቱን አገራት ግንኙነትን ለማጠናከር እንዲሁም በቀጠናው ጸጥታ እና መረጋጋት ዙሪያ የሶስትዮች ጉባኤ ያደርጋሉ ተብሏል።    @topmereja

15 ሰው መጋበዝ አቅም ያለው 10$ ያገኛል ስንት ሰው ደረሳችሁ 17 በላይ 👍 25 በላይ 🔥 50 በላይ 🫡 100 በላይ 🤗 250 በላይ 🤝 500 በላይ ❤️ 1000 በላይ ⚡️ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/cherrygame_io_bot/game?startapp=r_1879841685 Join the cherry game using this referral link and win prizes! Play and win!!!!