en
Feedback
👑TesfaMichael Assefa

👑TesfaMichael Assefa

Open in Telegram

ነገን ከዛሬ የተሻለ እና ያማረ ውጤት በህይወታቸው ማምጣት ለሚፈልጉ፣ለአዲሱ ነገ ዝግጁ የሆኑ ሰዎችን አግዛለሁ። እንዲሁም ሁሌም የኔ ሀሳብ እና ውጤቶችን በየእለቱ በዚህ ገፅ ያገኛሉ። ቤተሰብ ስለሆኑ ከልብ አመሰግናለሁ። ለማንኛውም ሀሳብ ሆነ ጥያቄ- @tesfish85 0985158551 ይጠቀሙ።

Show more
Ethiopia17 708The category is not specified
733
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
🙏❤️ join 👇👇channel
🙏❤️ join 👇👇channel

መልካም የጥምቀት በዓል ይሁንል።
+2
መልካም የጥምቀት በዓል ይሁንል።

My family endet nachihu 😍🙏
My family endet nachihu 😍🙏

በብዙ መልኩ እማራለሁ! ሕይወት መደበኛ እና መደበኛ ያልሆኑ ዘርፈ-ብዙ ትምህርት ቤቶች አሏት - የሚማር ካለ! በመደበኛው ትምህርት ቤት ሰዎች ለእኛ ሊሰጡን በፈለጉት እውቀት እንገደባለን፡፡ መደበኛ ባልሆነው ትምህርት ቤት ግን መማር የምንችለውንም ሆነ የምንፈልገውን ነገር የምንወስነው እኛው ነን፡፡ ለዛሬ መደበኛ ካልሆነው የትምህርት መስክ ውስጥ አንዱን ዘርፍ ላስታውሳችሁ፡፡  • ባገኘኋቸው ስኬቶቼ ከመኩራራትና ከማን እንደምሻል ለማሳየት ከመሞከር ይልቅ ምን ስላደረኩኝ እንደተሳካልኝ በማሰብና ለወደፊቱ ምን በማድረግ የበለጠ ስኬት ውስጥ መግባት እንዳለብኝ ካለማቋረጥ እማራለሁ፡፡ • በምሰራቸው ስህተቶች ከመጸጸትና ራስን ከመኮነን ይልቅ ለወደፊቱ ደግሜ ልሰራ ስለማይገባኝ ስህተት ካለማቋረጥ እማራለሁ፡፡ • ሰዎች ሲሳካላቸው ሳይ በእነሱ ከመቅናትና ከመፎካከር ይልቅ እንዴት ሊሳካላቸው እንደቻለ በማጥናት ካለማቋረጥ እማራለሁ፡፡ • ሰዎች ስህተትን ሲሰሊ ስመለከት የእነሱን ውድቀት እኔ የተሻልኩ እንደሆንኩኝ ለማሰብና ሾለ እነሱ ውድቀት ለማውራት ከመጠቀም ይልቅ ከሁኔታው ካለማቋረጥ እማራለሁ፡፡ በሁሉም ነገር፣ ሁል ጊዜ እንማር! ሁሉንም ነገር ወደ ትምህርት እንቀይር! ይህንን ልምምድ ስናዳብር . . . 1. የማያቋርጥ እድገት ውስጥ ራሳችንን እናገኘዋለን፡፡ 2. ትኩረታችንን ከሰዎች ላይ በማንሳት በራሳችን ላይና በዓላማችን ላይ ማድረግ እንጀምራለን፡፡ 3. ሁል ጊዜ የአሸናፊነትና ልቆ የመገኘት ስሜትን ስለምናስተናግድ መነሳሳታችንን እንደጠበቅን እንኖራለን፡፡

#3ቱ_አመለካከትህን_የሚቀይሩ_እውነታዎች #አንደኛ ሁሌም በየትኛውም የህይወት ደረጃ ላይ ብትሆን የሆነ ችግር ሊያጋጥምህ እንደሚችል አትርሳ። ስለዚህ አንድ ግድ መማር ያለብህ ነገር አለ። ምንድንነው አትልም? በህይወት ችግር ውስጥ ሆነህም እንኳ መዝናናት እንዳለብህ፧ ከደስታህ ሳትርቅ ችግሮችህን መፍታት ይኖርብሃል። ልምድ ስታደርገው ስቃይም ቢሆን ውበት ሆኖ የሚታይህ ጊዜ አለ። አንተ ብቻ አመለካከትህን ቀይር። ሁሌም ምቾትና ማግኘት አሊያም ማሸነፍ በዚህች አለም አታገኝምና። በማእበል ውስጥ ማልቀስ በዝናብ ጊዜ መደነስ ትችላለህ። #ሁለተኛ ፍቅር ማለት ትክክለኛውን ሰው ማግኘት ነው ብለህ አትመን በእውነታው ፍቅር ማለት ትክክለኛ ሰው መሆን ነው። ህይወትን ሙሉ አብረኸው ልትሆነው የምትችለው ሰው ለመፈለግ ወዴትም አትሂድ። ይልቁንስ ህይወትህን ሙሉ አብረኸው የምትሆነው ያንን ሰው ራስህ ሁን። በህይወት የሚገቡህ ሰዎች በተፈጥሮ ስብከት ወደፊት ወዳንተ የሚመጡ ናቸው። #ሶስተኛ ሰዎችን ሁሉ አስደስታለሁ ብለህ አትመን አይገርምህም… ይህን ማድረግ ማንም አይችልም፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን በሁሉም ሰው ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም፡፡ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት መድከሙን ትተህ በታማኝነትና በመርህ ተንቀሳቀስ፡፡ እነሱን ለማስደሰት የምታደርገው ጥረት ከማንነትህ ያወጣሃል፤ መወደድ እንዳለው ሁሉ አለመወደድም ይኖራልና ተቀበለው! @tesfamichaelAsefa

#ቃላቶችህ_ገዳይ_አይሁኑ! ስለ ጓደኛዬ ናስር ልንገራችሁ። አባቱን እጅግ ይወደው ነበር፤ ሁሌም ያስበዋል፣ አባቱን ደስተኛ ለማድረግ ሁሌም ለትጋት የተሰጠ ነው። ነገር ግን የናስር አባት በቀላሉ ነገሮች የሚስቡት እና የሚያስደስቱት አይነት ሰው አልነበረም። ለብዙ አመታት የናስር ጥረት በአባቱ ፊት ምንም ነበር። የመጀመሪያ አመት የኮሌጅ ተማሪ እያለ፤ ናስር 'ስትሬት ኤ' አመጣ እናም ለራሱ ይሄን አለ ''ይሄ ነው! በመጨረሻም አባቴን በትክክል የማኮራበት ጊዜ ደረሰ..'' እናም ስልኩን አንስቶ ደወለ -ለአባቱ። ''አባቴ'' ድምጹ ላይ የማስደነቅ ደስታ እየተሰማበት ''አባቴ 'ስትሬት ኤ' አግኝቻለሁ። አሁን በኔ ኩራት ተሰማህ??" አባትዬውም ''እሺ ልጄ... መልሼ እደውልልሃለው። ስራ ላይ ነኝ '' በማለት ስልኩን ይዘጋል። ስራ ላይ ነኝ! ይሄ አንድ አረፍተ ነገር ይጎዳል። ከዚህ ጊዜ በኋላ ነበር ጓደኛዬ ናስር መጠጣት፣ ማጨስ፣ ስሜት ማጣት የጀመረው። ከዚያች ቀን ጀምሮ ነበር ከማይሆኑ ሰዎች ጋር ግንኙነት የጀመረው። ናስር ይሄን ለምን ያደረገ ይመስልሃል?? ለምን ህይወቱን ወደማይረባው ነገር ጣለ? ናስር እየጠጣ በስካር ሆኖ፤ ይህን ተናግሮ ነበር... ''በዚህች ምድር እጅግ አብልጬ የምወደውና የማስብለት ሰው፣ ስለ እኔ ምንም ግድ የማይሰጠው ከሆነ፣ ህይወት ለምን ይገደኛል??'' ...... አንድ ቀን ስልክ ተደወለልኝ፤ ጓደኛዬ -ናስር ''ኢመርጀንሲ'' ክፍል ውስጥ ገብቶ ራሱን ስቶ የሞት አፋፍ ላይ ደርሷል...ምክንያቱ ደግሞ ከሚችለው በላይ አደንዛ እጽ፣ እንዲሁም መጠጥ መውሰዱ ነበር፡፡ ስደርስ ናስር ስጋው እንጂ ነፍሱ አልነበረችም። ☑️ አየህ ቃላቶች የሚፈጥሩት አረፍተነገር ጥንቃቄ እንደሚጠይቅ። ምላስ በአእምሮ ቁጥጥር ውስጥ ካልሆነ መረዳት እንደማችል -አየህ? ናስር የአባቱን አድናቆት ብቻ ነበር የፈለገው። አባቱ ግን የልጁን ስሜት አልተረዳም። ስድብ-ማ ፣ ሰውን ዝቅ አድርጎ መናገርማ፣ አይ አይሆንልህም ማለትማ ምን ያህል ይገድል?? ቃላትህን ለመግደል ሳይሆን ለማዳን ተጠቀምባቸው፡፡ @tesfamichaelAsefa

ስኬት መጨረሻ የለዉም፤ ውድቀትም መጨረሻ የለዉም። 12ኛ አለፍክ ማለት ስኬትን ተቆናጨፍክ ማለት አይደለም፤ 12ኛ ክፍል ወደቅክ ማለት ደግሞ ያንተ ህይወት እዚህ ጋር አበቃለት ማለት አይደለም።         መልካም እድል ተፈታኞች❤ @tesfamichaelAsefa

በእምነት የዘራሀውን በመጠራጠር አትንቀለው¡ እምነት 🔑
በእምነት የዘራሀውን በመጠራጠር አትንቀለው¡ እምነት 🔑

🎆 Happy New Year, everyone! 🎉✨ As the clock strikes midnight and we bid farewell to the old year, let's welcome the new one
🎆 Happy New Year, everyone! 🎉✨ As the clock strikes midnight and we bid farewell to the old year, let's welcome the new one with open arms and hopeful hearts. May this coming year bring you an abundance of joy, love, prosperity, and fulfillment in all areas of your life. 🌟✨ Cheers to new beginnings, exciting adventures, and endless possibilities! Let's make 2016 the best year yet!

በጨዋታ መሃል ፦ <<በራስህ አትተማመንም አይደል>> አለቺኝ ? እንዴት ልበ ሙሉነት የተጠናወተኝ ሰው እንደሆንኩ ከራሴ ጋ እየተሻማው አወራሁ... አብራራሁ... ዘበዘብኩ በእርጋታ ከሰማቺኝ በኃላ <<እንዴት እንደዚህ አልሽ ብትለኝ እና ያስተዋልኩትን ብነግርህ  አይሻልም?>> አለቺኝ <<ቀጥይ>> አልኳት ደስ ባላለው ፊት እያየኃት <<ስላለህ፣ ስላስደመምከው  ፣ስላደረከው ነገር ብዙ ሰአት ሁል ግዜ ታብራራልህ ።  የተጣላኸውን የጠላኸውን ያናደደህን  ሰው ስህተት እና ያንተን ቅድስና ታስረዳለህ ፣ ሰው ሾለልሹ ሲያወራህ ቀጥለህ እኔ.. እኔም.. ብለህ ሾለ ልሾ ታወራለህ ምንም ነገር ስትሰማ ከራስህ ጋ እያወዳደርክ ነው መሰለኝ ። ሰው ሲቃወምክ ስለምታወራው ነገር ሳይስማማ ሲቀር ቅር ይልሃል... ብዙ ታብራራለህ ። ያመንከው እና የሆንከውን እንዲመሰከርልህ እንዲጨበጨብልህ ጉንጭህ እስኪዝል ታስረዳለህ  ። ስላደረከው እና ስለሆንከው ነገር አስተያየት ትጠይቃለህ ደስታህ የሰው አስተያየት ላይ ተንጠልጥሎል። እምቢ ማለት ይከብደሃል ። እምቢ ከማለት መዋሸት ትመርጣለህ ። ባላሳቀህ ነገር ትስቃለህ ፣ የአዲስ ሰው ቀልብ ለመሳብ እሱ የሚወደውን ነገር ለማውራት ለመሆኑ ጥረት ስታደርግ ብዙ ግዜ ያስተዋልኩ ይመስለኛል ። ሰው እንዳይቀየም ስትል መጠየቅ ያለብህን አጠይቅም ። ያበደርከውን ብደር እንኳን ስትጠይቅ ችግር እንዳጋጠመክ አብራርተህ ነው ። ራስህን አታከብርም መሰለኝ እራስን አለማክበር  አንደኛው  በራስ ያለመተማመን ውጤት ነው !! ከጠላት ሁሉ ጠላት  የሚከፋው የውስጥ ጠላት ነው ። ከራስህ ጋ የታረክ  ግዜ አለም ቢጣላህ እንኳን አትሸበርም ። ስታወራ ረጋ ብለህ  ተናገር ! ለመወደድ ስቃይ አትብላ ! ሰው አክብር  እንጂ አክብደህ አትይ ! ሁሉንም እቅድህን ለሁሉም አታውራ! የተሰማህን ሁሉ አትናገር ! እምቢ አልችልም ማለት ልመድ ! ስለተሳካልህ ነገር ሂደት በየሜዳው አታብራራ ! ያልተቀበልከው ማንነት ካለ የበታችነት ስሜት የሚያሰማህ ሁነት ካለ ረጋ ብለህ አጥናውና መላ ፈልግለት ። ብቻህንም መሆን ልመድ ሁሌ አብሮ ሰው እንዲሆን አታስስ ዝም ብዬ አየኋት ። ልክ ካልሆንኩ፣ ያልኩት እውነት ከሌለው እንደቀባጠርኩ ከተሰማህ አፉ በለኝ ካወራውት ፍሬ ነገር ካገኘህበት ደሞ ደግ >> አሁንም ዝም አልኳት ።  ዝምታዬ ውስጥ ግን መደነቅ እና ድብርት  ነበረበት        Adhanom Mitiku @tesfamichaelAsefa

If you just focus on yourself and you don't care about anyone else, that's selfish. If you only focus on other people and not yourself, that's self-sabotage. But if you work on yourself, if you take care of your health, your mental health, your finances, in order to be more and give more to others that's the balance you want. Have a nice evening y'all❤️🙌