en
Feedback
SOZO YOUTH

SOZO YOUTH

Open in Telegram

Helping young Christians pursue purity, purpose, relationships, and spiritual maturity. » YOUTUBE https://www.youtube.com/@sozopodcast » TIKTOK https://www.tiktok.com/@s.o.z.o For comment: @inbox_sozo P.O.BOX 387 /1033 ADDIS ABABA

Show more
5 794
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive

እግዚአብሔር ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ይሆን?
እግዚአብሔር ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ይሆን?

እነዚህን ቅደም ተከተሎች እናስተውል!! ላጤነት 👇 እጮኝነት 👇 ትዳር 👇 ሩካቤ ስጋ(sex) ••• ትክክለኛው የክርስቲያን አካሔድ ይህን ቅደም ተከተል ፈፅሞ ባያዛባ መልካም ነው:: YOUTUBE | TIKTOKsʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ [ https://t.me/sozo_purity ]

. ማስተርቤሽንና ሴክስ? | SOZO VIEW | 🎙 Podcast | ፓስተር ቸሬ 🎙 YOUTUBE | TIKTOK ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ [ https://t.me/sozo_purity ]

ስለ ሴክስ መወራት አለበት ወይ? | SOZO VIEW | 🎙 Podcast | ፓስተር ቸሬ 🎙 YOUTUBE | TIKTOK ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ [ https://t.me/sozo_purity ]

ሴክስ ምንድነው? | SOZO VIEW 🎙 Podcast | ፓስተር ቸሬ 🎙 YOUTUBE | TIKTOK ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ [ https://t.me/sozo_purity ]

••• የተወደድሽ እህቴ [ ለፀሎት በጉልበቶቹ ያልተንበረከከ ወንድ ለጋብቻሽ ቀለበት እንዲንበረከክ ፈፅሞ አትፍቀጂ ] ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
••• የተወደድሽ እህቴ [ ለፀሎት በጉልበቶቹ ያልተንበረከከ ወንድ ለጋብቻሽ ቀለበት እንዲንበረከክ ፈፅሞ አትፍቀጂ ] ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

ከወጣቱ ፓስተር ጋር ፍቅር ያዘኝ " በቅርቡ በራሴ ላይ ባስተዋልኩት ነገር በጣም እየተረበሽኩኝ ነው:: ከቤተ-ክርስቲያናችን ፓስተር ጋር ፍቅር እንደያዘኝ እየተሰማኝ ነው:: ጤነኛ እንዳልሆንኩ ይታወቀኛል ምክንያቱም ይህ የምላችሁ ሰው ያገባና የሁለት ልጆች አባት ነው:: በዚህ ምክንያት ቸርቻችን እንድለቅ ብዙ ጊዜ ተነግሮኛል ነገር ግን አልቻልኩም:: የበለጠ ጤንነኛ መሆኔን እንድጠራጠር ያደረገኝ ካገባ ሰው ጋር ፍቅር ሲይዘኝ ይህ ሶስተኛ ጊዜዬ መሆኑ ነው:: ካለሁበት ቤ/ክ ግን ለቅቄ መሔድ አልፈልግም:: ከዛ ሳልወጣ የምስተካከልበት መንገድ ካለ እባካችሁ!! ምን ላድርግ?? " መልስ:- ••• በመጀመርያ ፓስተሩን ራቂ:: በምንም ሁኔታ እሱ ወዳለበት አከባቢ አትቅረቢ:: ምክንያቱም እሱ አሁን የሌላ ሰው ነው መቼም የአንቺ ሊሆን አይችልም:: ምክንያቱም የራሱን ህይወት መስርቷልና:: የራሱን ህይወት ባይመሰርት እንኳን በቤ/ክ ውስጥ በወጣቶች መሪ : አገልጋዮች እና በምዕመናን መካከል ያለ ቅርርብ ገደብ ያለው መሆን አለበት:: ብዙ ጊዜ የወጣቶች ህብረት መሪዎች እና አገልጋዮች መልካም የሚባልና በፍቅር አይን እንድናይ የሚያደርግ ስብዕና ስላላቸው ይህ ስሜት ቢሰማን አይገርመኝም:: ስለዚህ በተለይ አሁን ባለሽበት ሁኔታ ውስጥ በጊዜ መስመር ማበጀት ይኖርብሻል:: ያለበለዝያ ይበልጥ ራስሽን ልትጎጂ ትችያለሽ። ሴት ወጣት መሪዎች ያሉበት ቤ/ክ መካፈል ትችይ ይሆናል ነገር ይህ ሁኔታዎችን ያስተካክላል ብሎ ማሰቡ ከባድ ነው:: እንዳልሽኝ ይህ ሶስተኛ ዙርሽ ነው:: አሁን በቶሎ ማድረግ ያለብሽ በዙርያሽ ክርስቲያን አማካሪዎች(counciler) አግኝተሽ አናግሪያቸው:: ከምንም በላይ ደግሞ አብዝተሽ ፀልይ:: ጌታ በነገር ሁሉ ይርዳሽ!! YOUTUBE | TIKTOK ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

••• የህይወቴ አጋር ብለክ ለመረጥካት ሴት ታማኝ እና ፍፁም አክባሪ ሁን!! ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
••• የህይወቴ አጋር ብለክ ለመረጥካት ሴት ታማኝ እና ፍፁም አክባሪ ሁን!! ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

መደፈርና ይቅርታ | Sozo View 🎙 Podcast | Tamrat Tariku 🎙 YOUTUBE | TIKTOK ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

መደፈርና ይቅርታ

በራቁትነት አለም የተራቆተ ትውልድ ••• የዚህች አለም ነገር እጅጉን ይገርማል። ይህች እርቃኗን የቀረች አለም እድሜ ለስልጡን ነን ላሉ ሀገራት እርቃን ሆነው ራቁቷን አስቀሯት። እኔ የገረመኝ ግን ስልጡን ባዮች በጮሁ ቁጥር አለም ሁሉ ያለማስተዋል አብሮ ሲጮህ መኖሩ ነው። ሀብታም ሲናገር ደሃ ያለ ውስጣዊ ፍላጎቱ ሲያጨበጭብ እንመለከታለን። ያለው ካመጣ የሌለው ሳያማርጥ ከነግሳንግሱ ሲቀበል እናስተውላለን። ዛሬ ዛሬ እርቃንነት የአለማችን ታላቁ ስልጣኔ እየሆነ መጥቷል። መጥቀናል አድገናል ሰልጥነናል(ሰይጥነናል) ባዮች የአለም መሪ ሀገራት በተለይ ለሴቶች ከእግር በላይ ልብስን ከፍ ማድረግንን እና መገላለጥን የዘመናዊነት መለኪያው ካደረጉ ሰነበቱ። ዳሌን እና ባትን እንዲሁም ከፍ ካለ ሀፍረተ ስጋን ማሳየት የበለጠና የተሻለ ስልጣኔ እንደሆነ ከመከሩ ቆዩ። ሙሉ መልበስ ሙድ የለውም አይን አይገባም ብለው አጣጣሉ። ወደ እግር ዝቅ ያለ ልብስ የተሸፋፈነ ገላ የኋላ ቀርነት ምልክት ነው ከጊዜው ጋር ለመራመድ ልብስን ከላይም ዝቅ ከታችም ከፍ አስፈላጊ እየሆነ መጥቷል። (ወይ ጉድ ጊዜም ሴሰኛ ዝሙተኛ ሆነ እንዴ?) ••• በጥባጭ ካለ ማን ጥሩ ይጠጣል እንዲሉ ሰልጥነናል የሚሉ ምእራባዊያን ለሰው ልጅ ጥሩ ስብእናና የባህርይ ምጥቀት አዋጩን መንገድ መርጦ ከመከተል ይልቅ የአጥፍቶ መጥፋት ዘመቻቸውን በማጋጋል ርካሽ ባህሎቻቸውን ልቅ ስነምግባሮቻቸውን ለአለም ለማዳረስ ቅርጠው ተነስተዋል። (ቆዩ እኮ እየተሳካላቸውም ነው) ፈጥኖ የገባው ሲቀር የተጃጃለው የራሱን ምርጥ እምነት ባህልና አምላክ የወደደ እሴት ትቶ የነ ስልጡን ሰይጣናዊ እሴት ያለማገራገር ተቀብሏል። እየተቀበለም ነው። (እስኪ ኢንተርኔት ቤት ጎራ ይበሉ ለአቅመ ዝሙት ያልደረሰን ታዳጊ የከፈተውን የድህረገፅ አይነት ይመልከቱ) በሌላ ቅንፍ(እስኪ ወደ ትልቅ ትምህርት ተቋማት ይግቡና እድሉን ካገኙ ሞባይላቸው ላይ የተጫኑ ፊልሞችና ዘፈኖች ይመልከቱ። ተማሪዎቻችንም ይመልከቱ ሞባይል ላይ ካለው ልቅ ስነምግባር ጋር ልዩነቱ የጠበበ ነው)። ••• የእርቃንነት ጉዳይ በዋናነኛነት ዛሬ በአለም ላይ እጅጉን አሳሳቢ ከሆኑት ነገሮች መካከል ይጠቀሳል። በውበት ስም(የሴት ልጅ ውበትን ማድነቅ የጤንነት ምልክት ነው የምትለዋን መርዘኛ አባባልን የፈጠረ ምን ያህል ሊቅ ነው። ራቁት ገላን በአደባባይ ማሳየት በተለይ በወጣትነት የአፍላ(የእሳት) ስሜት ላይ ቤንዚን የማርከፍከፍ ያክል ፈታኝ ከሆኑት መካከል አንዱ ነው። ••• ስልጡን እናት ለልጇ የምትገዛላትን ልብስ ሄዳችሁ ተመልከቱማ... ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ♻️ https://t.me/sozo_purity ♻️ ♻️ tiktok.com/@s.o.z.o ♻️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

ምን አይነት ወንድ ለመሆን ታስባለክ? ••• እግዜአብሔር ለአብርሀም የወደፊት ህይወቱን በተለያየ መንገድ ሲገልፅለትና ሲያሳየው ነበር:: ከምንም በላይ አብርሀም ሁሉን ነገር ትቶ እግዜአብሔር ወደተናገረው ስፍራ ጨርቄን ማቄን ሳይል ወቷል:: ወደፊት ምን አይነት አባት መሆን ትፈልጋለህ? ••• እግዜአብሔር በህይወትህ ይሆናል የሚልህ ነገር ልክ እንደ አብርሀም ቢዘገይብህ ምን አይነት አባት የምትሆን ይመስልሀል? ••• አብርሀም ከአምላኩ ጋር እለት እለት ይነጋገር እና ይፀልይ ነበር:: በዚህ ፀሎት ስፍራው ከእግዜአብሔር ጋር የማይቋረጥ ህብረት ያደርግ ነበር:: ከእግዜአብሔር ብዙ ትዕዛዝ ተቀብሏል:: እግዜአብሔር የሚስቱን ስም የአብርሀምን ስም ቀይሯል በአጠቃላይ ቤተሰቡን ከመሀንነት እና ፍሬ ከሌለው ማንነት አንስቶ ለብዙዎች አባትና ፍሬያማ አድርጓቸዋል:: ወደፊት ምን አይነት አባት መሆን ትፈልጋለህ? ••• ይስሀቅም እንደ አባቱ አብርሀም የፀሎት ህይወት ነበረው:: እለት እለት ከእግዜአብሔር ትዕዛዝን ይቀበል ነበር:: በዛ የፀሎት ስፍራ አምላክ ይስሀቅን እና ቤተሰቡን ጎብኝቷል:: ••• ይስሀቅ ታጋሽ ነበር:: ልጅ ለመውለድ ዘግይታ ለነበረችው ሚስቱ ከምንም በላይ ክብርና ትልቅ ፍቅር ነበረው:: አንዳች መጥፎ ነገር አልተናገራትም:: ከሌላ ሰው እንድትወልድ አልመከራትም:: አላንቋሸሻትም:: አልፈታትም:: ወደ ሌላ ሴት አልሔደም:: ነገር ግን በእግዜአብሔር ቃል ላይ ታምኖ በፅናት ይጠብቅ ነበር:: እግዜአብሔር የሰጣችሁ ተስፋ ሲዘገይ ምን ታደርጋላችሁ? ••• ይስሀቅ አብዝቶ ወደ እግዜአብሔር ይቀርብ ነበር:: በፀሎት የበረታ ሰው በሸለቆም ይሁን በተራራ በእግዜአብሔር ታምኖ ይፀናል:: ዋናው ጥያቄ ወደፊት አባት እንደሚሆን ወንድ አሁን ላይ ምን ማድረግ አለባችሁ? ••• በፀሎት ህይወቷ ትጉ የሆነች ሚስት ከመጠበቃችሁ በፊት የምትመኙትን የፀሎት ህይወት ራሳችሁ ልመዱት:: በግል ህይወታችሁ ከአምላክ ጋር ያላችሁ ህብረት ካልጠነከረ የወደፊት የቤተሰባችሁ ህልውና አደጋ ላይ ነውና:: ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ♻️ https://t.me/sozo_purity ♻️ ♻️ tiktok.com/@s.o.z.o ♻️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

በአዕምሮ እንጂ በኪስ ማሰብ ከንቱ ነው ••• በአእምሮው የሚያስብ ወንድ ልጅ ጥቂት ነው ። አብዛኛው የሚያስበው በኪሱ ነው ። በራሱ የማይተማመን ወንድ በገንዘብ ለመግዛት ስለሚያስብ ሌባ ይሆናል ። በሌብነት የመጣ ኑሮም ሚስትን በሽተኛ ፣ ልጆችን ዓመፀኛ ያደርጋል ። ወንድ ልጅ ለትዳሩ የሚያስፈልገው ዋና ነገር የመጀመሪያው ፍቅር ፤ ሁለተኛው፡- ማዳመጥ ፤ ሦስተኛው፡- በጋራ መወሰን ነው ። ፍቅር ለማዳመጥና በጋራ ለመወሰን አስፈላጊ ነው ። ምክንያቱም ፍቅር የሚወደውን ሰው ይሰማልና ፤ ዳግመኛም ከእኔ የተሻለ አሳብ አለው ብሎ ስለሚያከብር በጋራ ይወስናል ። ብዙ ወንድ ልጆች የእኔ የሚሉትን ሰው በስስት ስለሚይዙ የዚያን ሰው ትንሽ ችግር መሸከም አይችሉም ። ማንኛውንም ወጪ አውጥተው ችግሩን ለመቅረፍ ያስባሉ ። ስለዚህ የማዳመጥ አቅም ያንሳቸዋል። ወንዶች ነፍሰ ገዳይ የሚሆኑት ብዙ ጊዜ ረጅም ሰዓት የማሳመንና የመታገሥ አቅም ስለሚያጡ ነው ። ሚስትህ ግን ከሁሉም በላይ መደመጥ ትፈልጋለች ። አንተ ርእስ ብቻ ተናግረህ ዝም ትላለህ ፣ እርሷ ግን ዝርዝሩን ተናግራ ማስረዳትና መታመን ትፈልጋለች ። ስለዚህ ማዳመጥ ይገባሃል ። ብዙ ዱርዬ ወንዶች ሴቶችን በጆሮ ያዳምጣሉ ፣ በውሸት ያሞግሳሉ ፣ ያጫውታሉ ። ብዙ የዋህ ሴቶች የሚታለሉት እውነተኛ ወዳጆቻቸው እነዚህ ስለሚመስሉአቸው ነው ። በትዳር አጠገብ የሚያደቡ ጨካኞች አሉና ተጠንቀቅ ። ••• ሚስትህ ከእጮኝነት ጊዜ ወደ ትዳር ስትገባ የመፈለግ ጊዜዋ ያቆመ ይመስላታል ። ስለዚህ ራሷን ትጥላለች ። አንተ ግን እንደ ቀድሞ ራሷን እንድትጠብቅና በእጮኝነት ጊዜያችሁ ወደምትዝናኑበት መልካም ቦታ ይዘሃት የመሄድ ልምድ ሊኖርህ ይገባል ። ስትወልድም ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ትገባለች ። በአገራችን አራስን አትለዩ የሚባለው ለዚህ ነው ። ስትወልድ የጥፋተኝነት ስሜት ፣ በጣም ስጉነትና ልጇን የማጣት ፍርሃት ይከባታል ። በዚህ ወቅትም አለመለየት በጣም ወሳኝ ነው ። በአጠቃላይ ትዳር የሚጸናው ጊዜ በመስጠት ነው ። አሊያ ፎቁን ሠርተህ ስትጨርስ ቤትህ ሊፈርስ ይችላል ። ✍አዶኒ ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ♻️ https://t.me/sozo_purity ♻️ ♻️ tiktok.com/@s.o.z.o ♻️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

ራስን መለወጥ ማሻሻል ••• ራስን መለወጥ ማሻሻል ማለት ባሉበት ሳይረኩ ከዛሬ ሁኔታ የተሻለ ነገር ውስጥ ለመግባት አስፈላጊውን ነገር ማድረግ ማለት ነው፡፡ የተግባር ጥራትና ውጤት ስለተመኘሁት ብቻ አይመጣም፡፡ በሌላ አባባል የእኔ መሻሻል በቀጥታ ከተግባሬና ከኑሮዬ መሻሻል ጋር ግንኙነት አለው፡፡ ብዙ ሰዎች ኑሮአቸው፣ የገቢ ምንጫቸውና የመሳሰሉት ነገሮች እንዲሻሻሉ ይመኛሉ፣ ራሳቸውን ስለማሻሻል ግን አስበውበትም አያውቁም፡፡ አእምሮዬ እንዲሻሸል ማንበብ የግድ ነው፡፡ የገቢ ምንጬ እንዲሻሻል እውቀቴንና ብቃቴን ማሻሻል የግድ ነው፡፡ የእኔነቴና የብቃቴ መሻሻል ዙሪያዬን ሁሉ የመለወጥና ነገሮችን ለመልካም የመለወጥ ብርታትና ተጽእኖ አለው፡፡ ራስን በማሻሻል የተግባር ስኬት ውስጥ ለመግባት መጠየቅ የምትችላቸው ጥያቄዎች፡- 1. ማድረግ የምፈልገውንና የሚሳካልኝን አውቄ መተግበር ጀምሬአለሁ? ••• ማድረግ የሚሳካልህን ነገር ለይተህ እወቀውና በዚያ ዙሪያ መገንባትን ጀምር፡፡ የማይሳካልህ ላይ ከማተኮርና ከመድከም ይልቅ የሚሳካልህ ላይ በማተኮር መገንባት የበለጠ ውጤታማ ያደርግሃል፡፡ 2. ይህንን ተግባር ማደግ የሚገባው ደረጃ ድረስ አሳድጌዋለሁ? ••• የሚሳካልህንና የምትፈልገውን ለይተህ መተግበር ከጀመርክ በኋላ ትኩረትህን ያንን ተግባር ወደ ማሳደግ ማዞር አለብህ፡፡ በቅጡ ካላዳበርካቸው ጥቃቅን ችሎታዎች ጋር ከምትታገል በአንድ ነገር በሚገባ መብሰል ውጤቱ የላቀ ነው፡፡ 3. ለእርማት ልቦናዬ ክፍት ነው? ••• “አውቃለሁ፣ ማንም ሊመክረኝና ሊያርመኝ አይችልም” የሚል አመለካከት ያለው ሰው ራሱን ለኋላ ቀርነት በማጨት ላይ ያለ ሰው ነው፡፡ እኛ ያላየነውን የሚያዩ ሰዎች በዙሪያችን እንዳሉ በማመን ራሳችንን ለእርማት መክፈት ጠቃሚ ነው ፡፡ ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ♻️ https://t.me/sozo_purity ♻️ ♻️ tiktok.com/@s.o.z.o ♻️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

. | Fact | √ BBFC ባወጣው ጥናት መሰረት በአሜሪካ 75% የሚሆኑ ወላጆች "ልጆቻችን ፖርኖግራፊ አይተው አያውቁም" ብለው ያምናሉ ነገር ግን በጥናቱ መሰረት ከነዚህ ወላጆች ልጆች 53% የሚሆኑት የፖርኖግራፊ ሱሰኞች ሆነው ተገኝተዋል። [ ጥናቱ የተደረገው በአሜሪካ ቢሆንም በአለም ላይ ልቅ የሆኑ ወሲባዊ ቪዲዮዎች በኢንተርኔት ሰርች በማድረግ ቁንጮ ላይ በምትገኘው ኢትዮጵያም እውነታው ይሰራል ተብሎ ይታመናል። ] √ ይህን ስነግራችሁ በዚህ ሱስ የታሰራችሁትን ጎበዝ በርቱ ለማለት አይደለም። ነገር ግን ብዙ ልማዶች ኖርማል በሆኑበት በዚህ ጊዜ ከመንጋው ተገንጥሎ እውነትን መከተል ነገ ላይ የሚሰጠንን ሰላም እንድታጣጥሙ እንጂ። √ በመንፋሳዊ ህይወት ትልቅ ቦታ የምትሰጠው ሰው ድንገት ስልኩን ስትበረብር የማይሆን ምስሎችን አየህ ማለት አንተም እሱ በሔደበት ርካሽ ጎዳና ተጓዝ ማለት አይደለም። [ በጌታ ቤት አገልጋይ በሆኑ ሰዎች ስልክና ላፕቶፕ ያልጠበኩትን ነገር ብዙ ጊዜ አጊኝቼ አውቃለው። ወደፊት በሰፊው በዚህ ርዕስ እመለስ ይሆናል።] √ ርካሽ ነገር የትም ይገኛል። በየቦታው ተገኘ ማለት ግን ዝምብለን ማግበስበስ አለብን ማለት አይደለም። አሁን አሁን ርኩሰት በየማህበራዊ ሚዲያው ከመብዛቱ በላይ ለብሶት እንደ ጀብድ የሚያጌጥበት ትውልድ ከመትረፍረፉ የተነሳ ትልቁን ልብሳችንን[ ክርስቶስን ] ረስተናል። √ ምን ያክል ወቅሽያችሁ ወይም አናድጅያችሁ እንደሆን ባላውቅም ግን ሁላችንንም የሚያስታርቅ አንድ እውነት አለ እርሱም መመለስ ነው። ••• ወደ ውዳችን እቅፍ እንመለስ ••• ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ♻️ https://t.me/sozo_purity ♻️ ♻️ tiktok.com/@s.o.z.o ♻️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

. | የኔ ✍ ኑዛዜ | የቀጠለ. . . ለውስጤ ጥያቄ መልስ ነው ያልኩት አማራጭ የጥፋት ጎዳናዬ ሆነ። መጥፎ እድሌ መቋቋም እስኪሳነኝ አንገላታኝ። በወሬ የምሰማውን አስነዋሪ ቪዲዮ አሁን አዲስ ባፈራኋቸው ጓደኞቼ ስልክ መመልከት ጀመርኩ። ድንገት አመለካከቴ ሲለወጥ ይታወቀኝ ነበር። ሴቶችን የማይበት መንገድ ፈጣሪን የሚያስከብር አልነበረም። ወንድ ሆኜ መፈጠሬን እስክጠላ ፈጣሪን አሳዝን ነበር። መፅሐፍ ቅዱስ በሮሜ መለእክት 1፡28 ላይ "እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው" ይላል። ይህን ክፍል ሳጠና ሁሌም የማስበው ጌታን ባለማወቅ እርሱን ባለመፈለግ ከህልውናው ውጪ የተንከራተትኩበትን ዘመን ነው። በቃ ሳላስበው የገባሁበት ነገር ውስጥ ለመላቀቅ ቀላል ጊዜ አልፈጀብኝም። እነዛን አስነዋሪ ነገሮች በ 1 ብር ስፖርት ቤት ገብቶ ከማየት ከዛም በጓደኞቼ ስልክ ከማየት አልፎ የተወሰነ ግሩፕ ፈጥረን ሲዲ እየተከራየን መመልከት ጀመርን። ትዝ የሚለኝ ሁሌም ከክላስ መልስ አንዱ ጓደኛዬ ቤት ሳናቋርጥ ሳምንቱን ሙሉ ለ 3 ሆነን እናይ ነበር። ያ ሁሉ ነገር በህይወቴ ያመጣው ነገር ቢኖር ከፈጠረኝ አምላክ መራቅ እና የቆሸሸ ማንነት ይዞ መኖር ነበር። ፈጣሪ ማን እንደሆነ መጠራጠር እና የማይጠቅም ፍልስፍና ውስጥ መግባት ነበር። ሰይጣን ይሄን ሁሉ ያደረገብኝ በአንድ ቀን አልነበረም። ሳምሶንን ከተጠራበት አላማ ቀስ በቀስ አንሸራትቶ እንደጣለ መልካም በሚመስሉ ነገሮች ልንኖር ከተጠራንበት ክልል ውጪ ያደርገናል። ምናልባት ይሄን ነገር ማድረግ ኖርማል የሆነባቸው ባለማወቅ እንዲሁም እያወቁ እቅም በማጣት ግራ በመጋባት ውስጥ ያሉ እህትና ወንድም ሊኖሩ ይችላሉ። መፍትሔው አንድ እና አንድ ነው። እርሱም ስለ እኛ ከኛ በላይ ለሚያስብልን ፈጣሪ እራሳችንን አሳልፈን መስጠት ነው። አዎ ያኔ ሃይል ከላይ ከአሪያም ይመጣልናል። ለእኔ ከዚ ነገር መፈታት ፀሎት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። እኔ እራሴ እስክደነቅ አምላክ በህይወቴ ላይ መልካምነቱን ያለገደብ ገለጠልኝ። ባልታወቀ ሁኔታ በራሴ ላይ ለውጥ መመልከት ጀመርኩ። ከዛ በፊት ግን አምላክ መጀመርያ ያደረገው እየተጓዝኩበት ያለሁት ጎዳና ትክክል እንዳልነበረ ነው። ያን ሁሉ ሳደርግ ድርጊቴ ትክክል እና ለውስጤ ጥያቄ መልስ ይመስለኝ ነበር። ድንገት በአንድ መድረክ ላይ የህሊና ሃጢያት በሚል ርእስ መንፈስ ቅዱስ አነቃኝ ያን ከተረዳው ወዲህ ለማምናቸው ሰዎች ያለሁበትን ሁኔታ ሳላሳወቅ ግን እንዲፀልዩልኝ ብቻ በመጠየቅ ቃሉን ማንበብና እራሴን በመልካም ነገር መወጠር ጀመርኩ። ከመዞር ይልቅ ትምህርቴን መማር ቸርች መዋል ምርጫዬ ሆነ። ሁል ጊዜም የጌታን መልካምነትና ምህረት ሳስብ እይኖቼ በእንባ ይሞላሉ። ከእዛ አሳፋሪ ነገር ውስጥ አውጥቶኝ ዛሬም ልጄ ይለኛል። አሁን ላይ ከምንም ጋር ላወዳድረው የማልችለውን ህብረት ሰጥቶኛል:: 1ዮሐንስ 1፡3 ". . .ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው። " ይላል። ዛሬ እራሴን ለማጥፋት ከሮጥኩባቸው መጥፎ ህብረቶች በመልካምነት ክርስቶስን እያየው እንዳድግ መልካም እድል ሰጠኝ። ተባረኩ!! . . .ይሔን መልካም እድል ስላዘጋጃቹልን @sozo_purity ፈጣሪ አብዝቶ ይባርካቹ። ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ♻️ https://t.me/sozo_purity ♻️ ♻️ tiktok.com/@s.o.z.o ♻️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

. | የኔ ✍ ኑዛዜ | የ19 አመት ወጣት ነኝ:: በአንድ ቤ/ክ በኳየር አገለግላለሁ ዛሬ ላጫውታቹ የምወደው በህይወቴ ጥቁር አሻራ ያሳደረብኝን መጥፎ እና ሁሌም ሳስበው በጌታ ፊት ስለማፍርበት ጉዳይ ነው:: ሀፍረቴን አስወግዶ በፊቱ ሞገስ ስላገኘው ታሪኬን ትምህርት እንድትወስዱበት ላወጋቹ ወደድኩ:: ከጥቂት አመታት በፊት ነው:: ክርስትና ምን እንደሆነ በወጉ ያልተረዳው የይስሙላ ፔንጤ ነበርኩ:: ለአቅመ አዳም የደረስኩበት ወቅት ስለነበር ውስጤ በብዙ የማንነት ጥያቄ የተወጠረበት ወቅት ነው:: የአገልጋይ ልጅ ልሁን እንጂ ህይወት ምን እንደሆነች እንዴት በቀና ጎዳና ማስኬድ እንደነበረብኝ ምንም አይነት እውቀት አልነበረኝም:: በክርስቶስ ደም የተገዛችው ነፍሴ በቅድስና እንድመላለስ የተሰጠኝ ማንነቴ እንደ ቀልድ በዙሪያዬ በነበሩ ጓደኞቼ ንግግር መገራት ጀመረ:: ቢላ ቢላን እንደሚስል አንደበታቸው ውሎዬን አስተሳሰቤን መቅረፅ ጀመረ:: ከክፍል ጓደኞቼ ጋር በትምህርት ጊዜ የምናወራቸው ነገሮች በእረፍት ጊዜ የምናደርጋቸው አሳፋሪ ድርጊቶች ውስጤ ለተነሳው የአፍላነት ጥያቄዎች መልስ ነኝ እያሉ ከማንነቴ ጋር መዋሀድ ጀመሩ:: በጊዜው ስለ ክርስትና ስለ ቅድስና ምንም መሰረት ውስጤ ስላልነበረ የጥፋት ማዕበል መረጋጋት እስኪያቅተኝ አናጋኝ በፈለገው አቅጣጫ መመለሴን እስክጠራጠር አርቆ ወሰደኝ:: ማዕበሉ የጀመረው እንደዋዛ መስማት ከጀመርነው ዘፈን ነበር:: በየሳምንቱ የቢልቦርድ ምርጥ 10 ዘፈኖች ከመስማት አልፎ መሸምደድ አዲስ የዳንስ ስታይል ከመጣም እሱን መለማመድ በሳምንቱ የመጀመርያ ቀን በጠዋት ት/ቤት ተገናኝተን የተለማመድነውን ዘፈን እና ዳንስ መመልከት የዘውትር ተግባራችን ነበር:: ይህን ሁሉ ሳደርግ ምንም አይነት ፀፀት አይሰማኝም ነበር ምክንያቱ ደግሞ እንደሚመስለኝ ምንም አይነት እውቀት ስላልነበረኝ ነው:: በየአመቱ አብረውኝ የሚማሩ ጓደኞቼ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ወጣ ያለ ፀባይ ያላቸው ናቸው:: ብዙ ጊዜ መጨረሻ ወንበር ላይ ነው የምቀመጠው:: ከውስጤ የማይጠፋው የምፀፀትበት ጊዜ ከሁለት ሙስሊም ሴቶች ጋር የተቀመጥኩበት የትምህርት ወቅት ነው:: አንደኛዋ በዛ እድሜዋ ከአስተማሪ ጋር የፍቅር ግንኙነት መጀመር እንደሚቻል አሳይታኛለች:: ከባዮሉጂ አስተማሪ ጋር በየቀኑ የምትፃፃፈውን ደብዳቤ ታስነብበኝ ነበር:: ብዙ ጊዜ ደብዳቤ ሲቀባበሉ ስላየዋቸው የምታመጣውን ደብዳቤ ያለጥርጥ እሰማትና አምናት ነበር:: ከዛ ባለፈ በዘፈን እንነጋገር ነበር:: ብዙ ግራ የሚያጋባ ታሪክ ሊሆን ይችላል ግን ይሔ ሁሉ ሲሆን በስም ክርስቲያን ነበርኩ:: ከሴት ተማሪ ጓደኞቼ ሌላ በሚቀፍ ነገር ውስጥ እንዳሳልፍ ያደረጉኝ ጓደኞች ነበሩኝ:: ትዝ ይለኛል ሁል ጊዜ ስለ ሴት የሚያወራ ዮሐንስ የሚባል ጓደኛ እንደነበረኝ:: በሳምንት ውስጥ ት/ቤት ከሚመጣበት ቀን ይልቅ የሚቀርበት ቀን ይበልጣል:: እውነቱን ልንገራቹ ሲቀር ይከፋኝ ነበር:: ለውስጤ ጥያቄ ብዙ ምላሽ የሚሰጠኝ ሁሉ ነገሬ ነው ብዬ አስብ ስለነበር ነው:: አንዳንዴ እቤቱ ድረስ እሔድ ነበር:: ብዙ ጊዜ የሚያወራኝ እንዳልኳችሁ ስለ ተቃራኒ ፆታ ነው:: በወቅቱ እንደዛ አይነት ወሬ እንደመስማት ሌላ ምንም ነገር አያስደስተኝም:: ከዮሐንስ ጋር በነበረን የትምህርት ህይወት ውስጤ በጣም በሚያስጠላ ሁኔታ ተለወጠ:: በአጭሩ ሴት ልጅን በሌላ እይታ እንድመለከት ማድረግ ቻለ:: በጣም ተፈተንኩበት:: ብዙ ነገር እንዳስብ አደረገኝ:: ለመወጣት በሚገብድ ነገር ውስጥ ህይወቴን ከተትኩ:: ለመጀመርያ ጊዜ ስለ ወሲብ የሰማሁትም እንደዛ አይነት ፊልሞች እንዳሉ ያወኩት ከዮሐንስ ነበር:: ወደ ቤቱ መሔድ ባበዛሁበት ወቅት ዮሐንስ ወላጆቹ እንደሌሉ እና ብዙ ጊዜ ቤተሰቡን ለማስተዳደር ውሎው አልፎ አልፎ አዳሩም ውጪ የሆነ ታላቅ ወንድም እንዳለው ነው የተረዳሁት:: ዮሐንስ ብዙ ጊዜ ከት/ቤት ሲቀር የሚውለው ካራቴ ቤት ነው:: ካራቴ ቤት ነው የዋልኩት ብሎ ሲነግረኝ ስፖርት ቤት ይመስለኝ ነበር:: በሁዋላ በሁዋላ ሲገባኝ ዮሐንስ ስፖርት ቤት የሚለኝ 1 ብር እየከፈለ ለአዕምሮ ለነፍስ የማይመች የብልግና ፊልም የሚመለከትበትን ቤት ነበር:: አልደብቃቹም እኔም 2 ቀን ስፖርት ቤት ገብቼ ነበር:: አዲስ ነገር እያወኩትኝ መጣው በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ ሳሳልፍ ቸርች ምን እንደሆነ አላውቅም:: ቤተሰቦቼም ምሳ እየቋጠሩ ት/ቤት ሒድ ከማለት ባለፈ ምን ስታደርግ ዋልክ ብለውኝ አያውቁም ነበር:: እስከዛሬ ድረስ በቤተሰብ ልዩ እንክብካቤ እየተደረገላቸው የእግዚአብሔርን ቃል በማወቅ ያደጉ ልጆችን ሳይ እቀናለሁ:: በእውነት እድለኛ ናቸው:: ልክ እንደ እኔ ባለማወቅ በብዙ ውጣ ውረድ እያሳለፉ ያሉ አፍላ ወጣቶችም አንጀቴን ይበሉኛል:: ዮሐንስ በፀባዩ ምክንያት ከት/ቤት ተባረረ:: ከ 2 አመት በሁዋላ ስፖርት ቤት አከባቢ እየቃመና እያጨሰ አግኝቼው ነበር:: ያኔም ቢሆን በክርስትና ህይወቴ ደካማ ስለነበርኩ ምንም ማድረግ አልቻልኩም:: ከዮሐንስ ወዲህም የገጠሙኝ ጓደኞቼም እጅግ የከፉ ሆኑ::1 ብር እየከፈልኩ የማየው ፊልም በስልክ ወደ እኔ መጣ:: ይቀጥላል. . . ◈sʜᴀʀᴇ◈ ✅|| ይቀላቀሉን ||✅ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ♻️ https://t.me/sozo_purity ♻️ ♻️ tiktok.com/@s.o.z.o ♻️ ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

መስጠት ነው። አዎ ያኔ ሃይል ከላይ ከአሪያም ይመጣልናል። ለእኔ ከዚ ነገር መፈታት ፀሎት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል። እኔ እራሴ እስክደነቅ አምላክ በህይወቴ ላይ መልካምነቱን ያለገደብ ገለጠልኝ። ባልታወቀ ሁኔታ በራሴ ላይ ለውጥ መመልከት ጀመርኩ። ከዛ በፊት ግን አምላክ መጀመርያ ያደረገው እየተጓዝኩበት ያለሁት ጎዳና ትክክል እንዳልነበረ ነው። ያን ሁሉ ሳደርግ ድርጊቴ ትክክል እና ለውስጤ ጥያቄ መልስ ይመስለኝ ነበር። ድንገት በአንድ መድረክ ላይ የህሊና ሃጢያት በሚል ርእስ መንፈስ ቅዱስ አነቃኝ ያን ከተረዳው ወዲህ ለማምናቸው ሰዎች ያለሁበትን ሁኔታ ሳላሳወቅ ግን እንዲፀልዩልኝ ብቻ በመጠየቅ ቃሉን ማንበብና እራሴን በመልካም ነገር መወጠር ጀመርኩ። ከመዞር ይልቅ ትምህርቴን መማር ቸርች መዋል ምርጫዬ ሆነ። ሁል ጊዜም የጌታን መልካምነትና ምህረት ሳስብ እይኖቼ በእንባ ይሞላሉ። ከእዛ አሳፋሪ ነገር ውስጥ አውጥቶኝ ዛሬም ልጄ ይለኛል። አሁን ላይ ከምንም ጋር ላወዳድረው የማልችለውን ህብረት ሰጥቶኛል:: 1ዮሐንስ 1፡3 ". . .ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው። " ይላል። ዛሬ እራሴን ለማጥፋት ከሮጥኩባቸው መጥፎ ህብረቶች በመልካምነት ክርስቶስን እያየው እንዳድግ መልካም እድል ሰጠኝ። ተባረኩ!! . . .ይሔን መልካም እድል ስላዘጋጃቹልን @sozo_purity ፈጣሪ አብዝቶ ይባርካቹ።

. | የኔ ✍ ኑዛዜ | የ19 አመት ወጣት ነኝ::በአንድ ቤ/ክ በኳየር አገለግላለሁ ዛሬ ላጫውታቹ የምወደው በህይወቴ ጥቁር አሻራ ያሳደረብኝን መጥፎ እና ሁሌም ሳስበው በጌታ ፊት ስለማፍርበት ጉዳይ ነው:: ሀፍረቴን አስወግዶ በፊቱ ሞገስ ስላገኘው ታሪኬን ትምህርት እንድትወስዱበት ላወጋቹ ወደድኩ:: ከጥቂት አመታት በፊት ነው:: ክርስትና ምን እንደሆነ በወጉ ያልተረዳው የይስሙላ ፔንጤ ነበርኩ:: ለአቅመ አዳም የደረስኩበት ወቅት ስለነበር ውስጤ በብዙ የማንነት ጥያቄ የተወጠረበት ወቅት ነው:: የአገልጋይ ልጅ ልሁን እንጂ ህይወት ምን እንደሆነች እንዴት በቀና ጎዳና ማስኬድ እንደነበረብኝ ምንም አይነት እውቀት አልነበረኝም:: በክርስቶስ ደም የተገዛችው ነፍሴ በቅድስና እንድመላለስ የተሰጠኝ ማንነቴ እንደ ቀልድ በዙሪያዬ በነበሩ ጓደኞቼ ንግግር መገራት ጀመረ:: ቢላ ቢላን እንደሚስል አንደበታቸው ውሎዬን አስተሳሰቤን መቅረፅ ጀመረ:: ከክፍል ጓደኞቼ ጋር በትምህርት ጊዜ የምናወራቸው ነገሮች በእረፍት ጊዜ የምናደርጋቸው አሳፋሪ ድርጊቶች ውስጤ ለተነሳው የአፍላነት ጥያቄዎች መልስ ነኝ እያሉ ከማንነቴ ጋር መዋሀድ ጀመሩ:: በጊዜው ስለ ክርስትና ስለ ቅድስና ምንም መሰረት ውስጤ ስላልነበረ የጥፋት ማዕበል መረጋጋት እስኪያቅተኝ አናጋኝ በፈለገው አቅጣጫ መመለሴን እስክጠራጠር አርቆ ወሰደኝ:: ማዕበሉ የጀመረው እንደዋዛ መስማት ከጀመርነው ዘፈን ነበር:: በየሳምንቱ የቢልቦርድ ምርጥ 10 ዘፈኖች ከመስማት አልፎ መሸምደድ አዲስ የዳንስ ስታይል ከመጣም እሱን መለማመድ በሳምንቱ የመጀመርያ ቀን በጠዋት ት/ቤት ተገናኝተን የተለማመድነውን ዘፈን እና ዳንስ መመልከት የዘውትር ተግባራችን ነበር:: ይህን ሁሉ ሳደርግ ምንም አይነት ፀፀት አይሰማኝም ነበር ምክንያቱ ደግሞ እንደሚመስለኝ ምንም አይነት እውቀት ስላልነበረኝ ነው:: በየአመቱ አብረውኝ የሚማሩ ጓደኞቼ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ወጣ ያለ ፀባይ ያላቸው ናቸው:: ብዙ ጊዜ መጨረሻ ወንበር ላይ ነው የምቀመጠው:: ከውስጤ የማይጠፋው የምፀፀትበት ጊዜ ከሁለት ሙስሊም ሴቶች ጋር የተቀመጥኩበት የትምህርት ወቅት ነው:: አንደኛዋ በዛ እድሜዋ ከአስተማሪ ጋር የፍቅር ግንኙነት መጀመር እንደሚቻል አሳይታኛለች:: ከባዮሉጂ አስተማሪ ጋር በየቀኑ የምትፃፃፈውን ደብዳቤ ታስነብበኝ ነበር:: ብዙ ጊዜ ደብዳቤ ሲቀባበሉ ስላየዋቸው የምታመጣውን ደብዳቤ ያለጥርጥ እሰማትና አምናት ነበር::ከዛ ባለፈ በዘፈን እንነጋገር ነበር:: ብዙ ግራ የሚያጋባ ታሪክ ሊሆን ይችላል ግን ይሔ ሁሉ ሲሆን በስም ክርስቲያን ነበርኩ:: ከሴት ተማሪ ጓደኞቼ ሌላ በሚቀፍ ነገር ውስጥ እንዳሳልፍ ያደረጉኝ ጓደኞች ነበሩኝ:: ትዝ ይለኛል ሁል ጊዜ ስለ ሴት የሚያወራ ዮሐንስ የሚባል ጓደኛ እንደነበረኝ:: በሳምንት ውስጥ ት/ቤት ከሚመጣበት ቀን ይልቅ የሚቀርበት ቀን ይበልጣል:: እውነቱን ልንገራቹ ሲቀር ይከፋኝ ነበር:: ለውስጤ ጥያቄ ብዙ ምላሽ የሚሰጠኝ ሁሉ ነገሬ ነው ብዬ አስብ ስለነበር ነው:: አንዳንዴ እቤቱ ድረስ እሔድ ነበር:: ብዙ ጊዜ የሚያወራኝ እንዳልኳችሁ ስለ ተቃራኒ ፆታ ነው:: በወቅቱ እንደዛ አይነት ወሬ እንደመስማት ሌላ ምንም ነገር አያስደስተኝም:: ከዮሐንስ ጋር በነበረን የትምህርት ህይወት ውስጤ በጣም በሚያስጠላ ሁኔታ ተለወጠ:: በአጭሩ ሴት ልጅን በሌላ እይታ እንድመለከት ማድረግ ቻለ:: በጣም ተፈተንኩበት:: ብዙ ነገር እንዳስብ አደረገኝ:: ለመወጣት በሚገብድ ነገር ውስጥ ህይወቴን ከተትኩ:: ለመጀመርያ ጊዜ ስለ ወሲብ የሰማሁትም እንደዛ አይነት ፊልሞች እንዳሉ ያወኩት ከዮሐንስ ነበር:: ወደ ቤቱ መሔድ ባበዛሁበት ወቅት ዮሐንስ ወላጆቹ እንደሌሉ እና ብዙ ጊዜ ቤተሰቡን ለማስተዳደር ውሎው አልፎ አልፎ አዳሩም ውጪ የሆነ ታላቅ ወንድም እንዳለው ነው የተረዳሁት:: ዮሐንስ ብዙ ጊዜ ከት/ቤት ሲቀር የሚውለው ካራቴ ቤት ነው:: ካራቴ ቤት ነው የዋልኩት ብሎ ሲነግረኝ ስፖርት ቤት ይመስለኝ ነበር:: በሁዋላ በሁዋላ ሲገባኝ ዮሐንስ ስፖርት ቤት የሚለኝ 1 ብር እየከፈለ ለአዕምሮ ለነፍስ የማይመች የብልግና ፊልም የሚመለከትበትን ቤት ነበር:: አልደብቃቹም እኔም 2 ቀን ስፖርት ቤት ገብቼ ነበር:: አዲስ ነገር እያወኩትኝ መጣው በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ ሳሳልፍ ቸርች ምን እንደሆነ አላውቅም:: ቤተሰቦቼም ምሳ እየቋጠሩ ት/ቤት ሒድ ከማለት ባለፈ ምን ስታደርግ ዋልክ ብለውኝ አያውቁም ነበር:: እስከዛሬ ድረስ በቤተሰብ ልዩ እንክብካቤ እየተደረገላቸው የእግዚአብሔርን ቃል በማወቅ ያደጉ ልጆችን ሳይ እቀናለሁ:: በእውነት እድለኛ ናቸው:: ልክ እንደ እኔ ባለማወቅ በብዙ ውጣ ውረድ እያሳለፉ ያሉ አፍላ ወጣቶችም አንጀቴን ይበሉኛል:: ዮሐንስ በፀባዩ ምክንያት ከት/ቤት ተባረረ:: ከ 2 አመት በሁዋላ ስፖርት ቤት አከባቢ እየቃመና እያጨሰ አግኝቼው ነበር:: ያኔም ቢሆን በክርስትና ህይወቴ ደካማ ስለነበርኩ ምንም ማድረግ አልቻልኩም:: ከዮሐንስ ወዲህም የገጠሙኝ ጓደኞቼም እጅግ የከፉ ሆኑ::1 ብር እየከፈልኩ የማየው ፊልም በስልክ ወደ እኔ መጣ:: ለውስጤ ጥያቄ መልስ ነው ያልኩት አማራጭ የጥፋት ጎዳናዬ ሆነ። መጥፎ እድሌ መቋቋም እስኪሳነኝ አንገላታኝ። በወሬ የምሰማውን አስነዋሪ ቪዲዮ አሁን አዲስ ባፈራኋቸው ጓደኞቼ ስልክ መመልከት ጀመርኩ። ድንገት አመለካከቴ ሲለወጥ ይታወቀኝ ነበር። ሴቶችን የማይበት መንገድ ፈጣሪን የሚያስከብር አልነበረም። ወንድ ሆኜ መፈጠሬን እስክጠላ ፈጣሪን አሳዝን ነበር። መፅሐፍ ቅዱስ በሮሜ መለእክት 1፡28 ላይ "እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው" ይላል። ይህን ክፍል ሳጠና ሁሌም የማስበው ጌታን ባለማወቅ እርሱን ባለመፈለግ ከህልውናው ውጪ የተንከራተትኩበትን ዘመን ነው። በቃ ሳላስበው የገባሁበት ነገር ውስጥ ለመላቀቅ ቀላል ጊዜ አልፈጀብኝም። እነዛን አስነዋሪ ነገሮች በ 1 ብር ስፖርት ቤት ገብቶ ከማየት ከዛም በጓደኞቼ ስልክ ከማየት አልፎ የተወሰነ ግሩፕ ፈጥረን ሲዲ እየተከራየን መመልከት ጀመርን። ትዝ የሚለኝ ሁሌም ከክላስ መልስ አንዱ ጓደኛዬ ቤት ሳናቋርጥ ሳምንቱን ሙሉ ለ 3 ሆነን እናይ ነበር። ያ ሁሉ ነገር በህይወቴ ያመጣው ነገር ቢኖር ከፈጠረኝ አምላክ መራቅ እና የቆሸሸ ማንነት ይዞ መኖር ነበር። ፈጣሪ ማን እንደሆነ መጠራጠር እና የማይጠቅም ፍልስፍና ውስጥ መግባት ነበር። ሰይጣን ይሄን ሁሉ ያደረገብኝ በአንድ ቀን አልነበረም። ሳምሶንን ከተጠራበት አላማ ቀስ በቀስ አንሸራትቶ እንደጣለ መልካም በሚመስሉ ነገሮች ልንኖር ከተጠራንበት ክልል ውጪ ያደርገናል። ምናልባት ይሄን ነገር ማድረግ ኖርማል የሆነባቸው ባለማወቅ እንዲሁም እያወቁ እቅም በማጣት ግራ በመጋባት ውስጥ ያሉ እህትና ወንድም ሊኖሩ ይችላሉ። መፍትሔው አንድ እና አንድ ነው። እርሱም ስለ እኛ ከኛ በላይ ለሚያስብልን ፈጣሪ እራሳችንን አሳልፈን