en
Feedback
መዝሙረ ተዋህዶ

መዝሙረ ተዋህዶ

Open in Telegram
4 356
Subscribers
+224 hours
+87 days
+15430 days
Posts Archive
ቅዱስ ኤፍሬም ስለ ልደተ ክርስቶስ እንዲህ አለ፦ ጌታ ሆይ ቅድስት እናትህ ድንግል ሳለች አንተን ፀንሳ በመውለድ እናትነትን ገንዘቧ አደረገች፤ ድንግል ሆና ሳለች ከጡቶቿ ወተት ፈሰሰ፤ ድንግል ከሆነች መሬት ንጹሕ ምንጭ እንዲፈልቅ፤ እንዲሁ ድንግል ከሆነችው እናትህ ጡቶች ወተት ፈለቀ፡፡ እርሱዋ አንተን ብትሸከምህ አንተ ጽንዕ ሰጥተሃት ነው፤ በተራብክ ጊዜ አንተን ከጡቶቹዋ ትመግብህ ዘንድ፣ ነቢዩ ዳንኤል በታላቅ ተራራ የመሰለህ አንተን አንደ ሕፃናት ታቀፈችህ፤ በፈቃድህ የተጠማህ አንተን በእጆቹዋ በፍቅር ትዳብስህ ዘንድ፤ የምህረት እሳት የሆንኽ አንተ ክንዶቿን መለኮታዊው እሳት እንዳይቃጥላቸው ጠበቅኻቸው፡፡ ጌታ ሆይ እናትህ ግሩም የሆኑ ተአምራት የተፈጸሙባት መካን ናት። ወደ እርሱዋ የሁሉ ጌታ የሆነው ገባ፤ የአገልጋዩን አርአያ ነስቶ ተወለደ። የእግዚአብሔር ቃሉ የሆነ እርሱ ወደ እርሱዋ ገባ፤ ዝምተኛ ሆኖ ተወለደ። ነጎድጓድ የሆነው እርሱ ወደ እርሱዋ ገባ፤ ጭምት ሆኖ ተወለደ። እረኛ የሆነው እርሱ ወደ እርሱዋ ገባ፤ በግ ሆኖ በመወለድ በአባግዕ ቋንቋ ተናገረ፡፡ ጌታ ሆይ የእናትህ ማኅፀን ከተፈጥሯዊው ሥርዓት በተቃራኒው ፈጸመ፤ ሁሉን ያከናወነ በባለጸግነቱ ወደ እርሷ ገባ፤ ደሃ ሆኖ ተወለደ። ከሁሉ በክብር የሚልቀው እርሱ ወደ እርሷ ገባ፤ ትሑት ሆኖ ተወለደ። በክብሩ ገናና የሆነው እርሱ ወደ እርሱዋ ገባ፤ የባሪያውን መልክ ይዞ ተወለደ። ብርቱ የሆነው እርሱ ወደ እርሱዋ ገባ፤ ጥበቃ እንደሚያስፈልገው ሕፃን ሆኖ በማኅፀን ተገኘ። ፍጥረትን ሁሉ የሚመግበው መራብንና መጠማትን ገንዘቡ አደረገ፤ (አጣጣመ) ሁሉን በበረከቱ የሚያለብሰውና የሚያስጌጠው እርሱ ራቁቱን ተወለደ። እኛን ለማዳን ሲል የእኛን ተፈጥሮ ገንዘቡ ላደረገ ለእርሱ ክብር ምስጋና ይሁን። መልካም በዓለ ልደት...... ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇                 •➢ ሼር // SHARE

+1
✞ ተወልደ_ኢየሱስ ✞ ተወልደ ኢየሱስ /በቤተልሔም/(፪)ዘይሁዳ በቤተልሔም አዋልደ ጢሮስ /አሜሃ ይሰግዳ/(፪) በቤተልሔም #ትርጉም የይሁዳ ቦታ በሆነችው በቤተልሔም ኢየሱስ ተወለደ ያን ጊዜም የጢሮስ ቆነጃጅቶ/ልጆች/ሰግደዋል #Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ። ╔ ​✞ ═════●◉❖◉●═════✞╗ ✢ ✥ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ ❖ @enamsgn @mezmuredawit ❖ ❖ @mezmuredawit @enamsgn ❖ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ ✥ ✢ ╚✞ ═════●◉❖◉●═════​✞╝ ✍ ወድሰኒ ✍ ዜማ ቅዱስ ያሬድ

#24 ሌቦች ወርቅና ብር ያለውን እንጂ ድርቆሽና ገለባ እንዲሁም ሰንበሌጥ ያለውን ቤት አይበረብሩም፡፡ ዲያብሎስም የሚያጠቃው (የሚፈትነው) መንፈሳዊ ምግባራትን የሚያበዙትን ሰዎች ነው፡፡" እንካን ለ
#24 ሌቦች ወርቅና ብር ያለውን እንጂ ድርቆሽና ገለባ እንዲሁም ሰንበሌጥ ያለውን ቤት አይበረብሩም፡፡ ዲያብሎስም የሚያጠቃው (የሚፈትነው) መንፈሳዊ ምግባራትን የሚያበዙትን ሰዎች ነው፡፡" እንካን ለጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት አመታዊ ክብረ ብአል አደረሳችሁ ታህሳስ 24 2015 ዓ/ም

#ከጠላት_ፈተናዎች_ተጠንቀቅ! ዲያቢሎስ ቀስቱን ሲወረውርብንና በውጊያው ሲያውከን ይህ በእኛ ላይ ብቻ የተደረገ ቁጣና ጠላትነት አይደለም፤ ምክንያቱም እርሱ የእግዚአብሔርም ጠላት ነውና በእኛ ላይ ሚደርሰው መከራ በእግዚአብሔር ላይ የሚደረግ ተቃውሞ ነው። ዲያቢሎስ እግዚአብሔርን ማጥቃት ባለመቻሉ ፍጥረታቱን በማታለልና ከእርሱ ከእርሱ ጋር ወደ ዘላለማዊ ቅጣት እንዲገቡ በማድረግ ሊበቀለው ይጥራል፡፡ የተወደድኸው ሆይ! ይህንን ነገር አስተውል! ዲያቢሎስን ስትቃወመውና ስትዋጋው ክፉን ነገር ከእናንተ እያራቅህ ብቻ አይደለም፤ ለእግዚአብሔርም ክብር እየተዋጋህ ነው፡፡ ስለዚህም የክፉውን ዲያቢሎስ ዲያቢሎስ ማማለያና መደለያ በመቀበል እግዚአብሔርን ከማሳዘን ይልቅ ፈተናውን በጽናት ስትታገል በውጊያው ላይ ብትሞት ይሻልሃል፡፡ ለአፍታም ቢሆን ብቻህ እየተዋጋ እንዳለህ አድርገህ አታስብ፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር በጠላትህ ላይ ድል መንሣትን ይሰጥሃል፡፡ "አቤቱ አምላክ ሆይ፥ ተነሥ እጅህም ከፍ ከፍ ትበል ድሆችን አትርሳ፡፡ ኃጢአተኛ ስለ ምን እግዚአብሔርን አስቆጣው? በልቡ:: አይመራመረኝም ይላልና፡፡" (መዝ ፲ ፥ ፲፪ -፲፫) ጥሩርና ጋሻ ያዝ፤ እኔንም ለመርዳት ተነሥ፡፡ ሰይፍህን ምዘዝ የሚያሳድዱኝንም መንገዳቸውን ዝጋ ነፍሴን፦ መድኃኒትሽ እኔ ነኝ በላት።›› (መዝ. ፴፭፥፪-፫) "አሁንም ያዕቆብ ሆይ፥ የፈጠረህ፥ እስራኤልም ሆይ፥ የሠራህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ተቤዥቼሃለሁና አትፍራ በስምህም ጠርቼሃለሁ፥ አንተ የእኔ ነህ፡፡ በውኃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፥ በወንዞችም ውስጥ ባለፍህ ጊዜ አያሰጥሙህም፤ በእሳትም ውስጥ በሄድህ ጊዜ አትቃጠልም፥ ነበልባሉም አይፈጅህም።" (ኢሳ. ፫፥፩-፪) በነፍሳችን ላይ ደካማነትን እስካላየ ድረስ ሰይጣን አያጠቃንም፡፡ ጎበዝ አዳኝ ወፎችን ለማደን እንደሚያደርገው ዲያቢሎስም ወጥመዱን ለማስገባት ሁልጊዜ ከእኛ ላይ ቀዳዳን ይፈልጋል፡፡ ብዙ ጊዜም ይዋጋናል፣ ይሸነግለናል በምኞቶቻችንም እየገባ ያገኘናል፡፡ አዳምን በሔዋን፣ ሶምሶንን በምወድደው ደሊላ፣ ንጉሥ ሰሎሞንን በእንግዶች ሴቶች ፍቅር፣ የአስቆሮቱ ይሁዳንም በገንዘብ ፍቅር እንደጣላቸው አላየህም፡፡ ስለዚህ እንደ ጎበዝ ሐኪም ሁን፣ ጉድለትህንና ሕመምህንም አክም፤ ኩራትህን በትሕትናና በየዋህነት ድል አድርገው፣ የትዕቢት በሽታህንም አንተነትህን በመናቅ ፈውሰው፡፡ በተአምራትና በታላቅ ነገሮችም ከመመካት ተጠበቅ ምክንያቱም ዲያቢሎስ ራሱ በብርሃን መልአክ መመስል ይችላል፡፡ በስብ ውስጥ መርዙን ሊከት፣ በማጥመጃው ዘንግ ውስጥም የመደለያ ጣፋጭ ምግብን ሊያደርግና መልካምና ጠቃሚ ነገር ይከተላል ብለህ እንድታምን ሊያታልልህ ይችላል፡፡ አንተ ግን ፈጽሞ አትታለል፣ በከንቱም አትነዳ፡፡ ይልቅስ ከዲያቢሎስ ጥቃት ትጠበቅ ዘንድ ሁሉን ነገር አስተውልና መርምር፡፡ ይሁዳ ጌታውን አልከዳምን? ኢዮአብስ ወዳጅና የሚታመን ሰው መስሎ አሜሳይን አልገደለውምን? (፪ነገ. ፳ ፥ ፱) በእግዚአብሔር ታመን! ከመሪ በላይ አጥብቀህ ያዘው፤ ሁሉን ነገር ወደ እርሱ አምጣው፡፡ ድጋፍህና መጠጊያህ አድርገው፤ እርሱ ሁለንተናህ አድርገው። (#ሊቀ_ዲያቆናት_ሀቢብ_ጊዮርጊስና_ሥራዎቹ ገጽ 43-45 - Deacon Henok Haile) ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇 •➢ ሼር // SHARE 💚 •✥• @ortodox_27•✥•💚 💛 •✥• @ortodox_27 •✥•💛 💖 •✥• @ortodox_27•✥• 💖 ✧━━━━━━━━━━━━━━━━✧

📖  ማርያምም እንዲህ አለች ። 📖 ነፍሴ #ጌታን_ታከብረዋለች፥ መንፈሴም #በአምላኬ_በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤ የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ #ትውልድ_ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤ #የሉቃስ ወንጌል  ምዕ. 1÷46-48

📖  ማርያምም እንዲህ አለች ። 📖 ነፍሴ #ጌታን_ታከብረዋለች፥ መንፈሴም #በአምላኬ_በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤ የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ #ትውልድ_ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤ #የሉቃስ ወንጌል  ምዕ. 1÷46-48

ሰይጣን በአንድ ኃጢአት ደጋግሞ በጣለህ ጊዜም ፈጥነህ ተስፋ አትቁረጥ። የፈጣሪህንም መሐሪነት አትጠራጠር። ለጠላትህም እንዲህ በቀላሉ እጅ አትስጥ። ስለዚህ ነገር በገነተ አበው (Paradise of fathers) የተጻፈን ታሪክ እስኪ እናስታውስ። ሰይጣን በተመሳሳይ ኃጢአት ብዙ ጊዜ እያሰነካከለ የሚጥለው አንድ መነኩሴ ነበር። ታዲያ ይህ መነኩሴ ሁል ጊዜ በአንድ ኃጢአት እየደጋገመ መውደቁ ቢያሳዝነውም፣ መልሶ ንስሐ እየገባ ፈጣሪውን "አውጣኝ" ብሎ መማጸን ግን አላቆመም ነበር። ከዕለታት በአንዱ ቀን መነኩሴው ቆሞ መዝሙረ ዳዊት ሲጸልይ ሳለ ድንገት ሰይጣን ወደ እርሱ መጣና "ፊቱ ቆመህ በእነዚህ ንጹሕ ባልሆኑ ከንፈሮችህ የእግዚአብሔርን ስም ስትጠራ አታፍርም?" አለው። ያም መነኩሴ "አንተ እኔን ጨክነህ ታሰናክላለህ። እኔ ደግሞ መሐሪውን አምላክ እንዲያዝንልኝ ሳላቋርጥ እለምነዋለሁ። እስኪ ከአንተ ጭካኔ እና ከአምላክ ምሕረት የቱ እንደሚበልጥ እናያለን።" ሲል መለሰለት። ሰይጣንም የመነኩሴውን ተስፋ አለመቁረጥ ባየ ጊዜ ከእርሱ ሸሽቶ ሄደ። የፈተና ማዕበል በሚበዛባት በዚህች ዓለም ስንኖር፣ ዐውሎና ወጀቡ ከሚያመጣው ጥፋት ለመዳን መልሕቃችንን የምንጥልበት የተስፋ መሬታችን አምላካችን እግዚአብሔር ነው።

እጅህ ላይ ባለው ነገር ከታመንህ እግዚአብሔር አምላክ በእጁ ውስጥ ያለውን ነገር ይሰጥሃል። በውስጥህ ያለውን አቅም መጠቅም ከቻልህ እግዚአብሔር የአንተ ያልሆነ ተጨማሪ አቅም ይሰጥሃል። ከእግረኞች ጋር ሳትደክም እኩል መራመድና መቅደም ከቻልህ እግዚአብሔር ፈረስን ለውድድር ይሰጥሃል። ኤር. 12፥5 የሚታዩ ኃጢአቶችን ለመዋጋት ታምነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር የተሸሸጉና የማይታዩ ኃጢአቶችን ድል እንድትነሣ ይሾምሃል። በሕፃንነትህ በልጅነትህ ለእግዚአብሔር የታመንህ ሆነህ ከተገኘህ እርሱ በወጣትነትህ በምታደርገው ውጊያ ውስጥ ታማኝነትን ያድልሃል። ልያን ለመቀበል ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር ራሔልን ሚስት አድርገህ ታገባት ዘንድ ይሰጥሃል። ዘፍ. 29፥27 በሲና ምድረ በዳ ለመቀመጥ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር አምላክ የተስፋይቱን ምድር ከንዓንን ያወርስሃል። በዚህ በተወሰነና አጭር ሕይወት ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር መጨረሻ የሌለውን ዘላለማዊ ሕይወት ያድልሃል። ትልቁ ቁም ነገር በእጅህ ውስጥ የገባው ነገር ትንሽም ይሁን ጥቂት በእርሱ መታመን መቻልህ ነው። ስለሆነም ባለህ አንድ መክሊት ታምነህ ስትገኝ እግዚአብሔር አምስት መክሊቶችን በአደራ ይሰጥሃል። አንተ በሚታዩት ነገሮች ላይ ታማኝ ሆነህ ስትገኝ እርሱ በማይታዩት ነገሮች ላይ ይሾምሃል።በመሆኑም ዓይን ያላየችውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልብ ያልታሰበውን መንግሥቱን ያወርስሃል። 1ኛ ቆሮ 2፥9 (#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ - #መንፈሳዊው_መንገድ መጽሐፍ #አያሌው_ዘኢየሱስ እንደተረጎመው።)

ድንግል ማርያም መድኃኒታችን ናት ! ~~~~~~~ ሐሳዊው ነብይ ዮናትን... ታምረ ማርያም ላይ ያገኘው ግዙፍ ስህተት አስመስሎ ባቀረበው ቪዲዮ ላይ በመሰረታዊነት በሁለት ነገር ላይ ብቻ ያጠነጥናል። ዝባዝንኬውን ሳንቆጥር ኦርቶዶክሶች በታምረ ማርያም መጽሐፋቸው ማርያምን "መድኃኒት ናት" ይሏታል የሚለው አንደኛው ሲሆን እንዲህም " የማርያም ሐሳቧ እንደ አምላክ ሐሳብ ነው " ይላሉ የሚለው ደግሞ ሁለተኛው ነው። በመቀጠልም ተናጋሪም ዳኛም እራሱ ሆኖ ይህ ጣዖት አምልኮ ነው ብሎ መንጋዎችን አስፈንጭቷል። የእግዚአብሔር ባለሟል የሆኑ ቅዱሳን እግዚአብሔር ይጠራባቸው የሆኑ ስሞችን ሲጋሩ አዲስ አይደሉም። "ቅዱስ፣አምላክ፣ ብርሃን፣መድኃኒት፣ፈራጅ ...ወዘተ የተባሉ ቃላት በህልውና የእግዚአብሔር ክብር መገለጫ ሆነው ሳሉ .....ለወደዳቸው ቅዱሳን ደግሞ እንዲሁ እኝን ቃል ሰያጎናጽፋቸው ይታያል። ለዛሬ ግን "መድኃኒት" በሚለው ቃል ላይ ብቻ ያለው እውነት ከመጽሐፍ ቅዱሳን ውስጥ እንበርብር ባሻዬ .....ናማ ተከተለኝ። ነብዩ ኢሳያስ በነብይነት ስለመመረጥ አገልግሎት የእስራኤል አምላክ የሆነው ቅዱስ እግዚአብሔር እራሱ ሰለነብዩ ኢሳያስ ክብር እና አገልግሎት በመሰከረው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ውስጥ እንዲህ ይላል። “....እስከ ምድር ዳር ድረስ #መድኃኒት ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ #ብርሃን አድርጌ ሰጥቼሃለሁ ፣ ኢሳ 49፥6" ሲል ከእግዚአብሔር ዘንድ መድኃኒት ሆኖ ለህዝብ እና አሕዛብ እንደተላከ ተጸፏል። ታድያ ይህ ክፍል የመልካም ወጣት ፕሮጀክት አዳራሽ ውስጥ ከተማቹ መጽሐፍ ቅዱሶች ውስጥ የለምን? በእዚህ የኢሳያስ ክፍል ውስጥ ያለው ቃል ኢሳያስ መድኃኒት ስለተባለ ጦዖት ነው ያስብለዋልን? ተጠየቅ ዮናቲንዚም ናማ ባሻዬ ሌላም ልጨምርልህ። ተከተለኝ የያዕቆብ ልጅ ዮሴፍ በርሃብ በደቀቁ ወገኖቹ ፊት ፣እሱንም በሸጡት ወንድሞቹ ላይ እግዚአብሔር እንዴት እንዳከበረው ሲገልጽ "እግዚአብሔርም በምድር ላይ ቅሬታን አስቀርላችሁ ዘንድ በታላቅ #መድኃኒትም አድናችሁ ዘንድ ከእናንተ በፊት ላከኝ። ዘፍ 45፥7" ታድያ ዮሴፍ ጣዖት ነውን? ኸረ እንደውም መጽሐፍ ቅዱስ በግርድፉ የሰለሞን የጥበብቅ ቃላት ሲከትብ ... “ደስ ያላት ልብ መልካም መድኃኒት ናት..ምሳ 17፥22" ሲል ይናገራል በዮናታኒዝም የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ " ደስ ያላት ልብ" ጣዖት ናት የሚል ትርጉም ይሰጣል ማለት ነው? አበስኩ ገበርኩ ። እንደውም ያን ያክል ወደ ሰፊ ክርክር ውስጥ ሳንገባ ነብዩ ኢሳያስ እንዲህ ሲል ይደመጣል "..... የገዛ ክንዴ መድኃኒት አመጣልኝ፥ ቍጣዬም እርሱ አገዘኝ። ኢሳ 63፥5" እና ዮኒ ጎፈሬው ..ታድያ ኢሳያስ የገዛ ክንዱን ለእርሶ ጦዖት ሆኖ ያመልከዋል ማለት ነውን? ባሻዬ... ቅዱስ እግዚአብሔር "እኔ ጻድቅ አምላክና #መድኃኒት ነኝ፥ ከእኔም በቀር ማንም የለም።ኢሳ 45፥21" ያለውን ቃል ሳይሽር ኢሳያስንም ሙሴንም መድኃኒት ብሎ ሲወክል በአይሳሳቴው፣ቅዱሱ፣ንጽሁ እና ፍጹሙ መጽሐፍ ዘግቦ አይተናል። ስለዚህ....ከዮናታም የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ወጣ ብለህ በህያው እግዚአብሔር ሐሳሽ መጽሐፍ ቅዱስ ስትገልጠው... አዳኝ የሆነውን አምላክ ብቻ ሳይሆን ለህጉ የተገዙ፣የወደዳቸውን፣የመረጣቸውን፣የመንግስቱ ወራሽ የስሙ ቀዳሽ የሆኑ ምክንያተ ድህነት ፣ምክንያተ ግብር የሆኑ ቅዱሳንንም (ሙሴን፣ኢሳያስን) መድኃኒት እንደሆኑ ተጽፈው ካነበብክ... ታድያ በታላቁ የታምረ ማርያም መጽሐፍ ላይ ድንግል ማርያም "መድኃኒት ናት" በሚል ቃል ተጠቅሳለች ብለህ ስለምን ታጓራለህ? እርሷ ከዮሴፍ እና ከኢሳያስያስ አትበልጥምን? ክብሯስ ከእነዚህ ቅዱሳን አይገዝፍምን ? ዮሴፍ እና ኢሳያስ እግዚአብሔርን በትንቢት ፣በራዕይ እና በቅድስና ገልጠው መድኃኒት ከተባሉ እግዚአብሔርን እራሱ በአካል የተገለጠባት ድንግል ማርያም ክብሯ ከመድኃኒትነትስ ከፍ አይልምን ባሻዬ ? እንኳን አዳራሽ ሙሉ ህዝብ ይቅርና ምድር ሙሉ መንጋ አሰልፈው ብትጮኸ የሚቀየር እውነት የለም ። ድንግል ማርያም እውነተኛውን መድኃኒት የወለደችልን ምክንያተ ድህነት የሆነች መድኃኒታችን ናት። ወለላይቱ፣አዛኝቷ ሆይ እንወድሻለን ! Next ...loading ርዕስ ሐሳቧ እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ነው ስለሚለው ደግሞ በሌላ ፓስት እናግኝህ። ድንግልን እያወደሳችሁ ልጇን እያመለካችሁ! Kune Demelash kassaye -Arba Minch

✟✟ሰይጣን የማይነካው ዕቃ ✟✟ በአንድ ሀገር ድንገት የአንድ ጠንቋይ ዝና ከዳር ዳር ተሰማ:: ሰውዬው የማያሳየው ምትሐት የለም:: አንበሳ ላለ አንበሳ ፣ ነብር ላለ ነብር ፣ የሞተ ዘመዴን ላለ የሞተ ዘመዱን ፣ የጠፋብኝን ዕቃ ከቤት ፈልገህ አምጣልኝ ላለ ዕቃውን ያመጣለታል:: እንደሚታወቀው አጋንንት ከክብራቸው የተዋረዱ መላእክት ናቸው:: መላእክት ደግሞ በፈለጉት ሁኔታ መገለጥ ይችላሉ:: ይህ ጠንቋይ የሚሰጣቸውን ገጸ ባሕርይ ተቀብለው አንዴ አንበሳ ፣ አንዴ ሰው እየሆኑ የሚተውኑት እንግዲህ አጋንንቱ ነበሩ:: የዚህ ጠንቋይ ዝና ወደ ንጉሡ ዘንድ ደረሰ:: ንጉሡ ደግሞ ክርስቲያን ቢሆንም ከመጽሐፍ ቅዱስ ይልቅ እንዲህ ያለ ተአምር እዚህ ቦታ ተፈጸመ ሲባል ለማየት የሚሮጥ ሰው ነበር:: ተአምር የሚወድ ሰው ደግሞ ክርስቲያንም ቢሆን ሰይጣን በሚሠራው ምትሐት መታለሉ የማይቀር ነው:: ስለዚህ ይህ ንጉሥ የተማረውን መጽሐፍ ቅዱስ ዘንግቶ በጠንቋዩ ምትሐት አመነ:: ይህንን የሰሙ የንጉሡ ንስሐ አባት ነገሩን ሰምተው ወደ ቤተ መንግሥት ሲሮጡ ደረሱ:: ሲደርሱ ንጉሡ ከቁም ነገር አልቆጠራቸውም:: እሱ የጠንቋዩን ትርዒት ማየት ቀጠለ:: ''እስቲ አሁን ደግሞ እእእ ነጭ ፈረስ አምጣልኝ'' ማለቱን ቀጠለ በነገሩ ያዘኑት ''ኧረ ንጉሥ ሆይ ይተዉ ፡ ይህ እኮ የሰይጣን ምትሐት ነው...'' ብለው ሊያስረዱት ሲሉ በቁጣ አስቆማቸው:: ተአምር የሚከተል ሰው መቼስ ቢነግሩት አይሰማም፡፡ ጭራሽ እንዲያው ለንስሐ አባቱ እንዲህ አላቸው፡፡ ‹‹የሰይጣን ሥራ ነው አትበሉ ፤ ቅናት ነው ይኼማ... ይልቅ እርስዎም የሚፈልጉትን ነገር ይጠይቁት ያምጣልዎት!›› አላቸው፡፡ ጠንቋዩም ‹‹የፈለጉትን ላምጣልዎት ... ምን ይፈልጋሉ ... የሞተ ዘመድ አለዎት... ወይስ ከቤትዎ.... ምን ይምጣልዎት›› አላቸው በኩራት፡፡ካህኑ ውስጣቸው በመንፈሳዊ ቅናት ተቃጠለ:: ‹‹እንግዲያውስ ፈለግኩትን ነገር ማምጣት ከቻልህ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደህ ልብሰ ተክህኖዬ ውስጥ መስቀል አለ እርሱን ይዘህልኝ ና›› አሉት፡፡ ይህን ጊዜ ጠንቋዩ ገና ድግምቱን ሲጀምር አጋንንቱ እላዩ ላይ ሰፍረው ጣሉት፡፡ በካህኑ ፊት ወደቀ፡፡ ሰይጣን ምንም ነገር ማምጣት ይችል ይሆናል፡፡ መስቀሉን ግን ማምጣት አይችልም፡፡ አባቶቻችን ሰይጣን እንኳን መስቀል ቀርቶ መስቀለኛ መንገድም አይወድም ይላሉ፡፡ የጌታችን ቅዱስ መስቀል ሆይ ቅዱስ ዳዊት እንዳለ ‹ብከ ንወግዖሙ ለኩሎሙ ጸርነ› ‹በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን!› ሰብሃት ለእግዚአብሄር //ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ "//

ጽዮንን ክበቧት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ። መዝ ፵፯ ፥ ፲፪። እንኳን ለኅዳር ጽዮን አደረሳችሁ !!!

የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ቤት መራቅ ሲጀምር ፍቅር ከእርሱ ትርቃለች ከሚያየውም ነገር ጋር ሁሉ ይጋጫል የሚጋጨው ከሰዎች ጋር ብቻ አይደለም ከተፈጥሮ ጋር፣ ከአካባቢው ጋር፣ ከራሱ ጋር ጭምር ነው፡፡ ፍቅር ከሌለ ባዶነት ነው፡፡ ፍቅር ከሌለ የውስጥ ሰላም አይገኝምና፡፡ ስለዚህ የሰው ልጅ ሆይ ሙሉ ፍቅርን እንድታገኝ ሁሌም እግሮችህን ወደ እግዚአብሔር ቤት ምራቸው ያኔ ፍፁም ሰላም ያኔ ፍፁም ፍቅር ታገኛለህና!!