4 356
Subscribers
+224 hours
+87 days
+15430 days
Posts Archive
4 356
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጾመ ነነዌን በማስመልከት ጾምና ጸሎት አወጀ።
ቅዱስ ሲኖዶስ አዋጁን ያስተላለፈው ዛሬ ከደቂቃዎች በፊት በሰጠው መግለጫ ነው።
ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ በቤተክርስቲያኗ በተከሰተው ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ መዋቅሮች በጣሰ ሁኔታ መፈንቅለ ሲኖዶስ በማድረግ በሕገወጥ መንገድ ኤጲስ ቆጶስነት ሢመት በሰጡትና በተሾመ ግለሰቦች ላይ ጥር 18 ቃለ ውግዘት ታላልፎ እንደነበር ገልጿል።
" ይሁን እንጂ እነዚህ ሕገወጥ ቡድኖች ከድርጊታቸው ሊታቀቡ አልቻሉም " ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ ከዚህም በላይ በመንግሥት ኃይሎች በመታገዝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምታስተዳድራቸውን መንበረ ጵጵስናዎችንና ቢሮዎችን በኃይል በመውረርና በመስበር ከፍተኛ ጥፋት እያደረጉ ነው ብሏል።
እንዲሁም የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆችን ፣ ሠራተኞች ካህናትና ምእመናን በማሰርና በማንገላታት ላይ ይገኛሉ ሲል ገልጿል።
ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ መንግሥት ሕግ ከማስከበር ይልቅ ለሕገ ወጥ ቡድኖች ድጋፍ በመስጠት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግና መብት ሊያስከብር አልቻለም ያለ ሲሆን " ሁሉን ማድረግ ወደሚቻለው አምላካችን በመማፀን ጸሎትና ምሕላ ማድረጉ አስፈላጊ መሆኑን ተረድተናል " ሲል አሳውቋል።
በዚህም " ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን #ጥቁር_ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፤ ጸሎትና ምሕላ እንድታቀርቡ " ሲል ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አስተላልፏል።
" ጥቁር ልብስ የምንለብሰው በመከራ መጽናት ለመግለጽ ነው " ሲልም አክሏል።
(ቅዱስ ሲኖዶስ ያወጣው መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
4 356
ስለ ጾመ ነነዌ የገዳማውያን አበው መልእክት!
(በጾም በጸሎቱ፣ በዕንባ በስግደቱ ከገዳማውያኑን ጋር ተባብረን በረከት ይቅርታ ምሕረት የምናገኝበት ይሁንልን።)
4 356
ቤተ ክርስቲያናችን እንደወትሮው ሁሉ አሁንም መከራ አልተለያትም:: በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያ እየተቀበልን ጸንተን መቆም የሚጠበቅብን ሲሆን በሚከተለው መንገድ ደግሞ ቤተ ክርስቲያናችንን እንድናግዛት በአክብሮት እጠይቃለሁ:: (መቼም ጸልዩ ማለት የዲያቆን ሥራ ነው)
የክርስቲያኖች ትልቁ መሣሪያችን እጃችንን ለጸሎት ወደ ሰማይ መዘርጋት ነው:: ዕንባችንም እንደ ራሔል ዕንባ ባሕርን ይከፍላል:: ራሳችንን በንስሓ ካዋረድንና ካለቀስን የማንቀለብሰው ነገር የለም::
የፊታችን ሰኞ የሦስት ቀናቱ ጾም ጾመ ነነዌ ይገባል::
ጾሙ ከመግባቱ አስቀድሞ ኦርቶዶክሳውያን ሁላችን ንስሓ እንግባ:: በመጪዎቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ ይህንን ያያችሁ ወንድሞቼና እኅቶቼ ሁላችሁ ንስሓ አባቶቻችሁን ምስክር አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር ተናዘዙ:: "ጌታ ሆይ ይህ የሆነው በእኔ በደል ነውና ኃጢአቴን ይቅር በለኝ" ብለን አብረን አምላካችንን እንማጸነው::
ከዚህ ንስሓ ጋር የታወጀውን የየነነዌ ጾም ጠዋት በኪዳንና ከሰዓት በቅዳሴ ማታ ደግሞ በጸሎተ ምሕላ በየአጥቢያችን እየተገኘን አምላካችንን እንማጸነው::
የቻልን ሦስቱን ቀናት እስከ ማታ እየጾምንና እየሰገድን የፈጣሪያችንን ምሕረት እንለምን::
በሦስት ቀን ጾም የነነዌን መዓት የመለሰ : በሦስት ቀን ጾም የግብፅን ተራራ ያፈለሰ የነስምዖን አምላክ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ሊመጣ ያለውን እሳት ሁሉ በቸርነቱ ይመልስልን ዘንድ በልባችን ጉልበት እንስገድ::
ከቤተ ክርስቲያን አንድነት የተለዩትን እንዲመልስልን!
በዚህ ምክንያት የሚጠፉ ነፍሳትን እንዲጠብቅልን!
የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መናወጽ የሚሻውን ሁሉ እንዲያስታግሥልን ወደ ፈጣሪያችን በጋራ እንጩኽ::
በየጊዜው ለችግራችን ስእለት እንደምንሣለው አንድ ጧፍ እንኩዋን ስለ ቤተ ክርስቲያን ሰላም ስእለት አድርገን እንጸልይ:: አርከ መሀይምናን (የምእመናን ወዳጅ) ለቤተ ክርስቲያንም ቅን መሪን የሚሠጥ ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ በፊቱ ስለሚማልሉ የዋሃን ብሎ ሰላማችንን ይመልስልን::
"እግዚአብሔር እንዳይቀየማቸው ከመዓትም ተመልሶ ፍጹም ዕረፍትን ይሠጣቸው ዘንድ ስለ በደሉ አባቶቻችንና ወንድሞቻችን እንማልዳለን" በእንተ ቅድሳት
#ነነዌ_ኢትዮጵያ
#ንስሓ_ግቡ
#ትጉና_ጸልዩ
#አንዲት_ቤተ_ክርስቲያን
#አንድ_ሲኖዶስ
#አንድ_ፓትርያርክ
#eotc_one_holy_synod
#one_church
#one_patriarch
#his_holiness_abune_mathias
#oriental_orthodox
4 356
እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን።
"" ስንክሳር ጥር ፳፩/21 ""
"ዕረፍተ ድንግል "
ጥር 20 - 2015
ዲ/ዮርዳኖስ አበበ
https://t.me/zikirekdusn/13162
4 356
4. በዚህ ጸረ ቤተ ክርስቲያን እና ኢ-ቀኖናዊ ድርጊት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ እየኖሩ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ወይም በቦታው በመገኘት የጥፋት ድርጊቱ ተባባሪ የሆኑ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በሥራ ላይ የሚገኙ ሠራተኞችን በተመለከተ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተገቢውን ክትትልና አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲሰጥ፤
5. ይህን ታሪክ ይቅር የማይለውን ሕገ ወጥ አድራጎት እና የቀኖና ጥሰት በሐሳብ፤ በገንዘብ እና በሌላ በማንኛውም ሁኔታ ድጋፍ ሲያደርጉ የቆዩ እና በማድረግ ላይ ያሉ ማናቸውም ተቋማት እና ግለሰቦች ከዚህ ሕገ ወጥ አድራጎታቸው እንዲቆጠቡ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥብቅ እያሳሰበ ይህ ባይሆን በሕግ አግባብ ተገቢው እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
6. በየደረጃው የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎች፤ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ መነኮሳት፤ አገልጋይ ካህናት፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፤ ልዩ ልዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ ማህበራት እና ምእመናን እና ምእመናት ይህን ሕገ ወጥ አድራጎት ከመከላከል እና የቤተ ክርስቲያናችሁን ደህንነት ከመጠበቅ በተጨማሪ ለዚህ ሕገ ወጥ አድራጎት ልዩ ልዩ ድጋፍ የሚያደረግ ተቋማት እና ግለሰቦችን አስፈላጊውን ክትትል እና ቁጥጥር በማድረግ የመከላከል ሥራችሁን እንድትወጡ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
7. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስምን ከፊትም ሆነ ከኃላ በመጨመር እና በመቀነስ በከፊልም ሆነ በሙሉ መጠቀም፤ ዓርማዋን፤ አድራሻዋን፤የአምልኮ እና የሥርዓት መፈጸሚያ የሆኑ ንዋያ ቅዱሳትንና አልባሳት እንዲሁም መጻሕፍት መገልገል የማይችሉ መሆኑ ታውቆ ይህንን ጉዳይ በየደረጃው ያሉ መንግሥታዊ አካላት እና የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎች ተከታትለው እንዲያስፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ ሲሆን በተጨማሪም ይህን ውሳኔ ተላልፈው በሚገኙ ማናቸውም ግለሰቦች እና ተቋማት ላይ ተገቢውን ሕግ አግባብ ተከትሎ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለማት የሚያስፈጽም ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የሕግ ባለሙያዎች በመመደብ ተገቢውን ሁሉ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
8. አሁን የተከሰተውን ችግር አስመልክቶ ዝርዝር ጥናት እና የመፍትሔ ሐሳብ የሚያቀርብ አንድ ዐቢይ ኮሚቴ በቋሚ ሲኖዶስ እንዲሰየም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
9. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ያሳለፈውን ውሳኔ ከክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጀምሮ በየደረጃው ላሉት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እንዲከናወኑ እና ይህ ውሳኔ ከሸኚ ደብዳቤ ጋር እንዲደርሳቸው ተወስኗል፡፡
10. ይህን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ክፍለ ዓለማት ለሚገኙ የቤተ ክርስቲኒቱ አገልጋዮች እና ምእመናን የግንዛቤ ማስጨበጫ የንቅናቄ መድረኮች እንዲካሔዱ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በማእከል የአህጉረ ስብከት ሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ታላቅ የንቅናቄ እና የግንዛቤ መድረክ እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
11. በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የሚገኙ መንግስታዊም ሆነ መነግስታዊ ያልሆነ ተቋማት፤ አኃት አቢያተ ክርስቲያናት፤ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት፤ የሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት፤ የዓለም አቢያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ የመላው አፍሪካ አብያት ክርስቲያናት ጉባዔ እና ሌሎች የአብያተ ክርስቲያናት እና የሃይማኖት ጉባኤዎች በሙሉ እነዚህ የተወገዙት ግለሰቦች የኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ እና ምንም አይነት የሥራ ግንኙነት የሌላቸው መሆኑ ታውቆ ማናቸውም ግንኙነት በቤተ ክርስቲያኑቱ ስም እንዳያደርጉ በጽሑፍ አንዲገለጽ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
12. እነዚህ ግለሰቦች ከሚሰጡት የተሳሳተ መረጃ አንዱ እኩይ ተግባራቸው የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ እንደሆነ ማስመሰል ሲሆን ይኽ ተግባር ሃይማኖቱን የሚወድ፣ አባቶቹን የሚያከብር እና አስተዋይ የሆነውን የኦሮሞ ሕዝብ የማይወክል፣ የራሳቸውን የሥልጣን ጥማት ለማርካት ያደረጉት ሕገወጥ የቀኖና ጥሰት መሆኑ እንዲታወቅ፤ በተጨማሪም ለሚያሠራጩት የሐሰት አሉባልታ ወደፊት ተገቢው መልስ እንዲሰጥበት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
እስከ አሁን ድረስ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጎን በመሆን አጋርነታችሁን ያሳያችሁ፣ ለቤተ ክርስቲያን አንድነት እና ሉዐላዊነት መከበር የበኩላችሁን በመወጣት መግለጫ የሰጣችሁ ሁሉ በልዑል እግዚአብሔር ስም እያመሰገንን ለወደፊቱም በጸሎታችሁ እና በመልካም አጋርነታችሁ ከጎናችን እንድትሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ
ጥር 18 ቀን 2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
4 356
1፣5-7 ፍትሕ መን አንቀጽ 4)
- ይህንም ቅዱሳን ሐዋርያት ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ በ3ኛው ቀሌምንጦስ “ኤጲስ ቆጶስ የሀገሩ ሰዎች፣ የሀገሩ ጳጳስ፣ ፈቅደውለት ይሾም፤ ቢገኙ ሦስት፣ ባይገኙ ሁለት፣ ኤጲስ ቆጶሳት ሁነው ይሹሙት” ብለዋል፡፡ ይህም ቅዱስ ሲኖዶስ በሌለበት ሀገር፣ ፓትርያርክ በሌለ ጊዜ ምእመናን እንዳይበተኑ ተብሎ የሚደረግ ነው እንጅ በቅዱስ ፓትርያርኩ ሊቀመንበርነት በመንፈስ ቅዱስ የሚመራውን የቅዱስ ሲኖዶስን ሉዓላዊ ሥልጣን በመጋፋት የሚፈጸም ከሆነ ግን ይህን ቀኖና በሕገወጥ መንገድ ለተፈጸመ ድርጊት መጥቀሱ በቅዱስ ወንጌል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል እንደመናገር ተቆጥሮ የማይሠረይ ኃጢአት መሆኑ ሊሠመርበት ይገባል፡፡ (ማቴ.12፣30-32 ሉቃስ 12፣10፣ ማርቆስ 3፡28-29 1ኛ ጢሞ 1፣13) የእነዚህ ሰዎች ተግባር በሥራ ላይ ያለውን በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ ሕጋዊ የኢትዮጵያ ቅዱስ ሲኖዶስ የመፈንቅል፣ የታላቋን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መዋቅር የመናድ፣ ሕጋዊ ተቋምን የማፍረስ ወይም የመናድ ተግባር በመሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዟል፣
- ሠለስቱ ምዕትም ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ በኒቅያ በጻፉት ቀኖና በዘጠነኛው አንቀጽ አንዱም አንዱ ኤጲስ ቆጶስነት ሊሾም ቢሻ፣ የሀገሩ ሰዎች ቢፈቅዱለት፣ የሀገሩ ጳጳስ ካልፈቀደለት ኤጲስ ቆጶስነት መሾም አይገባውም ይህን አፍርሶ ቢገኝ ሲኖዶስ ያወግዘዋል፤ ሹመቱም ይቀራል” ብለዋል፡፡ ይህም በዚህ ወቅት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ የጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ ብሔራዊትና ዓለም አቀፋዊት ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲየን ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ስልጣን በመጋፋት በድፍረት ተፈጸመ የተባለው ሹመት አስቀድሞ በአበው ቅዱሳን የተወገዘ ነው፤
- ከዚህም ጋር ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት በሚፈጸምበት ጊዜ፣ ያለ ቅዱስ ፓትርያርኩ ፈቃድ ማንም ወደ ቤተ መንግሥት እንዲሔድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን አይፈቅድም፡፡ ይህንንም የተላለፈ ቢኖር ከጳጳሳና ከኤጲስ ቆጶሳት ማንም ማን ሊቀጳጳሳቱ ሳይፈቅድለት ወደ ንጉሥ ቤት አይሒድ ወለኲሉ ዘዐለወ ዘንተ ሲኖዶስ ያወግዞ ይህን ትእዛዝ ያፈረሰውን ሲኖዶስ ያወግዘዋል” ተብሎ ስለተወሰነ ዛሬም ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እና ከቅዱስ ፓትርያርኩ ውጭ የሚደረግ ማናቸውም እንቅስቃሴ ሕገወጥ በመሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘዋል፤
- በቀኖና ቤተ ክርስቲያን … ሰው ሁሉ ማዕርጉን ጠብቆ ይኑር እንጅ፣ አንዱ ወደ አንዱ ማዕርግ አይተላለፍ፤ ይህን የሠራነውን ሥርዐት ያፈረሰውን ሰው ሲኖዶስ ያወግዘዋል ተብሎ በተጻፈው መሰረት እነዚህ ሕገወጥ አካላት በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘዋል፤
- በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 16 ንዑስ ቁጥር 30 የአጲስ ቀጶሳት መሾም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፣ በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት እንዲመረጡና እንዲሾሙ የመወሰን ሥልጣን የቅዱስ ሲኖዶስ መሆኑን የሚደነግገውን ክፍል በግልጽ የጣሰ በመሆኑ፤
- በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 37 ንዑስ ቁ.1 የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ የሚፈጸመው ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ አስፈላጊ መሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሲታመንበትና ሲወሰን ብቻ እንደሚፈጸምና መደንገጉ፤
- በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 18 ንዑስ ቁጥር 5 የቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖታዊ ሕግጋትንና ቀኖናን የሚያፋልስ ሊቀ ጳጳስ /ኤጲስ ቆጶስ/ ከአባልነት እንደሚሰረዝ በመደንገጉ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዟቸዋል፡፡
በአጠቃላይ የተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር በሕገ ሰብእም ሆነ በሕገ እግዚአብሔር ሚዛን የተወገዘ ከመሠረተ እምነት የተለየ፣ በአበው ቀኖና፣ በሕገ ቤተ ክርስቲያን እና በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር በአጠቃላይ ተቀባይት የሌለው ነው፡፡ ስለዚህ
1ኛ. በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 138 መሠረት ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጩ ወረዳ ሐሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ
1ኛ. አባ ሳዊሮስ
2ኛ. አባ ኤዎስጣቴዎስ
3ኛ. አባ ዜና ማርቆስ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ ባልተሰጣቸው ስልጣን 26 ኤጴስ ቆጰሳትን ሾመናል፤ ሲኖዶስ አቋቁመናል በማለት በማኅህበራዊ እና በብሮድካስት ሚዲያዎች በሰጡት መግለጫ የተረጋገጠ በመሆኑ በዚሁ ድርጊታቸው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያንን በማታለል የክህደት እና የኑፋቄ ተግባር በመፈጸማቸው በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ፤ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት በመሻር አውግዞ ለይቷቸዋል፡፡
በመሆኑም፡-
ሀ. ሥልጣነ ክህነታቸውና የማዕረግ ስማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ የተነሣ ስለሆነ ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀድሞ ዓለማዊ ስማቸው እንዲጠሩ፤
ለ. በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያም በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን ለይቷቸዋል፡፡
ሐ. በነዚህ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ አውግዞ በለያቸው ግለሰቦች ይመሯቸው በነበሩ አህጉረ ስብከት መንፈሳዊ አገልግሎት በማከናወን ሀገረ ስብከቱን የሚመሩ ብፁዐን አባቶችን
• ለደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት
• ለኬንያ፤ኡጋንዳ፤ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ሀገረ ስብከት
• ለኢሉ አባቦራ እና በኖ በደሌ ሀገረ ስብከት
• በሰሜን አሜሪካ ለሜኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት
• ለጉጂ፤ ምዕራብ ጉጂ እና ቦረና ሊበን ዞኖች ሀገረ ስብከት
• ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም
በአባትነት የሚመሩ አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲመደቡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ወስኗል፡፡
ይሁን እንጅ ከላይ በስም ተጠቅሰው የተወገዙት ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳውቃል፤
2. የቅዱስ ሲኖዶሱንና የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልና በመዳፈር እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ በተነሳሱ ግለሰቦች አማካኝነት የኤጲስ ቆጶስነት ሺመት አግኝተናል፤ ተሸመናል እያሉ የሚገኙ 25 መነኰሳት በሕገ ወጥ መንገድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንንን ጥሰው የተገኙ በመሆኑ አስቀድሞ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸው ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት ተሽሮ ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተወግዘው ከቤተ ክርስቲያን ተለይተዋል፡፡
3. ከነዚሁ ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት አባ ጸጋዘአብ አዱኛን ከቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዐተ ጉባኤ ስብሰባ በፊት የቀኖና ጥሰቱንና ሕገ ወጥ አድራጎቱን በመረዳትና በመጸጸት ድርጊቱን በመቃወም ለቤተ ክርስቲያኒቱ ባቀረቡት የይቅርታ አቤቱታ መሠረት ቅዱስ ሲኖዶሱ ይቅርታውን የተቀበላቸው ሲሆን እንደሳቸው ሁሉ ከላይ የተወገዙት 25 ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን እንገልጻለን
4 356
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ እንዲሁም በሕገ ቤተክርስቲያን አንቀጽ 19 ንዑስ ቁጥር 3 አስቸኳይና ድንገተኛ ጉዳይ ሲያጋጥም ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያደርግ በተደነገገው መሠረት ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የሃይማኖት፣ የቀኖና እና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡
ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነች ቅድስት ቤተክርስቲያን ሕዝብና አሕዛብን፣ ሰውና መላእክትን፣ ፍጡራን እና ፈጣሪን ይልቁንም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ልዩነት አጥፍቶ የሰው ልጅ ሁሉ በቋንቋ፣ በቀለምና በጐሣ ሳይከፋፈሉ በአንድነት ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና አግኝተው ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማህፀነ ዮርዳኖስ የተወለዱ በማየ ገቦ የተጠመቁ የቤተ ክርስቲያን ልጆች እንዲሆኑ ልዩነት የሌለባትን ዘለዓለማዊት መንግሥተ እግዚአብሔር እንዲወርሱ በደመ ክርስቶስ የተመሠረተች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ የተነሣባትን ፈተና ሁሉ አልፋ ከእኛ ዘመን ደርሳለች፤
ምንም እንኳ ከቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ ከኦርቶዶክስ ትምህርተ ሃይማኖት ፈጽሞ በተለየ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያንን በጐሣና በቋንቋ የመለየት ሂደት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንግዳ ክስተት ቢሆንም ቤተ ክርስቲየን ከሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ጠባይዋ በተለየ፣ ታሪኳንና ሥርዓቷን በማይመጥን፣ ከሕግ መንፈሳዊ፣ ከሕግ ጠባይአዊ እና ከሕገ አእምሮ በወጣ መልኩ የደረሰባት ጥቃት፣ እና የመፈንቅለ ሲኖዶስን ተግባር ቅዱስ ሲኖዶስን እጅግ አሳዝኖታል፤
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ ውስጥ ለሀገር አንድነት፣ ለፍትሕ፣ ለጥበብ፣ ለሕዝብ ትስስር፣ ለማኅበራዊ ዕድገት፣ ለጤና፣ ለሥነ-ምግባር መሠረት እና ዐምድ፤ ምሰሶ እና ማገር ሆና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተፈራች፣ የተከበረች እና የተወደደች፤ ዕሴቷ እና ዕምቅ የዕውቀት ሀብቷ በምሁራን የታወቀ፣ በትምህርተ ዓለም ሳይቀር የተቀረጸ፤ በእውነተኛ ሊቃውንት የተመሠከረ፣ ቅርሶቿ የተመዘገቡላት ስትሆን፤
በቅርቡ ራስዋ በሾመቻቸው በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ከፍተኛውና ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲወጡ አደራ በተሰጣቸው ሊቃነ ጳጳሳት መሠረተ እምነትን፣ ሃይማኖታዊ ቀኖናን፣ የአስተዳደር ሥርዓት ሁሉ በጣሰ፣ መንገድ በማኅበረሰብ ዕድገትና አስተዳደር ውስጥ ከሕዝብ ጋር የቆመች፣ ከፖለቲካ የጸዳች መንፈሳዊና ሕዝባዊት ተቋምነቷን በመካድ ከፍተኛ የሆነ ሕገ ወጥ ድርጊት፣ ተቋምን የመናድና መዋቅሯን የማፍረስ ተግባር ተከናውኗል፡-
በዚሁ መሠረት፡-
ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጡ ወረዳ ከወሊሶ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው አሮ ባለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጸመውን እጅግ አሳዛኝ እና ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፤ ሕገ ወጥ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አስመልከቶ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት አስቸኳይ የምልዐተ ጉባዔ አድርጓል፤
ቅዱስ ሲኖዶስም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ያሉ መላው አህጉረ ስብከት፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባዔ፣ የሊቃውንተ ጉባኤ፤ የሕግ አገልግሎት መምሪያ፤ በዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የወጣቶች እና የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት፣ መንፈሳውያን ማኅበራት፤ የምእመናን እና አገልጋዮች ኅብረት፣ ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በደብዳቤ፣ በሚዲያ እና በአካል ከሰጡት ምክረ ሐሳብ እና የአቋም መግለጫ በመነሣት፤
በሀገር ውስጥ እና በውጪው ዓለም የሚገኙ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ወዳጆች፣ በተለይም የግብጽ እስክንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶከስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ፓትርያርክ ውጭ የሚደረግ ሢመትን እንደማይቀበሉና ዕውቅና እንደማይሰጡ በላኩት የአቋም መግለጫ፣ የኤርትራ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶከስ ቤተ ክርስቲያን፣ እና የሌሎች አኀት ኦርቶዶከስ አብያተ ክርስያናት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፣ ዓለም አቀፍ መንፈሳዉያን ተቋማት፣ የልማት እና የበጎ አድርጎት አጋር ድርጅቶች፤ ድርጊቱን በማውገዝ የማይቀበሉት መሆኑን የአቋም መግለጫ በመላክ ባሳዩት አጋርነት፤
አስቀድሞ እንደተገለጸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በደመ ክርስቶስ ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈተና የኖረችበት ጊዜ እንደሌለ ቅዱሳት መጻሕፍትና የታሪክ መዛግብት ሲመሰክሩ በዘመነ ሐዋርያት ቢጽ ሐሳውያን፣ በዘመነ ሊቃውንት የተለያዩ መናፍቃን፣… በየጊዜው እየተነሡ ሲፈታተኗት ኑረዋል፡፡ አሁንም በግልጽ እንደሚታየው ከውጭም ከውስጥም በተደራጁ ምንደኞች በመፈተን ላይ ትገኛለች፡፡
ለዚህም ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም. በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ በሶዶ ዳጩ ወረዳ፣ ሀሮ በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአባ ሳዊሮስ መሪነት እጅግ አሳዛኝ ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፣ ሕገ-ወጥ፣ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አንዱ ሲሆን፤ በአባ ሳዊሮስ መሪነት የተፈጸመው የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት ፳፮ መነኰሳትን ከቀኖና የወጣ ሢመት በመስጠትና ሊቃነ ጳጳሳት በሚመሯቸው አህጉረ ስብከት በሕገ ወጥ መንገድ በመመደብ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አልፎ ሃይማኖትን የሚከፋፍል፤ የሀገር አንድነትን የሚሸረሽር እና የሚያፈርስ፣ ምእመናንን ከምእመናን፣ ካህናትን ከካህናት፣ ሊቃውንትን ከሊቃውንት ወጣትን ከወጣት … የሚያጋጭና ደም የሚያፋስስ ፀጥታን የሚያናጋ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ተገንዝሟል፤ በመሆኑም፤
- ከላይ እንደተገለጸው ሐዋርያት በሦስተኛው ቀሌምንጦስ በሃያ አምስተኛው አንቀጽ “በአውራጃው ሁሉ ያሉ ኤጲስ ቆጶሳት አለቃቸው ማንም እንደሆነ ማወቅ ይገባቸዋል፡፡ አለቃ ያድርጉት፤ ያለ ፍቃዱ ጥቃቅኑንም ደጋጉንም ሥራ ምንም ምን አይሥሩ፤ እርሱም ዳግመኛ ኤጲስ ቆጶሳቱ ሳይፈቅዱ ደጋጉን ሥራ አይሥራ ጥቃቅኑን ቢሠራ እዳ የለበትም፡፡ ሁሉም እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ ሁነው በአንድነት ይኑሩ” ብለው ወስነዋል፡፡ እነዚህ ሕገ ወጥ አካላት ይህን የሐዋርያት ቀኖናን በመሻራቸው፡፡
- ሁለተኛም በአርባ አራተኛው አንቀጽ “ሊቀጳጳሳት (ፓትርያርክ) ኤጲስ ቆጶሳት በተሾሙባቸው አገሮች የሚሠሩትን ሥራ፣ የሚያዙትን ትእዛዝ ይመርምር፡፡ የማይገባ ሥራ ሠርተው፣ የማይገባ ትእዛዝ አዝዘው፣ ቢያኝ ለውጦ የተገለጸለትን ትእዛዝ ይዘዝ፡፡ እርሱ ለሁሉ የሹመት አባታቸው ነውና፤ እነሱም ልጆቹ ናቸውና…” ብለዋል፡፡ ይህን ኢ-ቀኖናዊ ሥርዐተ ሲመት የፈጸሙት ግለሰቦች በሕገወጥ መንገድ በአደባባይ የቅዱስ ሲኖዶስን ሉዓላዊ ሥልጣን እና የቅዱስ ፓትርያርኩን መብት በመጣሳቸው፡፡
- ሢመተ ክህነትን በተመለከተ “ወአልቦ ዘይነሥእ ክብረ ለርእሱ ዘእንበለ ዘጸውዖ እግዚአብሔር … እንደ አሮን በእግዚአብሔር ከተጠራ በቀር ማንም ለራሱ ክብርን የሚወስድ የለም” (ዕብ 5፤4) እንደሚለው የእግዚአበሔር ቃል ከዲቁና ጀምሮ እስከ ፓትርያርክ ሹመት ድረስ ያለው ሹመት በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር መጠራቱን የሚጠይቅ ሲሆን እንኳንስ ለተሿሟዎች ለመራጮችና ለአስመራጮች በቀኖና ቤተ ክርስቲያን የተወሰነ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መስፈርት ያለው፣ መሆኑ ለሁሉም ግልጽ ነው፡፡ ይህንም ቅዱስ ጳውሎስ በጻፈው መልእክቱ በሰፊው ገልጾታል፡፡ (ጢሞ.3፣10፣ ቲቶ፣
4 356
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለ3 ቀናት የሚቆይ ጸሎት አወጀች፡፡
በዛሬው ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻ ጸሎት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ቅድስት ማርያም ገዳም ከተጠናቀቀነ በኋላ ሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሦስት ቀናት የጸሎትና የሱባኤ ጊዜ እንዲሆን አዋጅ መታወጁን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ( ዶ/ር ) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል፡፡
4 356
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ(ዶ/ር) በሕገ ወጥ እንቅስቃሴው ውስጥ የተሳተፍ ሌሎች አባቶችም እንዲመለሱ ጥሪ አቀረቡ።
ሰው ሆኖ የማይሳሳት የለም ያሉትና የይቅርታ ደብዳቤውን የተቀበሉት የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ(ዶ/ር)ቤተ ክርስቲያን ችግር የለም አንልም ነገር ግን ችግሩ የሚፈታው በንስሐ በይቅርታ አንድ ሆነን ስናገለግል ነው ብለዋል።
ጸሎታችንን እንቀጥል ሕያው እግዚአብሔር ይሰማናል ያሉት ብፁዕነታቸው ሌሎች አባቶችም እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል።
አባ ጸጋ ዘአብ በበኩላቸው ባለፉት ቀናት አይደለም ኦርቶዶክሳውያን የሌላ ቤተ እምነት ተከታዮች እየደወሉ ራሴን እንድወቅስ አድርገውኛል ብለዋል።
እነሱ ለሰጡኝ "ክብር" የማልገባ በመሆኑ የተሰጠኝን አስኬማና አልባስ አስረክባለሁ ሲሉም ተናግረዋል።
4 356
ሰበር ዜና
ከቀኖናና ከህግ ውጪ በተደረገው ሲመት ከተሾሙት መካከል አባ ጸጋዘአብ አዱኛ በዚህ ሰዓት ቤተክርስቲያንን ይቅርታ ለመጠየቅ ቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ተገኝተው ለብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር የይቅርታ ደብዳቤ አስገብተዋል።
በደብዳቤአቸውም ያሳደገቻቸውን፣ ያስተማረቻቸውንና ለዚህ ክብር ያበቃቻቸውን ቤተክርስቲያን ማሳዘናቸውን ገልጸው ቅዱስ ሲኖዶስ ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።
ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
4 356
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መግለጫ ተሰጠ ።
መግለጫውን ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) የሠጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፖትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት; ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ : በመንበረ ፓትርያርክ የተገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ናቸው።
ቅዱስነታቸው ዛሬ ማለዳ በተሰማው ሕገ ወጥ "ሢመተ ጳጳሳት" ጉዳይ በሰጡት መግለጫ ጉዳዩ ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ውጪ በሕገወጥነት የተከናወነ መሆኑን በመግለጽ :-
1. በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት በአስቸኳይ ወደ መንበረ ፓትርያርክ እንዲመጡ ጥሪ ቀርቧል።
2. መንግሥት ክስተቱ በሀገር ላይ ጭምር የሚያስከትለውን ጉዳት ተመልክቶ በጉዳዩ ላይ ሕጋዊ ሓላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
3. ምዕመናን ቤተክርስቲያንን ከመቸውም ጊዜ በላይ በንቃት በሀሣብና በጸሎት እንዲጠብቁ ቅዱስነታቸው ጥሪ አቅርበዋል።
ምንጭ: EOTC TV
4 356
+++ ‹‹በእግዚአብሔር ፈንታ›› +++
የአእምሮ ሕመም ሕክምና ይሰጥባቸው ከነበሩ ማዕከላት በአንዱ እንዲህ ሆነ፡፡ ነርሷ ሕመምተኛውን ‹‹አንተ ማን ነህ?›› ስትል ትጠይቀዋለች፡፡ እርሱም ‹‹ናፖሌዎን›› ነኝ ብሎ ይመልሳል፡፡ ‹‹ናፖሌዎን መሆንህን ማን ነገረህ?›› ብትለው ‹‹እግዚአብሔር ነዋ›› ሲል ፈርጠም ብሎ መለሰ፡፡ ይህን ጊዜ ከአጠገባቸው ሆኖ ምልልሱን ይሰማ የነበረ ሌላ ታካሚ ድንገት ጣልቃ ገብቶ ‹‹ኸረ እኔ አልነገርኩት›› አለ፡፡
ይህን ታሪክ ስትሰማ ፈገግ አላልህም? ‹ሰው ራሱን ‹‹እንደ እግዚአብሔር›› አድርጎ የሚቆጥረው አእምሮውን ሲታመም ብቻ ነው› ብለህስ አላሰብህም፡፡ እውነታው ግን ሌላ ነው፡፡ ጤነኛ አእምሮ እንዳለን የምናስብ ብዙዎቻችን ኑሯችን እና እንቅስቃሴያችንን ብንፈትሽ ነገረ ሥራችን ሁሉ ‹‹በአምላክ ፋንታ›› ነው፡፡ አፍ አውጥተን ‹‹እኔ እግዚአብሔር ነኝ›› አንበል እንጂ እንዲህ ከማለት የማይተናነስ ሥራ ግን እንሠራለን፡፡
ፍርድ የእግዚአብሔር ነው፡፡ እኛ ግን ወንድሞቻችን ላይ በመጨከን ስንት ጊዜ በክርስቶስ የፍርዱ ዙፋን ላይ ተቀመጥን፡፡ የሰውን ድካም ሳንረዳ ፈጥነን በመፍረድ ስንት ጊዜ ራሳችንን በእግዚአብሔር ቦታ አስገባን? እስኪ ዮሴፍን እናስበው፡፡ ወደ ግብጽ ባሪያ አድርገው በግፍ የሸጡት ወንድሞቹ ከአባታቸው ሞት በኋላ እርሱ ወደ ተሾመበት ግብጽ መምጣት በፈለጉ ጊዜ፣ የክፋታችንን ብድራት ያስከፍለናል ብለው ስለፈሩ ‹‹በደላችንን ተውልን›› ሲሉ መልእክተኛ ልከውበት ነበር፡፡ የዋሁ ዮሴፍም ይህንን ሲሰማ እያለቀሰ እንዲህ አላቸው ‹‹አትፍሩ፤ እኔ በእግዚአብሔር ፋንታ ነኝን?››፤ አይደለም ሳታውቀው ዐውቀኸው እንኳን በበደለህ ወገንህ ላይ ለመፍረድ ልብህ በከጀለህ ጊዜ ለራስህ የዮሴፍን ጥያቄ ጠይቀው፡፡ ‹‹እኔ በእግዚአብሔር ፋንታ ነኝን?›› (ዘፍ 50፡19)
ራሱን መምራት ያልቻለ ደካማ ሌላው ላይ በፍርድ ለመሠልጠን ሲሞክር ከማየት በላይ እግዚአብሔርን ምን የሚያሳዝን ነገር አለ?
ሁሉን የሚያውቅ እግዚአብሔር ነው፡፡ ነገር ግን የሁሉ ጥበብ መፍለቂያዎች እንደ ሆንን፣ ከእኛ የተሠወረ አንዳች እንደሌለ እያሰብን ‹‹አምላክ አምላክ የምንጫወት›› ጥቂቶች አይደለንም፡፡ የእኛ ጣት ያልገባበት ሁሉ የማይጥመንና ትክክል የማይመስለን፣ እኛ ካልመራን፣ የእኛ ቡራኬ ከሌለበት የምናራክስ፣ ‹‹አላውቅምን›› የማናውቅ፣ ብዙኃኑን እንደ ጨዋ (ምንም የማያውቅ) የምንቆጥር አያሌ ነን፡፡ የሚያሳዝነው ግን ዓለም በአንድ ወይም በጥቂት ሰው ፈቃድ ስላልተገነባች በአንድ ወይም በጥቂቶች ፈቃድ ብቻ ልትመራ አትችልም፡፡ ሁሉን በሁሉ ማድረግ የሚችለው ሁሉን የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡
‹‹ዕረፉ፤ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ ዕወቁ›› መዝ 46፡10
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
selam@dnabel.com
ጥቅምት 15/ 2015 ዓ.ም.
አዲስ አበባ
ድረ ገጹን ይጎብኙ
https://dnabel.com
ቴሌግራም
https://t.me/Dnabel
4 356
"በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።...ቃልም ስጋ ሆነ" ይህን ቃል ያነበበ ሰው ግን እንዴት ይስታል፤ እግዚኦ አታድርስ ማለት ነው፤ "አቤቱ ምሳሌ ስጠኝ እንጂ ምሳሌ አታድርገኝ" የምትለዋ ጸሎት እንዴት መልካም ነች፤ በነገራችን ላይ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን የጻፈው በኤፌሶን ነው ዘመኑ መቼ ነው ቢሉ ጌታ ባረገ በ 30 ዓመቱ፤ የጻፈበት ቋንቋ ጽርዕ ይባላል፤ እናም ወንጌሉን ሲጀምር በመጀመሪያ ቃል ነበር ብሎ መጻፍ ሲጀምር ራዕይ ያያል ከዋንኞቹ መልአክት አንዱ ከትልቅ ሐይቅ ዳር ቁጭ ብሎ የሐይቁን ውኃ በእንቁላል ቅርፊት እየጨለፈ ወደ መሬት ያፈሳል ቅዱስ ዮሐንስ ጠጋ ብሎ ምን እየሰራህ ነው ይለዋል የሐይቁን ውኃ ወደ መሬት እፍስሼ ለመጨረስ ነው ይለዋል ይህ እንዴት ይሆናል ደግሞም በእንቁላል ቅርፊት ይለዋል፤ ይህ ሐይቅ ፍጡር ነው ከረጅም ዘመን በኋላ ሊሳካሊኝ ይችላል አንተስ አለክ አይደል ቢቀዱት የማያልቀውን ቢጀምሩት የማይጨርሱትን የመለኮት ነገር የምትመራመር አለው በዚህ ጊዜ ነው ዮሐንስ የጀመረውን አቁሞ ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። ብሎ ወደ ሚስጢረ ስጋዌ የገባው ዮሐ 1፤14።
በረከቱ በሁላችንም ላይ ይደርብን አሜን !!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን። ይቆየን
4 356
የሐመሮች ቃል ለሊቀጳጳሱ =የእኛ አምላክ ቦርጆ ነው። የአንተ አምላክ ከቦርጆ ከበለጠ ነገ ዝናብ እንዲያዘንብ ንገረው።
~~
በአንድ ወቅት የሰሜን ኦሞ ሀገረሰብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት አባት ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ ሐመሮች መንደር ይሄዳሉ።
ክላሽ ታጥቀው፤መፋቂያ ጥርሳቸው ላይ ሰክተው ለአፍረተ ስጋቸው ብቻ ብጣሽ ጨርቅ ገላቸው ላይ ጥለው በእዛ ሐሩር በሆነው በረሐ እራቁታቸውን የሚሄዱ የሐመር አርብቶ አደር ወጣቶቸው ጥቁር ቀሚስ ከጥቁር አስኬማ ጋር ያጠለቁትን ሊቀ ጳጳስ እንደ ልዩ ፍጥረት በአግራሞት ያያሉ።
በሐመሮች መንደር ለሐዋርያዊ አገልግሎት መጥቻለው ተብሎ ዝም ብሎ መስበክ አይቻልም። ምንአልባትም በድፍረት አደርጋለው ከተባለም ህይወትን የሚያስገብር ታላቅ ድፍረት ይሆናል። ለምንም ዓይነት መንግስታዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ተግባር ቅድሚያ የሐመር መሪ የሆኑት በዕድሜ የጎለመሱት አባትን ፍቃድና ይሁንታ ማግኘት ግዴታ ነው።
ሊቀ ጳጳሱም የሐመሮችን ባለአባት ለማግኘት ወደ ሐመሮች መሪ እልፍኝ ውስጥ ከአስተርጓሚያቸው ጋር ገቡ። የሐመር ባለአባትም ጥቁር በጥቁር ሆነው የመጡትን ሊቀ ጳጳስ ተመለከቱ። ቁርበት እንዲነጠፍላቸው ሎሌያቸውን አዘዙ። ለሊቀ ጳጳሱ ተነጠፈላቸው። በተነጠፈውም ቁርበት ላይ ሊቀ ጳጳሱ እንዲቀመጥ አዘዙ።
ሊቀ ጳጳሱ የመጡበትን ለሐመሩ ባለአባት አስረዱ፤"የሐመር አባላትን ጥምቀት አስጠምቀው ኦርቶዶክስ ለማድረግ እንደሚፈልጉ" ተናገሩ።
የሐመር ባላባትም ለረጅም ሰዓት በዝምታ ሆነው ሰሙ። በስተመጨረሻም አንድ ቃል ከሐመር ከአንደበታቸው አወጡ። ......"ዝናብ ከዘነበ ሣር ይበቅላል። ሣር ካለ ከብት ሣሩን ይመገባል። ከብት ካለ ወተት እና ሥጋ አለ። ወተት እና ሥጋ ካለ ደግሞ ሰው ይኖራል።ስለዚህ የእኛ አምላክ ቦርጆ ነው። ዝናብ እያዘነበ ከብቶቻችንን የሚያኖረው እሱ ነው።በእዚህ ወር ውስጥ ግን ለብዙ ቀናት ዝናብ ጠፍቷል።ቦርጆ ተጣልቶናል መሠለኝ። ነገር ግን የአንተ አምላክ የእኛ አምላክ ከሆነው ቦርጆ የሚበልጥ ከሆነ ነገ ዝናብ እንዲያዘንብ ንገረው።" ሲል ሊቀ ጳጳሱን አጣብቂኝ ውስጥ ከተቱቻቸው።
የወንጌል አንቀጽ ተጠቅሶ፤መጸሐፍት ተዘርግቶ ማስተማር የማይቻልበት ማህበረሰብ ውስጥ በምንም ነገር ወንጌልን ማስረዳት እንደማይቻል ያወቁት ሊቀ ጳጳሱ እግዚአብሔር ይህን ህዝብ ከወደደ ዝናብ አዝንቦ ለቤቱ እንዲጠራቸው ለመኑ።
የእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ ሆኖ በነጋታው ምድርን የሚያረሰርስ ዶፍ ዝናብ ዘነብ ። የሐመሩም ባላባት ተደነቁ። በንጋታው ሊቀጳጳሱን ጠርተው ተደንቀው አመሰገኑ። የሊቀ ጳጳሱንም እጅ ይዘው ሰፊ ባዶ ቦታ በጦቃሚ ጣታቸው እያመላከቱ "እኔ አርጅቻለውኝ ፤መሄጃዬም ደርሷል። አንተ ቤት ሠርተህ ህዝቤን ጠብቅ" ሲሉ ትንቢት የሚመስል ቃል ለሊቀ ጳጳሱ አሳሳቡ። ቤተክርስቲያንም በስፍራው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሠራ።ሐመሮችም መጥተው እንዲጠመቁ በሀመር ባላባት በኩል አዋጅ ታወጀ። የባለአባታቸውን ድምጽ የሰሙ ሐመሮች ከብታቸውን ትተው ወደ መቅደስ መጥተው የካህናት መዳፍ እስኪዝል ድረስ ተጠመቁ።
እልፍ ነፍሳት ዳኑ። የሐመሩም ባላባት ህዝቤን ጠብቅ ብሎ በነገሩት ትንቢት በሚመስም ቃላቸው ስርዓተ ጥምቀት ከተፈፅሞላቸው በኃላ ይህችን ዓለም ተሰናበቱ፣ ከካራን ወጥተው ከነዓንን ወረሱ።
ትላንት በእዚህ መልኩ ሐመር ላይ የተጀመረው ሐዋርያ አገልግሎት ዛሬ ከ90% በላይ ሐመሮችን ኦርቶዶክስ ማድረግ ተችሏል። የሐመር ልጅ የሆኑ ዲያቆናት እና ካህናትን ፈርተዋል።
እንደ ሙሴ ጸሊም የመሳሳሉ ታላላቅ ገዳማት በሐመሮች መንደር ተገድሟል። ይህ የወንጌል እሳት
ኦሞ ዛሬም ተቀጣጥሎ በዓመት እስከ 50ሺህ አርብቶአደሮች ሐብተ ወልድ ስመ ክርስትና ማግኘት ችለዋል።ዛሬ ወደ ሐመር የሚሄድ ቱሪስት ኢቫንጋዲን ብቻ ተመልክቶ ሳይሆን የሚመለሰው ታላላቅ ገዳማትንም ተሳልሞ በረከት ያፍሳል።።ቅድስ ቤተክርስቲያን ሐመር ላይ ተቃዋሚዎቿን ዘርራ፣የሚፃረሯትን ጥላ በአሸናፊነት ተሰይማለች።
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
በደቡብ ኢትዮጵያ ካለች ቤተክርስቲያን የታየ
4 356
የሐመሮች ቃል ለሊቀጳጳሱ =የእኛ አምላክ ቦርጆ ነው። የአንተ አምላክ ከቦርጆ ከበለጠ ነገ ዝናብ እንዲያዘንብ ንገረው።
~~~~~~
በአንድ ወቅት የሰሜን ኦሞ ሀገረሰብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት አባት ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ ሐመሮች መንደር ይሄዳሉ።
ክላሽ ታጥቀው፤መፋቂያ ጥርሳቸው ላይ ሰክተው ለአፍረተ ስጋቸው ብቻ ብጣሽ ጨርቅ ገላቸው ላይ ጥለው በእዛ ሐሩር በሆነው በረሐ እራቁታቸውን የሚሄዱ የሐመር አርብቶ አደር ወጣቶቸው ጥቁር ቀሚስ ከጥቁር አስኬማ ጋር ያጠለቁትን ሊቀ ጳጳስ እንደ ልዩ ፍጥረት በአግራሞት ያያሉ።
በሐመሮች መንደር ለሐዋርያዊ አገልግሎት መጥቻለው ተብሎ ዝም ብሎ መስበክ አይቻልም። ምንአልባትም በድፍረት አደርጋለው ከተባለም ህይወትን የሚያስገብር ታላቅ ድፍረት ይሆናል። ለምንም ዓይነት መንግስታዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ተግባር ቅድሚያ የሐመር መሪ የሆኑት በዕድሜ የጎለመሱት አባትን ፍቃድና ይሁንታ ማግኘት ግዴታ ነው።
ሊቀ ጳጳሱም የሐመሮችን ባለአባት ለማግኘት ወደ ሐመሮች መሪ እልፍኝ ውስጥ ከአስተርጓሚያቸው ጋር ገቡ። የሐመር ባለአባትም ጥቁር በጥቁር ሆነው የመጡትን ሊቀ ጳጳስ ተመለከቱ። ቁርበት እንዲነጠፍላቸው ሎሌያቸውን አዘዙ። ለሊቀ ጳጳሱ ተነጠፈላቸው። በተነጠፈውም ቁርበት ላይ ሊቀ ጳጳሱ እንዲቀመጥ አዘዙ።
ሊቀ ጳጳሱ የመጡበትን ለሐመሩ ባለአባት አስረዱ፤"የሐመር አባላትን ጥምቀት አስጠምቀው ኦርቶዶክስ ለማድረግ እንደሚፈልጉ" ተናገሩ።
የሐመር ባላባትም ለረጅም ሰዓት በዝምታ ሆነው ሰሙ። በስተመጨረሻም አንድ ቃል ከሐመር ከአንደበታቸው አወጡ። ......"ዝናብ ከዘነበ ሣር ይበቅላል። ሣር ካለ ከብት ሣሩን ይመገባል። ከብት ካለ ወተት እና ሥጋ አለ። ወተት እና ሥጋ ካለ ደግሞ ሰው ይኖራል።ስለዚህ የእኛ አምላክ ቦርጆ ነው። ዝናብ እያዘነበ ከብቶቻችንን የሚያኖረው እሱ ነው።በእዚህ ወር ውስጥ ግን ለብዙ ቀናት ዝናብ ጠፍቷል።ቦርጆ ተጣልቶናል መሠለኝ። ነገር ግን የአንተ አምላክ የእኛ አምላክ ከሆነው ቦርጆ የሚበልጥ ከሆነ ነገ ዝናብ እንዲያዘንብ ንገረው።" ሲል ሊቀ ጳጳሱን አጣብቂኝ ውስጥ ከተቱቻቸው።
የወንጌል አንቀጽ ተጠቅሶ፤መጸሐፍት ተዘርግቶ ማስተማር የማይቻልበት ማህበረሰብ ውስጥ በምንም ነገር ወንጌልን ማስረዳት እንደማይቻል ያወቁት ሊቀ ጳጳሱ እግዚአብሔር ይህን ህዝብ ከወደደ ዝናብ አዝንቦ ለቤቱ እንዲጠራቸው ለመኑ።
የእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ ሆኖ በነጋታው ምድርን የሚያረሰርስ ዶፍ ዝናብ ዘነብ ። የሐመሩም ባላባት ተደነቁ። በንጋታው ሊቀጳጳሱን ጠርተው ተደንቀው አመሰገኑ። የሊቀ ጳጳሱንም እጅ ይዘው ሰፊ ባዶ ቦታ በጦቃሚ ጣታቸው እያመላከቱ "እኔ አርጅቻለውኝ ፤መሄጃዬም ደርሷል። አንተ ቤት ሠርተህ ህዝቤን ጠብቅ" ሲሉ ትንቢት የሚመስል ቃል ለሊቀ ጳጳሱ አሳሳቡ። ቤተክርስቲያንም በስፍራው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሠራ።ሐመሮችም መጥተው እንዲጠመቁ በሀመር ባላባት በኩል አዋጅ ታወጀ። የባለአባታቸውን ድምጽ የሰሙ ሐመሮች ከብታቸውን ትተው ወደ መቅደስ መጥተው የካህናት መዳፍ እስኪዝል ድረስ ተጠመቁ።
እልፍ ነፍሳት ዳኑ። የሐመሩም ባላባት ህዝቤን ጠብቅ ብሎ በነገሩት ትንቢት በሚመስም ቃላቸው ስርዓተ ጥምቀት ከተፈፅሞላቸው በኃላ ይህችን ዓለም ተሰናበቱ፣ ከካራን ወጥተው ከነዓንን ወረሱ።
ትላንት በእዚህ መልኩ ሐመር ላይ የተጀመረው ሐዋርያ አገልግሎት ዛሬ ከ90% በላይ ሐመሮችን ኦርቶዶክስ ማድረግ ተችሏል። የሐመር ልጅ የሆኑ ዲያቆናት እና ካህናትን ፈርተዋል።
እንደ ሙሴ ጸሊም የመሳሳሉ ታላላቅ ገዳማት በሐመሮች መንደር ተገድሟል። ይህ የወንጌል እሳት
ኦሞ ዛሬም ተቀጣጥሎ በዓመት እስከ 50ሺህ አርብቶአደሮች ሐብተ ወልድ ስመ ክርስትና ማግኘት ችለዋል።ዛሬ ወደ ሐመር የሚሄድ ቱሪስት ኢቫንጋዲን ብቻ ተመልክቶ ሳይሆን የሚመለሰው ታላላቅ ገዳማትንም ተሳልሞ በረከት ያፍሳል።።ቅድስ ቤተክርስቲያን ሐመር ላይ ተቃዋሚዎቿን ዘርራ፣የሚፃረሯትን ጥላ በአሸናፊነት ተሰይማለች።
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
በደቡብ ኢትዮጵያ ካለች ቤተክርስቲያን የታየ
