en
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Top Mereja

Channel Top Mereja (@topmereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 338 subscribers, ranking 10 174 in the News & Media category and 1 514 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 338 subscribers.

According to the latest data from 04 October, 2025, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -234 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 October, 2025), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 338
Subscribers
No data24 hours
-547 days
-23430 days
Posts Archive
ኢትዮ ቴሌኮም በቢሾፍቱ የ5ጂ ኢንተርኔት ኔትዎርክ አገልግሎት አስጀመረ‼️ በቢሾፍቱ ከተማ የቱሪዝም ዘርፉን ወደላቀ ደረጃ ለማሻገር ያስችላል የተባለው የ5ጂ አገልግሎቱን የቢሾፍቱ ከተማና የኢትዮ ቴሌ
ኢትዮ ቴሌኮም በቢሾፍቱ የ5ጂ ኢንተርኔት ኔትዎርክ አገልግሎት አስጀመረ‼️ በቢሾፍቱ ከተማ የቱሪዝም ዘርፉን ወደላቀ ደረጃ ለማሻገር ያስችላል የተባለው የ5ጂ አገልግሎቱን የቢሾፍቱ ከተማና የኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራሮች በይፋ አስጀምረዋል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህወት ታምሩ የ5ጂ አገልግሎት በቢሾፍቱ ከተማ መጀመሩ ከተማዋ በቱሪዝም፣ በንግድና በሌሎችም ዘርፎች ከፍተኛ ዕድገት ለማምጣት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። በከተማዋ የ5ጂ አገልግሎት መጀመር ስማርት ቢሾፍቱን ለመገንባት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑንም ተናግረዋል። የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ አቶ አለማየሁ አሰፋ፥ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጨረሻው ፈጣን የሆነውን የ5ጂ አገልግሎት በከተማዋ መጀመር የቢሮ ስራዎችን ለማቀላጠፍ፣ ለተገልጋዩ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት፣ ስማርት ሲቲን ለመገንባት፣ የቢሾፍቱን የቱሪስት መስህብነት አቅም ለማሳደግና በርካታ አገልግሎቶችን ለማከናወን የሚረዳ መሆኑን ገልፀዋል። 130 ዓመታት ለህዝቡ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ኢትዮ ቴሌኮም ዓለማችን የደረሰችበትን የ5ጂ ኔትዎርክ አገልግሎት በቀጣይ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለማስጀመር እየሰራ መሆኑ ተገልጿል። @topmereja

ጎግል ፕሌይ ኢትዮጵያውያን አልሚዎችን መቀበል ጀመረ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ጉዳዩን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልእክት፤ የጎግል ፕሌይ የአልሚዎች ምዝገባ ኢትዮጵያውያን
ጎግል ፕሌይ ኢትዮጵያውያን አልሚዎችን መቀበል ጀመረ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ጉዳዩን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልእክት፤ የጎግል ፕሌይ የአልሚዎች ምዝገባ ኢትዮጵያውያን አልሚዎችን መቀበል መጀመሩ ለኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ ተጽእኖ የሚፈጥር ነው ብለዋል። ይህ ምዕራፍ የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ተሰጥኦ ባለቤቶች መተግበሪያዎቻቸውን በዓለም ላይ ካሉት ትላልቅ ዲጂታል መድረኮች ላይ እንዲያትሙ አዲስ እድሎችን እንደሚከፍትም ገልፀዋል። መንግስት የዲጂታል ኢኮኖሚውን ለመገንባት በርካታ ተነሳሽነቶችን በመተግበር እየሰራ መሆኑን ገልጸው ይህ አዲስ ጅማሮ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ነው ብለዋል። የዘርፉ ባለሙያዎች ይህንን እድል ተጠቅመው ችግር ፈቺ መተግበርያዎችን በማልማት በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት የድርሻቸውን እንደሚወጡ ጥሪ አቅርበዋል። በሚኒስቴሩ አማካሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን ሙሉጌታ ለኢትዮጵያውያን ስታርታፖች ምቹ ሥነ-ምህዳርን ለማዳበር ከሚተገበሩ ሰራዎች መካከል በአለም አቀፍ የዲጂታል መድረኮች እንዲሳተፉ የሚያስችሉ አለማቀፋዊ ግንኙነቶችን ማጠናከር ወሳኝ በመሆኑ እድሉን ለማመቻቸት የተለያዩ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል። እያይዘውም ይህ አዲስ እድል ኢትዮጵያውያን ገንቢዎች የጎግል ፕሌይን አለምአቀፍ ታዳሚዎች በቀጥታ በማግኘት መተግበሪያዎቻቸው ሰፊ እይታን እንዲያገኝ እና አለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስችላል ማለታቸውን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። የሀገር ውስጥ ገንቢዎች ከአካባቢው፣ ከማህበረሰቡ ወግና አኗኗር ጋር ተዛማጅነት ያላቸውን መተግበሪያዎች በማልማት እንዲሁም ለአለማቀፍ ገበያው የሚመጥን ስራ እንዲሰሩ እንደሚበረታቱም ገልፀዋል። @topmereja

https://t.me/PAWSOG_bot/PAWS?startapp=3wFfO3pQ LFG! PAWS is the new top dog! 🐾

#መገናኛ " የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መሾመር ግንባታ ተጀምሯል ፤ ለገንቢው እንዲያጠናቅቅ የተሰጠው 45 ቀናት ነው " - አቶ ጥራቱ በየነ ከፍተኛ መጨናነቅ ባለበት " መገናኛ ' አካባቢ የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መሾመር ግንባታ መጀመሩ ተገልጿል። በአዲስ አበባ ከፍተኛ የሆነ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት ፣ መኪና የሚበዛበትና የሚገናኝበት ፣ እጅግ በርካታ እግረኞችም የሚንቀሳቀሱበት ስፍራ ነው " መገናኛ " አካባቢ። በዚህ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የትራንስፖርት መጨናነቅ ለመፍታት ያግዛል የተባለ የመሬት ውስጥ ለውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መሰራት ጀምሯል። ይህ ፕሮጀክት ከቦሌ ኤርፖርት እስከ መገናኛ ባለው የመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ሾል አንዱ አካል እንደሆነ ተመላክቷል። ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ምን አሉ ? " መገናኛ በጣም ብዙ ሰዎች ተሽከርካሪዎችም የሚገናኙበት በመሆኑ ከፍተኛ መጨናነቅ አለ። ቀድም ብሎ የቀለበት መንገድ የሚባለው ስለነበር መንገዱ ለእግረኞች ማቋረጫ በቂ አልነበረም። በዚህም ህብረተሰቡ በርካታ ችግር እንዲያሳልፍ ሆኗል። ይሄ ትልቅ ጎዳና እንደመሆኑ የሚሰራው እግረኞች ደህንነታቸው ተጠብቆ ምንም ሳይቸገሩ በመሬት ውስጥ መሻገር የሚችሉበት ነው። የታክሲ መጫኛና ማውረጃ ተርሚናልም ይገነባል በማዶ በኩል። በሙልጌታ ህንጻ ስርም ሁለት ወለል ያለው ተርሚናል ይገነባል። እግረኞች ከአንዱ ተርሚናል ወደሌላኛው ተርሚናል የሚገናኙት በመሬት ውስጥ ይሆናል። ከላይ ምንም አይነት የሰው እንቅስቃሴ በማይኖርበት ወይም በኒቀንስበት ሁኔታ ነው እየሰራን ያለነው። ገንቢው ተቋራጭ ይህንን ሾል እንዲያጠናቅቅ የተሰጠው ጊዜ 45 ቀን ነው። ትንሽ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል። ለ45 ቀናት መንገዱን ስንዘጋው የነዋሪዎች እና የመኪና እንቅስቃሴ በተለይ መገናኛ ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት እንደመሆኑ ጫና መፍጠሩ አይቀርም። ዛሬ የምንወስነው ውሳኔ ምናልባት ለወደፊቱ ለበርከታ ረጅም አመታት ዘላቂ መፍትሄ ይሆናል። ለ45 ቀናት በ3 ሺፍት ነው የምንሰራው። ከዛም ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ ከሚሰሩት ኮንትራክተሮች ጋር ተግባብተናል " ብለዋል። የግንባታ ስራውን የሚያማክረው ማነው ? ስራውን የሚያማክረው የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ነው። ኮርፖሬሽኑ " የመገናኛ እግረኛ መተለለፊያ ሾል በአይነቱ የተለየ እና ዘመናዊ ነው " ብሎታል። ሱቆችን ጨምሮ የተለያዩ የፅዳት ቦታዎችም ይሰራሉ ብሏል። " ፕሮጀክቱን በተባለው በ45 ቀናት እንደሚያልቅ እርግጠኞች ነን ፤ 24 ሰዓት ነው የሚሰራው  ፣ በቂ ማሽነሪ አለ፣ በተጓዳኝ ብረትና ሌሎች ዥግጅቶች እየተደረጉ ነው " ሲል ገልጿል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከኤኤምኤን ቲቪ መውሰዱን ይገልጻል። @topmereja

#accident " 7 ሰው ሞቷል ፤ 2 ሰው ተጎድቷል " - በወላይታ ዞን የካዎ ኮይሻ ወረዳ በወላይታ ዞን፤ ካዎ ኮይሻ ወረዳ ላሾ 01 ቀበሌ እና ኮይሻ ላሾ ቀበሌ በትናንትናው ዕለት በቀን 19/02
+2
#accident " 7 ሰው ሞቷል ፤ 2 ሰው ተጎድቷል " - በወላይታ ዞን የካዎ ኮይሻ ወረዳ በወላይታ ዞን፤ ካዎ ኮይሻ ወረዳ ላሾ 01 ቀበሌ እና ኮይሻ ላሾ ቀበሌ በትናንትናው ዕለት በቀን 19/02/2017 ዓ.ም ማታ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት 7 (ሰባት) ሰው የሞተ ሲሆን በ2 ሰው ጉዳት ደርሷል። በንብረት ላይም ጉዳት ደርሷል። ከዚህ በፊት በዛው በካዎ ኮይሻ ወረዳ ላይ ጤፓ ቀበሌ በመሬት ናዳ ምክንያት የተፈናቀሉትን መልሶ ለማቋቋም ስሰራ ቢቆይም ተደጋጋሚ አደጋ በመከሰቱ ችግሩ እያባባሰው መምጣቱ ተገልጿል። መረጀው የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ሥራ ሂደት ነው። @topmereja

#Update እስራኤል አዲሱን የሂዝቦላህ መሪ ሀሽም ሳፊይዲንን መግደሏን አረጋገጠች የእስራኤል መከላከያ ሃይል እንዳስታወቀው÷ የቀድሞው የሂዝቦላህ መሪ ሀሰን ናስራላህ የአጎት ልጅ የሆነው ሀሽም ሳፊይዲን ከሶስት ሳምንት በፊት እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ በወሰደችው የአየር ጥቃት ተገድሏል። ከሀሽም ሳፊይዲን በተጨማሪ የሂዝቦላህ ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ሃላፊ አሊ ሁሴን ሃዚማ እና የቡድኑ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች በጥቃቱ ተገድለዋል ተብሏል፡፡ በጉዳዩ ላይ ሂዝቦላህ የሰጠው ምላሽ አለመኖሩ ተገልጿል። ቀደም ሲል በፈረንጆቹ ጥቅምት 8 ቀን 2024 የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ የእስራኤል መከላከያ ሀይል ሀሰን ሳፊይዲንን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ የሂዝቦላህ መሪዎችና ታጣቂዎች መገደላቸውን ተናግረው ነበር። በወቅቱም ሀሰን ነስራላህን በመተካት ወደ ሂዝቦላህ መሪነት የመጣው ሀሽም ሳፊይዲን ሳይገደል እንዳልቀረ እየተነገረ ነበር። ይሁን እንጂ በእስራኤል ጥቃት የመሪውን መገደል የእስራኤል መከላከያ ሃይል አዛዥ ሌተና ጄኔራል ሄርዚ ሃሌቪ በሰጡት መግለጫ አረጋግጠዋል። @topmereja

ሂዝቦላ የኔታንያሁን የመኝታ ክፍል በድሮን መምታቱ ተዘገበ ሄዝቦላህ ከሊባኖስ የተኮሰው ሰው አልባ አውሮፕላን ቅዳሜ እለት በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ በቂሳሪያ የሚገኘውን መኖሪያ ቤት በመም
ሂዝቦላ የኔታንያሁን የመኝታ ክፍል በድሮን መምታቱ ተዘገበ ሄዝቦላህ ከሊባኖስ የተኮሰው ሰው አልባ አውሮፕላን ቅዳሜ እለት በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ በቂሳሪያ የሚገኘውን መኖሪያ ቤት በመምታቱ በመኖሪያ ቤታቸው ላይ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል። አስቀድሞ በእስራኤል ወታደራዊ ኃይሉ ሳንሱር እንዳይታተም የተከለከለው ምስል አሁን ላይ ይፋ የተደረገ ሲሆን የድሮን ተፅእኖ በቤቱ ላይ ያደረሰውን ጉዳት ያሳያል። ፍንዳታው በመኝታ ክፍል መስኮት ውስጥ መስታወቱ እንዲሰነጠቅ ያደረገ ሲሆን ወደ ቤቱ ውስጥ ግን አልገባም። በተጠናከረ መስታወት እና ሌሎች መከላከያዎች ምክንያት ወደ ውስጥ ዘልቆ መግባት አልቻለም።የመስታወት ቁርጥራጮች በግቢው ውስጥ በቤተሰቡ የውሃ ዋና ገንዳ ውስጥ እንዳረፉ ተነግሯል። በጥቃቱ ምንም ጉዳት በሰው ላይ አልደረሰም። ኔታንያሁ እና ባለቤታቸው በወቅቱ ቤት ውስጥ እንዳልነበሩም ጄሩሳሌም ፖስት ዘግቧል።ሂዝቦላህ ማክሰኞ በሰጠው መግለጫ “በቂሳርያ በኔታንያሁ መኖሪያ ቤት ላይ ኢላማ ያደረገውን ኦፕሬሽን ሙሉ በሙሉ ሀላፊነቱን እንደሚወስድ አስታውቋል። ኔታኒያሁ በበኩላቸው ይህንን ጥቃት የፈፀመ ከባድ አፀፋ ይጠብቀዋል ሲሉ ተደምጠዋል። @topmereja

#ኢትዮጵያ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከ271 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ ተሰበሰበ በጽ/ቤቱ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን ዳንኤል እንዳሉት፥ በ201
#ኢትዮጵያ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከ271 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ ተሰበሰበ በጽ/ቤቱ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን ዳንኤል እንዳሉት፥ በ2017 በጀት ዓመት ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ድጋፍ ለመሰብሰብ ታቅዷል፡፡ በሩብ ዓመቱም በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን በቦንድ ሽያጭ፣ በ8100 አጭር የጽሑፍ መልዕክትና በስጦታ ከ271 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡን ተናግረዋል። በበጅት ዓመቱ የታቀደውን ድጋፍ ለማሰባሰብ በትኩረት ይሰራል ያሉት ስራ አስፈጻሚው፥ ሕዝቡም እስከ ግንባታው ፍጻሜ ድጋፉን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። መገናኛ ብዙሃንና የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች የገቢ ማሰባሰቢያ አማራጮችን ለሕብረተሰቡ በማሳወቅ ሚናቸውን እንዲወጡ መጠየቃቸውንም ኢዜአ ዘግቧል፡፡ @topmereja

# Accident!!!! በግንባታ ላይ ባለው የመቄዶኒያ ህንጻ ስር ባለ መጋዘን ላይ የተከሰተ የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ዋለ በግንባታ ላይ ባለው የመቄዶኒያ የአእምሮ ህሙማንና የአረጋዊያን መርጃ ህ
+3
# Accident!!!! በግንባታ ላይ ባለው የመቄዶኒያ ህንጻ ስር ባለ መጋዘን ላይ የተከሰተ የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ዋለ በግንባታ ላይ ባለው የመቄዶኒያ የአእምሮ ህሙማንና የአረጋዊያን መርጃ ህንጻ ስር ባለ መጋዘን ላይ ተከስቶ የነበረ እሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ዋለ። ዛሬ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም በለሚኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 3 መቄዶኒያ የአእምሮ ህሙማንና የአረጋዊያን መርጃ ማህበር እያስገነባ ባለዉ ህንጻ ስር ባለ መጋዘን ላይ እሳት አደጋ መከሰቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል። የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ንጋቱ ማሞ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፤ ኮሚሽኑ በደረሰዉ ጥሪ መሰረት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በቦታዉ ፈጥነዉ በመድረስ እሳቱ ሳይስፋፋ በፍጥነት መቆጣጠር ችለዋል። በእሳት አደጋዉ በመጋዘን ውስጥ የነበሩ ልዩ ቁሳቁሶች ላይ መጠነኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት አለመድረሱን ተናግረዋል። @topmereja

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት የሚከተሉትን ሹመቶች ሰጥተዋል:- 1. ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ - የቱርዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር 2. ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት የሚከተሉትን ሹመቶች ሰጥተዋል:- 1. ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ - የቱርዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር 2. ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ -  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር 3. ወ/ሮ ሃና አርአያስላሴ-  የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር

የያህያ ሲንዋር መገደል የጦርነቱ ፍጻሜ አይደለም- ጠ/ሚ ኔታንያሁ ይህን ተከትሎም የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በሰጡት መግለጫ÷ የያህያ ሲንዋር መገደል ከፍተኛ ድል ቢሆንም የጦርነቱ ፍጻሜ እንዳልሆነ አስታውቀዋል፡፡ በዚሁ መሠረት በሀማስ እገታ ሥር የሚገኙ እስራኤላውያን እስከሚለቀቁ ድረስ ጦርነቱ ይቀጥላል ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ በርካታ እስራኤላውያን እንዲገደሉ እና እንዲታገቱ በተደረገበት የጥቅምት 7 ጥቃት የያህያ ሲንዋር ሚና ከፍተኛ እንደነበር አንስተው÷ የመሪው መገደል በአካባቢው ያለውን ሁኔታ ሊቀይረው እንደሚችል አመላክተዋል፡፡ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በበኩላቸው የያህያ ሲንዋር መገደል ለእስራኤል ብሎም ለአሜሪካ ትልቅ ድል መሆኑን ገልጸው÷ የመሪው መገደል ምን አልባትም ጦርነቱ በአጭር ጊዜ እንዲቋጭ ሊያደርገው ይችላል ብለዋል፡፡ በአንጻሩ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የኢራን ልዩ መልዕክተኛ በበኩላቸው÷ የያህያ ሲንዋር መገደል እስራኤልን ከምን ጊዜውም በላይ ለመፋለም የሚያነሳሳ የመንፈስ ጥንካሬ ይሰጠናል ብለዋል፡፡ ሁኔታው ጦርነቱን ከማብረድ ይልቅ ሊያባብሰው እንደሚችልም ነው ያስረዱት፡፡ @topmereja

#international news የሐማስ መሪ ያህያ ሲንዋር ተገድሎ ሊሆን እንደሚችል እስራኤል ገለጸች የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ጋዛ ውስጥ ባደረገው ኦፕሬሽን አዲሱ የሐማስ መሪ ያህያ ሲንዋር ተገድ
+1
#international news የሐማስ መሪ ያህያ ሲንዋር ተገድሎ ሊሆን እንደሚችል እስራኤል ገለጸች የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ጋዛ ውስጥ ባደረገው ኦፕሬሽን አዲሱ የሐማስ መሪ ያህያ ሲንዋር ተገድሎ ሊሆን እንደሚችል እያጣራ መሆኑን ገልጿል። የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት እና የደህንነት ኤጀንሲ በጋራ ባወጡት መግለጫ የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ጋዛ ውስጥ ባደረገው ኦፕሬሽን ሦስት የሐማስ ቁልፍ አመራሮች ተገድለዋል። ከተገደሉት መሪዎች ውስጥም አንዱ ያህያ ሲንዋር ሊሆን እንደሚችል በመግለጫው ተጠቁሟል። ሐማስ በእስራኤል ላይ በፈጸመው የጥቅምት 7 ጥቃት ዋነኛ መሪ የነበረው ያህያ ሲንዋር እስራኤል ልትገድላቸው ከምትፈልጋቸው ሰዎች መካከል በግምባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው። @topmereja

ዛሬ ከቀኑ 6 ሰዓት አካባቢ በአዋሽ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበባ ተሰማ በዛሬው ዕለት ከቀኑ 6 ሰዓት አከባቢ በአዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበ
ዛሬ ከቀኑ 6 ሰዓት አካባቢ በአዋሽ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበባ ተሰማ በዛሬው ዕለት ከቀኑ 6 ሰዓት አከባቢ በአዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ተሰምቷል፡፡ ትናንት ምሽት የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በመዲናዋ አሁንም ዳግም መከሰቱን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶ/ር ኤሊያስ ሌዊ ለኢቢሲ ሳይበር አረጋግጠዋል። ከቀኑ 6 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ከ9 ሰኮንድ በአዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.6 አካባቢ እነደሆነም ዶ/ር ኤሊያስ ገልጸዋል። የመሬት መንቀጥቀጡ የተከሰተው ባለፈው በተከሰተበት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ሲሆን በአካባቢው ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ እንቅስቃሴ አሁንም እንዳልቆመ ዶ/ር ኤሊያስ ተናግረዋል። አሁን የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት መጠኑ አነስተኛ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ኤሊያስ፤ በአዋሽ ፈንታሌ እና ሳቡሬ ከተማ መካከል ላይ ያለው የቅልጥ ዓለት እንቅስቀሴ እስከቀጠለ ድረስ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቱ የመቀጠል እድል እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡      @topmereja

#accident ድምፃዊው ህይወቱ አለፈ የቀድሞው የ one direction አባል ድምፃዊ ሊያም ፓይኒ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል ። የ 31ዓመት እድሜ ያለው ድምፃዊው ፤ በአርጀንቲና ቦነስ
#accident ድምፃዊው ህይወቱ አለፈ የቀድሞው የ one direction አባል ድምፃዊ ሊያም ፓይኒ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል ። የ 31ዓመት እድሜ ያለው ድምፃዊው ፤ በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በመዝናናት ላይ የነበረ ሲሆን ፤ ከአንድ ሆቴል ወለል ላይ ወድቆ ህይወቱ እንዳለፈ ነው እየወጡ ያሉ መረጃዎች የሚናገሩት። የአሟሟቱ መንስኤ ፖሊሶች እያጣሩ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። @topmereja

#Ethiopia ለማረፍ ሲዘጋጅ ጭስ የታየበት አውሮፕላን በተሳካ ሁኔታ አርፏል- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር
#Ethiopia ለማረፍ ሲዘጋጅ ጭስ የታየበት አውሮፕላን በተሳካ ሁኔታ አርፏል- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET248 አውሮፕላን ድሬዳዋ አውሮፕላን ማረፊያ ለማረፍ በዝግጅት ላይ ሳለ በአውሮፕላኑ ውስጥ ጭስ መታየቱ ተገልጿል፡፡ አውሮፕላኑ በድሬዳዋ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላም በማረፍ መንገደኞችን በተለመደው መልኩ ከአውሮፕላኑ ማውረድ መቻሉን የአየር መንገዱ መረጃ አመላክቷል፡፡ አየር መንገዱ ጭሱ የተነሳበትን ምክንያት በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ገልጾ÷ ለተፈጠረው ክስተት መንገደኞቹን ይቅርታ ጠይቋል፡፡ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቁጥር ET154 ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ከሐዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ ሳለ በአውሮፕላን ውስጥ ጭስ መታየቱ ይታወሳል፡፡ በወቅቱም አውሮፕላኑ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተመደበለት የመንገደኞች ማስተናገጃ በር ያለ ምንም እክል በማረፍ መንገደኞቹ ደኅንነታቸው እንደተጠበቀ ማውረዱ ይታወቃል፡፡

#AddisAbaba በአዲስ አበባ የህዝብ ትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ጭማሪ ተደረገ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ዛሬ አዲስ ታሪፍ ይፋ አድርጓል። በዚህም በሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ
#AddisAbaba በአዲስ አበባ የህዝብ ትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ጭማሪ ተደረገ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ዛሬ አዲስ ታሪፍ ይፋ አድርጓል። በዚህም በሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ በተሰማሩ ሚኒ-ባሶች ፣ ሚዲ-ባስ ታክሲዎችና የከተማ አውቶብሶች ላይ የአገልግሎት ታሪፍ ጭማሪ ተደርጓል። አዲሱ ታሪፍ ከነገ ጥቅምት 06 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል። ጭማሪ በተደረገበት በአዲሱ ታሪፍ ዝቅተኛው 10 ብር ሲሆን ከፍተኛው 65 ብር ገብቷል። " ቀድሞ አገልግሎት ሲሰጥበት የነበረው የታሪፍ ተመን ከጥቅምት 20 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ አገልግሎት ላይ የዋለ ነበር ፤ ስሌቱም የነዳጅ ጭማሪ ዋጋን ብቻ ታሳቢ ያደረገ ነበር " ሲል ቢሮው ገልጿል። @topmereja

#ባሕርዳር በባሕርዳር በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 3 ሺህ ሊትር ነዳጅ ተያዘ በባሕርዳር ዳር ከተማ ግሽ አባይ ክፍለ ከተማ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 3 ሺህ ሊትር ነዳጅ ተያዘ፡፡ ነዳጁ በሕገ-ወጥ መንገድ ከማደያዎች በሌሊት ተቀድቶ ሲወጣ በተደረገ ክትትል ከነተጠርጣሪዎቹ እጅ ከፍንጅ መያዙን የክፍለ ከተማው ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት አስታውቋል። 10 በርሚል እና ከ50 በላይ ባለሁለት ሊትር ቤንዚን በክትትል ከተጠርጣሪዎቹ እጅ እንደተገኘም የከተማዋ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመልክቷል፡፡ @topmereja

#Accident #ባሕር_ዳር የተወዳጇ ድምፃዊት አምሳል ምትኬ የባህል ምሽት ቤት እና የምግብ አዳራሽ ዛሬ ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:30 አካባቢ በተነሳ የእሳት ቃጠሎ መውደሙ ተሰምቷል።
#Accident #ባሕር_ዳር የተወዳጇ ድምፃዊት አምሳል ምትኬ የባህል ምሽት ቤት እና የምግብ አዳራሽ ዛሬ ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:30 አካባቢ በተነሳ የእሳት ቃጠሎ መውደሙ ተሰምቷል። የባሕር ዳር ነዋሪ እሳቱን ለመቆጣጠር ያደረገው ርብርብ ጥሩ ነበር። ሆኖም የእሳቱ ሁኔታ ከባድ ስለነበር ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን እና በሰው ላይ እስካሁን ጉዳት አለማድረሱን ሰምተናል። @topmereja