የነብዩ ☪ሠ,ዐ,ወ☪ ሀዲሶች
Open in Telegram
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ ተማሪ ነኝ። Telegram የምጠቀመው «✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ ለማድረስ ብዮ ነው። ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot አላህ ይ ቀበለን✔ JOIN 👇 @Adnan567mh 🌐💚💛❤️
Show more2 077
Subscribers
No data24 hours
+137 days
+1630 days
Posts Archive
2 077
ራሴን ታዘብኩት
ከሁለት ቀን በፊት የረመዷን የመጀመሪያውን ጁሙዐ ለመታደም ወደመስጂድ አቀናው። ያው ረመዷንም ስለሆነ ሰው ይበዛልና መስጂድ ውስጥ ቦታ ማግኘት ማይታሰብ ስለሆነ ብዙ ሰው ውጪ እያነጠፈ ይቀመጣል። እኔን ጨምሮ ግን ሁላችንም ጥላ ቦታ ፍለጋ አይናችንን ብናማትርም ስለሌለ ፀሀይ ላይ ተቀመጥን። የተወሰነ ሰው ደሞ ሰላቱ እስኪጀመር ወደጥግ ሄዶ ከፀሀይ ተጠለለ። ይሄኔ ነው የቂያማ እለቷ ፀሀይ ትዝ ያለችኝ። ዘንግቻት ነበር እንዳሁኑ ብዙ ሺ ኪሎ ሜትር ርቃን ሳይሆን አንድ ስንዝር ያህል ቀርባን የምታቃጥለን ግዜ መኖሩን መዘንጋቴ አስገረመኝ። ብዙ ሰውም ይህን የዘነጋ ይመስለኛል። በዚያ ቀን በነጯ ምድር ላይ የሰው ዘር በሙሉ እንዲቆም ሆኖ በፀሀይ ቃጠሎ ሲነድ ሰባት ሰዎች ግን ከአላህ አርሽ ስር እንደሚጠለሉ ተነግሯል። የዱንያ ፀሀይ እንዲ ያማረረን እኛ በአርሽ ጥላ ስር ከሚጠለሉት ለመሆን መጣር ታድያ የኛ ፋንታ ነው።
እስኪ ለማስታወስ ያህል እነዚህ 7 አይነት ሰዎች እነማን እንደሆኑ እንመልከት👇
🔹አቡ ሁረይራ(ረ.ዐ)እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ(ሰ.ዐ.ወ)እንዲህ ብለዋል። ሰባት ሰዎች አላህ ከርሱ ውጪ ሌላ ጥላ በማይኖርበት ቀን ከአርሽ ጥላ ስር ያስጠልላቸዋል።እነርሱም:
1 ፍትሀዊ መሪ፣
2 በጌታው አምልኮ ተኮትኩቶ ያደገ እና በዚያ መንገድ ወጣትነቱን ያሳለፈ
3 አላህን እያመለከ ያደረ(አላህን ብቻውን ሆኖ ያወሳ)፣
4 ልቦናው መስጂድ ላይ የተንጠለጠለ(ከመስጂድ ጋር የተሳሰረ)፣
5 ለአላህ ሲሉ የተዋደዱ በርሱ የተገናኙና በርሱም የተለያዩ ሁለት ሰዎች፣
6 ክብርና ውበት ያላት እንስት(ለወሲብ)ጋብዛው አላህን እፈራለሁ ያላት(ግለሰብ)፣
7 የቀኝ እጁ ምትመፀውተው የግራ እጁ የማታይ ያክል ምፅዋትን የደበቀ (ግለሰብ)ናቸው።
(ቡኻሪና ሙስሊም)
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
ረመዷን - 4
***
ረመዷን ቀላል ወር አይደለም ። ዱዓ የሚሰማበት፣ ተውባ ተቀባይነት የሚያገኝበት፣ መልካም ሥራ የሚወደድበት ወር ነው። ደጋጎች ይህን ወር እንደ ትልቅ አጋጣሚ ይጠብቁታል። ወሩ የዱዓ ተቀባይነት የሚያገኝበት ነዉና ለረመዷን ብቻ የሚያስቀምጡት ዱዓ አላቸው። በመንፈስ ተዘጋጅተው፤ ዉስጥ ዉጪያቸዉን አጽድተው ይጠባበቁታል። ከወሣኝ ዱዓኦች መካከል የረመዷን ዉስጥ ዱዓ አንዱ ነው።
ሱሑር ላይ ፆም ስትይዙ፣ ማታ ስታፈጥሩ፣ በአዛንና ኢቃማ መካከል፣ ሱብሒ ከመድረሱ በፊት ያለዉን ጊዜ፣ በሱጁድ ዉስጥ፣ ከያንዳንዱ የግዴታ ሶላት በኋላ ዱዓ በማብዛት ተጠቀሙበት። ማን ያውቃል የልባችሁ መሻት ምላሽ የሚያገኘው በዚህ ወር ዉስጥ ሊሆን ይችላል ።
@Adnan567mh
2 077
🍂🍁🍂የረመዷን ሌቦች🍁🍂🍁
👉 ክፍል አንድ
ቢስሚላሂ ረህማኒ ረሂም አልሃምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚን ወሰላቱ ወሰላም ወአላ አሽረፊል አምቢያኢ ወል ሙርሰሊን ነብይና ሙሃመዲን ወአላ አሊሂ ወሰህቢሂ አጅመኢን
አማ በዕድ አሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ
የተከበራችሁ ውድ እህት ወንድሞች የአላህ ራህመት ሆኖ ይህ የተከበረው ረመዷን ወር ላይ አላህ አድርሶናል ከሚፆሙትም አድርጎናል ይህ ማለት በጣም ትልቅ ኒዕማ ነው አላህን(ሱብሃነ ወተዓላ)ልናመሰግነው ይገባል። እናም ይሄንን ትልቅ እድል ልንጠቀምበትና በአግባቡ በመጠቀም ለኼራችን ስንቅ ልንይዝበት ይገባናል።
አላህ ያላቀው የሆነ ትልቅ ወር ነው አላህ ያላቀውን ይህን ወር ደግሞ እኛም በተግባር መልካም ስራ በመስራት ልናከብረው ይገባል።
እንጂ መጥፎ ስራ በመስራት አላህን ከማመፅ ልንቆጠብ ይገባል። ሃቂቃ ይህ ወር ለአማኝ ባሮቹ ብዙ የጀነት ሰበቦች የደገሰበት የሆነ ትልቅ ወር ነው። ስለዚህ አንድ ሙስሊም የሆነ አካል አኼራ የሚያሳስበው ነገ ጀነትን የሚናፍቅ የሆነ ሰው የሄንን ትልቅ አድል ሊጠቀመው ይገባል።
አላህ (ሱብሃነ ወተዓነላ) በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል "አያመን መእዱዳት" በጣት የሚቆጠሩ ቀናቶች ናቸው አለ።
"በናንተም ላይ ፆም ተደነገገ ከናንተ በስተፊት በነበሩት ሰዎች ላይ እንደተደነገገው" ዋናው የተደነገገበትም ምክንየት ተቅዋና ታገኙና "አላህን ልትፈሩ ዘንድ ነው" አለን
ይህ የተከበረው ወር ደግሞ ቀናቶቹ በጣት የሚቆጠሩ የሚታወቁ ቀናቶች ናቸው ምክንያቱም ወሩ ከሰላሳ አይበልጥምና ከነዚህ ወር ቀናቶችም አስረኛው ቀን ላይ እንገኛለን ስለዚህ አንድ ሰው አንድ ቀን አሳልፎ ወደሌላ ቀን በተሸጋገረ ቁጥር ይህ የረህመት ወር ረመዷን እያመለጠው ነው ማለት ነው ስለዚህ ራስን በማጠንከር ወደ ኋላ ሚያደርጉንን ነገር ትተን በኢባዳ ልንጠነክር ይገባል ቀን በቀን ራሳችንን ልንፈትሽና ያለብንን ጉድለት ልንጠግን ይገባል ማለት ነው።
እንደሚታወቀው ይህ ረመዷን የመልካም ስራ የቁርዓን ወር ነው የሶላት የኢባዳ ወር ነው የዚክር ወር ነው ስለዚህ አቅማችን በቻለ ልክ በኢባዳ ልንጠነክር ይገባል።
በአልባሌ ነገሮች ይሄንን ውድ ትልቅ ወር ልናጠፋው አይገባም።
ግዚያችንን በመልካም ነገር ልንጠቀመው ይገባል እያንዳንዱ አቅለኛ የሆነ ሰው እያንዳንዷን ሰከንድ እያንዳንዷን ደቂቃ በአልባሌ በሆነ ነገር እንዲያልፍ መፈቀድ የለብንም
ይቺ ደቂቃ ይቺ ሰከንድ ናት ረመዷን ማለት የረመዷን ሰላሳ ቀን ማለት አሁን እያሳለፍናቸው ያሉት እያንዳንዷ ደቂቃና ሰከንድ ናቸው።
ስለዚህ እያንዳንዷን ሰአት እያንዳንዷን ቀን እያንዳንዷን ሰከንድ በመልካም ስራ ልናሳልፈው ይገባል ማለት ነው።
ወንጀል ሊበቃን ይገባል ወደ አላህ ትክክለኛ ተውበት ልናደርግ ይገባል እውነተኛ ተመላሾች ልንሆን ይገባል አስራ አንድ ወራቶች ላይ ብዙ ወንጀል አሳልፈናል ብዙ ወንጀል ሊኖርብን ይችላል አላህ (ሱብሃነ ወተዓላ) ደግሞ የዛን ወንጀላችንነ ማበሻ ረመዷንን አመጣልን እናም ይሄን የሰጠንን እድል እንጠቀምበት።
ወላሂ ይሄ ትልቅ ኒዕማ ነው ስንት ሰዎች አሉ የተከለከሉ ትናንተ እንደኛው የነበሩ ረመዷንን በጉጉት የሚጠብቁ የነበሩ ሰዎችን ዛሬ አፈር በላያቸው ላይ ተጭኖባቸው ቀብር ውስጥ ገብተዋል። እንደኛው ሲጓጉ የነበሩ ሰዎች ረመዷን አንድ ቀን ሲቀረው ወደ አኼራ የሄደ ሰው አለ። ወይም ደግሞ በሌላ ምክንያት ወደ አኼራ ባይሄድም እንኳ መፆም ያልቻሉ አሉ አልጋ ቁራኛ ሆነው የተቀመጡ መፆም የእፈለጉ ያልቻሉ ብዙዎች አሉ እኛን ከነሱ አላደረገንም ሳንሞት በጤናችን ወዶን እዚህ የራህመት ወር ውስጥ አስገባን። ሃቂቃ ትልቅ እድል ሰጦናል ይሄን እድል ልንጠቀምበት ይገባል። ሁላችንም ልንጠቀምበት ይገባል ቁርዓን በመቅራት ሶላት በማብዛት ዚክር በማለት ተራዊህም በመስገድ ሰደቃ በማብዛት ለእናት አባቶቻችን ለወንድም እህቶቻችን ባጠቃላይ መልካም በመስራት ዝምድናንም በመቀጠል መልካም ስነ ምግባር በማሳየት ባጠቃላይ አላህ በደነገጋቸው ኢባዳዎች በኢኽላስ ልንጠነክር ይገባል።
(አላህ የበለጠ ያውቃል)
መልዕክቱን ሼር በማድረግ በዚህ ውድ ወር ከኢባዳ የተዘናጉትን ወንድም እህቶቻችንን እናንቃቸው።
(በውስጥ መስመር ከአስር ላላነሰ ሰው በመላክ አብሮነታችሁን ግለፁልን።)
ባረከላሁ ፊኩም
በዱዓችሁ አትርሱኝ
https://t.me/Adnan567mh
2 077
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
አቡ ማሊክ ሀሪስ ኢብኑ ዓሊም አል አሽዐሪይ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብሏል ‹‹ንፅህና የእምነት (ኢማን) ግማሽ ነው፡፡ ‹አልሐምዱሊላህ› ያለችው ቃል ሚዛን ትሞላለች፤ ‹ሱብሀነላህ ወልሐምዱሊላህ› የሚሉት ቃላት በምድርና በሰማይ መካከል (ያለውን ቦታ) ይሞላሉ ወይም ትሞላለች፡፡
ሶላት ብርሃን ነው፡፡ ምፅዋት (ሶደቃ) የኢማን ዋቢ ነው፡፡ ትግስት (ሶብር) ብርሃን ነው፡፡ ቁርዓን ላንተ ወይም በአንተ ላይ አስረጅና መስካሪ ነው፡፡ ሁሉም ሰው ነፍሱን ነፃ ያወጣ ወይም ለጥፋት የዳረገ ሆኖ ዕለቱን ይጀምራል፡፡
ሐዲሱን ሙስሊም ዘግበውታል
‹‹ ውዱዕ የሶላት መስፈርት፤ የሰላትን ጠቀሜታ፤ ሶደቃን ማብዛት የሙዕሚን እውነተኝነት፣ ታማኝነትና ቅንነትን ያመለክታል፡፡
‹‹ የሶብር ትሩፋት፤ ቁርዓን ለሁሉም ሸሪዓዊ ብይኖች መነሻ መሰረት መሆኑን፡፡
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
☑️ ሼኸ ፈውዛን አላህ ይጠብቀዉና እንዲህ ይላሉ።
🌐 ከሰዎች መካከል (لا إله إلا الله) የምትለዋን ቃል እንዳይሉ ሸይጣን ያዘናጋቻቸው በጣም ብዙ ሰዎች አሉ።
➷☑️ ሼኸ ፈውዛን አላህ ይጠብቀዉና እንዲህ ይላሉ።
🌐 ከሰዎች መካከል (لا إله إلا الله) የምትለዋን ቃል እንዳይሉ ሸይጣን ያዘናጋቻቸው በጣም ብዙ ሰዎች አሉ።
➷አንዳንዴ ቢሆን እንጂ ሁሌም አይላትም
➷በዚህች ውድ ቃል አላህን አያወሳበትም
➷የውመል ቂያማ ሚዛንን የምትደፋ ከመሆኗም ጋር አይደጋግማትም
➷ ይህች ቃል ማለት በጣም ትልቅ የሆነች ንግግር ናት።
♦️ነገር ግን ትኩረት የሚሰጧት
➷በአዕምሯቸው ሚያስታውሷት፦ በምላሳቸው ያለማመዷት፦ የሚደጋግሟት አላህ ኸይርን የወፈቃቸው በጣም ጥቂት የሆኑ አነስተኛ ሰዎች ብቻ ናቸው።
📚 تفسير كلمة التوحيد
👉ስለዚህ لا اله الا الله የምትለዋን ቃል ምላስህ ከማለት አይዘናጋ!!
◂ تفسير كلمة التوحيد
👉ስለዚህ لا اله الا الله የምትለዋን ቃል ምላስህ ከማለት አይዘናጋ!!
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
እውን ቁርኣን የአላህ ቃል አይደለምን?
~
ቁርኣን የአላህ ቃል ለመሆኑ የሚጠራጠር ሙስሊም የለም። ሙስሊሙ ልጆቹን ቁርኣን እንዲቀሩለት ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርገው፣ ያለ ውዱእ የማይነካው፣ ጧት ማታ የሚቀራው፣ የሚማረው፣ የሚያስተምረው፣ ማስረጃ አድርጎ የሚያጣቅሰው፣ የሚተገብረው “ቁርኣን የጌታዬ ንግግር ነው” ከሚል ፅኑ እምነት ተነስቶ ነው።
ግና የፈጣሪ ቃል የማይገታቸው፣ የሰለፎች ኢጅማዕ የማይከብዳቸው ሃፍረተ ቢስ ፍጡሮች ተተኩና “ቁርኣን የአላህ ሳይሆን የሙሐመድ ወይም የጂብሪል ቃል ነው” አሉ። አሻዒራ! አሕ^ባሽ የዚህ ቡድን ተቀፅላ ነው። ይህ እምነታቸው {ይህ የሰው ቃል እንጂ ሌላ አይደለም} ያለውን ሙሽ'ሪኩ ወሊድ ብኑ ሙጊራን ያስታውሰናል። [አልሙደሢር፡ 25] በተውሒድ ስም የነ አቡ ጀህል ዐቂዳ ዳግም ሲሰበክ አስቡት! የአሕ^ባሾቹ ቁንጮ ዐብደላህ አልሀረሪም ቁርኣን የጂብሪል እንጂ በሐቂቃ የአላህ ንግግር አይደለም ከሚሉት ነው። በቅርቡ ፌስቡክ ላይ ተዋሽቶበት እንጂ እሱ እንደዚህ አይልም የሚል ወዶ ገብ አሕባሽ ስላየሁኝ ንግግሩን ላጣቅስ፡-
فهو عبارة عن كلام الله بمعنى أنه يحكي كلام الله، ليس هو بنفسه كلام الله
“እሱ (ቁርኣን) የአላህን ንግግር የሚገልፅ ነው፡፡ ማለትም የአላህን ንግግር የሚተርክ ነው፡፡ እንጂ በራሱ የአላህ ንግግር አይደለም፡፡” [አደሊሉል ቀዊም፡ 66 - 69]
ሰውየው ምን ያክል ሙጅ' ሪም እንደሆነም ተመልከቱ፡፡ አዎ “ሙጅ^ሪም ነው” ሲባል የሚከፋው እንደሚኖር አይጠፋኝም፡፡ ግና ቁርኣንን የአላህ ቃል አይደለም ከማለት በላይ ምን አይነት ብል ^ግና አለ?! የሸሪዐ ግንዛቤ የሌለው ጃሂል እንኳ እንዲህ አይነት ጥፋት አይፈፅምም፡፡
"ኪታቦቹ ላይ ‘አላህ እንዲህ ብሏል’ እያለ ቁርኣንን ማጣቀሱ ‘ቁርኣን የአላህ ንግግር ነው’ ብሎ እንደሚያምን ያሳያል" በማለት ማስረጃ ሊያደርጉለት የሚሞክሩ አሉ፡፡ ሰውየው በማያሻማ ቃል “ቁርኣን በራሱ የአላህ ንግግር አይደለም” እያለ አጉል መንደፋደፍ የትም አያደርስም፡፡ “እሺ ‘አላህ እንዲህ ብሏል’ ሲል ምን ማለቱ ነው?” ከተባለ ይሄው እራሱ ሃሳቡን ግልፅ ያደርግላችኋል፡-
فكلام الله النفسي الذي ليس هو حرفا ولا لغة هو كلام الله الحقيقي؛ أما القرآن المتضمن للألفاظ فهو مخلوق، لكن يمكن إطلاق لفظ القرآن عليه من باب المجاز
“ፊደልም ሆነ ቋንቋ ያልሆነው ነፍሳዊ የሆነው የአላህ ንግግር እርሱ ነው በተጨባጭ የአላህ ንግግር የሚባለው፡፡ ቃላትን የያዘው ቁርኣን ግን እርሱ ፍጡር ነው፡፡ ባይሆን ከዘይቤያዊ አነጋገር አኳያ ቁርኣን (የአላህ ንግግር) በሚል ቃል ሊጠራ ይችላል፡፡” [አነህጁ ሰሊም፡ 26]
የዚህ የዐብደላህ አልሀረሪ ንግግር ጭብጥ፡-
- ትክክለኛው የአላህ ንግግር በፊደልም ሆነ በቋንቋ አይገለፅም፣
- በእጃችን ላይ ያለው ቁርኣን ግን በፊደልም በቋንቋም ስለሚገለፅ ፍጡር እንጂ በሐቂቃ የአላህ ንግግር አይደለም፣
- ሆኖም ግን በራሱ የአላህ ንግግር ባይሆንም፣ የአላህን ንግግር ስለሚተርክ በሐቂቃም ባይሆን በዘይቤያዊ አነጋገር ‘ቁርኣን’ (የአላህ ንግግር) ተብሎ ሊጠራ ይችላል እያለ ነው፡፡
ስለዚህ “አላህ እንዲህ ብሏል” ሲል የሚፈልገው በዚህ አገባብ ማለትም ዘይቤያዊ አነጋገርን በማሰብ እንጂ በሐቂቃ ቁርኣን የአላህ ንግግር ነው ለማለት አይደለም፡፡ ይሄ ከንቱ ዐቂዳ አሕ^ባሽ ከወላጁ አሻዒራ የቀዳው እንደሆነ ይሰመርበት፡፡ [አልኢንሷፍ፡ 147] [ሸርሑ ጀውሀረት ተውሒድ፣ አልበይጁሪ፡ 73] [ሸርሑ ጀውሀረት ተውሒድ፣ አሚር]
ይስተዋል! እነዚህ ሰዎች ለሽፋን ያክል ብቻ ቁርኣን የአላህ ንግግር ነው ይላሉ። “የሐቂቃ ነው ወይ?” ስትሉ ግን ጉዳቸው ይከተላል። በዘይቤያዊ አነጋገር (መጃዝ) የአላህ ቃል ተባለ እንጂ በተጨባጭ ግን የአላህን ንግግር የሚገልፅ፣ የሚተርክ (ዒባራ/ ሒካያ) እንጂ የጂብሪል ንግግር ነው ይላሉ። ለዚህ ብልሹ እምነታቸውም ይህቺን አንቀፅ ይጠቀማሉ፡-
إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ
“እርሱ በርግጥም የክቡር መልእክተኛ ቃል ነው።”
ይህ መልእክት ቁርኣን ውስጥ ሁለት ቦታ ይገኛል፡፡ [አተክዊር፡ 19] [አልሐቃ፡ 40] በሱረቱ ተክዊር ላይ የተገለፀው “መልእክተኛ” ጂብሪል ሲሆን በሱረቱል ሐቃ ላይ ደግሞ ሙሐመድ ﷺ ናቸው። ይህም አንዱን መዞ ሌላኛውን በመተው “የጂብሪል ነው” “የለም የሙሐመድ ነው” የሚሉ ሞገደኞችን ቅርቃር ውስጥ የሚከት ነው። ከዚህ ቅርቃር መውጫው ለቁርኣኑ ሙሉ በሙሉ እንጅ መስጠት ብቻ ነው። ጂብሪልም ሆነ ሙሐመድ ﷺ መልእክተኞች እንጂ ሌላ አይደሉም። የመልእክተኛ የስራ ድርሻ ደግሞ ማድረስ ነው።
{وَمَا عَلَى الرَّسُولِ إِلَّا الْبَلاغُ الْمُبِينُ}
“በመልእክተኛውም ላይ ግልፅ ማድረስ እንጂ ሌላ የለበትም።” [አኑር፡ 54]
ቁርኣኑ ተጠብቆ እንደደረሰ ለማመላከት የሸይጧን ሳይሆን የመልአክ፣ የጠንቋይና የገጣሚ ሳይሆን የመልእክተኛ ቃል እንደሆነ ተገለፀ። ከአስተላላፊነታቸው አንፃር ብቻ ሲታይ አንድ ቦታ የጂብሪል፤ ሌላ ቦታ የሙሐመድ ﷺ ንግግር ተብሏል። እንጂ ጂብሪል ተቀባይ እንደሆነ እንዲህ ፍንትው ብሎ ተቀምጧል’ኮ፡-
(قُلۡ نَزَّلَهُۥ رُوحُ ٱلۡقُدُسِ مِن رَّبِّكَ بِٱلۡحَقِّ)
{‘ቅዱሱ መንፈስ በእውነት #ከጌታህ አወረደው’ በላቸው።} [አነሕል፡ 102]
ይሄው የጂብሪል የራሱ ንግግር ሳይሆን ከአላህ ተቀብሎ ያወረደው እንደሆነ በግልፅ እየተነገረን ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ልብ የሚያንሸራትት ሞገ^ደኛ ቢኖር አላህ ቅናቻን እንዲያድለው ከመማፀን ውጭ ምን እእናደርገዋለን? በተጨማሪም አላህ እንዲህ ብሏል፡-
وَإِنَّهُ لَتَنْزِيلُ رَبِّ الْعَالَمِينَ (192) نَزَلَ بِهِ الرُّوحُ الْأَمِينُ (193) عَلَى قَلْبِكَ لِتَكُونَ مِنَ الْمُنْذِرِينَ (194)
{እርሱም በእርግጥ #ከአለማት_ጌታ_የተወረደ ነው። ታማኙ መንፈስ አወረደው። ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትሆን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረድነው)፡፡} [አሹዐራእ፡ 192-193]
ስለዚህ ጂብሪል ከራሱ ሳይሆን ከጌታ ተቀብሎ ነው ይዞት የወረደው። እንጂ ቁርኣኑ የአላህ ንግግር ለመሆኑማ እንዲህ ተነግሮናል’ኮ፡-
(وَإِنۡ أَحَدࣱ مِّنَ ٱلۡمُشۡرِكِینَ ٱسۡتَجَارَكَ فَأَجِرۡهُ حَتَّىٰ یَسۡمَعَ كَلَـٰمَ ٱللَّه)
{ከአጋሪዎቹም አንዱ ጥገኝነትን ከጠየቀህ #የአላህን_ንግግር ይሰማ ዘንድ አስጠጋው።} [ተውባህ፡ 6]
ነብዩም ﷺ በዐረፋ ሐጅ ላይ ለታደመው ህዝብ እንዲህ ይሉ ነበር፡-
أَلاَ رَجُلٌ يَحْمِلُنِى إِلَى قَوْمِهِ فَإِنَّ قُرَيْشًا قَدْ مَنَعُونِى أَنْ أُبَلِّغَ كَلاَمَ رَبِّى
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
✅♻️ምንም አይነት ሙሲባ ቢደርስብህ የውዱ ነብይህን ሞት አስታውስ
👈قال رسول الله صلى الله عليه وسلم፡
《 إذا أصيب أحدكم بمصيبة فليذكر مصيبته بي فإنها أعظم المصائب》
📚 الصحيحة للألباني (١١٠٦)
♻️📌 የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ብለዋል።
《ከናንተ መሀከል አንዳችሁ ሙሲባ ካጋጠመው እኔ በማጣቱ የደረሰበትን ሙሲባ ያስታውስ። ምክንያቱም እኔን ማጣታችሁ ከሙሲባዎች ሁሉ ትልቁ ነውና።》
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
አቢ የህያ ሱሀይብ ኢብኑ ሲናን (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፡- አንሷር የሆኑ ሰዎች የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብሏል ‹‹የሙዕሚን ጉዳይ እጅግ የሚደንቅ ነው፡፡ ሁለ ነገሩ ኸይር ነው፡፡ ይህ የሙዕሚን (ዕጣ ፈንታ) እንጂ ለማንም (የተሰጠ) አይደለም፡፡ አስደሳች ነገር ከገጠመው ለአላህ ምስጋና ያደርሳል፤ መልካም ይሆንለታል፡፡ ጉዳት ካገኘውም (አስከፊ ነገር ከገጠመውም) ትዕግስት (ሶብር) ያደርጋል፤ ይህም ለርሱ መልካም ይሆንለታል፡፡››
ሐዲሱን ሙስሊም ዘግበውታል
‹‹ የአንድ ሙስሊም ህይወት ውስጥ ክፉም ሆነ በጎ መልካም ነው፡፡ በሁለቱም ከአላህ ዘንድ ምንዳ ያገኝበታል፡፡
‹‹ መልካም ነገር ሲያጋጥም መመስገን እንዲሁም ክፉ ነገር ሲገጥም በሶብር ማሳለፍ፡፡
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
❥ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
أَبِي هُرَيْرَةَ ، قَالَ : سُئِلَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : مَا أَكْثَرُ مَا يُدْخِلُ النَّاسَ الْجَنَّةَ ؟ قَالَ : " تَقْوَى اللَّهِ وَحُسْنُ الْخُلُقِ
ረሱል ﷺ ከሰዎች በብዛት ጀነት ሚገቡት የትኞቹ ናቸው ተብለው ሲጠየቁ፦
የሰው ልጅን በብዛት ጀነት የሚያስገባው
☞አላህን መፍራትና
☞ሰናይ ስነ ምግባር ነው፡፡ ብለዋል።
✍አል ቲርሚዚ 2004 📚ኢብኒ ማጃህ 4246📚
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
☞ሉቅማን (አልሃኪም) ለልጁ እነዲህ ብሎት ነበር ፦
"ልጄ ሆይ፡ አሏህንተጠንቀቅ(ፍራ) ፣ ልብህ ብልሹ ሆኖ ሳለ፣ ሰዎች እንዲያከብሩክ ስትል እርሱን (አላህን) እንደምትፈራ አታሳያቸው(አታስመስል)" »
[አብዱላህ ኢብኑ አልሙባረክ ፡
📚 አዝዙህድ ወርረቃኢቅ ቁ63
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
📌وَلَئِنْ أَذَقْنَا ٱلْإِنسَٰنَ مِنَّا رَحْمَةً ثُمَّ نَزَعْنَٰهَا مِنْهُ إِنَّهُۥ لَيَـُٔوسٌ كَفُورٌ
♻️ሰውንም ከእኛ ችሮታን ብናቀምሰው ከዚያም ከርሱ ብንወስዳት እርሱ በእርግጥ ተስፋ ቆራጭ ክህደተ ብርቱ ነው፡፡
📌وَلَئِنْ أَذَقْنَٰهُ نَعْمَآءَ بَعْدَ ضَرَّآءَ مَسَّتْهُ لَيَقُولَنَّ ذَهَبَ ٱلسَّيِّـَٔاتُ عَنِّىٓ إِنَّهُۥ لَفَرِحٌ فَخُورٌ
♻️ካገኘችውም ችግር በኋላ ጸጋዎችን ብናቀምሰው «ችግሮች ከኔ ላይ በእርግጥ ተወገዱ» ይላል (አያመሰግንም)፡፡ እርሱ ተደሳች ጉረኛ ነውና ።
📌إِلَّا ٱلَّذِينَ صَبَرُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ أُو۟لَٰٓئِكَ لَهُم مَّغْفِرَةٌ وَأَجْرٌ كَبِيرٌ
♻️ግን እነዚያ የታገሱ መልካም ሥራዎችንም የሠሩ እነዚያ ለእነሱ ምሕረትና ታላቅ ምንዳ አልላቸው፡፡
📚سورة الهود (11 ـ 9)
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
አቡ ሙሳ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብሏል ‹‹እያንዳንዱ ሙስሊም ምፅዋት የመለገስ ግዴታ አለበት›› አሉ፡፡ ‹የሚመፀውተው ካላገኘስ?› አለ (አንድ ጠያቂ)፡፡ ‹በእጁ ሰርቶ ራሱን ይጥቀም፣ ይመፅውትም› አሉ፡፡ ‹ካልቻለስ?› አላቸው፡፡ ‹የተቸገረን ባለጉዳይ ይርዳ› ሲሉ መለሱ፡፡ ‹ካልቻለስ?› አላቸው፡፡ ‹በፅድቅ ወይም በመልካም ይዘዝ› አሉ፡፡ ‹ይህን ካልፈፀመስ?› ሲል ጠየቃቸው፡፡ ‹ከተንኮል ይቆጠብ፡፡ ይህን ምፅዋት ነው፡፡› የሚል ምላሽ ሰጡ፡፡
ሐዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
‹‹ አንድ ሙስሊም ሰርቶ ራሱን መርዳት እንዳለበት ከቻለ መመፅወት፡፡
‹‹ መልካም ተግባር ሁሉ ሶደቃ መሆኑን የሚያሳይ ሀዲስ ነው፡፡
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
አቡ ማሊክ ሀሪስ ኢብኑ ዓሊም አል አሽዐሪይ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብሏል ‹‹ንፅህና የእምነት (ኢማን) ግማሽ ነው፡፡ ‹አልሐምዱሊላህ› ያለችው ቃል ሚዛን ትሞላለች፤ ‹ሱብሀነላህ ወልሐምዱሊላህ› የሚሉት ቃላት በምድርና በሰማይ መካከል (ያለውን ቦታ) ይሞላሉ ወይም ትሞላለች፡፡
ሶላት ብርሃን ነው፡፡ ምፅዋት (ሶደቃ) የኢማን ዋቢ ነው፡፡ ትግስት (ሶብር) ብርሃን ነው፡፡ ቁርዓን ላንተ ወይም በአንተ ላይ አስረጅና መስካሪ ነው፡፡ ሁሉም ሰው ነፍሱን ነፃ ያወጣ ወይም ለጥፋት የዳረገ ሆኖ ዕለቱን ይጀምራል፡፡
ሐዲሱን ሙስሊም ዘግበውታል
‹‹ ውዱዕ የሶላት መስፈርት፤ የሰላትን ጠቀሜታ፤ ሶደቃን ማብዛት የሙዕሚን እውነተኝነት፣ ታማኝነትና ቅንነትን ያመለክታል፡፡
‹‹ የሶብር ትሩፋት፤ ቁርዓን ለሁሉም ሸሪዓዊ ብይኖች መነሻ መሰረት መሆኑን፡፡
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
#የአሹራ_ፆም!
አሹራእ ተብሎ የሚጠራው ይህ የሙሃረም አስረኛ ቀን ነው፡፡ በዚህ ቀን አላህ ነብዩላህ ሙሳንና ተከታዮቻቸውን ከአምባገነኑ ከፊርዐውን አደጋ ባህሩን በማሻገር ያዳነበት ቀን በመሆኑ፡ እኛም ሙስሊሞች ከአይሁዶች ይልቅ ለሙሳ (ዐለይሂ ሰላም) ወንድምነት የተገባን በመሆናችን ልንጾመው ይገባል በማለት ነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ቀኑን በፆም እንድናሳልፈው አሳውቀውናል፡፡
በተለይ ይህን 10ኛውን ቀን (ዐሹራእ) መጾም ያለውን ጥቅም ተጠይቀው ሲመልሱ፡- ‹‹አላህ ያለፈውን አንድ ዓመት (ትናንሽ) ኃጢአት እንዲምር ተስፋ አደርጋለሁ›› ብለዋል(ሙስሊም ዘግበውታል )፡፡
ከአይሁዶች ጋርም ለመለየት ሲባል ቀደም ተብሎ የሙሃረምን ዘጠነኛውን ቀን ጨምሮ መፆም አልያ ደግሞ የሙሃረም 11ኛ ቀኑን ጨምሮ መፆም ሱና ነው፡፡ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል “አሏህ ካለ የሚመጣው ዓመት ላይ 9ኛውንም ቀን እንጾማለን “ ብለዋል ከዚህም በመነሳት ዑለማዎች ዘጠነኛውንም ቀን መጾም ሱና ነው ብለዋል።
በመሆኑም #ሀሙስ ሙሃረም 9 እና የሙሃረም 10 እለተ #አርብ የአሹራ ፆም ቤተሰቦቻችን፣ወዳጆቻችን እና ሙስሊም ወንድሞቻችን ሁሉ ቀኑን በመፆም በኢባዳ እንዲያሳልፉት እናስታውሳቸው::
ለሃገራችን ሰላም እና መረጋጋትም ዱዓ ማድረግ አንዘንጋ
መልካም ስራ እንዲሰራ ማስታወስ የሰሪውን ያህል ሙሉ ምንዳ ከአላህ (ሱ.ወ) ያስገኝልናል፡፡
አላህ ቀኑን ፆመው የአንድ አመት ወንጀላቸው ከሚማርላቸው ያድርገን
አሚን
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
«ዱኒያ ላይ ከሚገኙት ነገሮች ሁሉ እኔ ዘንድ ተወዳጅ የሆኑት (ሴትና ሽቶ) ናቸው፣ የአይኔ ማረፊያ ደግሞ በሠላት ላይ ተደረገች»።
ረሱል (ሠለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
አዲይ ኢብኑ ሀቲም (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብሏል ‹‹ከናንተ ውስጥ ጌታው ያለ አስተርጓሚ የማያናግረው ማንም የለም፡፡ (በዚያ ወቅት ሰውዬው) ወደቀኙ ሲመለከት ካስቀደመው (ስራ) ውጭ ምንም ነገር አይታየውም፡፡ ወደ ግራው ሲመለከት ካስቀደመው (ስራው) ውጭ ምንም ነገር አይታየውም፡፡ ወደ ፊት ሲመለከትም ከፊት ለለፊቱ ከእሳት ውጭ ምንም ነገር አያይም፡፡ በክፋይ ተምርም ቢሆን ከእሳት ተጠበቁ፡፡››
ሐዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
‹‹ ከእሳት ለመጠበቁ አንዱ ተግባር መልካም ወይም በጎ ማድረግ ነው፡፡ የተምር ክፋይም ብትሆን ሶደቃ ማድረግ ቢሆን እንኳ ማድረግ ነው፡፡
‹‹ አላህ በመጭው አለም ለባሮቹ ይቀርባል፡፡ በባሪያውና በእሱ መካከል ምንም አይነት ማዕከል ወይም አስተርጓሚ ሳይኖር፡፡
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
አቡ ሁሬይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብሏል ‹‹አላህ ውጫዊ ቅርፅና ውበታችሁን አይመለከትም፡፡ ልቦናችሁን ነው የሚመለከተው››፡፡
ሐዲሱን ሙስሊም ዘግበውታል፡፡
‹‹ ተግባር ከኒያ ጋር መቆራኘት እንዳለበት፡፡
‹‹ ልቦናችን ማፅዳት ከሌሎች ተግባራት ይልቅ ትኩረት የሚቸረው መሆኑን፡፡
@Adnan567mh
2 077
አቢ ዋኢል ሸቂቅ ኢብኑ ሰለማህ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፡- ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) ዘወትር ሀሙስ ሀሙስ ብቻ ይመክሩን ነበር፡፡ አንድ ሰው፡ ‹‹አቡ አብዱረህማ ሆይ! በየቀኑ ቢመክሩን እወዳለሁ›› አላቸው፡፡ ‹‹ይህን እንዳላደርግ የከለከለኝ እንዳትሰላቹ መስጋቴ ብቻ ነው፡፡ የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዳንሰለች በመስጋት አለፍ አለፍ እያሉ ያስተምሩን እንደነበረው እኔም እንደርሳቸው አለፍ አለፍ እያልኩ እናንተን ማስተማርን መረጥኩ›› አሉ፡፡
ሐዲን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
‹‹ የሰው ልጅ በባህሪው ንግግር ሆነ ሌላ ነገር ሲበዛበት ይሰለቻል ስለዚህ ንግግርን መመጠን ተገቢ ነው፡፡
‹‹ ለትምህርትና ምክር ሰዎች ንቁ የሚሆኑባቸውን ጊዜያት መመረጥ አስፈላጊ ነው፡፡
☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
2 077
አቡ ሁሬይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት አንድ ሰው የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ቀረበና፡- ‹‹የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሆይ! ይበልጥ ሎጎዳኘው የሚገባኝ ሰው ማንነው?›› አላቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹እናትህ›› አሉት፤ በድጋሚ ‹‹ከዚያስ ቀጥሎ ማንነው?›› አላቸው፤ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹እናትህ›› አሉት፡፡ ሰውዬው ‹‹ከዚያስ ቀጥሎ?›› አላቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹እናትህ›› አሉት፡፡ (ለአራተኛ ጊዜ) ‹‹ከዚያስ ቀጥሎ?›› አላቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹አባትህ› አሉት፡፡
ሐዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
በሌላ ዘገባ ደግሞ ‹‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ይበልጥ ልጎዳኘው የሚገባኝ ሰው ማንነው?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹እናትህ ከዚያም እናትህን ከዚያም እናትህን ከዚያም የቅርብ ዘመድህን ከዚያም የቅርብ ዘመድህን›› አሉት፡፡
‹‹ እናት ከልጁ መወለድ እስከ ሞቱ ድረስ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለችና የምትከፍልም በመሆኗ ከፍተኛ አትኩሮት ለመስጠት ነው፡፡
‹‹ የእናት ደረጃ ከአባት የበለጠ ከፍተኛ ስፍራ እንዳለው ማሳያ ነው☞ አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ ነገር ግን ገና እታች ክፍል ያለሁ
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው
«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።
ለአሥተያየት @Adnanmoh_bot
አላህ ይ ቀበለን✔
JOIN 👇
@Adnan567mh
🌐💚💛❤️
