West Gojjam Zone Education Department/ምዕራብ ጎጃም ዞን ትም/መምሪያ
Open in Telegram
Education
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
1 440
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ተፈታኝ ተማሪዎች እንደ ሙሽራ ናቸው በቅርብ አድርገን ልንከባከባቸው፣ ልንመክራቸው እና ልናግዛቸው ይገባል።
===============================================
የምዕ/ጎጃም ዞን ትም/መምሪያ ለሰሜን ጎጃም ትም/ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና የ12ኛ ክፍል አስፈታኝ ርዕሳነ መምህራን ጋር ስለ ቀጣዩ አገር አቀፍ ፈተና ዝግጅት ውይይቱን በባህርዳር ከተማ አድርጓል። በመድረኩም የሰ/ጎጃም ዞን ብልጽግና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኝነት ተገኝተው አወያይተዋል።
ለ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ እና 12ኛ ክፍል በተሰጠው ሞዴል ፈተና በተፈታኝ ተማሪዎች ላይ የተለዩ ጥንካሬ እና ክፍተቶች ላይ ውይይት ተደርጓል። በስራችን ልክ የተማሪው ስነ-ባህሪ እና የአዕምሮ ዝግጅት በምን ያህል እንደተቀየረ በተሰጡት ፈተናዎች ያሳየው ለውጥ ምን እንደነበር እና ክፍተቶችን በመለየት ለቀጣዩ ፈተና በቀሪ ቀናት መሞላት እናዳለብን ውይይት ተደርጓል።
ይልማና ዴንሳ ወረዳ ላይ የ12ኛን ክፍል ተማሪዎችን ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ ከ90 በላይ ውጤት ያላቸውን ፈትሾ በማውጣት የስፔሻል ስፔሻል 324 ተማሪዎችን ፈትሾ በማውጣት የአዳር መረሃግብር መያዙን እና በተመረጡ መምህራን እየታገዙ መሆኑን ኃላፊው አቶ በቃሉ ገልጸዋል።
ጎንጅ ቆለላ 45 የተመረጡ ተማሪዎችን የአዳር ፕሮግራም በማመቻቸት የቁርስ፣ ምሳና እራት ወጭን ሸፍናው እየደገፉ መሆኑ እና የሞዴል ፈተና ጥያቄዎች በመምህሮቻቸው አማካኝነት እየተሰራላቸው መሆኑ፣ በተጨማሪም ለስነ ልቦና ዝግጅታቸውን የበለጠ ለማጠንከር በቀድሞ ተማሪዎች ኦሬንቴሽን ለመስጠት እቅድ መያዙን የጸ/ቤት ኃላፊ አቶ መንገሻ የገለፁ ሲሆን። ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከክልላዊ ሞዴል ፈተና በተጨማሪ በትምህርት ቤቱ መምህራኖቻቸው premodel ተዘጋጅቶ የተፈተኑ ሲሆን ውጤቱንም ተተንትኖ ክፍተት የተለየበታና በዛ ልክ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አክለው ገልፀዋል።
ሰ/አቸፈር ቤተሙከራን መሰረት አድርገው የተዘጋጁት የሞዴል ፈተናዎችን ከመምህራን ጋር ቤተሙከራውን እያዩ በተግባር እየሰሩላቸው ቢሆንም የአዳር መረሃግብር ለማዘጋጀት በወረዳው ላይ ከ8 ወር በላይ የመብራት አገልግሎት ባለመኖሩ መስጠት አለመቻላቸውን እና ችግሩን ለመቅረፍ ሶላር በመግዛት ቤተመጽሐፍት እስከ ምሸቱ 3 ሰአት እንዲያነቡ እያደረጉ መሆኑን ገልጸው ተፈታኝ ተማሪዎች በተመረጡ መምህራን አመቱን በሙሉ በልዩ ሁኔታ ድጋፍ ሲደረግላቸው መቆየቱን የጸ/ቤት ኃላፊው አቶ መንግሰቱ ደጉ አክለው ገልጸዋል። ።
የቆየ እዳ ተሸክመን ዋጋ የምንከፍል ባለ እጣዎች ፣ እዳዎችን ታግለን ካሸነፍንን ደግሞ ባለ ታሪኮች መሆን የምንችል እድለኞች ነን እና ተፈታኝ ተማሪዎችእንደ ሙሽራ ናቸው እና በየቀኑ እያገኘን ልንከባከባቸው ልንመክራቸው ልናግዛቸው ይገባል።
ጌትነት ሙሉጌታ አያሌው ትም/መምሪያ ኃላፊ።
ተፈታኝ ተማሪዎች እንደ ሙሽራ ናቸው በቅርብ አድርገን ልንከባከባቸው፣ ልንመክራቸው እና ልናግዛቸው ይገባል።
ፈተናን እንደ አንድ እድል ወስደን የምንመራውን ተቋም እንቀይር ተማሪዎች የኢመደበኛ ኃይል መጠቀሚያ አይሁኑ!
ክልል አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተናን፣ 12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና እና
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝግጅት አፈጻፀም ተገመገመ ።
=======================================
የምዕራብ ጎጃም ዞን ትም/መምሪያ የ 9 ወረዳ ትም/ጽ/ቤት ኃላፊ እና በስራቸው ያሉ የ2ኛ ደረጃ ርዕሳና መምህራን የተሳተፉበት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝግጅት ምን እየተሰራ እንደሆነ፣ በመከለስ፣ በመደገፍ፣ ሞዴሉን በመስራት ለአዳሪ ተማሪዎች ምቹ ሁኔታ በመፍጠር፣ የምገባ ፕሮግራም በመያዝ እና በስነ ልቦና ተማሪዎችን በማብቃት በኩል የተሰሩ ስራዎችን በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
አብዛኞቹ አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች ሁለቱንም የክልል ፈተናዎች አንድ ወንበር ለአንድ ተማሪ በማዘጋጀት ፈተናውን በአንጻራዊ ሰላም ማስፈተናቸውን የመድረኩ ተሳታፊዎች ገልጸዋል። አንዳንድ ወረዳዎች የግል ተፈታኞችንም ጭምር ሞዴል ፈተናን በግላቸው ሁነው እንዲፈተኑ እና የስነ ልቦና ዝግጅትም እንዲወስዱ ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ተማሪዎች እርስ በርስ የመረዳዳት እና ቤተመፀሐፍት ገብቶ የማንበብ ባህላቸው ከመቸውም ጊዜ የተሻለ መሆኑን ርዕሳነ መምህራን ገልጸዋል።
የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ድጋፍን በተመለከተ ፍ/ሰላም 124 ተማሪዎችን መርጠው የአዳር ፕሮግራም መያዙን ሰከላ በአባግስ ት/ቤት አዳር ፕሮግራም መጀመሩ ፣ አባይ ምንጭ የምግብ ፕሮግራም እና 2 በርሚል ነዳጅ በመግዛት ላይበራሪው የ24 ሰዓት አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ፣ ቡሬ ከተማ 100 ፍራሽ ከባህርዳር ዩኒበርሲቲ በማስመጣት ለተመረጡ ተማሪዎች የአዳር መረሃ ግብር አዘጋጅቶ ሽኩዳድ መሰናዶ ከአዳር ፕሮግራም በተጨማሪ የግቢውን ውበት ሳቢ እና ማራኪ በማድረግ ተማሪዎች ሙሉ ጊዜያቸውን ትምህርት ቤት እንዲያሳልፉ ማድረጉ እና ለሴት ተማሪዎች ብቻ የተዘጋጀ ቤተመፀሐፍት በመኖሩ ሴቶች በየክፍል ደረጃው ከኦል ሴክሽን 97.7 ፣ 97 እና 96% በማምጣት አንደኛ ደረጃ መውጣታቸውን፣ ደምበጫ ከክልሉ ሞዴል በተጨማሪ በአስተማሪዎቻቸው የተዘጋጀ ሞዴል መፈተናቸውን እና 160 ተማሪዎችን በአዳር መረሃ ግብር እየሰጡ እንደሚገኙ በኃላፊዎች እና በርዕሳነ መምህራን ገለፃ ተደርጓል።
ተማሪዎች በራሳቸው ከማንበብ፣ ከመረዳዳት፣ በተመረጡ መምህራን የክለሳ ፕሮግራም ከማካሔድ ባልተናነሰ ለመልቀቂያ ፈተናው ያላቸውን የስነልቦና ዝግጅት ጠንቅቀን ማወቅ፣ በራስ የመተማመናቸውን ልክ መረዳት እና የአመታት ድካማቸውን ሚገባቸውን ውጤት እንዲያመጡ ድጋፋችን እስከ 11ኛው ሰዓት ድረስ በየትምህርት ቤቱ መካሄዱን ማቋረጥ የለበትም።
ፈተናን እንደ አንድ እድል ወስደን የምንመራውን ተቋም ውበት እና ይዘት እንቀይር!
ጌትነት ሙሉጌታ አያሌው
የምዕራብ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ
#Update
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም እንዲጠናቀቅ የጋራ የፀጥታ ዕቅድ ላይ ምክክር መደረጉን ለማወቅ ተችሏል።
በመድረኩ፦
- የትምህርት ሚኒስቴር፣
- የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣
- የክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች እና የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ፤ ከሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በ102 የፈተና ጣቢያዎች የሚካሄደው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሀገራዊ የፀጥታ ሁኔታውንና የክረምቱን የአየር ሁኔታ ያገናዘበ በርካታ የሰው ኃይል መመደቡን አሳውቋል።
ፈተናው ከሥርቆት በፀዳ መልኩ እንዲካሄድ ሁሉም ኃላፊነቱን ወስዶ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባም ኮሚሽኑ አሳስቧል።
በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች በፈተና ጣቢያዎች የፀጥታ ችግሮች እንዳይከሰቱ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በቂ ዝግጅት ማድረጉንም ኮሚሽኑ አሳውቋል።
ተማሪዎች ለፈተና ሲመጡ ፦
- የሀኪም ማዘዣ የሌለው መድሃኒት በሽሮፕም ሆነ በታብሌት፣
- የህክምና መስጫ መርፌ፣
- የአንገት ሀብል፣
- የፀጉርና የጆሮ ጌጥ፣
- ከጋብቻ ቀለበት ውጭ ፈርጥ ያለው የጣት ቀለበት እና የእጅ አንባር አድርገው መምጣት እንደማይችሉ ፖሊስ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
በተጨማሪም ፦
- ተንቀሳቃሽ ስልክ፣
- አይ-ፓድ፣
- ታብሌት፣
- ላፕቶፕ፣
- ስማርት ሰዓት፣
- ሲዲ፣
- ሚሞሪ ሪደርና ኦ-ቲጂ ኮንቨርተር እንዲሁም ፎቶ የሚያነሱ እና ድምፅ የሚቀርፁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ይዞ መገኘት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ተገልጿል።
የተከለከሉ መሣሪያዎችን በዩኒቨርሲቲዎቹ ግቢ ውስጥም ሆነ በዙሪያው ይዞ መገኘት፣ ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል መግባት እና ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ከፈተና ክፍል መውጣት እንዲሁም በዩኒቨርሲቲ ግቢ ወስጥ በግልም ሆነ በቡድን ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት የተከለከለ ነው።
ይህንን ተላልፎ በተገኘ ተማሪ ላይ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ አንዳንድ የትራንስፖርት ችግሮችን ለመቅረፍ፣ ለተማሪዎች ከትምህርት ቤት ጀምሮ በወረዳና በዞን ትምህርት ቢሮ አማካኝነት የፈተና መመሪያ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እንደተደረገ መሆኑን አሳውቋል።
መረጃው የፌዴራል ፖሊስ ነው።
የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በተሳካ ሁኔታ እንዲሰጥ የቅድመ ዝግጅት ስራው በሁሉም ወረዳ ትም/ቤቶች ላይ የተሠጠ መሆኑን የዞኑ ትም/ት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጌትነት ሙሉጌታ ገልጸዋል።
በአብዛኛው ወረዳ ለፈተና አስፈፃሚ እና ለፀጥታ ሃይሉ ኦረንቴሽን መሰጠቱን እና ፈተናው ተጀምሮ እስከሚያልቅ ድረስ በኮር አመራሮች የሚመራ መሆኑንም ገልፀዋል ።
ፈተናው ሲጀመር በማህበራዊ ሚዲያ የተለያዩ አሉባልታዎች ሊለቀቁ ስለሚችሉ ከተማሪዎች ጋር ቅድም ውይይት በማድረግ ፈተናው ደረጃውን በሚመጥን ሁኔታ ምስጢርነቱ የተጠበቀ መሆኑን ግንዛቤ ተፈጥሮላቸው ለወሬ ጀሮ ሳይሰጡ በተፈቀደላቸው የፈተና ሰዓት ውስጥ ተረጋግተው እንዲፈተኑ ማድረግ ከእያንዳንዱ ፈታኝ እና የፈተና አስፈጻሚ አካል የሚጠበቅ ተግባር ይሆናል ብለዋል ።
ተማሪዎች ወደ ፈተና ከመግባታቸው በፊት የመፈተኛ ክፍሎች ንፅህና ፣ የወንበር አደረጃጀት፣ የተማሪዎች መለያ ቁጥር አሟልተው: የተከለከሉ ነገሮችን/ ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ መፅሐፍ፣ የተፃፈበት ወረቀት፣እስክርቢቶ፣ ካልኩሌተር፣በህክምና ያልታዘዘ መነፀር መያዝ የተከለከለ ስለሆነ ሙሉ ፍተሻ እንዲደረግ እና ዩኒፎርም፣ እርሳስ፣መቅረጫ፣ላፒስ ፣መታወቂያ እና አድሜሽን ካርድ መያዝ እንዳለባቸው ግንዛቤ ተፈጥሮ የፈተና አስፈፃሚዎች በምንም አይነት ምክንያት የፈተና ስዓት ማባከን የተከለከለ መሆኑን ገልጸው ለሁሉም የምዕራብ ጎጃም ዞን የ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ መምህራን እና የትምህርት ባለድርሻዎች ሰላማዊ የፈተና ስርዓት ተካሂዶ በውጤት እንደምነገናኝ ተስፋ እያደረግሁ መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ አየተመኘሁ ።
ፈተናው ሰኞ ሰኔ 26 ከጣዋቱ 3 እስከ 5 ሰዓት አማርኛ እና እንግሊዘኛን ፣ ከሰዓት 8 እስከ 10 ሰዓት የዜግነት ትምህርት እና ሒሳብ የሚሰጥ ሲሆን ሰኔ 27 ጠዋት 3 እስከ 5 ሰዓት ማህበራዊ ሳይንስና አጠ/ሳይንስ የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል ።
ጌትነት ሙሉጌታ አያሌው
የምዕ/ጎ/ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ
