en
Feedback
Furi ሰልሰቢል

Furi ሰልሰቢል

Open in Telegram
618
Subscribers
-224 hours
-27 days
-1030 days
Posts Archive
ለሁላቹም አላህ በገንዘባቹ ላይ በረካ ያድርግ አላህ ይቀበላቹ ያ ጀመዐ እንደየ አቅማችን ሁላችንም እንሳተፍ,

ውድና የተከበራችሁ በመላው አለም የምትገኙ የቻናሌ ቤተሰቦች አንድ አንገብጋቢና የሁላችንም እርዳታ የሚፈልግ በአካባቢያችን የሚታወቅና በኑሮ ደካማ የሆኑ ቤተሰቦቹን ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይል ያገኘውን ስራ
+1
ውድና የተከበራችሁ በመላው አለም የምትገኙ የቻናሌ ቤተሰቦች አንድ አንገብጋቢና የሁላችንም እርዳታ የሚፈልግ በአካባቢያችን የሚታወቅና በኑሮ ደካማ የሆኑ ቤተሰቦቹን ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይል ያገኘውን ስራ በመስራት ሲጦር ቆይቶ አሁን ላይ ባጋጠመው የእግር ህመም(የጉልበት ዕጢ)  እርሱንም ሆነ ቤተሰቦቹን ማገዝ አልቻለም።ይህን ችግር ያዩ የአካባቢው ወጣቶች የሚችሉትን የህክምናና የተለያዩ ድጋፎች ሲያደርጉ ቆይተዋል። የኢትዩ ጠቢብ የሐኪም ቲም እግሩ ከመቆረጡ ይልቅ ጉልበቱ አካባቢ ያገጠውን ችግር በሌሎች የህክምና አማራጮች መፍትሔ ማገኘት እንደሚችል ነግረውታል። አጠቃላይ የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን 200,000ብር ታካሚ:–ሸምሱ ወልዴ 1000240553566 ንግድ ባንክ የዚድ አሽረቃ 1000089554776 coop 01425731361600/4851 አዋሽ ጅላሉ ጀማል 📩ደረሰኙን በዚህ ላኩልኝ @AbuHiba1

[{ የሸሪያ ዕውቀት አስፈላጊነት }] 🎙 በኡስታዝ ሲራጅ ንጋቱ ➽ በሙሐደራው ከተዳሰሱ ነጥቦች መካከል ➪ ሸሪያዊ ዕውቀትን መፈለግ ያለው ደረጃ ➱ ዕቀትን ለመፈለግ በዋነኝነት ምንድነው የሚያስፈልገን? ➩ የሸሪያን ዕውቀት መፈለግ ብይኑ ምንድነው? ➩ ዕውቀትን ከማን ነው የምንወስደው 🔎 @furiselsebla @furiselsebla

خطبة عيد 🎁እመኑኝ ይህን ኹጥባ እንዳያመልጣቹ 🎁 🎁አስደናቂ የሆነ ኹጥባ 🌹 🎁በፉሪ ኢድ ላይ የተደረግ 🌹 ✨በሱናው አንበሳ ✨ 🎙በሸይኽ ሲራጅ ንጋቱ (በኡስታዝ ሉጋ)ሀፊዘሁላህ✨ የኢድ ሁጥባ ድሮ እዲ ነበር ለካ ኒማው ከጅህ ካልወገደ አይታወቅም የሚባለው ለዚ ነው ተረግታቹኛል አይደል እንዴታ 📖በኹጥባው ከተዳሰሱ ነጥቦች 📚 💫ከረመዳን ቡሀላ ስላለው 💫 🪴ስለ እህቶቻ ( ስለሴቶች)🎋 🕌ስለ ጎንደር ወንድሞቻችን 🕌 👇👇👇👇👇👇 👉@furiselsebla👈 👉@furiselsebla👈 👆👆👆👆👆👆

የዒድ አደራ ~ አይናችንን እንስበር፣ አጅነቢይ ከመመልከት እንቆጠብ። ሀሳን ብኑ አቢ ሲናን - ረሒመሁላህ - ከዒድ ሲመለሱ "ስንት ቆንጆ ሴቶችን ተመለከትክ?" ብላ ሚስታቸው ብትጠይቃቸው "ወጥቼ እስ
የዒድ አደራ ~ አይናችንን እንስበር፣ አጅነቢይ ከመመልከት እንቆጠብ። ሀሳን ብኑ አቢ ሲናን - ረሒመሁላህ - ከዒድ ሲመለሱ "ስንት ቆንጆ ሴቶችን ተመለከትክ?" ብላ ሚስታቸው ብትጠይቃቸው "ወጥቼ እስከምመለስ ድረስ ከአውራ ጣቴ ውጭ አልተመለከትኩም" ብለው ነበር የመለሱት። ሱፍያን አሠውሪ - ረሒመሁላህ - ደግሞ "በዚህ ቀናችን የመጀመሪያ ስራችን እይታችንን መስበር ነው" ብለዋል። አደራ በዚህ በተከበረ ቀን ከየትኛውም ሐራም ነገር እንቆጠብ። ጌታችንን አናምፅ። ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም ሳሊሐል አዕማል። #ከደጋጎቹ_ቀዬ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

🌙🌙عيدكم مبارك !! 🌙🌙 🎈عيدكم مبارك !! ⭐️⭐️تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال 🤲نسئل الله أن يعده علينا أعوام عديدة ………
🌙🌙عيدكم مبارك !! 🌙🌙 🎈عيدكم مبارك !! ⭐️⭐️تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال 🤲نسئل الله أن يعده علينا أعوام عديدة ………

በየተክቢራዎቹ እጅን እስከ ትከሻ ወይም ጆሮ ድረስ ማንሳት ከሰለፎች ተገኝቷል። [ሙሶነፍ ዐብዲረዛቅ፡ 5699] ይሄ የብዙሃኑ ዑለማእ አቋም እንደሆነም በገዊይ ጠቅሰዋል። [ሸርሑ ሱናህ፡ 4/310] 4.9. በየተክቢራዎቹ መሃል የሚባልን ዚክር በተመለከተ ከነብዩ ﷺ የተላለፈ ሶሒሕ ማስረጃ የለም። (ክፍተቱ ካለ) አላህን ማመስገንና በነብዩ ﷺ ላይ ሶለዋት ማውረድ እንደሚቻል ከኢብኑ መስዑድ ተገኝቷል። [አልኢርዋእ፡ 642] 4.10. የተክቢራዎቹን ቁጥር የተጠራጠረ እርግጠኛ የሆነበትን ዝቅተኛውን ይዞ ቀሪውን ይሞላል። 4.11. ልክ እንደሌሎች ሶላቶች የመክፈቻ ዱዓእ መቅራቱ ተገቢ ሲሆን ቦታውም ከመክፈቻው ተክቢራ ቀጥሎ ከተጨማሪዎቹ ተክቢራዎች በፊት መሆን እንዳለበት የብዙሃን ዑለማዎች እይታ ነው። 4.12. ፋቲሐን መቅራት ግዴታ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ለኢማሙ ሱረቱል አዕላን እና ሱረቱል ጋሺያን ወይም ሱረቱል ቃፍና ሱረቱል ቀመርን መቅራቱ ከሱና ነው። [ሙስሊም] ለኢማሙ በቂራአህ ድምፅን ከፍ ማድረግ ሱና ነው። 4.13. የዒድ ሰላት ያለፈው ሰው ሳይሰላመት ከደረሰ ያገኘውን አብሮ ሰግዶ ያለፈውን ይሞላል። ከተሰላመተ በኋላ የደረሰ ደግሞ ካገኘ ከሰዎች ጋር ካልሆነ ብቻውንም ቢሆን ይሰግዳል። በሆነ ምክንያት ወደ መስገጃው ቦታ መውጣት ያልቻሉ ከቤታቸውም ቢሆን መስገድ ይችላሉ። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 369]፣ [ቡኻሪይ፣ ተዕሊቅ፡ 2/471] 4.14. ከዒድ ሶላት በፊትም በኋላም ከመስገጃው ቦታ የሚሰገድ መደበኛ ሱና የለም። ቤት ከተመለሱ በኋላ ግን ነብዩ ﷺ 2 ረከዐ ይሰግዱ ነበር። [ቡኻሪይ]፣ [አልኢርዋእ፡ 3/100] የዒዱ ሶላት የሚሰገደው መስጂድ ውስጥ ከሆነ ግን መስጂድ እንደገባን የዒድ ሱና ሳይሆን “ተሒየተል መስጂድ” መስገድ አለብን። 4.15. ዒድ መሆኑ ከእኩለ-ቀን በኋላ ከታወቀ በቀጣዩ ቀን ይሰገዳል። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1050] 4.16. ዒድድና ጁሙዐ በአንድ ቀን ከገጠሙ፡- የዒድ ሶላትን የሰገደ ሰው ጁሙዐ ሰላት ላይ የመገኘት ግዴታ የለበትም። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 984] 5. ኹጥባ፡- 5.1. የሚደረገው ከሶላት በኋላ ነው። [ቡኻሪይ፡ 963] [ሙስሊም፡ 888] 5.2. ለኹጥባው ሚንበር ይዞ መውጣት ከሱና አይደለም። [ቡኻሪይ፡ 956] 5.3. ኹጥባው አንዳንዶች እንደሚሉት አንድ ብቻ ሳይሆን ሁለት ነው። ከሰለፎች የተገኘው በዚህ መልኩ ነው። ኢብኑ ሐዝም የዑለማእ ስምምነት አለበት ብለዋል። [አልሙሐላ: 3/543] ዝርዝር የፈለገ በዚህ ሊንክ ይግባ። https://rb.gy/m3wrx 5.4. ኹጥባውን ማዳመጡ ግዴታም ባይሆን ተወዳጅ ነው። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 2289] 5.5. ኹጥባው እየተደረገ ወሬ ማውራት አይገባም። 6. የዒድ ቀን ምግብ፡- 6.1. ዒደል ፊጥርን እና ዒደል አድሐን መፆም ፈፅሞ አይፈቀድም! [ቡኻሪይና ሙስሊም] እንዲሁም ከዒደል አድሐ በኋላ ያሉትን ሶስቱን ቀናትም (አያመ ተሸሪቅ) ሐጅ ላይ ሆኖ እርድ ያላገኘ ሰው ካልሆነ በስተቀር ለሌሎች መፆም አይፈቀድም። [ቡኻሪይ] [አሶሒሐ፡ 3573] 6.2. በዒደል ፊጥር ቀን ወደ ሶላት የሚውወጣው ከተመገቡ በኋላ ነው። የዒደል አድሐ ቀን ግን ሳይመገቡ ወጥቶ ከሶላት በኋላ መመገብ ከሱና ነው። [ቡኻሪይና ሙስሊም] [ሙስነድ አሕመድ፡ 23042] 6.3. በዒደል ፊጥር የምንመገበው ተምር ቢሆንና በተናጠል በዊትር ብንበላው የነብዩ ﷺ ሱና ነው። [ቡኻሪይ] ተምር ከሌለ ቤት ያፈራውን በመቅመስ በልቶ የመውጣቱን ሱና ልንተገብር ይገባል። 6.4. በዒደል አድሐ ቀን ከሶላት መልስ መጀመሪያ የሚፈፀመው መመገብ ሳይሆን ኡዱሒያን ማረድ ነው። [ሙስነድ አሕመድ፡ 23042] አላህ መልካም ስራዎቻችንን ይቀበለን። ኣሚን። * ቴሌግራም ቻናል፡- 👉👉https://t.me/furiselsebla

ዒድ - ህግጋትና ስርአቱ ~ በኢስላም አመታዊ በአሎቻችን ሁለት ናቸው። እነሱም ዒደል ፊጥርና ዒደል አድሐ። የመጀመሪያው ረመዳን እንዳለቀ በሸዋል ወር የመጀመሪያ ቀን ላይ ይውላል። ሁለተኛው - ዒደል አድሐ- ደግሞ የዙልሒጃ ወር በ10ኛው ቀን ላይ። ነብዩ ﷺ መዲና ሲገቡ የመዲና ሰዎች የሚጫወቱባቸው ሁለት በአላት ነበሯቸው። “ምንድን ናቸው እነኚህ ቀናት?” ሲሉ ጠየቁ መልእክተኛው ﷺ። እነሱም “ከጃሂሊያህ ዘመን ጀምሮ የምንጫወትባቸው ቀናት ናቸው” ብለው መለሱ። ነብዩ ﷺ “አላህ ከነሱ በተሻሉ ቀናት ተክቷችኋል፡- በአድሐ ቀን እና በፊጥር ቀን” አሉ። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1039] ጥቂት ስለዒድ፡- 1. ቀኑ የደስታ ቀን ነው፡- 1.1. “ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም” እያሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት መለዋወጥ ከሶሐቦች ተገኝቷል። [አልፈታዋ፡ 24/253] 1.2. ልጃገረዶች እየዘፈኑ መጫወት ይችላሉ። [ቡኻሪ፡ 949] [ሙስሊም፡ 892] 1.3. እለቱ የደስታ፣ የመብያና የመጠጫ ቀን ነው። [ሶሒሑ ቲርሚዚይ፡ 777] 1.4. ስለሆነም ቀብር ዚያራና የመሳሰሉ የእለቱን የደስታ ድባብ የሚያደፈርሱ ድርጊቶችን መፈፀም አይገባም። [አልኢብዳዕ፡ 263] 1.5. የምንደሰትበት ግን ፈፅሞ በሐራም ነገር መሆን የለበትም። “የትም ብትሆን አላህን ፍራ!” የሚለው ሐዲሥ አይረሳ። 2. ተክቢራ፡- 2.1. የሚባልበት ጊዜ፡- * በዒደል ፊጥር - የረመዷን ወር መጨረሻ ቀን ፀሐይ ከጠለቀችበት ወይም የሸዋል ጨረቃ ከታየችበት ጊዜ ጀምሮ ነው። ምክንያቱም አላህ ተክቢራውን ከረመዷን ፍፃሜ ጋር አያይዞ ነውና የገለፀው። [አልበቀረህ፡ 185] ተክቢራው እስከ ዒድ ሰላት ድረስ ይዘልቃል። * በዒደል አድሐ - ደግሞ ከዐረፋ ቀን ፈጅር ሶላት አንስቶ እስከ ዙልሒጃ 13 ዐስር ድረስ ከግዴታ ሰላቶች በኋላ ተክቢራ ማድረጉ ከሶሐቦች ተገኝቷል። [አልኢርዋእ፡ 653] እንዲያውም ኢጅማዕ (ወጥ ስምምነት) የመጣበት ጉዳይ እንደሆነ ነወዊይና ኢብኑ ረጀብ ጠቅሰዋል። [አልመጅሙዕ፡ 5/32] [ፈትሑል ባሪ] በዒደል ፊጥር ጊዜ ከግዴታ ሶላቶች በኋላ ተክቢራ ማድረጉ በቂ ማስረጃ የለውም። 2.3. አደራረጉ፡- ሁሉም በየፊናው እንጂ አንዱ እያወጣ ሌሎች በመከተል በህብረት ባንድ ድምፅ አይባልም። [መጅሙዑፈታዋ ኢብኒ ባዝ፡ 13/21] ባይሆን ይሄ ጉዳይ በዑለማዎች የተለያየ ሀሳብ የተሰነዘረበት ፊቅሃዊ ጉዳይ እንደመሆኑ ጉዳዩን በልኩ መያዝ ይገባል። 2.4. ድምፅን በተክቢራ ከፍ ማድረግ የተወደደ ነው። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 4934] 2.5. ተክቢራው ሴቶችንም በተመሳሳይ የሚመለከት ነው። [ቡኻሪና ሙስሊም] ድምፃቸውን ግን ዝቅ ሊያደርጉ እንደሚገባ ዑለማዎች ይመክራሉ። 2.5. አንዳንድ አካባቢዎች እንደሚታየው በተክቢራ ሙሉ ሌሊቱን ሳይተኙ ማሳለፍ፣ ሰፈር ጎረቤቱን በከፍተኛ ድምፅ ማወክ ማስረጃ የሌለው ስራ ነው። “የሁለቱን ዒድ ሌሊቶች ነቅቶ ያደረ ሰው ልቦች በሚሞቱበት ቀን ልቡ አይሞትም” የሚለው “ሐዲሥ” በነብዩ ﷺ ላይ የተቀጠፈ እንጂ ጤነኛ መረጃ አይደለም። [አዶዒፋህ፡ 520] 2.6. ከሶሐቦች የተለያዩ የተክቢራ አፈፃፀሞች የመጡ ሲሆን የተለየ አይነት ገደብ የለውም። ከሰሐቦች የተገኙትን መያዙ በላጭ ነው። 2.7. እነዚህን ተክቢራዎች ማለት በጀማዐ ለሰገደም፣ ብቻውን ለሰገደም የተወደደ ነው። ግዴታ ግን አይደለም። [ሸርሑል ሙምቲዕ፡ 5/165] 3. ወደ መስገጃው ቦታ መውጣት፡- 3.1. ወደ መስገጃ ቦታ ሲወጣ መታጠብን፣ ሽቶ መቀባትን የሚመለከት ከሶሐቢዩ ኢብኑ ዑመር ተገኝቷል። [አልኢርዋእ፡ 104] ከነብዩ ﷺ ግን ምንም የለም። የመታጠቢያ ጊዜውም ከእለቱ ፈጅር ሶላት መልስ ቢሆን ይመረጣል። ይህን የሚያመላክት ከሰለፎች ተገኝቷል። [አልመጣሊቡል ዓሊያህ፡ 2753]፣ [አሕካሙል ዒደይን ሊልፊርያቢይ፡ 16] ትጥበቱም ሴት ከወንድ፣ ህፃን ከአዋቂ ሳይለይ ሁሉንም እንደሚመለከት ነወዊይ ጠቁመዋል። [አልመጅሙዕ፡ 2/233] 3.2. በእለቱ አቅም በፈቀደ ባማረ ልብስ ሽክ ማለት ተወዳጅ ነው። [ቡኻሪና ሙስሊም] 3.3. ለቻለ ሰው ወደ መስገጃው ቦታ በእግር መሄዱ ሱና ነው። [አልኢርዋእ፡ 636] 3.4. የወር አበባ ላይ ያሉ ሴቶች ወደ መስገጃው ሜዳ መውጣታቸው ከሱና ነው። ከመስገጃው ቦታ ግን ገለል ይላሉ። [ቡኻሪ] ሴቶች ወደ መስገጃው ቦታ ሲወጡ ሽቶ ከመቀባትና ካላስፈላጊ አለባበስ መራቅ አለባቸው። 3.5. ስጋትና እንቅፋት ከሌለ ልጆችም ሊወጡ እንደሚችሉ የሚጠቁም ማስረጃ አለ። [ቡኻሪ፡ 977] ባይሆን ሰጋጆችን እንዳይበጠብጡ ወላጆች ሊቆጣጠሯቸው ይገባል። 3.6. ከመስገጃው ቦታ ሲመለሱ መንገድ ቀይሮ መመለሱ በላጭ ነው። [ቡኻሪ፡ 986] 4. የዒድ ሶላት፡- 4.1. ሶላቱን በተመለከተ ሚዛን የሚደፋው አቋም “ግዴታ ነው” የሚለው እንደሆነ ኢብኑ ተይሚያ፣ ሶንዓኒይ፣ ሲዲቅ ሐሰን ኻን፣ ሸውካኒይ፣ አልባኒይ፣ ኢብኑ ዑሠይሚን እና ሌሎችም አስረግጠው ተናግረዋል። 4.2. ወቅቱ፡- ፀሀይ ወጥታ የጦር ቁመት ያክል ከፍ ካለች ጀምሮ በአናት ትይዩ እስከምትሆን ድረስ ያለው ነው። የዒደል ፊጥር ሶላት ዘግየት፣ የዒደል አድሐ ደግሞ ቀደም ቢል ተመራጭ ነው። [አተልኺስ፡ 144] [ሙስነዱ ሻፊዒይ፡ 74] ምክንያቱም የዒደል ፊጥር ጊዜ ዘግየት ማለቱ ዘካተል ፊጥር ለሚሰጡ ሰዎች ጊዜ እንዲኖራቸው ሲያደርግ የዒደል አድሐ ጊዜ ቀደም ማለቱ ደግሞ ከሶላት ቶሎ ተመልሰው ኡዱሒያ የሚያርዱበት ጊዜ እንዲያገኙ ያደርጋቸዋል። 4.3. የሚሰገድበት ቦታ፡- ዝናብ፣ የፀጥታ ስጋት፣ ወዘተ ካልኖረ ወጣ ያለ ሰፊ ሜዳ ላይ መሆኑ ሱና ነው። [ቡኻሪይና ሙስሊም] 4.4. ለዒድ ሶላት አዛንም ኢቃማም አይደረግም። [ቡኻሪይ፡ 962] [ሙስሊም፡ 886] 4.5. የረከዐው ብዛት፡- 2 ነው። [ቡኻሪይ፡ 964] [ሙስሊም፡ 884] 4.6. የዒድ ሶላት ውስጥ ያሉት ተጨማሪ ተክቢራዎቹ ሙስተሐብ እንጂ ግዴታ አይደሉምና በመርሳትም ሆነ ሆን ተብሎ ቢቀሩ ሶላቱ አይበላሽም። [አልሙግኒ፡ 3/275] 4.7. ቁጥራቸውም የመጀመሪያው ረከዐ ላይ ከመክፈቻው ተክቢራ ውጭ 7፤ ሁለተኛው ረከዐ ላይ ደግሞ ከመነሻው ተክቢራ ውጭ 5 ተክቢራ ነው። ይሄ ከብዙሃኑ ሶሐቦችና አኢማዎች የተገኘው እንደሆነ ኢብኑ ተይሚያ ገልፀዋል። [አልፈታዋ፡ 24/220] ብዙሃኑ ዑለማዎች ያሉትም እዚህ ላይ ነው። ባይሆን የመጀመሪያውን 7 የሁለተኛውን ስድስት፣ የመጀመሪያውን 6 የሁለተኛውን 5 ማድረጉም ተገኝቷል። 4፣ 11፣ 12፣ 13 ተክቢራዎችን ማለት እንደሚቻልም ከሰለፎች ተገኝቷል። ከዚህ በመነሳት ነገሩ ሰፊ እንደሆነና በሶሒሕ ማስረጃ በመጡት ሁሉ መስራት እንደሚቻል ያሳያል ይላሉ ሸይኹል አልባኒይ ረሒመሁላህ። [አልኢርዋእ፡ 639] 4.8. በተጨማሪ የዒድ ተክቢራዎች ላይ እጅን ማንሳት ከሶሐቦች፣ ከዐጣእ፣ አውዛዒይ፣ አቡ ሐኒፋህ፣ ሻፊዒይ፣ አሕመድና ሌሎችም ተገኝቷል። ነብዩ ﷺ ደግሞ ጥቅል በሆነ መልኩ የሶላት ተክቢራዎች ላይ እጃቸውን ያነሱ እንደነበር ማስረጃ አለ። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 715] 👉👉https://t.me/furiselsebla 👉

ይድረስ! ~ 1- ይድረስ ሚስትህን ለፈታኸው፡ ልጆችህን ለዒድ አስበሃቸዋል? ወይስ እነሱንም ከናታቸው ጋር ፈተሃቸዋል? 2- ይድረስ የየቲሞች አጎት ለሆንከው፡ የሟች ወንድምህን ልጆች ትጠይቃለህ? ወይስ ከቀበርከው ወንድምህ ጋር ረስተሃቸዋል? 3- ይድረስ ባሏ የሞተባት እህት ያለችህ : እህትህን ትኑር ትሙት ጠይቀሀል? በልታለች ወይስ ተርባለች? ወይስ እህትነቷ ቁጥር ብቻ ነው? ይድረስ ለሁላችን፡ እጃችንን የሚጠብቁ፣ ከኛ የቀረበ ሰው የሌላቸው ቤተሰቦቻችን በምን ላይ ናቸው? በዒድ በምን መልኩ እንዲያስታውሱን እንፈልጋለን? ያቅማችንን ያክል ከልባቸው ውስጥ ደስታ ማስገባት ያሳስበናል? ወይስ ሀዘን ትካዜያቸው ምንም አይመስለንም?! - ተነካክቶ ከዐረብኛ የተመለሰ 👉👉https://t.me/furiselsebla

ጋብቻን አስመልክቶ በኡስታዝ ስራጅ ንጋቱ የተደረገ አስተማሪና መካሪ ሙሀደራ (ክፍል2) አህመድ ነጃሽ ሱና መስጂድ

ጋብቻን አስመልክቶ (ክፍል1)በኡስታዝ ስራጅ ንጋቱ የተደረገ አስተማሪና መካሪ ሙሀደራ በአህመድ ነጃሽ ሱና መስጂድ

🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት 📚 الأصول الثلاثة وأدلتها لشيخ الإسلام محمد بن عبدالوهاب رحمه الله تعالى -٠٧ ✸| ክፍል 07 (የመጨረሻው ክፍል ) 🔗 የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ Mp3 https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4230 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በ Pdf መልክ በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ↓↓↓ https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4220 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ 🕌 በፉሪ አቡበክር አስ-ሲዲቅ መስጂድ ለሙእተኪፎች የተዘጋጀ ኮርስ 🗓 ዛሬ እሁድ ረመዷን 28-1445 ሂጅሪ (29 -07-2016)[07-04-2024] ከዙሁር ሰላት በኃላ የተሰጠ ደርስ ነው 🎙በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም ሀፊዘሁላህ ወረዓህ 📍ትምህርቱን ለመከታተል ቻናሎቹን ይቀላቀሉ 👇👇👇 https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam & http://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn

#አያህ_ቁርአን || በሸይኽ ሙሐመድዘይን ሸይኽ አደም

👉አሰራጩት በአስቸኳይ???? ከአርሹ በላይ pdf ኢንሻአላህ ኪታቡን ለማናገኘ በተለይ አውሮፓ ሀገራቶች እንድሁም በከፊል አረብ ሀገራቶች እና በገጠር ለሚሰሩ ወንድሞች pdfን ሙሉውን በቅርቡ አዘጋጀተው ይለቁልናል ይህ ከላይ ያለው ግማሽ ነው እህቶች ከኪታባቸው ቀርፀው የላኩልኘን ለራሴም ለማንበብ እንድመቸኘ ባንድ ሰብሰብ ያደረኳቸው ገፆች ናቸው ሽፋኑን ብቻ ነበር በየፕሮፋይል ላይ ተሰቅሎ የማውቀው ለመጀመሪያ ከመግቢያው ራሱ ሳነበው በጣም ነው የጎጎሁት ኪታቡንማገኘት የምትችሉ ግዙት ተነቦ የማይጠገብ መፅሀፍ ነው ይህ ኪታብ በየቤታችን ሊኖር ይገባል https://t.me/nhwdr https://t.me/nhwdr https://t.me/nhwdr https://t.me/nhwdr

🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት 📚 الأصول الثلاثة وأدلتها لشيخ الإسلام محمد بن عبدالوهاب رحمه الله تعالى -٠٦ ✸| ክፍል 06 🔗 የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ Mp3 https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4228 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በ Pdf መልክ በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ↓↓↓ https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4220 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ 🕌 በፉሪ አቡበክር አስ-ሲዲቅ መስጂድ ለሙእተኪፎች የተዘጋጀ ኮርስ 🗓 ዛሬ ቅዳሜ ረመዷን 27-1445 ሂጅሪ (28 -07-2016)[06-04-2024] ከዙሁር ሰላት በኃላ የተሰጠ ደርስ ነው 🎙በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም ሀፊዘሁላህ ወረዓህ 📍ትምህርቱን ለመከታተል ቻናሎቹን ይቀላቀሉ 👇👇👇 https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam & http://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn

+3
🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት 📚 الأصول الثلاثة وأدلتها لشيخ الإسلام محمد بن عبدالوهاب رحمه الله تعالى -٠٢ ✸| ክፍል 02 🔗 የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ Mp3 https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4223 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በ Pdf መልክ በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ↓↓↓ https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4220 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ 🕌 በፉሪ አቡበክር አስ-ሲዲቅ መስጂድ ለሙእተኪፎች የተዘጋጀ ኮርስ 🗓 ዛሬ ሰኞ ረመዷን 22-1445 ሂጅሪ (23 -07-2016)[01-04-2024] ከዙሁር ሰላት በኃላ የተሰጠ ደርስ ነው 🎙በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም ሀፊዘሁላህ ወረዓህ 📍ትምህርቱን ለመከታተል ቻናሎቹን ይቀላቀሉ 👇👇👇 https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam & http://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn

🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት 📚 الأصول الثلاثة وأدلتها لشيخ الإسلام محمد بن عبدالوهاب رحمه الله تعالى -٠١ ✸| ክፍል 01 (የመጀመሪያው ክፍል) 🔗 የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ Mp3 https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4222 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በ Pdf መልክ በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ↓↓↓ https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4220 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ 🕌 በፉሪ አቡበክር አስ-ሲዲቅ መስጂድ ለሙእተኪፎች የተዘጋጀ ኮርስ 🗓 ዛሬ እሁድ ረመዷን 21-1445 ሂጅሪ (22 -07-2016)[31-03-2024] ከዙሁር ሰላት በኃላ የተሰጠ ደርስ ነው 🎙በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም ሀፊዘሁላህ ወረዓህ 📍ትምህርቱን ለመከታተል ቻናሎቹን ይቀላቀሉ 👇👇👇 https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam & http://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn

متن ثلاثة الأصول የሠላሠቱል ኡሱል ሶፍት ኮፒ በፒዲኤፍ መልኩ ለምትፈልጉ ከዚህ አውርዳችሁ መጠቀም ትችላላችሁ። https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam/7906

🌹 بشرى سارة 🌹 የዐሽረል አዋኺር ኮርስ 📚 በኮርሱ የሚቀራው ኪታብ :- ''ሠለሠቱል ኡሱል" 🎙 ኪታቡን ሚያቀሩት :- ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም 🕌 ትምህርቱ የሚሰጥበት ቦታ:- ፉሪ(በፉ
🌹 بشرى سارة 🌹 የዐሽረል አዋኺር ኮርስ 📚 በኮርሱ የሚቀራው ኪታብ :- ''ሠለሠቱል ኡሱል" 🎙 ኪታቡን ሚያቀሩት :- ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም 🕌 ትምህርቱ የሚሰጥበት ቦታ:- ፉሪ(በፉሪ ሜዳ ፊት ለፊት ባለው ቅያስ ገባ ብሎ)  አቡበክር አስሲዲቅ መስጂድ 🕖 የትምህርቱ ቀንና ሰዐት :- ዐሽረል አዋኺር ከዙህር ሰላት በኃላ 🗓 ትምህርቱ ሚጀመረው :- እሁድ ረመዳን 21-1445 ሂጅሪ ይሆናል። * በአካል ተገኝታችሁ መከታተል ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል በቀጥታ ስርጭት ይተላለፋል እንዲሁም ሪከርዱም ይለቀቃል ኢንሻአሏህ። https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam & https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn