en
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Open in Telegram

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Channel ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) is an active participant. Currently, the community unites 11 983 subscribers, ranking 17 269 in the Education category and 2 838 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 983 subscribers.

According to the latest data from 04 March, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -107 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 March, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

11 983
Subscribers
No data24 hours
-337 days
-10730 days
Posts Archive
3 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች የኮሮና ቫይረስ አንደተገኘባቸው ስራ አስፈፃሚውን አቶ ተወልደን ጠቅሶ #CGTN ዘግቧል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#DrLiaTadesse #በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ ሁኔታ፦ 🔸አጠቃላይ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ - 2271 🔸በ24 ሰዓት የተከናወነ ላብራቶሪ ምርመራ - 264 🔸ዛሬ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ - 8 🔸በቫይረሱ ተይዘው በለይቶ ህክምና ያሉ - 44 🔸 በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ - 1 🔸 ያገገሙ - 4 🔸በበሽታው ህይወታቸው ያለፈ - 2 🔸 ወደሀገራቸው የተመለሱ - 2 🔸እስካሁን በበሽታው የተያዙ - 52 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#Ethiopia : በኢትዮጵያ አንድ የ9 ወር ህጻንን ጨምሮ ተጨማሪ ስምንት ሰዎች በኮሮናቫይረስ ተያዙ በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 264 ሰዎች ውስጥ 8 ሰዎች በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ። በቫይረሱ ከተያዙት ሰዎች መካከል አንድ የዘጠኝ ወር ህጻን የተያዘ ሲሆን እናቱም ቫይረሱ ተገኝቶባታል። የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በ24 ሰዓታት ውስጥ ምርመራ ከተደረገላቸው ሰዎች መካካል አንዱ ኤርትራዊ ሲሆን ቀሪዎቹ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው። ይህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 52 አድርሶታል ነው ያሉት። በበሽታው መያዛቸው ከተረጋገጠ ስምንቱ ሰዎች መካከል አምስቱ ከዱባይ የመጡና በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል ሲደረግላቸው የነበሩ ናቸው። ከእነዚህም ውስጥ አንድ የዘጠኝ ወር ህጻንና ወላጅ እናቱ ይገኙበታል። አንድ የ25 ዓመት ሴት ኢትዮጵያዊት ከታይላንድ መጥታ በለይቶ ማቆያ ክትትል ስታደርግ የነበረች ሲሆን፤ አንድ የ19 ዓመት ኢትዮጵያዊ የውጭ አገር ጉዞ ታሪክ የሌለው ሲሆን የንክኪ ሁኔታውም በመጣራት ላይ ይገኛል ብለዋል። ወጣቱ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ እንዳለው ተጠርጥሮ በለይቶ ማቆያ የነበረ ነው። ሌላኛዋ የ30 ዓመት ሴት ኤርትራዊት ስትሆን ከእንግሊዝ ለንደን መጥታ በአዲስ አበባ በለይቶ ማቆያ ክትትል እያደረገች የምትገኝ ናት። በአዲስ አበባ እና በሌሎች የክልል ከተሞች የኮሮናቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ አቅም እየጨመረ መጣቱንም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መካከል አንድ ግለሰብ በጽኑ ህሙማን ማቆያ ይገኛሉ። አራቱ ያገገሙ ሲሆን፤ ሁለቱ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል። ሌላ ሁለት ግለሰቦች ደግሞ ወደ ሀገራቸው ተሸኝተዋል። Via #ENE ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#የኮቲዲቯር_መከላከያ_ሚኒስትር በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል፡፡ የመከላከያ ሚኒስትር ሃማድ ባካያኮ በተደረገላቸው ምርመራ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን ቢቢሲ ዘግቧል። ሚኒስትሩ እርግጥ ምንም አይነት ምልክት አላሳዩም ነበረ ተብሏል፡፡ይሆን እንጂ ድንገት ባደረጉት ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው በመረጋገጡ ወደ ለይቶ ማቆያ መግባታቸው ተነግሯል፡፡ መከላከያ ሚኒስትሩ ዜጎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉም መልዕክታቸውን በትዊተር ገፃቸው አስተላልፈዋል። በኮቲዲቯር በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 323 ሲሆን፤ ሶስት ሰዎችም ህይወታቸው አልፏል፡፡ የሀገሪቱ መንግሥት በዋና ከተማዋ አቢጃን የእንቅስቃሴ ገደብን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ የሰአት እላፊ አውጇል። ባሳለፍነው ቅዳሜ ዕለትም የጤና ባለሙያዎች ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የፊት ጭምብል እንዲያደርጉም ትእዛዝ አስተላልፈዋል። Via #ethiofm ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

ለኮሮና በሽታ ታማሚዎች የሚሰጠው ህክምና ምንድነው ? ============================= ①. #የህክምናው_ዓላማ ---------------- የኮሮና ቫይረስ በህዋሳት ላይ የሚያደርሰውን ቀጥተኛ ጉዳት ለማስቆም የሚያስችል ፍቱን መድሃኒት ባለመኖሩ የህክምና ድጋፉ ዋና አላማ ለተፈጠረው የጤና ችግር የሕክምና ድጋፍ በማድረግ የጎንዮሽ ጉዳትንና የህመም ስቃይን በመቀነስ ቶሎ እንዲያገግሙ ማገዝ ነው:: ②. #የህክምና_ድጋፍ_አይነቶች -------------------- እንደ ህመሙ ክብደትና ተጓዳኝ ችግሮች የሚለያይ ቢሆንም በህክምና መስጫ ተቋማት የሚደረጉ ዋና ዋና የህክምና ድጋፍ አይነቶች የሚከተሉት ናቸው፡- 1. በቂ እረፍት እንዲያደርጉ ማስቻል፣ 2. ህመምና ትኩሳት የሚቀንሱ መድሃኒቶች መስጠት፣ 3. ለህክምና አገልግሎት የሚውል ኦክስጅን (Medical Oxygen) መስጠት፣ 4. ሰውነት በቂ ፈሳሽ፣ ምግብና ንጥረ ነገር እንዲኖረው ማድረግ፣ 5. በፅኑ ለታመሙና በራሳቸው መተንፈስ ለማይችሉ በመሳሪያ (Mechanical Ventilator) ታግዘው እንዲተነፍሱ ማስቻል፣ 6. በባክቴሪያዎች አማክኝነት የተከሰተ ተደራቢ የሳንባ ምች፣ የደም መመርቀዝ ላለባቸው ተገቢውን ፀረ-ባክቴሪያ መድሃኒት/መድሃኒቶች (antibiotics) መስጠት፣ 7. በፅኑ ለታመሙና በከፍተኛ ደረጃ ስራቸውን መስራት ለማይችሉ የዉስጥ ክፍለ አካላት (ለምሳሌ ኩላሊት፣ ወዘተ) ችግር፣ ተገቢውን የህክምና ድጋፍ ማድረግ፣ 8. ሌላ ተጨማሪ የጤና ችግር (የደም ግፊት፣ የስኳር ህመም፣ አስም፣ ወዘተ) ካለ ተገቢውን ህክምና ማድረግ፣ 9. በሐኪሞች ምክር ሙከራ/ጥናት ላይ ያሉ ለሌላ በሽታ ተብለው የተሰሩ ፀረ-ቫይረስነት ባህሪ ያላቸውን ተስፋ ሰጪ መድሃኒቶች (ለምሳሌ ክሎሮኩዊን (Chloroquine/ hydroxychloroquine) ከባድ ህመም ላለባቸው ታማሚዎች መስጠት:: ③. #ማጠቃለያ ----------- በኮሮና በሽታ የተያዘ ሰው ተገቢውን የህክምና ድጋፍና እንክብካቤ ለማግኘት ለዚህ አላማ ተብለው ወደ ተዘጋጁ የህክምና ተቋማት መሄድ ይኖርበታል:: የሚደረገው የህክምና ድጋፍና እንክብካቤም በሽታው የሚያመጣውን ጉዳት ለመቀነስና ታማማዊ ቶሎ እንዲያገግም በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ አለው:: ተገቢውን የህክምና ድጋፍ አለማግኘት ከፍተኛ የህመም ስቃይ ከማስከተሉም ባሻገር ሳምባና ኩላሊት ስራቸውን እንዲያቆሙ በማድረግ ለሞት ሊዳርግ ይችላል:: የህክምና ድጋፉ ታማሚዎች ከኮሮና በሽታ እንዲድኑ ከማገዙም በላይ ከበድ ያለ ህመም የገጠማቸው ታማሚዎች ላይ ሊከሰት የሚችለውን ዘላቂ የጤና ችግር (ለምሳሌ በሳንባ ጠባሳ ምክንያት የሚመጣ ዘላቂ የአተነፋፈስ ችግር፣ የኩላሊት ድክመት፣ ወዘተ) ለመቀነስ ጉልህ ድርሻ አለው። ❖ ስለሆነም የኮሮና በሽታ ምልክቶች የታየበት ማንኛውም ሰው እራሱን/እራሷን በቤት ዉስጥ ለይቶ ከማቆየት ባሻገር ወደ ጤና ተቋም በመሄድ በጤና ባለሙያዎች በሚሰጠው የውሳኔ ሃሳብ መሰረት ተገቢውን የኮሮና ምርመራ በማድረግ ለዚህ አላማ ተብለው በተዘጋጁ የለይቶ ማከሚያ ክፍሎች ገብቶ ሕክምና ማድረግ የግድ ይላል:: ኮሮናን ለመከላከልና ስርጭቱን ለመቆጣጠርም አንዱና ወሳኙ መንገድ ነውና:: ④. #ትኩረት ! -------- ·► እጃችንን በሳሙና ደጋግመን እንታጠብ ·► አካላዊ ርቀትን እንጠብቅ ·► በተቻለ መጠን ከቤት አንዉጣ ·► ሰባዊነትን በማስቀደም እንተሳሰብ፤ እንረዳዳ ·► ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን እናጠናክር ·► በመንግስትና በሃይማኖት ተቋማት የሚተላለፉ ምክሮችንና ዉሳኔዎችን እንተግብር ·► ጤና ተቋማትን እንደግፍ ✅ ፈጣሪ በምህረቱ እንዲጎበኘን እንፀልይ ==================== በፕሮፌሰር የሺጌታ ገላው ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

የዕለቱ 29/7/2012 ኮቭድ 19 ስርጭት ሰዓት ከጧቱ 2.30 ✅✅ በኢትዮጵያ • ባለፉት 24 ሰዓታት አዲስ የተያዙ =1 • ሞት=2 • ሙሉ ለሙሉ ያገገሙ=4 • ወደ ሀገራቸው የተወሰዱ=2 • በፅኑ የታመሙ=1 • አሁን ለይቶ ማከሚያ ያሉ=38 • አጠቃላይ የተጠቁ ሰዎች =44 ✅✅ የዓለም አቀፍ ገፅታ ፦ • በ 24 ሰዓታት በበሽታው የመሞቱት ሰዎች =5,229 • አዲስ በበሽታው የተያዙ ሰዎች =73,142 • አጠቃላይ እስካሁን በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች=1,346,004 • እስካሁን በበሽታው የሞቱት =74,654 • እስካሁን እያገገሙ =286,234 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

ጠ/ሚ ቦሪስ ጆንሰን ወደፅኑ ህሙማን ክፍል ገቡ! #የብሪታንያው ጠቅላይ ሚንስትር ቦሪስ ጆንሰን ወደ ሆስፒታል ከገቡ በኃላ የህመማቸው ሁኔታ ስለጠነከረባቸው ወደ ጽኑ ህሙማን ክፍል እንደገቡ ቃል አቀባ
ጠ/ሚ ቦሪስ ጆንሰን ወደፅኑ ህሙማን ክፍል ገቡ! #የብሪታንያው ጠቅላይ ሚንስትር ቦሪስ ጆንሰን ወደ ሆስፒታል ከገቡ በኃላ የህመማቸው ሁኔታ ስለጠነከረባቸው ወደ ጽኑ ህሙማን ክፍል እንደገቡ ቃል አቀባያቸው ተናግረዋል። ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1, BBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#የኢትዮጵያ_የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች ወቅታዊውን የኮሮና ወረርሽኝን በማስመልከት ለመላው ምዕመናን ለአንድ ወር የሚቆይ #ሀገራዊ_የጸሎት_ጥሪ ማስተላለፋቸው ይታወሳል፡፡ ዛሬ ከ3
#የኢትዮጵያ_የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች ወቅታዊውን የኮሮና ወረርሽኝን በማስመልከት ለመላው ምዕመናን ለአንድ ወር የሚቆይ #ሀገራዊ_የጸሎት_ጥሪ ማስተላለፋቸው ይታወሳል፡፡ ዛሬ ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ ለሃይማኖት ተቋማቱ በወጣው ድልድል መሰረት በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡ በዚህም፡- 🔸 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ....በEBC 🔸 የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት...FANA 🔸የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን.... Addis Tv 🔸 የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን.....Walta ሁሉም በያለበት እንደየእምነቱ ፈጣሪ ይራራልን ዘንድ ጸሎቱን ያቅርብ! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

የአለም ጤና ድርጅት (WHO) ዳይሬክተር ዶ/ር #ቴድሮስ_አድሃኖም ከቀናት በፊት ሁለት ፈረንሳያዊያን ሳይንቲስቶች የኮቪድ-19 ሙከራ በአፍሪካ መደረግ አለበት ባሉት ዙሪያ ጋዜጠኞች ሲጠይቋቸው ሳይንቲ
የአለም ጤና ድርጅት (WHO) ዳይሬክተር ዶ/ር #ቴድሮስ_አድሃኖም ከቀናት በፊት ሁለት ፈረንሳያዊያን ሳይንቲስቶች የኮቪድ-19 ሙከራ በአፍሪካ መደረግ አለበት ባሉት ዙሪያ ጋዜጠኞች ሲጠይቋቸው ሳይንቲስቶቹን "ዘረኛ" በማለት ኮንነዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

ኢትዮጵያ ኮሮናን በመመርመር ከ50 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ካላቸው የአለም ሀገራት ኢትዮጵያ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች። የኮሮና ቫይረስ የምርመራ መጠንን ከህዝብ ብዛት አንፃር እንዲሁም የስርጭቱን አጠቃላይ መረጃ እንደሚያወጣው Worldometer እንደተባለው ድረ ገፅ ከሆነ፤ ኢትዮጵያ የኮሮና ምርመራን በማድረግ ግርጌ ላይ ከሚገኙት ሀገራት መካከል ነች፡፡ የህዝብ ብዛታቸው ከ 50 ሚሊዮን በላይ ከሆኑት ጋር ስትወዳደር ደግሞ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ነው የምትገኘው፡፡ ከ 1 ሚሊዮን ህዝብ 16 ሰው ነው ምርመራውን እያገኘ ያለው፡፡ በኢትዮጵያ ቁጥሩ ያነሰበት ምክንያት ምልክቱ የታየባቸውና በቫይረሱ ተጠቂ ከሆኑ ሰዎች ጋር ንክኪ ያላቸው ሰዎች ብቻ የሚመረመሩ በመሆኑ ሲሆን ትናንት የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በስራ ባህሪያቸው ለቫይረሱ ተጋላጭ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ የሚደረገው ምርመራ በተለይም ቫይረሱ በተገኘባቸው አካባቢዎች ላይ ምርመራው በስፋት እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። የኮሮና ምርመራን ለህዝባቸው በማድረስ ከኢትዮጵያ ቀጥሎ የከፋ አፈፃፀም ያሳዩት ባንግላዴሽና ናይጄርያ ናቸው፡፡ ባንግላዴሽ ከ 1 ሚሊዮኑ 18 ሰው እየተመረመረ ሲሆን ናይጀርያ ደግሞ 19 ነው እያስመረመረች ያለችው፡፡ ደቡብ ኮርያ በብዛት ምርመራውን በማድረግ በአንደኝነት ስትቀመጥ ከአንድ ሚሊዮን ህዝብ ውስጥ 8 ሺህ 9 መቶ 96 ምርመራውን ያገኛል፡፡ ሲንጋፖር ከ 1 ሚሊዮን ህዝብ ውስጥ 6 ሺህ 6 መቶ 66 በማስመርመር ሁለተኛ ፤ ማሌዢያ ደግሞ ከ 1 ሚሊዮን ህዝብ ውስጥ 1 ሺህ 6 መቶ 5 በማስመርመር ሶስተኛ ሆነዋል፡፡ በእንግሊዝ መንግስት በቀን ከ 100 ሺህ ሰው በላይ ማስመርመር እንደማይችል ለህዝቡ በመግለፁ ከፍተኛ ቁጣን አስተናግዷል፡፡ ምንጭ-ኢትዮ FM ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በኮት ዲቮር የተቃውሞ ሰልፈኞች የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ማእከል አቃጠሉ! #Coronavirus በኮት ዲቮር አቢጃን ከተማ አቅራቢያ በግንባታ ላይ የነበረ የኮሮና ቫይረስ ማእከል በተቃውሞ ሰልፈኞች መቃ
በኮት ዲቮር የተቃውሞ ሰልፈኞች የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ማእከል አቃጠሉ! #Coronavirus በኮት ዲቮር አቢጃን ከተማ አቅራቢያ በግንባታ ላይ የነበረ የኮሮና ቫይረስ ማእከል በተቃውሞ ሰልፈኞች መቃጠሉን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል፡፡ ማእከሉን ከማቃጠላቸው በፊት ሰልፈኞቹ ጎማ ሲያቃጥሉ ነበር፡፡ ከአካባቢው የተውጣጡት ሰልፈኞቹ ማእከሉን በሚያቃጥሉበት ወቅት “ማእከሉን አንፈልገውም፤ ቫይረሱን አምጥታችሁብን ልትገሉን ነው” የሚል የተቃውሞ ድምጽ እያሰሙ እንደነበር ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ተቃውሟቸውን ትናንት የጀመሩት ሰልፈኞቹ በዛሬው እለትም ከፖሊስ ጋር ሲጋጩ መዋላቸውም በዘገባው ተካቷል፡፡ በተፈጠረው ግጭት የተጎዳ የለም ተብሏል፡፡ ሀገሪቱ እስካሁን ከ260 በላይ የቫይረሱ ታማሚዎች የተገኙባት ሲሆን ሶስት ሰዎች ሞተዋል፡፡ ማእከሉ በአቢጃን ከሚገነቡ መሰል ማእከላት አንዱ ነው፡፡ ምንጭ፡- አል ዓይን ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#ፕሬዚዳንት ትራምፕ አሜሪካ ኮሮና ቫይረስ ለመቆጣጠር ተስፋ አላት ሲሉ ተናገሩ፡፡ በአሜሪካዋ ኒውዮርክ በኮሮና ቫይረስ የማቾች ቁጥር ለመጀመሪያ ጊዜ ሰኞ እለት መቀነሱ ተከትሎ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወረ
#ፕሬዚዳንት ትራምፕ አሜሪካ ኮሮና ቫይረስ ለመቆጣጠር ተስፋ አላት ሲሉ ተናገሩ፡፡ በአሜሪካዋ ኒውዮርክ በኮሮና ቫይረስ የማቾች ቁጥር ለመጀመሪያ ጊዜ ሰኞ እለት መቀነሱ ተከትሎ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የተስፋ ጭላንጭል አለን ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጨምረው እንደገለፁት ወረርሽኙን ለመዋጋት መንግስታቸው አስፈላጊውን የህክምና ግብአቶች ለሁሉም ግዛቶች ያሰራጫል ብለዋል፡፡ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በኢትዮጵያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 44 ደረሱ! ✒️በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 164 ሰዎች ውስጥ አንድ ግለሰብ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ። ✒️የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳስታወቁት፤ በ24 ሰዓታት ውስጥ ምርመራ ከተደረገላቸው ሰዎች መካካል 26ቱ በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ ናቸው። ✒️ቀሪዎቹ ደግሞ ለቫይረሱ ተጋላጭ ከሆኑ ማህበረሰቦች ናቸው ተብለው የተመረመሩ መሆናቸውን ነው የገለጹት። ✒️ዛሬ በቫይረሱ የተያዙት ግለሰብ የ65 ዓመት ሴት ኢትዮጵያዊት ሲሆኑ የዱከም ከተማ ነዋሪና የውጭ አገር የጉዞ ታሪክ የሌላቸው ናቸው። ✒️ግለሰቧ ተጓዳኝ ለሆነ በሽታ ወደ ህክምና ተቋም ከሄዱ በኋላ የቫይረሱን ምልክት በማሳየታቸው ነው ምርመራ የተደረገላቸው። ✒️በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ግለሰቦች ቁጥር 44 የደረሰ ሲሆን ከእነዚህ መካከል አንድ ግለሰብ በጽኑ ህሙማን ማቆያ ይገኛሉ። ምንጭ፦ ኢዜአ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#በአፍሪካ_የኮሮና_ቫይረስ_ስርጭት_ወቅታዊ_መረጃ ⏰ሰኞ መጋቢት 28-2012 እስከ ጠዋቱ 04:00 ድረስ ✅ሙረጃ ኃይል ነው Share ማድረጋችሁን አትርሱ 🔸እስካሁን በአፍሪካ 8,549 የቫይረሱ ተጠቂዎች ተገኝተዋል 🔸በአፍሪካ 51 ሀገራት ላይ ቫይረሱ ተሰራጭቷል 🔸በአህጉሪቱ የተመዘገበው ጠቅላላ ሞትም 435 ደርሷል 🔸አገግመው ከሆስፒታል የወጡት 816 ደርሰዋል 🔹ደቡብ አፍሪካ በርካታ ኬዝ የተገኘባት ሀገር ነች (1,655) 🔹አልጄሪያ በቫይረሱ በርካታ ሰው የሞተባት ሀገር ነች (152) 🔹32 የአፍሪካ ሃገራት ላይ የሞት ሪፖርት ተደርጓል 🔹3 የአፍሪካ ሃገራት ከአንድ ሺህ በላይ ኬዝ አለባቸው 🔹19 የአፍሪካ ሃገራት ከ100 በላይ ኬዝ አለባቸው 🔹ደቡብ ሱዳን ቫይረሱ የተገኘባት 51ኛ የአፍሪካ ሀገር ሆናለች 🔹እስካሁን 3 የአፍሪካ ሀገር ላይ ቫይረሱ አልገባም 🇪🇹 በሀገራችን ትላንት 5 አዲስ ኬዝ የተገኘ ሲሆን ለሀገራችን የመጀመሪያ የሆነ 2 ሞት ተመዝግቧል። ▪️በሀገራችን የተገኘ ጠቅላላ ኬዝ 43 ደርሷል ▪️በለይቶ የህክምና ክትትል ውስጥ ያሉ (37) ▪️ከቫይረሱ ያገገሙ (4) ▪️ወደ ሀገራቸው የተመለሱ (2) ✅ ጎረቤት ሀገራትን ስንመለከት (ኬኒያ 142 ኬዝና 4 ሞት ፣ ጂቡቲ 59 ኬዝ ፣ ኤርትራ 29 ኬዝ ፣ ሱዳን 12 ኬዝና 2 ሞት እንዲሁም ሶማሊያ 7 ኬዝ አሉባቸው) ─────────────────────────── ✅ በአፍሪካ እስካሁን ቫይረሱ ያልታየባቸው 3 ሀገራት ይገኛሉ 🇰🇲 ኮሞሮስ 🇱🇸 ሌሴቶ 🇸🇹 ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ ─────────────────────────── 🔴 በአፍሪካ አጠቃላይ የኮሮና ቫይረስ ኬዝ ይህን ይመስላል 🇿🇦 1,655 ደ. አፍሪካ 🇩🇿 1,320 አልጄሪያ 🇪🇬 1,173 ግብፅ 🇲🇦 990 ሞሮኮ 🇨🇲 650 ካሜሮን 🇹🇳 574 ቱኒዝያ 🇧🇫 345 ቡርኪናፋሶ 🇨🇮 261 ኮትዲቯር 🇳🇬 232 ናይጄሪያ 🇲🇺 227 ሞሪሺየስ 🇸🇳 222 ሴኔጋል 🇬🇭 214 ጋና 🇳🇪 184 ኒጀር 🇨🇩 148 ዲ.ሪ. ኮንጎ 🇰🇪 142 ኬንያ 🇬🇳 121 ጊኒ 🇷🇼 104 ሩዋንዳ 🇲🇬 72 ማዳጋስካር 🇩🇯 59 ጅቡቲ 🇺🇬 52 ኡጋንዳ 🇨🇬 45 ሪ.ኮንጎ 🇲🇱 45 ማሊ 🇹🇬 44 ቶጎ 🇪🇹 43 ኢትዮጵያ 🇿🇲 39 ዛምቢያ 🇪🇷 29 ኤርትራ 🇧🇯 22 ቤኒን 🇹🇿 22 ታንዛኒያ 🇬🇼 18 ጊኒ ቢሳው 🇱🇾 17 ሊቢያ 🇬🇶 16 ኢኳቶሪያል ጊኒ 🇳🇦 16 ናሚቢያ 🇬🇦 16 ጋቦን 🇦🇴 14 አንጎላ 🇱🇷 13 ላይቤሪያ 🇸🇩 12 ሱዳን 🇲🇿 10 ሞዛምቢክ 🇸🇨 10 ሲሼልስ 🇸🇿 9 ኢስዋቲኒ 🇨🇫 8 ሴንትራል አፍሪካ 🇿🇼 8 ዚምቧቡዌ 🇨🇻 7 ኬፕ ቨርዴ 🇹🇩 7 ቻድ 🇸🇴 7 ሶማሊያ 🇧🇼 6 ቦትስዋና 🇲🇷 6 ሞሪታኒያ 🇸🇱 6 ሴራሊዮን 🇬🇲 4 ጋምቢያ 🇲🇼 4 ማላዊ 🇧🇮 3 ቡሩንዲ 🇸🇸 1 ደቡብ ሱዳን ─────────────────────────── 🔵 በአፍሪካ ሞት ያስተናገዱ ሀገራት 30 ደርሰዋል 🇩🇿 152 አልጄሪያ 🇪🇬 78 ግብፅ 🇲🇦 69 ሞሮኮ 🇹🇳 22 ቱኒዚያ 🇧🇫 17 ቡርኪናፋሶ 🇨🇩 16 ዲ.ሪ. ኮንጎ 🇿🇦 11 ደ. አፍሪካ 🇳🇪 10 ኒጀር 🇨🇲 9 ካሜሮን 🇲🇺 7 ሞሪሺየስ 🇬🇭 5 ጋና 🇳🇬 5 ናይጄሪያ 🇲🇱 5 ማሊ 🇨🇬 5 ሪ.ኮንጎ 🇰🇪 4 ኬንያ 🇨🇮 3 ኮትዲቯር 🇹🇬 3 ቶጎ 🇱🇷 3 ላይቤሪያ 🇦🇴 2 አንጎላ 🇪🇹 2 ኢትዮጵያ 🇸🇩 2 ሱዳን 🇸🇳 2 ሴኔጋል 🇿🇲 1 ዛምቢያ 🇹🇿 1 ታንዛኒያ 🇱🇾 1 ሊቢያ 🇬🇦 1 ጋቦን 🇿🇼 1 ዚምቧቡዌ 🇨🇻 1 ኬፕ ቬርዴ 🇧🇼 1 ቦትስዋና 🇲🇷 1 ሞሪታኒያ 🇬🇲 1 ጋምቢያ ─────────────────────────── √ የኮሮና ቫይረስን በጋራ እና በግል እንከላከል ✅የእጃችንን ንፅህና በአግባቡ እንጠብቅ ✅ሰዎች በተሰበሰቡበት ቦታ ላይ አንገኝ ✅ከሰዎች ጋር ያለንን ርቀት እንጠብቅ ✅የተጨናነቁ የትራንስፖርት አመራጮችን አንጠቀም ✅የጤና ባለሞያዎችን ምክር ሁሌም እንተግብር ✅የጤና ሚኒስቴር መምሪያዎችን እንከታተል ✅ስለ ኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ትክክለኛ መረጃ ከWHO ፣ ከጤና ሚኒስቴር እና ከህበረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብቻ ያግኙ! በተጨማሪ በነፃ የስልክ መስመሮች 8335 / 952 ላይ ደውለው መረጃዎችን ያግኙ 🦠 በከኮሮና ቫይረስ የተጠቃ ሰው ከሚያሳያቸው ምልክቶች ውስጥ √ ከፍተኛ ትኩሳት √ ሳል √ ለመተንፈስ መቸገር ዋነኞቹ ናቸው #በቅድመ_ጥንቃቄ_እና_በፀሎት_እንበርታ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

አስገራሚ ዜና 😍 መልካም ስራና ሰይጣን ይፈር !! ያኔ በሽታው በቻይና ሰፍቶ አውጡኝ ሲሉ ዝም የተባሉት በቻይና የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች እና ነዋሪዎች ለኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከላከያ የሚ
አስገራሚ ዜና 😍 መልካም ስራና ሰይጣን ይፈር !! ያኔ በሽታው በቻይና ሰፍቶ አውጡኝ ሲሉ ዝም የተባሉት በቻይና የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች እና ነዋሪዎች ለኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከላከያ የሚውል 452 ሺህ 589 የቻይና ዩዋን ድጋፍ እንዳደረጉ በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ። ከዚህም ውስጥ 100 ሺህ ዩዋን ያህሉ የሕክምና መሣሪያዎች ተገዝተው እንደሚላኩበት ኤምባሲው ገልጿል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

የኮሮና ቫይረስ በሽታና የጤና ባለሙያዎች የአዕምሮ ጤና ================================= በዚህ ጊዜ የአዕምሮ ጤናን እንዲሁም ስነልቦናዊ ሆነ ማህበራዊ ጤናን መጠበቅ ልክ አካላዊ ጤናን እንደመጠበቅ ጠቃሚ ነው!! የጤና ባለሙያ ኖት? እንግዲያውስ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሀገራችንም ብቅ ካለ በኋላ በተደጋጋሚ የትኛው አየለብዎ? ➦ግራ መጋባት ➦ቁጡነት ➦መናደድ ➦ኃይለኝነት ➦የሃዘን ስሜት ➦መደናገጥ ➦ድካም ➦በሃሳብ መናወጥ/መብሰልሰል ➦ጭንቀት ከዚህ ቀደም ከለመዱት የድህረ ፅኑ ክስተቶች ጭንቀት በተለዬ የጤና ባለሙያዎች ከስራቸው ጋር ተያይዞ በዚህ ወቅት የተለዬ ጭንቀት ብስጭት ረዳት የለሽነት የጥፋተኝነት ስሜት ሊያሳዩ ይችላሉ። ይሄም ከሚከተሉት ነጥቦች ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል። 1. እስካሁን ድረስ ውጤታማ መድሃኒት የሌለው አዲስ በሽታ በመሆኑ 2. የስራው ጫና በመጨመሩ 3. ከዚህ በላይ/አሁን ከምሰራው በላይ/መስራት አለብኝ/መስራት መቻል አለብኝ ብሎ በማሰብ 4. በበሽታ እያዝ ይሆን በሚል ፍራቻና ጭንቀት 5. ከታማሚውና ከሌሎች በሚደርስበት ጫና/እጅግ መጠበቅ 6. የሚሰራበት የስራ ቦታና በቂ ድጋፍ አለመኖር 7. የታማሚንና ጭንቀት ህመም ስቃይ ማየቱ እንግዲያውስ ከላይ የተጠቀሱት ምክንያቶች ቢኖሩም በዚህ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት የስነልቦና ጤናን ለመጠበቅ ምን ማድረግ አለብህ/ሽ? ምንስ ማድረግ የለብሽም/ህም? መደረግ ያለበት ========== 1. ግብ ባለውና በሚመዘን ሁኔታ ሚናን ሃላፊነትን ችሎታን አጋላጭ ሁኔታዎችን መረዳትና መገምገም 2. ተገቢውን ውሳኔ መወሰን ያስችልህ ዘንድ ለራስህ ጊዜ ስጥ 3. ስሜትህንና ፍላጎትህን ለመረዳትና ለመግለፅ ጊዜ ውሰድ 4. በአስቸጋሪና በተጨነቅክበት ወቅት እንዲሁም ጠቃሚ ውሳኔዎችን ስትወስን ወዳጆችህ ጋር ተገናኝ 5. በሰአቱ በቂና ጤናማ ምግብ ለመመገብ ሞክር እንዲሁም በቂ እንቅልፍና እረፍት እንደወሰድክ አረጋግጥ 6. ከዚህ ቀደም አስቸጋሪ/ከባድ ሁኔታዎች ሲገጥሙህ የተጠቀምክበትን ሊረዳ የሚችል ክህሎት መጠቀም 7. በአካላዊ እንቅስቃሴ ራስን መጥመድ 8. እረፍት መውሰድ 9. በCOVID-19 ለተያዙ ሰዎች እንዴት እርዳታ ማድረግ እንዳለብህ ማወቅ መደረግ የሌለበት =========== ⓵ አንድ ሰው ማድረግ/መስራት ከሚችለው በላይ ኃላፊነቶችንና ስራን መቀበል ➁ ምንም እረፍት ሳይወሰድ እስኪዝሉ ድረስ ከመጠን በላይ መስራት ➂ ምክንያታዊ ያልሆነና እውነታነት የሌለው ግብ ማስቀመጥ 'እያንዳንዱን ታካሚ አድናለሁ' እስከማለት ➃ የግል የሆኑ ጉዳዮችንና ፍላጎቶችን መቀነስ እንዲሁም እንደማይጠቅሙ ማሰብ ➄ ከማህበራዊ ትስስርና እርዳታ ራስን መገንጠል ከጓደኛ/ከቤተሰብ ➅ ጭንቀትን ለመከላከል አልኮል ሲጋራና ሌሎች አነቃቂና አደንዛዥ እፆች መጠቀም ናቸው በዚህ ጊዜ አንዳንድ የጤና ባለሙያዎች እንዳለመታደል ሆኖ በራሳቸው ቤተሰብና ህብረተሰብ ሊገለሉ ይችላሉ። ይሄም መጀመርያ ፈታኝ የሆነውን ሁኔታ የበለጠ አስቸጋሪ ያደርገዋል (የቤት አከራይ ጉዳይ ይሰመርበትና😠❗) #ከጤናባለሙያዎችጎንእንሁን #በጤናባለሙያዎችየሚሰጠውንትዕዛዝእናክብር #የነሱንምጫናለመቀነስእቤትመሆንአማራጭየሌለውምርጫእናድርግ ክብር ለጤና ባለሙያዎች በሙሉ!! ያለ አዕምሮ ጤና ጤና የለም! ቃልኪዳን ዮሐንስ የስነ አዕምሮ ባለሙያ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ከዚህ ቀጥሎ ባሉት የስራ መደቦች በቋሚነት አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይ
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ከዚህ ቀጥሎ ባሉት የስራ መደቦች በቋሚነት አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ እንድትመዘገቡ አስታውቋል፡፡ ለመመዝገብ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScbQ6dTcrU3MiA17C-2U0KMCCJNQZIPuWyTZ7vDmIpDDahYTg/viewform [ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ] ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በአሜሪካ ነብር በኮሮና ቫይረስ ተያዘች! በአሜሪካ ኒው ዮርክ ግዛት ውስጥ በሚገኝ ብሮንክስ በተባለ የእንሰሳት ማቆያ ማእከል ውስጥ የምትገኝ አንዲት ነብር በተደረገላት ምርመራ በኮሮና ቫይረስ መያዟ
በአሜሪካ ነብር በኮሮና ቫይረስ ተያዘች! በአሜሪካ ኒው ዮርክ ግዛት ውስጥ በሚገኝ ብሮንክስ በተባለ የእንሰሳት ማቆያ ማእከል ውስጥ የምትገኝ አንዲት ነብር በተደረገላት ምርመራ በኮሮና ቫይረስ መያዟ ተረጋግጧል፡፡ የአራት አመት እድሜ ያላት ነብር ደረቅ ሳል መሳል ከጀመረች በኋላ በተደረገላት ምርመራ መሆኑን የብሮንክስ እንሰሳት ማቆያ ባወጣው መግላጫ መስታወቁን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡ Via #CNN ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#JackMa የኢለባባ ኩባንያ ዋን ስራ አስፈፃሚ ጃክ ማ ሁለተኛ (2) ዙር የኮሮና ቫይርስ መከላከያ ቁሳቁሶችን ለአፍሪካ ሀገራት መላካቸውን በይፋዊ የትዊተር ገፃቸድ አስታውቀዋል። #ኤፍቢሲ ━━━━━
#JackMa የኢለባባ ኩባንያ ዋን ስራ አስፈፃሚ ጃክ ማ ሁለተኛ (2) ዙር የኮሮና ቫይርስ መከላከያ ቁሳቁሶችን ለአፍሪካ ሀገራት መላካቸውን በይፋዊ የትዊተር ገፃቸድ አስታውቀዋል። #ኤፍቢሲ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks