en
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Open in Telegram

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

Channel ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) is an active participant. Currently, the community unites 11 983 subscribers, ranking 17 269 in the Education category and 2 838 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 983 subscribers.

According to the latest data from 04 March, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -107 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 March, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

11 983
Subscribers
No data24 hours
-337 days
-10730 days
Posts Archive
#መጋቢት 18፣ 2012 #በስፔን በ24 ሰዓት ውስጥ ብቻ 769 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሕይወታቸው ማለፉ ተሰማ፡፡ ይሄም በአገሪቱ በቫይረሱ ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች ብዛት 4858 እንዳደረሰው ተሰምቷል፡፡ በአገሪቱ 64 ሺ 59 ሰዎች በቫይረሱ የተጠቁ ሲሆን 9 ሺ 357 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ ማገገማቸውን ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ ያወጣው መረጃ ያሳያል፡፡ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ማስተካከያ *** ከዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ የሚደርሱ እና ለለይቶ መከታተያ በተዘጋጁት ሆቴሎች ለመቆየት አቅም የሌላቸው መንገደኞች ወደ አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ተዛውረው ከውጪ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ መንገደኞች ለ15 ቀናት ተለይተው እንዲቆዩ የወጣውን መመሪያ ላይ ቦታው የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሳይሆን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሆኖ ይስተካከልልኝ ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት እወቁልኝ ብሏል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#BREAKING የብሪታኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] መጠቃታቸው BBC ዘግቧል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━
#BREAKING የብሪታኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] መጠቃታቸው BBC ዘግቧል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#መጋቢት 18፣ 2012 መንግስት የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት የሚወሰዱ አዳዲስ እርምጃዎችን ይፋ አደረገ፣ በዚህም መሰረት፦ 1. ከዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ወደ አዲስ አበባ የሚደርሱ እና ለለይቶ መከታተያ በተዘጋጁት ሆቴሎች ለመቆየት አቅም የሌላቸው መንገደኞች ወደ አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ተዛውረው ከውጪ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ መንገደኞች ለ15 ቀናት ተለይተው እንዲቆዩ የወጣውን መመሪያ ተግባራዊ የሚያደርጉ ይሆናል፡፡ 2. ከዛሬ አንስቶ ለተጨማሪ ሁለት ሳምንታት ከፍተኛ የትምሕርት ተቋማትን ጨምሮ፣ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው የሚቆዩ ይሆናል፡፡ 3. በገበያ ስፍራዎች እና በሀይማኖት ተቋማት ውስጥ ማኅበራዊ ርቀትን መጠበቅ በጥብቅ ተፈጻሚ ሊደረጉ ያስፈልጋል፡፡ የፌደራል መንግሥት አስከፊ ብሔራዊ አደጋ በሚከሰት ጊዜ ሀይማኖታዊ ስብሰባዎች እንዲቋረጡ የማድረግ ሕገመንግሥታዊ መብት አለው፡፡ ሆኖም፣ በሕገ መንግሥቱ የተደነገጉትን እርምጃዎች ተግባራዊ ከመደረጋቸው በፊት፣ ዜጎች የማኅበራዊ ርቀት መመሪያን ተግባራዊ እንዲያደርጉ በድጋሚ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ 4. ሁኔታው ተጨማሪ ድጋፍን የሚጠይቅ ከሆነ ሁሉም ጡረታ የወጡ እንዲሁም በትምሕርት ላይ ያሉ የሕክምና ባለሙያዎች ለብሔራዊ ግዳጅ እንዲዘጋጁ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡ 5. የተለያየ መጠን እና ዓይነት ያላቸው መገልገያዎችን የያዙ ከ134 በላይ ተቋማት ለለይቶ መከታተያ፣ ለይቶ ማቆያ እና ሕክምና እንዲሆኑ ተለይተዋል፡፡ ስለዚህ፣ መንግሥት ሁሉም ዜጎች እንደ አልጋዎች፣ ፍራሾች፣ አንሶላዎች፣ የመተንፈሻ ቬንትሌተሮች እና ሌሎች ከሕክምና ጋር ተያያዥነት ያላቸው እና የሌላቸው መገልገያዎችን ለማሰባሰብ በመሥራት ላይ የሚገኘውን የብሔራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ጥረት እንዲደግፉ ጥሪ ያቀርባል፡፡ 6. የማክሮ-ኢኮኖሚ ንዑስ ኮሚቴው የኢኮኖሚ ዘርፉን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችሉ አማራጮችን ለመቀየስ በልዩ ልዩ ዘርፍ ከተሠማሩት ዐበይት የኢንደስትሪ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይትን ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ይህንኑ ተከትሎም፣ ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት የሚከተሉት እርምጃዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ፡- የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስፈልጉ የገቢ ዕቃዎች እና ግብአቶች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ ይደረጋል፡፡ የፋይናንስ ዘርፉን ጤንነት አስጠብቆ የመቀጠል እና ባንኮች በኮቪድ-19 ቫይረስ ለተጎዱ ደንበኞቻቸው ጊዜያዊ የብድር እፎይታ እና ተጨማሪ ብድር ለመስጠት እንዲያስችላቸው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተጨማሪ 15 ቢሊየን ብር ለግል ባንኮች ይሰጣል፡፡ የውጪ ምንዛሬ የሚያስፈልጋቸው እና የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችሉ ዕቃዎችን እና ግብአቶችን ወደ ሀገር ውስጥ ለሚያስገቡ አስመጪዎች ባንኮች ቅድሚያ በመስጠት እንዲያስተናግዱ ይደረጋል፡፡ በፋይናንስ አገልግሎት የተነሳ ገጽ ለገጽ መገናኘት እና የብር ንክኪን ለመቀነስ እንዲቻል፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሞባይል አማካኝነት የሚደረግ ክፍያ እና ገንዘብ የማስተላለፍ ጣሪያውን ከፍ ያደርጋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለውጭ ገበያ በሚቀርብ አበባ ላይ የጣለው ዝቅተኛ የመሸጫ ዋጋ ገደብ በጊዜያዊነት እንዲነሳ ተደርጓል፡፡ ኩባንያዎች የተሻለ የገንዘብ ፍሰት እንዲኖራቸው ለማስቻል፣ የገቢዎች ሚኒስቴር የተጨማሪ እሴት ታክስ አመላለስ ሂደቱን በተለየ መልኩ እንዲያፋጥን ይደረጋል፡፡ የኮቪድ-19ን ወረርሽኝ ተከትሎ ሊከሰት የሚችለውን የሸቀጦች እጥረት እና አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ ለመቆጣጠር በንግድና ኢንደስትሪ ሚኒስቴር የጀመረው ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ_19) በሽታ የተያዙ ተጨማሪ ሰዎች መገኘታቸውን ለማሳወቅ የተሰጠ መግለጫ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ #መጋቢት 3/2012 ዓ.ም የመጀመሪያው በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው በሀገራችን ከተገኘ ወዲህ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ አራት (4) ተጨማሪ ሰዎች በመገኘታቸው በአጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አስራ ስድስት (16) ደርሷል፡፡ ❖የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ፡- #ታማሚ 1፡ የ72 ዓመት ሞሪሸሳዊ ሲሆኑ መጋቢት 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከኮንጎ ብራዛቪል የተመለሱ ናቸው፡፡ መጋቢት 13፣2012 ዓ.ም ወደ ጤና ተቋም የሄዱ ሲሆን ተቋሙም ለኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖርት በማደረጉ በተደረገላቸው የላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፡፡ ታማሚውም በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከታማሚው ጋር ግንኙነት የነበራቸው 6 ሰዎች በክትትል ላይ የሚገኙ ሲሆን ከነሱ ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሌሎች ሰዎችን የማጣራት ሂደት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ #ታማሚ 2፡ የ61 ዓመት የአዳማ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያዊ ናቸው፡፡ በተገኘው መረጃ መሠረት ግለሰቡ የውጭ የጉዞ ታሪክ ባይኖራቸውም በስራ ባህሪያቸው ምክንያት ከአንድ የውጭ ሀገር ዜጋ ጋር ግንኙነት ነበራቸዉ፡፡ ታማሚው ግለሰብ መጋቢት 9 ቀን 2012 ዓ.ም የህመም ስሜት ሲሰማቸው ራሳቻውን አግልለው እንደቆዩና መጋቢት 16፣2012 ዓ.ም ወደ ጤና ተቋም የሄዱ ሲሆን ተቋሙም ሪፖርት ባደረገው መሰረት በላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፡፡ በአሁኑ ወቅት ታማሚው በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከታማሚው ጋር ግንኙነት የነበራቸው 24 ሰዎች በክትትል ላይ የሚገኙ ሲሆን ከነሱ ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሌሎች ሰዎችን የማጣራት ሂደት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ #ታማሚ 3፡ የ28 ዓመት ኢትዮጵያዊት ስትሆን የመጨረሻ ጉዞዋም መጋቢት 12፣ 2012 ዓ.ም እስራኤል ሀገር ደርሳ የተመለሰች ናት፡፡ ግለሰቧም በቀን 16፣ 2012 ዓ.ም በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በተደረገላት የላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዙዋ ተረጋግጧል፡፡ በአሁኑ ወቅትታማሚዋ በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የህክምና ክትትል እየተደረገላት ይገኛል፡፡ ከታማሚዋ ጋር ግንኙነት የነበራቸው 7 ሰዎች በክትትል ላይ የሚገኙ ሲሆን ከነሱ ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሌሎች ሰዎችን ማጣራት ሂደት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ #ታማሚ 4፡ የ24 ዓመት ኢትዮጵያዊት ስትሆን የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የሌላት ቢሆንም የበሽታው ምልክት ከታየባቸው ሰዎች ጋር የነበራት ግንኙነት እየተጣራ መሆኑ እና ግለሰቧም በቀን 17፣ 2012 ዓ.ም በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በተደረገላት የላብራቶሪ ምርመራ በቫይረሱ መያዙዋ ተረጋግጧል፡ በአሁኑ ወቅት ታማሚዋ በለይቶ ማከሚያ ውስጥ የህክምና ክትትል እየተደረገላት ይገኛል፡፡ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አማካኝነት እስከ አሁን 718 የላራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 33 በ24 ሰዓት ( መጋቢት 17 ጥዋት 1፡00 ሰዓት እስከ መጋቢት 18 ጥዋት 1፡00 ሰዓት) ውስጥ የተከናወነ ነው፡፡ [Ministry of Health,Ethiopia] ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በኮሮና ቫይረስ የተያዙ አራት 4 ተጨማሪ ሰዎች በመገኘታቸው በአጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር #አስራ_ስድስት 16 መድረሱን የጤና ሚኒስትር አስታወቀ። Rest in home🏠 or rest i
#በኮሮና ቫይረስ የተያዙ አራት 4 ተጨማሪ ሰዎች በመገኘታቸው በአጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር #አስራ_ስድስት 16 መድረሱን የጤና ሚኒስትር አስታወቀ። Rest in home🏠 or rest in peace⚰ ምርጫው የራሳችን ነው!! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በአዳማ ከተማ 1 በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ተገኘ! በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አንድ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው መገኘቱን በክልሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተቋቋመው ግብረ ሃይል ገለጸ፡፡
#በአዳማ ከተማ 1 በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ተገኘ! በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አንድ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው መገኘቱን በክልሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተቋቋመው ግብረ ሃይል ገለጸ፡፡ ከግለሰቡ ጋር ንክኪ የነበራቸው 24 ሰዎች ተለይተዋልም ነው የተባለው። ግብረ ሃይሉ በህብረተሰቡና በተቋማት የሚታየው ቸልተኝነት አሁንም #አሳሳቢ ነው ብሏል። #FBC Rest in home🏠 or rest in peace⚰ ምርጫው የራሳችን ነው!! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#Coronavirus በአሜሪካ አውሮፕላን ተሸካሚ የጦር መርከብ ላይ በተሰማሩ የባህር ኃይል አባላት ላይ የኮሮናቫይረስ በሽታ ክስተት ቁጥር እየጨመረ መሆኑ ተነገረ። አውሮፕላን ተሸካሚ መርከቧ በውስጧ
#Coronavirus በአሜሪካ አውሮፕላን ተሸካሚ የጦር መርከብ ላይ በተሰማሩ የባህር ኃይል አባላት ላይ የኮሮናቫይረስ በሽታ ክስተት ቁጥር እየጨመረ መሆኑ ተነገረ። አውሮፕላን ተሸካሚ መርከቧ በውስጧ ካሉ አባላቷ መካከል ኮሮናቫይረስ መገኘቱን ይፋ በማድረግ የመጀመሪያዋ ስትሆን፤ አሁን የታማሚዎቹ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን ሲኤንኤን የባህር ኃይል ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል። በመጀመሪያ በሦስት መርከበኞች ላይ በተደረገ ምርመራ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሲሆን አሁን ቁጥሩ 25 ደርሷል ተብሏል። በአሜሪካ ባህር ኃይል በኩል የወጣው መግለጫም ቁጥሩን ሳያመለክት “ዩኤስኤስ ቴዎዶር ሩዝቬልት በተባለችው መርከብ ላይ ተጨማሪ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ተገኝተዋል” ብሏል። በበሽታው የተያዙት ሰዎች ተለይተው የሚገኙ መሆኑንና መርከቧም እየተጸዳች መሆኑ ተነግሯል። Via:- BBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

⏰መጋቢት 17፣2012⏰ 📌ምጥን የዓለም ወሬዎች 📝 #ፊሊፒንስ ውስጥ 9 ዶክተሮች በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተው መሞታቸው ተሰምቷል። የሰዎችን ህይወት ለማትረፍ ከፍተኛ ትግል እያደረጉ ያሉት የፊሊፒንስ የጤና ባለሞያዎች በቂ መከላከያ እያገኙ አይደለም ተብሏል። #ጣልያን ውስጥ በ24 ሰዓት ተጨማሪ 662 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ሞተዋል። ከትላንትናው ሪፖርትም መቀነስ አሳይቷል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 8,165 ደርሷል። በሀገሪቱ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥርም 80,539 የደረሱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 6,153 ኬዝ በ24 ሰዓት ነው የተመዘገበው። #የኬንያ ጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ዛሬ ከሰዓት በኮሮና ቫይረስ የተጠቃ አንድ 66 ዓመት ኬንያዊ ዜጋ ህይወቱ አልፏል። #በቻይና በኮሮና ቫይረስ ተይዘዉ ካገገሙ ህሙማን 14 በመቶ የሚሆኑት ድጋሚ ሲመረመሩ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል፡፡ #ዓለም_አቀፍ ትብብር እና ከ2 እስከ 3 ትሪሊዮን ዶላር። አዎ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዳለው የኮሮና ወረርሽኝን ለመዋጋት የሚያስፈልጉት እነሱ ናቸው። የድርጅቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በሰዉ ዘር ላይ ለመጣው ለዚህ አደጋ የየግል ሩጫ የትም አያደርስም። የአደጉት ሀገራት አዳጊዎችን ቸል አሉ ማለት፣ ቫይረሱ ራሱን ቀይሮና አጠናክሮ እንዲመለስባቸወ ዕድል መስጠት ነው። #የኒውዮርክ ከተማ #ወረርሽኙ የበረታባት በ24 ሰዓታት ብቻ 285 ሰዎቿን አጥታለች ብለዋል። የምድራችን ሀብታም ከተማ በሆነችው ኒውዮርክ የህክምና ባለሙያዎች ጋዋን አልቆባቸው ቆሻሻ መጣያ ላስቲኮች ለመደረብ ተገደዋል ። #የኒውዮርክ አገረ ገዢ ግን ማኅበራዊ ርቀት የሆስፒታል አልጋ ፈላጊዎችን ቁጥር እየቀነሰ ነው።ወረርሽኙ ከአሜሪካ አጠቃላይ ሕዝብ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በየቤቱ እንዲከተት አስገድዷል። #ሩሲያ ሁለት ሚሊዮን ያህል ዜጎቿ ከሰዉ ተነጥለው እንዲሰነብቱ አዘዘች። ሀገሪቱ ትዕዛዙን ያስተላለፈችው ለኮሮናቫይረስ እጅግ ተጋላጭ ናቸው ባለቻቸው ላይ ነው። #በሩሲያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል ቢባልም፣ ብዙዎች ግን እዉነተኛዉ ቁጥር ከዚያ በብዙ እጅ እንደሚልቅ ይጠረጥራሉ። #አሜሪካ የኮሮና ቫይረስ ያሽመደመደዉን ኢኮኖሚዋን ለመደጎም የ2.2 ሚሊዮን ዶላር በጀት አፅድቃ ነበር። አዲሱ መረጃ ግን የዛን በጀት በቂነት ጥያቄ ውስጥ ከትቶታል። #በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች 1000 ሊደፍን ነው። ዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (#IMF) እና የዓለም ባንክ ሀብታሞቹ ሀገራት ለአዳጊዎቹ የዕዳ ቅነሳ እና የክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ እንዲያደርጉ ጠየቁ። የፋይናንስ ድርጅቶቹ የኮሮና ወረርሽኝ በአዳጊ ሀገራት ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ በድምሩ 60 ቢሊዮን ዶላር መመደባቸውንም ይፋ አድርገዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አንድ ሺህ ስምንት መቶ ስምንት መድረሱን የዓለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቅርንጫፍ ይፋ አድርጓል፡፡ ባለፉት ሃያ አራት ሰዓታት በ15 ሀገራት ውስጥ ሁለ
#በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አንድ ሺህ ስምንት መቶ ስምንት መድረሱን የዓለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቅርንጫፍ ይፋ አድርጓል፡፡ ባለፉት ሃያ አራት ሰዓታት በ15 ሀገራት ውስጥ ሁለት መቶ አስራ ስድስት አዲስ ታማሚዎች መመዝገባቸው ተገልጿል፡፡ ኮሮና ቫይረስ ጊኒ ቢሳዎ እና ማሊ ለመጀመሪያ ጊዜ መግባቱ እና እያንዳንዳቸው አንድ ታማሚ ማግኘታቸውም ተገልጿል፡፡ #WHO #AfricaCDC #etv Rest in home🏠 or rest in peace⚰ ምርጫው የራሳችን ነው!! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#በዓለም ዙሪያ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 21ሺ 297 ሰዎች ደርሷል። በቫይረሱ የተያዙት ደግሞ 471ሺ 820 ሲሆን ያገገሙት ሰዎች 114ሺ 703 እንደደረሱ መረጃዎች አመላክተዋል። ━━━━━
#በዓለም ዙሪያ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 21ሺ 297 ሰዎች ደርሷል። በቫይረሱ የተያዙት ደግሞ 471ሺ 820 ሲሆን ያገገሙት ሰዎች 114ሺ 703 እንደደረሱ መረጃዎች አመላክተዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

የኮቪድ-19 በሽታን አስመልክቶ ጥቆማ ለመስጠት፦ ❖ ለኦሮሚያ ክልል - 6955 ❖ ለትግራይ ክልል - 6244 ❖ ለአማራ ክልል - 6981 ❖ ለሱማሌ ክልል - 6599 ❖ ለድሬዳዋ ከተማ - 6407 ❖
የኮቪድ-19 በሽታን አስመልክቶ ጥቆማ ለመስጠት፦ ❖ ለኦሮሚያ ክልል - 6955 ❖ ለትግራይ ክልል - 6244 ❖ ለአማራ ክልል - 6981 ❖ ለሱማሌ ክልል - 6599 ❖ ለድሬዳዋ ከተማ - 6407 ❖ ለደቡብ ክልል - 6929 «ወረርሽኝ እሳት ሲሆን ማገዶው እናንተ ናችሁ እሳቱ ማገዶ አጥቶ ይከስም ዘንድ በተናጥል ቆዩ» ዐምር ኢብኑል ዐስ (ረ.ዐ) ▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️ Rest in home🏠 or rest in peace⚰ ምርጫው የራሳችን ነው!! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

🖍 #Coronavirus‼️ #USA : አሜሪካን ቻይናን እና ጣልያን ተከትላ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች:: በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 60,653 ደርሷል:: በጣልያን 74,386 ሲደርስ በቻይና 81,218 እንደሆነ ታውቋል:: #በሩዋንዳ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 41 ደርሷል። የሩዋንዳ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ 1 ተጨማሪ የኮቪድ-19 ተጠቂ ሪፖርት ተደርጓል። ቫይረሱ የተገኘበት ግለሰብ ከዱባይ ወደሩዋንዳ የገባ ነው። ከዱባይ??? ከረምናታ ፍጣሪ ይሁኑን #ግብፅ 54 አዲስ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎችን ማግኘቷን አሳወቀች:: በግብፅ በአጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 456 ሲሆን የሞቱት 21 ደርሰዋል:: #የኢንተርናሽናሉ ገንዘብ ተቋም (IMF ) በድህረ ገፁ እንዳሰፈረው ኮሮና ቫይረሰ ኢትዮጵያን ጨምሮ ኢኮኖሚያቸውን ለጎዳው ከሰሀራ በታች ላሉ አፍሪካ ሀገራት 50 ቢልየን ዶላር በሁለት ሳምንት ግዜ ውስጥ አሰጣለው ብሏል ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

📌Title - Contagion (2011) 📌Language - English 📌Quality - 360p BDRip x264 950MB ESubs 📌Size - 322Mb 🎬በ360 pixels 📎322ሜጋባይት ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

📌Title - Contagion (2011) 📌Language - English 📌Quality - 720p BDRip x264 950MB ESubs 📌Size - 1GB 🎬በ720 pixels 📎1ጂቢ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

📌ከኮሮና ቫይረስ ጀርባ ያለው የማይሻር እውነት! ⚠️የ2003 ዓ/ም የContagion ፊልም ስለኮሮና በሽታ ትንቢት ❗️ከዛሬ 9 ዓመታት በፊት እ.አ.አ 2011 በእኛ አቆጣጠር 2003 ዓ/ም Contagion የተባለ ፊልም ይፋ ሆነ፡፡ ፊልሙ ሙሉ በሙሉ የሚያጠነጥነው አንድ ከየት እንደመጣ ባልታወቀ ቫይረስ ላይ ነው፡፡ የፊልሙ መቼት በቻይና፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ… ሲሆን የቫይረሱ መነሻ መቼት ደግሞ ቻይና ነበር፡፡ 📌ይህ ፊልም፣ አንዲት የምታስል እንስት ሴት በአውሮፕላን ወደ ቤቷ ታመራና ቤት ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንቀጠቀጠች አረፋም እየደፈቀች ስትሞት ይጀምራል፡፡ በኋላ እንደምጠቅሰው፣ እንስቷ ከአንድ የአሳማ በላች ሼፍ ቫይረሱ ለመጀመርያ ጊዜ እንደያዛት እንመለከታለን፡፡ ቫይረሱም ከዛች የመጀመርያ ቀን ጀምሮ ሲነሣ እናያለን፡፡ ዋናው ዓላማዬ በዚህ ፊልም ስለ ቫይረሱ እንዴት እንደነገሩን ማሳየት ነውና ወደሱ እናምራ ! 1. በፊልሙ ላይ ቫይረሱ ከቻይና እንደተነሳ ይታያል፡፡ የኮሮና ቫይረስ መነሻም ቻይና እንደሆነ ልብ በሉ፡፡ 2. በፊልሙ ላይ ቫይረሱ የማሳል፣ የማስነጠስና የትኩሳት ባሕርይ እንዳለው ይታያል፡፡ የኮሮና ቫይረስ ምልክትን ልብ በሉ፡፡ 3. በፊልሙ ላይ በቫይረሱ የተጠቃ ሰው የሚነካውን ማንኛውም ዕቃ ሌላ ሰው ቢነካ በቫይረሱ እንደሚጠቃ ያሳያል፡፡ የኮሮና ቫይረስ መተላለፊያን ልብ በሉ፡፡ 4. በፊልሙ ላይ ቫይረሱ የመተንፈሻ አካላትን የሚያጠቃ ቫይረስ እንደሆነ ይታያል፡፡ የኮሮና ቫይረስ ዋና ታርጌቱን ልብ በሉ፡፡ 5. በፊልሙ ላይ ቫይረሱ በመተንፈሻ አካላት ላይ ካሉት Receptor ሴሎች ላይ ልክ እንደ ቁልፍ እንደሚሰካ ይታያል፡፡ የኮሮና ቫይረስን ተመሳሳይ ባሕርይ ልብ በሉ፡፡ 6. በፊልሙ ላይ ቻይናዊያንን ወክሎ የምናየው አንድ ቻይናዊ ካራክተር ቫይረሱ በአሜሪካኖች ሆን ተብሎ እንደተለቀቀና የዓለም የጤና ድርጅትም ዐውቆ እንደደበቀው ሲናገር ይታያል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የቻይናና የአሜሪካ ሰጣ ገባ ልብ በሉ፡፡ 7. በፊልሙ ላይ በቫይረሱ ምክንያት ት/ቤቶች፣ የንግድ ሱቆች ሲዘጉ ይታያል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ያለውን ሁኔታ ልብ በሉ፡፡ 8. በፊልሙ ላይ ቫይረሱ በተከሰተበት ጊዜ የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ጥቁር እንደነበረ ይታያል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የኮሮና ቫይረስ ሲከሰት የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ጥቁር ያውም አፍሪካዊ ያውም ኢትዮጵያዊ መሆኑ አጋጣሚ ይመስልሃል? 9. በፊልሙ ላይ ቫይረሱ የተነሣው በአንድ ሌሊት አንድ ዛፍ በግሬንደር ሲቆረጥ የተበጠበጡት የሌሊት ወፎች መንቀሳቀስ ይጀምሩና አንድ ሙዝ መሰል ምግብን በአፋቸው ቆርጠው ሲጥሉና ያንን ምግብም አንድ አሳማ ሲመገብ፣ ይህን አሳማ ደግሞ ቻይናዊው ሼፍ ቆራርጦ ለምግብ በማዘጋጀት ላይ እንዳለ የቫይረሱ መጀመሪያ ተጠቂ የሆነችው ካራክተር ሼፉን ሰላም ስትለው ቫይረሱ እንደተነሣ ይታያል፡፡ የኮሮና ቫይረስ አመጣጥም በሌሊት ወፍ ምክንያት ነው የሚለውን ተረት ተረት ልብ በል፡፡ 10. በፊልሙ ላይ ቫይረሱን ለመከላከል ብቸኛ መፍትሔ ተደርጎ የቀረበው እጅን መታጠብ፣ አለመጨባበጥ፣ ፊትን አለመነካካትና ተነጥሎ መቆየት ነው፡፡ የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ተደርጎ የተነገሩንን መንገዶች ልብ በሉ፡፡ ፊልሙ ወደፊት የሚመጣውን አስቀምጧል..!? 📌ሚስጥራ ብድኖቹ ብልህ ናቸው፡፡ ሊያደርጉ ያሰቡትን እያንዳንዱን ሴራ ቁልጭ አድርገው አስቀድመው በማሳየት አስተዋይ ሰዎችን በፍርሃት ብቻ የማሽመድመድ ሴራን ተክነውበታል፡፡ ⚠️ ወደፊት ይምጣ አይምጣ የማይታወቁ ጥቂት ነገሮችን ደግሞ እንዲህ አሳይተውናል.... 1. በፊልሙ ላይ ከ26 ሚልየን በላይ ሕዝብ እንደሚያልቅ ይታያል፡፡ 2. በፊልሙ ላይ ብዙ ሚልየን ሕዝብ ካለቀ በኋላ በአፍንጫ የሚወሰድ መድኃኒት እንደሚያገኙ ይታያል፡፡ 3. በፊልሙ ላይ የተገኘው መድኃኒት ለዓለም ሕዝብ ሁሉ ስለማይበቃ የሰዎችን የልደት ቀን በዕጣ በማውጣት ዕጣው የወጣላቸውን ብቻ መድኃኒቱን ሲያስወስዱ ይታያል፡፡ 4. በፊልሙ ላይ ተገኘ የተባለው መድኃኒት ሕዝቡን ለተጨማሪ በሽታዎች የሚዳርግ እንደሆነ ጋዜጠኛ ሆኖ ከተወነው ካራክተር አፍ ሲወራ ይታያል፡፡ እነዚህ ገና ሊመጣ ያለውን ሊያሳዩ የሚችሉ ከሴራዊ ፊልማቸው የተወሰዱ ዐሳቦች ናቸው፡፡ ዕድሜ ከሰጠን ወደፊት እያስተያየን የምንታዘባቸው ይሆናል፡፡ ⚠️በአጠቃላይ.. ሚስጢራዊ ቡድኖቹ Order Out of Chaos በሚባል መርሐቸው አንድን ሴራ መፈፀም ሲፈልጉ ያን ሴራ ከመፈፀማቸው በፊት በፊልማቸው ይነግሩናል፡፡ በዚህ ፊልም ያየነውም እሱን ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ያለውን ሁኔታ ቁልጭ አድርገው አሳይተውናል፡፡ ⚠️ኮሮና ቫይረስ አንዳንዴ ከፈጣሪ የተላከ ቁጣ አንዳንዴም ከእንሳስት የመጣ በሽታ እንደሆነ ብዙዎቻችን እያመነታን እንከራከራለን፡፡ እውነታው ግን እርሱ አይደለም፡፡ ብዙ የዓለም ሕዝቦች ለሚገዙለት ለሰይጣናዊ መንፈስ ቃል የገቡት ሚስጢራዊ ቡድኖቹ ... እንዲህ አይነት ገዳይ በሽታዎችን ለመፈብረክ ከምድር በታች በተገነቡት ምሥጢራዊ የበሽታ መፈብረኪያ ፋብሪካዎቻቸው የዓለምን ሕዝብ የሚቀንሱ በሽታዎችን እያመረቱ ይገኛሉ፡፡ በአሁን ሰዓት የዓለም ሕዝብ ካያቸው በየትኛውም ዘመን ከተነሡ ችግሮች እጅግ አስቸጋሪ የሆነ ቫይረስን ነው ያመረቱት፡፡ <<በችግር-እርምጃ-መፍትሔ በተባለ ዕቅዳቸው መሠረት አንድን ችግር ከፈጠሩ በኋላ፤ መፍትሔ ብለው ሕዝቡን በሚያሳምኑት ግን መፍትሔ ባልሆነ መንገድ #ሌላ_ተያያዥ_ሴራ_ያክላሉ ፡፡>> በአሁኑ ሰዓት የሚታየውም ይህ ነው፡፡ ለኮሮና ቫይረስ መፍትሔ ብለው ያቀረቡዋቸው መንገዶች ከማኅበራዊነት ይልቅ በግላዊነት እንድናምን የሚያደርጉ፣ ብቸኝነትን እንድንለማመድና ከሀገራዊ ፍቅር የወጣን ራስ ወዳድ እንድንሆን የሚያደርጉ፣ ባሕሎችን በመሸርሸር ባሕል የለሽ እንድንሆን የሚያደርጉ መንገዶች ናቸው፡፡ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ!!! በክርስትና፣ ቤተክርስትያን የሚደረጉ ሥርዓቶችን፣ መስቀል መሳለም፣ ቅጥር መሳም… ወ.ዘ.ተ እንዲቀሩ በእስልምናም ተሰብስቦ መስገድ እንዲቀሩ የሚያደርግ የመፍትሔ ዐሳቦችን ዘወትር በየሚድያው እየተነገሩ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ሥርዓቶችን ቤት ቁጭ ብለን በቲቪ እንድንፈፅምም ሲነገር ተመልክተናል፡፡ እነዚህ ለጊዜው አሪፍ መፍትሔ የሚመስሉ፣ በረጅም ጊዜ ዕቅድ ግን እጅግ ተንኮል ያለባቸውን መፍትሔዎችን ዘወትር በሚድያዎቻቸው ሊያሳምኑን ይሞክራሉ፡፡ እውነታው ግን ይህ ነው፤ #እምነትና_ባሕል_የለሽ_ትውልድን_መፍጠር፡፡ እውነታው ግን ይህ ነው፤ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን መሸርሸር፡፡ ከዚህ ሌላ እውነት የለም፡፡ ለማንኛውም መፍትሔዎቹን አትጠቀሙ አልልም፡፡ መጠንቀቅም መልካም ነው። ግን ሴራውን ተረዱ፣ ተገንዘቡ፡፡ ሴራውን መረዳት ብቻ ሳይሆን ተጠቀሙበት፡፡ ውጤቱ አሁን አይታይም፡፡ ምናልባት ከደረስን በልጆቻችን እናየው ይሆናል እንጂ፡፡ "is that Corona virus biological weapon or Not " ? ለማንኛውም ይህን ፊልም ተመልከቱት Corona Vs. Contagion ስለ ኮሮና ቀድሞ የነገረን ፊልም ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

Corona Vs. Contagion ስለ ኮሮና ቀድሞ የነገረን ፊልም ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━
Corona Vs. Contagion ስለ ኮሮና ቀድሞ የነገረን ፊልም ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#NewsAlert ጣልያን ተጨማሪ 683 ዜጎቿን አጣች! #Coronavirus : ጣልያን ውስጥ በ24 ሰዓት ተጨማሪ 683 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ሞተዋል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 7,503 ደርሷል። በሀገሪቱ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥርም 74,386 የደረሱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 5,210 ኬዝ በ24 ሰዓት ነው የተመዘገበው።

ኮሮና ቫይረስን ምርመራ ውጤት በ15 ደቂቃ የሚነግር መሳርያ በብሪታንያ ሊከፋፈል ነው ብሪታንያ ሰዎች ከቤታቸው ሆነው ደማቸውን ብልቃጥ ላይ ጠብ አርገው ኮሮና ቫይረስ በእራሳቸው የሚመረምሩበት ውጤቱንም በ15 ደቂቃ የሚያውቁበት የምርመራ መሳርያ ለገበያ በቅርብ ሳምንት ለማቅረብ እየሰራው ነው ብላለች መሳርያውም ለህዝቡ በስፋት ይሰራጫል ሲል የእንግሊዝ ህብረተሰብ ጤና ዳይሬክተር ነግረውኛል ሲል ኢንዲፔንዳንት ጋዜጣ ፅፏል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━