en
Feedback
☪ አኑ ኢስላሚክ ፔጅ☪

☪ አኑ ኢስላሚክ ፔጅ☪

Open in Telegram

✅ አኑ ኢስላሚክ ፔጅ ✅ በቻናላችን 🌍🎵🎵ነሺዳ 🎵🎵 መንዙማ 🌿🌿ግጥም 🌿🌿ሀዲሶች እና🌿🌿ወቅታዊ መረጃዎች ያገኙበታል

Show more
642
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-330 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
August '24
August '24
+20
in 0 channels
July '24
+46
in 0 channels
Get PRO
June '24
+33
in 0 channels
Get PRO
May '24
+43
in 0 channels
Get PRO
April '24
+59
in 1 channels
Get PRO
March '24
+90
in 1 channels
Get PRO
February '24
+55
in 0 channels
Get PRO
January '24
+48
in 1 channels
Get PRO
December '23
+32
in 0 channels
Get PRO
November '23
+10
in 0 channels
Get PRO
October '23
+13
in 0 channels
Get PRO
September '23
+8
in 0 channels
Get PRO
August '23
+21
in 0 channels
Get PRO
July '23
+32
in 0 channels
Get PRO
June '23
+8
in 0 channels
Get PRO
May '23
+14
in 0 channels
Get PRO
April '23
+38
in 0 channels
Get PRO
March '23
+34
in 0 channels
Get PRO
February '23
+8
in 0 channels
Get PRO
January '23
+13
in 0 channels
Get PRO
December '22
+10
in 0 channels
Get PRO
November '22
+8
in 0 channels
Get PRO
October '22
+5
in 0 channels
Get PRO
September '22
+11
in 0 channels
Get PRO
August '22
+13
in 0 channels
Get PRO
July '22
+12
in 0 channels
Get PRO
June '22
+10
in 0 channels
Get PRO
May '22
+19
in 0 channels
Get PRO
April '22
+68
in 0 channels
Get PRO
March '22
+40
in 0 channels
Get PRO
February '22
+13
in 0 channels
Get PRO
January '22
+22
in 0 channels
Get PRO
December '21
+12
in 0 channels
Get PRO
November '21
+19
in 0 channels
Get PRO
October '21
+1
in 0 channels
Get PRO
September '21
+8
in 0 channels
Get PRO
August '21
+4
in 0 channels
Get PRO
July '21
+13
in 0 channels
Get PRO
June '21
+7
in 0 channels
Get PRO
May '21
+21
in 0 channels
Get PRO
April '21
+33
in 0 channels
Get PRO
March '21
+13
in 0 channels
Get PRO
February '21
+11
in 0 channels
Get PRO
January '21
+9
in 0 channels
Get PRO
December '20
+1 693
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
17 August0
16 August+1
15 August0
14 August+1
13 August+1
12 August0
11 August0
10 August0
09 August+2
08 August+1
07 August0
06 August+3
05 August+5
04 August+1
03 August+2
02 August+2
01 August+1
Channel Posts
ሸህ አሊ ሰማን የማሽ መንዙማ || She Aley seman mash menzuma MEDINA||TUBE https://t.me/medina_tube

2
#ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ! ከውኑ ሲበጃጅ በሥርዓት ተሟሽቶ፣ በስነ ምግባር ተኩሎ ነው። ከስነ ምግባር ደግሞ መልካም የተባለው ሁሉ በውዱ ነብይ ሙሐመድ ላይ ታትሟል። የዓለሙ ሹም ሲመጡ لقد كان لكم في رسول الله أسوة حسنة ያለውን ዘውድ ራሳቸው ላይ ደፍተው፣ በሙላት ዙፋን ላይ ተደላድለው፣ የተሽሪፍ የክብር ካባ ደርበው ነው። ታድያ ለእርሳቸው ሲዘንብ ለባልንጀሮቻቸውም አካፍቷል። ካፊያው አስሃባውን ሁላ አረስርሷል። ውዱን ነቢ ማላቅ፣ ዘይንዬን ማክበርና ለእርሳቸው ማርገድ በዚያ ሁላ ወዳጅ ሰብቷል። ሰይዲ ﷺ ከመካ ተነስተው መዲና የገቡ ጊዜ አረዳው ሁላ ነቢን በቤቱ ለማሳረፍ ተሽቀዳደመ። ግና ሰይዳችን "ተዋት እርሷ ታዛለች" ሲሉ ግመሏን እንዳይኮለኩሏት አዘዙ። ሁሉም የቤቱን መመረጥ በጉጉት ተጠባበቀ። አንዱን ቤት አልፋ በሄደች ጊዜ ቤታቸውን ሀዘን ይወርሰው ጀመር። ልባቸውም እጅግ ትከፋ ገባች። የመዲና ሰዎች በሙሉ ግመሏን ከኋላ ኋላ እየተከተሉ ቤቱን የምትመርጠውን እድለኛ ሊያውቁ ፈለጉ። ተጓዘች እና ሰይዱና አቡ አዩብ አልአንሷሪ ቤት በረከች። ጥቂት ቆይታ ተነስታ ሄደችና ተመልሳ መጥታ የቀድሞው መብረኪያዋ ጋር አረፈች። ሰይዱና አቡ አዩብ ተደሰቱ። ወደ ረሱሉ ﷺ ተሽቀዳድመው ተቀበሏቸው። እቃቸውን ተሸክመው ከፊት ከፊት መሩ። የሰማይ የምድሩን ሐብት ተሸክመዋልና እየፈነጠዙ ሄዱ። የሰይድ አቡ አዩብ ቤት ፎቅ እና ምድር ነበረና የላዩን ክፍል ለነቢ ለቀቁ። ሰይዳችን ﷺ የምድሩን መረጡ። አቡ አዩብም የነቢን ፍላጎት ተቀብለው ፈፀሙ። ምሽቱ ሲፀና ሰይዳችን ወደ ፍራሻቸው አመሩ። አቡ አዩብም ከባለቤታቸው ጋር ወደላይኛዋ ክፍል መኝታቸው ወጡ። መቼስ አላህ ያላቀው እንዲያው ዳኢሙን ትልቅ ነው። ነቢን ያወቃቸውኮ ሐጅረው የደረሱ እለት ነበረ። ወሕዩን አላዳመጠ፣ ሙዕጂዛቸውን ገና አላላመጠ። ይሁን እንጂ የነቢ ከስር ማደር ከነከነው። ለልቡ ጠናው። ሀሳብ ሆነው። ለሚስቱ ታዲያ "ወዮልን! የሰማዩ ነጋሴ ምድር ተኝተው እኔና አንቺ እዚህ ምን እየሰራን ነው? እንዴት ከነብዩ በላይ እንሆናለን? ኧረ መጥፋታችን ነው።" አላት። የሚያደርጉት ጠፋቸው። በጣቶቻቸው ጫፍ እየረገጡ ነብዩ ካሉበት ክፍል የማይደርሰውን የላይኛውን ክፍል ትንሽዬ ቦታ ይዘው አመሹ፣ አደሩ። ጎህ እንደቀደደ "ያ ረሱለላህ እንቅልፍ አጥቼ አደርኩ፣ እርሶ ከስር እኔ ከላይ ልሆን አልተቻለኝም። የተረማመድኩ ጊዜ በላይዎ ላይ አቧራ እየተራገፈ አስቸግርዎታለሁ ብዬ ተጨነቅኩ።" ቢላቸው ጊዜ "አቡ አዩብ ነገሩን ቀለል አድርገው‘ንጂ እኛን መጥቶ ለሚያዬንም ሰው ከስር መሆናችን ይቀለዋል ከመውጣት መውረድ።" አሉትና አሁንም የነቢን ፍላጎት ተቀበለ። አንድ ሌሊት ታዲያ ብርዱ እጅግ በረታ። የውሃ ማቆሪያቸው ተሰበረችና ውሃውም ፈሰሰ። ማታ ለብሰዋት የሚያድሯት አንዲት እራፊ ጨርቅ ነበረቻቸውና በዚያች ጨርቅ ውሃውን ያደራርቁ ጀመር። ወደ ነቢ ዘንድ እንዳይፈስ ባከኑ። አይነጋ የለም ነጋላቸው። ወደ ነቢ ተጣድፈው ለሊቱ ያደረጋቸውን አወጓቸው። የሙጥኝ ብለው ወደላይኛው ክፍል ወተወቷቸው። ነቢም ተስማምተው ወደላይኛው ክፍል ወጡ። እነ አቡ አዩብ ወደ ምድር ወረዱ። ቀልባቸውም ሰከነ። ነቢ ቤትና መስጂዳቸውን ሠርተው በወጡ ጊዜ ከአቡ አዩብ ቤት ተጎራበቱ። አላህ ሲመርጥ እንዲህ ይሠራል። በየትም አምር ቢሆን ሙእሚን ቀልቡ ከነቢ አታገልም። ነቢ ከበላዩ፣ የበላዩ መሆናቸውን አይዘነጋም። ለትልቅም ለትንሹም ጉዳዩ ነቢ አዛዡና፣ ገዢው ናቸው። እንዲህ ነቢን ከፍ ያደረገ ነው አላህ ከፍ የሚያደርገው። እነዚያማ አላህ ያስቀደማቸው ነቢን በማተለቅ የደረሳቸው የለም። ሰይዱና ማሊክ ኢብኑ አነስ በመዲና ከተማ ልቅና ተሰጥቷቸው፣ የዒልምና ተቅዋ ሸማውን ለብሰው ሲኖሩ አንድም ቀን ጫማ አልተጫሙም። በግመል ላይም አልወጡም። የነቢን ገላ የረገጡ፣ ያቆሸሹ ያህል መስሎ እየተሰማቸው በኢስቲጝፋር ነው የኖሩት። የነቢን ሐዲስ በነቢ ዶሪሕ ተጠግተው፣ በነቢ መስጂድ ውስጥ ሲያቀሩ ውዱእ አድርገው፣ ፂማቸውን አበጥረው፣ ሽቶ ተቀብተው ፣ በግርማ ተሞልተው ነው። እነዚያማ ቀደምቶቹ ለነቢ ልቅና የሚቻሉ አይደሉም። የኛም አባዬ ሾንኬ በመዲና ውሃሽንት አሻፈረኝ ሲሉ ነው የምናውቀው። በእኛም የሚወጅበው ይሄው ነው። የነቢን ሥም ማክበር፣ ቤተሰቦቻቸውን መውደድ፣ ሸማኢላቸውን እያደመጡ መሳከር። ይህ እውነት አሁንም የገባቸው አሉ። በርካቶችን በመዲና ሐረም በባዶ እግራቸው ሲዘዋወሩ አይቻለሁ። ድምፆቻችሁን ከነቢዩ ድምፅ በላይ ከፍ አታድርጉ። ያለው ቃሉ ዛሬም ይሠራል። وَاعْلَمُوا أَنَّ فِيكُمْ رَسُولَ اللَّهِ የሚለው ከላሙ ዛሬም ማዕና አለው። በየትኛውም ዘመን ሃይ፣ ግኝም ናቸውና። በዛትም በሩሕም ሐዲር ናቸውና። እናማ እንደ አይነታዎቹ ማደግደግ፣ እንደ አካቢሮቹ መጎናበስ ነው እጣ ‘ሚያሳምረው። ይህ ነው ከደጋጎቹ የቀመስነው ሸራብ። #ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ! አሏሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም💚💚💚
219
3
No text...
169
4
#ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ! ከጅምሩ የቲምነት ወደቀባቸው። አያትም አጎትም አልተወላቸው። ከከተማ ከተማ መንከራተትም አልቀረላቸው። ቀያቸውን ይወዷታል፣ ይሳሱላታል። ተወልደው አድገውባታል። ነግደውባታል። ከነዋሪው ሁሉ ተጎዳኝተውባታል። ታምነው "አል‐አሚን" ተሰኝተውባታል። ጥበባቸውን ችረዋታል። አግብተው ወልደውባታል። የኑቡዋን ሸማ ደርበውባታል። በራሳቸው እና በጓዶቻቸው ላይ መከራ አስተናግደውባታል። ከዚህ ሁሉ ታሪካቸው በኋላ ግና ጌታቸው ያቺን የሚወዷትን መንደር ጥለው እንዲወጡ አዘዛቸው። ከውሸት ወደ እውነት፣ ከፍጡር ወደ ፈጣሪ። በፍራሻቸው ላይ ዋሪሳቸውን አስተኝተው፣ ሲዲቁን አስከትለው ተጓዙ። አገር ለቀቁ። ከ400 የበለጡ ኪሎሜትሮችን ኳተኑ። ጋራ ተራራ ወጡ ወረዱ። ሰይዱና ሙሐመድ ሶለላሁዓለይሂ ወሰለም ሒጅራን ጀመሩ። ያቺን ሩቅ ከተማ ሊያነግሱ፣ በብርሃናቸው ሊያድሱ፣ ከመልእክታቸው ሊያቋድሱ ተነሱ። የኢስላምን መግነን ሊያውጁ፣ የሙስሊሞችን አንድነትና የጠራ ማንነት ሊያበጁ ዋጁ። በጌታቸው እገዛ ሃሩርና አሸዋውን ተሻግረው ከነፋሱ ጋር ፈሰሱ። ሲዲቁ አንዴ ከፊት ሲቀድሙ፣ ተመልሰው ከኋላ ሲቆሙ፣ በቀኝ እያለፉ አየሩን ሲገመግሙ፣ በግራቸው እየተሰለፉ ዙሪያ ገባውን ሲመረምሩ በሰይዳችን "አብሽር" ተሰኙ። ለቀናት ከለላ የምትሆናቸው አንዲት ሰዋራ ዋሻ አገኙ። ሲዲቅ ተቀድመው ቀዳዳዋን ሁላ በጨርቅ ደፋፈኑ፣ ድንጋዩን ጠራረጉ፣ ለነቢ አስመቹ። ነቢ ተከትለው ገቡ። ሲዲቁ ተቀምጠው የቀረች ክፍተት ቢያዩ በእግራቸው ሸፈኑ፣ ነቢ ያርፉ ዘንድ ታፋቸውን አዋሱ። የሚያምሩት ነብዬ በዚያ ውብ ገላ ጋደም አሉ። ይህኔ ነቢን ከጅሎ መንገድ ያጣ እባብ የሲዲቁን እግር ነካከሰ። ህመማቸውን ዋጥ፣ ቻል አደረጉ። ግና እንባቸው ፈሰሰ። "እሱ አላለቀሰም ላልቅስለት እኔ" አሏቸዋ የነቢ ዘይኔው ጌታ። ይሄኔ ነብዬ ተንቀሳቀሱ። ሁኔታቸውን አጢነው በፈውስ እጃቸው ደባበሷቸው። በቱፍታ አሻሯቸው። በዚህ መካከል የተፈራው ደረሰ። እኚያ ነብዬን የሚያሳድዱ ቁረይሾች ከተፍ አሉ። ድምፃቸው ተደመጠ፣ የፈረሶቻቸው ኮቴ መሬቱን ናጠ። ሲዲቁ ለነቢ ሰግተው ጭንቀታቸው አየለ። የዋሻው በር በደካማ ፍጡራን አጥሮች ታጠረ፣ ወዲህም በጌትዬው ጁንዶች ተማገረ፣ በመላኢካ አጀብ ተወረረ። እንዲያው አንዳቸው ጎንበስ ቢሉ ነቢን ያዩብን ነበረ፣ ግንሳ ለዐጃኢበቱ አላህ ከለላቸው። ጠላቶቻቸውን መለሳቸው። ሲዲቁ ሲጨነቁ ቢሻራ ደረሳቸው። لاَ تَحْزَنْ إِنَّ اللهَ مَعَناَ ያለው ቀለም ፈሰሰላቸው። ጉዞው ቀጥሎ መዲና ጎራ ላይ ብቅ ሲሉ መዲና አበራች። አንሷር የተባለ ሁሉ ለአቀባበል ተሰማራ። ስለት ያለባት ጃሪያ ጭንቀቷን ልትተነፍስ ድቤዋን መታች፣ እጆቿን እያጋጨች አዜመች። "ጦለዓ" እያሉ ሁሉም ተደለቁ። ላይጠግን አይሰብርምና እንዲህ የተጀመረው ሒጅራ በፈትሁል መካ ተደመደመ። ከዚያ በኋላ ያለው ሒጅራ ሙሒብ ከሸውቅ አምልጦ ወደ ሩዕያ የሚሄድበት ነው። ከፊሉ ዓሊይን ይሆናል፣ በዕዱም አቡበክርን፣ አንዳንዱ አስማእን፣ ሌላው ሰይድ ሐምዛን፣ የተቀረው ጃሪያን ይሆናል። የሙሒብ ሐሉ በእነዚህ ይተካካል። ፈተና በበዛ ሰዓት የተደረገ ዒባዳ እንደ ሒጅራ ነው አሉ ዓይናማው ሰው። እናማ ፈሳድ ሲበራከት የጨመተ፣ ኻኢን ሲበዛ የታመነ፣ የሁሉ ቀልብ ሲደርቅ በቁርዓን የረጠበ እንደ ሙሐጂር ነው። ከፈጅር እስከ ኢሽራቅ በዊርድ የሚሰክር ሰው ሒጅራው ወደ ነቢ ነው። ሐያቱን ሁላ በሶለዋት፣ መውሊድ እና መድሕ የፈጀ ሰው ወደ ዳሩ ሰላም ተቅጣጭቷል። የኸሚሱም መጅሊስ እንዲሁ ከነቢ ለነቢ ወደነቢ ነው። #ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ! አሏሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም💚💚💚 T.me/anueslami
253
5
No text...
192
6
🎉🎉በሒጅሪ አቆጣጠር አዲስ አመት ነገ እሁድ አንድ ብሎ ይጀምራል ሙሐረም 1/1446 አላህ መጪውን አዲስ አመት የኢማን የአፊያ እና የሰላም ያድርግልን!🎉🎉 እንኳን አደረሳቹህ‼
🎉🎉በሒጅሪ አቆጣጠር አዲስ አመት ነገ እሁድ አንድ ብሎ ይጀምራል ሙሐረም 1/1446 አላህ መጪውን አዲስ አመት የኢማን የአፊያ እና የሰላም ያድርግልን!🎉🎉 እንኳን አደረሳቹህ‼
242
7
➣, የህመም-ጭስ-ስያፍናችሁ፣ የዱዐን መስኮት ክፈቱ። @anueslami
265
8
አሏህ_አሏህ_ሙንሺድ_ሙአዝ_ረዲ_Allah_Allah_Munshid_Muaz_Redi_New_Sudan_.m4a
279
9
ጧሀ_ጀማሌ_ሰለሀዲን_ሁሴን_TUHA_JEMALE_SELEHADIN_HUSSEN_NEW_MENZUMA_20.m4a
303
10
#ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ! ፍቅራቸው እንደሌላው ፍጡር አይነት አይደለም። አይጨበጥም። በዚህ ሲይዙት በዚያ ይሾልካል። እንኳንስ ነፍሱ ላልረገበች ደካማ ገበር ቀርቶ በዒልም ለተራቀቀ፣ በመቃማት ለራቀ፣ በሸውቅ ለተንሰቀሰቀ፣ በዒሽቅ ለላሸቀም የቸገረ ነው። ደግሞም ከሰው ሰው ይለያያል። አንዳንዱን ጨርሶ ይጎትተውና ዳኢም በናፍቆት ይገርፈዋል። ከፊሉን ደግሞ ወሰድ መለስ እያደረገ፣ አራጋቢ ሲገኝ እሳቱን እያነደደ በሸውቅ ይፈጀዋል። ያሻውን ይመርጥና ከሐድራው ግቢ ይዶለዋል። እንዲያ ሲልም ደጅ አሳድሮ በቁር ይጠብሰዋል። ለማንም አይራራም፣ ለሁሉም አይገራም። ሁሉም በየአጥናፉ ተቀምጦ "እንዴት ነሁ" እያለ ይብሰከሰካል። በሀበሻዎቹ ብሶ እጅጉን ፈጅቷቸዋል። ገጠር ከተማውን ወዝውዞ ጨርሷቸዋል። ቅኔን ከዜማ እያጋባ ለራሱ አሳድሯቸዋል። ከቶ እኔን መገን የሚያሰኘኝ እንዲህ አድርጎ የሚለዋወጠው ተፈቃሪው ነው ወይስ ፍቅሩ ራሱ ነው? የሚለው ነው። ያ ምስኪኑ ሰው "ወዳጁን ገዳይ ፍርዱ ምንድን ነው?" እያለ መልስ በሌለው ጥያቄ ይናውዛል። የኛ ሰይድ አርባ በርቀት ፍቅር የናፍቆቱን ዜማ ሲያንፈቀፍቁት ሰማይ ምድሩ ናሽሯል። ማዲሁ በኸበር ያወቋቸው ሰው ቢናፍቋቸው ነው "እንደምን ነው የጦይባው አሕመዴ መሐመዴ" እያሉ መባዘናቸው። አርፈው በተቀመጡበት፣ ነገሩን ረስተው በተመሰጡበት አንድ ወዳጅ ሰተት ብሎ የዛን የማዶውን ሰው ወስፍ ሲያወጋቸው ዳግም የናፍቆቱ እሳት ተቀጣጥሎ አቃጠላቸው፣ ፍሙ ተፋፍሞ ለበለባቸው። ባይችሉና ቢያቅታቸው ቀለምን ከብዕር አዛምደው ለራቃቸው ወዳጅ መልዕክት ሰደዱ። ለእኚሁ ሙሒብ አጋዥ፣ ሌላ አበጋር፣ ወዳጅ ገበር፣ የዒልም ባህር የመድሕ ስፍር ሰፍረው "እንዴት ነሁ እንዴት ነሁ" ሲሉ ያዩትን ትዝታ እየመላለሱ አብረው ተላወሱ። አየሩን ሰንጥቀው የዘለቁበት ቀዬ እየታዬ፣ ያዋዩት ደግ ሠው እየታወሰ ጤና ነሳቸው። "ሆነብኝና እንዳዲስ ሆዴ ተንቀሳቀሰ" ብለው ፊታቸውን ለዚያ ደግ ሰው አዞሩ። ሐገሩን ያዩ ጊዜ ቀለል የሚል መስሏቸው ነበረ። ሲመለሱ ባሰባቸው። ደግሞ ለእኚህ ሕመም ሌላው ሲታገልላቸው "ጉድ የቀመሳት ሰው፣ ብሶበታል ሄዶ ካላዬው" አለላቸው። ሕመሙ ለጉድ ሆኖ ሲጠናበት ደግሞ "ሔጄ ከመጣሁኝ ሰንብቻለሁና፣ አሁንም አሁንም ና በሉኝ መዲና" ብሎ የራሱን ተነፈሰ። ቢሄድ የሚሽር መስሎት፣ የሄደበት ሕመም ሲመላለስ እንደሚጠና ስቶት "አንቱ ጋ መምጣቴ ናፍቆት ጨመረብኝ፣ ደግመሁ ጥሩኝና ናፍቆቴን አሽሩኝ" ይላቸዋል። ሁሉም እንዲሁ ይሰቃያል። ያያቸውም ያላያቸውም ታጥቆ ተሸምሮ ይንገበገባል። ካላያቸው ያያቸው ሲብሰው፣ ካያቸው ያላያቸው ሲጠናው እንዲሁ እየተለዋወጠ ጉድ ያሰኛል መውደዳቸው። "ጌታዬ እንዴትነሁ ምነው ባየንሁ" እያሉ የሚማቅቁት የናፍቆት እስረኞች ቀለምና ብእር የከተበውን መልክ አይተው፣ የነጋሪ ነጋሪ ያወጋቸውን ወስፍ ይዘው፣ በዓቅል በልባቸው ፊቱን ከ’ነ ሙሐባው ቀርፀው ነው። ይህ ተፈቃሪ ያሻውን ሲሰራ ከሳሽ የለውም። አፍቃሪውም ሊከሰው አይሻም። ይጥመዋል’ንጂ። እንዲሁ "እንደምነው" እንዳለ ይኖራል። የመዲናውን ዓሩስ፣ የከውኑን ራስ፣ የመኽሉቁን አድማስ፣ የሰኪናውን ንፋስ፣ የረውዳውን ንጉስ፣ የሐድራውን አድሩስ ሰይዲ ሙስጦፋን ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ኢማን እስኪሞላ ድረስ ከሁሉ ከሁሉ አብልጠው ሲወዱ እንዲህ ነው። አካቢሮቹ የአላህ ወዳጁ፣ ኸይር አጋዳጁ፣ ሐቅ ፈራጁ፣ በላእ ጋራጁ፣ ለወደቀ አንሺው፣ ለተራበ አጉራሹ፣ ለታረዘ አልባሹ፣ ለተቸገረ ደራሹ ነብዬል ሙጅተባ ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም "ከየትም ብትሆኑ ሰላምታችሁን አድርሱኝ መልስ እሰጣችኋለሁ" ያሉቱን ይዘው "ጌታዬ እንዴት ነሁ? እንደምነሁ የጦይባው አሕመዴ?እንዴት ነሁ ባያሌው?" እያሉ ተሐድረው ደብዳቤ ተመላልሰዋል። ከሪሙ ነቢ እንዲሁ ሲናፈቁ ከውኑ ተጀምሮ፣ ዱንያ ትሰበራለች። ተወዳጁ ሠው በቀላሉ አይተውምና ሙሐባቸው የዘለቀው ጀሰዱ ያስታውቃል። እርሳቸውን ያሉ ጅስማቸው ሰለለ ፣ስጋቸው ቀለለ፣ ደማቸው ጠለለ፣ አጥንታቸው አገለለ። ይሄው ወዳጆቻቸው በየጊዜው እየነጎዱ ነው። ወዳጁን ገዳይ እንዳንቱም የለ ወረቴ! #ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ! አሏሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም 💚💚💚 T.me/anueslami
317
11
No text...
206
12
#በሕመምሀ_ከአላህ_ጋር_ተገናኝ ሸይኼ ሆይ! አላህን የምለምነው ነገር ለምን አልሆነልኝም? ሲል ጠየቃቸው አንድ በተስፋ መቁረጥ የዋለለ ተማሪ .. * እርሱ የሚፈልገው ሆኗል አሉት። ጥያቄው ቀጠለ ... አላህ የእኔን ደስታ አይፈልግም? * በደንብ ይፈልጋል እንጂ እና ለምንድነው የሚያስደስተኝን (የጠየቅኩትን) የማያደርግልኝ? * አንተ የፈለግከው በእውኑ ስለማያስደስትህ ይኾናል ነገር ግን የፈለግኩት ነገር ባለመሆኑ አዝኛለኹ እኮ! * አንተ የፈለግከው ነገር ቢሆን ኖር የሚያገኝህ ሐዘን የበለጠ ይኾናል። እንዴት ነው ታዲያ የምደሰተው? * የእርሱን (ውሳኔውን) በመውደድ እንዴት? * አላህ የሚያቀውን አንተ አላውቅም በማለት ታዲያ እርሱ አላህ ዛሬ ይመልስልኛል? * አላህ ሁሌ የተጣሪውን ጥያቄ ይመልሳል! ግን እኮ የጠየቅኩትን አልመለሰልኝም። * የአላህ ምላሽ የግድ አሁን ይሆናል ማለት አይደለም። እንዲመልስልኝ አይደል የምጣራው? * አዎን ልክ ነህ! ታዲያ የታለ ምላሹ?! * እርሱ ሲሰጥም ምላሽ ነው፣ ሲከለክልም ምላሽ ነው፣ ሲያዘገይም ምላሽ ነው። ነገር ግን እኔ ምላሹ ሲቀርብኝ እታመማለሁ ። * ምንዳ ሊጨምርህ ነው! ነገር ግን የጠየቅኩትን በማጣቴ ሐዘኔ ይጨምራል እኮ! * ሊያስደስትህ ፈልጎ ነው። ጭንቅ ጥብብ ይለኛል። * ሊያሰፋልህ ነው። እኔ ደካማ ነኝ አልችልም። * እርሱ ግን ሐያል ነው። አይወደኝምን? * ይወድሀል ከወደደኝ ለምን ያስለቅሰኛል? * ሊያጠራህ ፈልጎ ነው። ከወደደኝ ለምን ይፈትነኛል? * ወደርሱ ሊያቀርብህ ፈልጎ ነው። ማቅረብ ማለት ምንድነው? * ስኬት ማለት ነው። ልቤ ተሰበረ * እርሱ ይጠግነዋል ለዓመታት ባዶነት ይሰማኛል * እርሱ ይሞላልሀል አሁን ወደርሱ የተመለስኩ ይመሰልዎታል? * በድጋሚ ተመለስ ሁለተኛ ጊዜ የተመለስኩ ሆኜ ተመለከቱኝ? * ለሦስተኛ ጊዜ ለአራተኛ ... ለዐሥረኛ ጊዜ ተመለስ። የዕድሜ እስትንፋስህ እሰከሚቋረጥ ደጋግመህ ወደርሱ ተመለስ። እርሱ አላህ አዛኝ ነው። * ስለዚህ አትዳከም ሁሌም በርሱ በርታ ♥ በሕመምህ ወቅት ወደ አላህ የሚመራህ ጋር ሒድ! አላህ ይምራና ♥ Anuman
259
13
No text...
201
14
+1
_የዒድ ተክቢራ_ tekbira __AL Widad Tube(MP3_128K).mp3
278
15
#ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ! ባለቅኔ የተባለ ቢቀኝ፣ ገጣሚ ነኝ ያለ ስንኝ ቢደረድር፣ አለሁ ያለ ጸሐፊ ፊደል እንደ ቆሎ ቢዘራ ጥቂት መመሰል እንጂ መግለጽ የሚቻለው አንድም የለም። ሠይዳችን ትልቁ ሐድራ ዘልቀው የተመለሱ ጊዜና ያዩትን የወሰፉበትን መንገድ ማዲሑ «ባሕሩን ሙሒጥ አሉ ሌላም አልጀወቡ» ይሉታል። ይህንኑ ተውሰው እርሳቸውንም ወሰፉበት። በርዘንጅዩ መውሊዳቸውን እየከተቡ የሲሩ ሃገር ቢርቅባቸው የሲቲና ኡመ ማዕበድን ቂሷ አውስተው በአጭሩ አኸተሙት። ቢገቡበትማ ኪታቡም አያልቅ እርሳቸውም አይተርፉ ነበር። ሰይዲ አነስ ነብዬን ሊዘይሩ እጃቸውን ጨበጡና «ሐር የተባለን ጨርቅ ሁሉ ዳስሻለሁ እንደ እጅዎ ያለ የለሰለሰ አላየሁ» ሲሉ ደመደሙ። ለመልኩማ ማማር ይሄን ላውጋህ..! ሷሂባቸው በሞላች ጨረቃ፣ በደቀደቀው ለይል፣ በጠቆረው ሰማይ፣ ከነቢ ጓዳ ዘልቆ አብሯቸው ቢቀማመጥ ጨረቃው የትኛው እንደሆነ ለራሱ ተደናገረው። ዓይኑን በነቢ እና በጨረቃዋ መሀል እያንከላወሰ "ከቶ ጨረቃ ምድር ወረደች፣ ወይስ ሰይዴዋ ሰማይ ዘልቀው ተቀመጡ!?" እያስባለ የነቢ ጀማላ አዋለለው። ላክልልህ ወዳጄ..! ቁመታቸው ተደላድሎ ጎራውን ቢቅጣጩት ተራራው አነሰና ሰይዲዋ ገዝፈው ተስተዋሉ። ፀጉራቸው ተዘናፍሎ ሲንከባለል የጠራ ወንዝ መስሎ ያዋጅጃል። ከቶም ፍንጭታቸውን ገልጠው ፈገግ ያሉ እንደሆን የተገማሸረች ኮረዳ አትመስለውን ውበት ይላበሳሉ። ዓይናቸው ተኩሎ ጥቁሩ በነጩ ላይ ሲንከባለል፣ ነጩ በቀይ ቀለም ሲደፈርስ ለሚያይ ሰው ልቡን ሰንጥቆ ያደባዬዋል። "ሚምዩል ፈሚ" ብሎ ከከንፈራቸው የዘለቀው ዋሲፍ ከቶ ምን ያለ አፍቃሪ ነው አሰኘን። ልስልስ ነው፤ ላዩ ተቀምቅሞ ዙሪያውን በፂም የተከበበ። "ዘይደህ ንገረኝ የከንፈሩን ጣዕም" ያስብላል ማማሩ። የማኛ ጤፍ እንስፍስፍ እንጀራ የመሰለው ለስላሳ ተረከዙ መብራት ቢያበሩበት ያንፀባርቃል፤ ቅልጭ አባባሉ ዓይንን ያዞራል። ውስጥ እግሩ የሞላ፣ ደግሞ እንደ ጨረቃ የሰረጎደ ነው። ጣቶቹ ተቀምቅመው እንደ ፈትል የተቋጩ ድርድር ወታደር ይመስላሉ። የደረቱ አሞላል ኸበሩ እንኳንስ ላየው ለሰሚም ያስደነግጣል። ምን ይዓጅብሃል ይሄ፣ የወዳጆቹ ተከታትሎ ወስፍ በወስፍ ማኖራቸው ይድነቅህ እንጂ። የከበበው ሁሉ ቢጠየቅ‘ኮ "ኧረ ቀና ብዬም አላየሁት፣ በሙሉ ዓይኔማ እንዴትስ ችዬ?" ነው መልሱ። እውነታው ይሄ ሆኖ እያለ እንዲያ እንዲያ መተንተናቸው ጉድ ያሰኛል። የሙሐባ ጠጅ ተጥሎ፣ ነጋሪቱ ተጎስሞ፣ ድቤው ተደልቆ፣ ሐድራ ተኮልኩሎ እነ ሰይድ ጫሌ ቀለም ላይ የቀለጠው ሆታ ተነግሮ አይዘለቅም። ወስፍ በሳቸው ብዕር ተደመደመ። ጥቂት ከቸርነታቸው ቆንጥረው ደግሞ ለሰይድ አርባ አዋሷቸውና እንደተዳፈነ እሳት ተጋግሞ አነደዳቸው። ጌታው ሰይድ ሙሐመድ አመዴ "የኛኛው ሩሕ ሁላ፣ ሞተች አንቱን ብላ" ይላሉ አቅቷቸው መዓበሩ። "ሲሩል አዘል" ናቸውና ከጀሰዳቸው ያለፈው ኸበር ይጀመራል እንጂ እንኳንስ በኛ መዝገብ ባህሩ ቀለም ሆኖ መድ ቢነከር፣ ዛፉ ሁላ መቃ ቢቀረፅ፣ ሰማይ ብራና ቢዳመጥ አይጨረስም። መለክ ታጥቆ ቢቀዳ የሲሩ ሸራብ ጋኑም አያልቅ ጥሙም አይወጣ። #ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ! አሏሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም!💚💚💚
300
16
#ዙልሒጃ_ገባ ለዚህ ክቡር ወር ከፊታችን ለሚገኙ ዐሥር ውድ የአላህ ቀናት ሐጃቸውን የሚያስቀምጡ አወሊያዎች (የእርሱ ወዳጆች) ነበሩን። መውላና ሡልጣን ዐብዲልቃዲር ከይላኒ (ቁዲሰ ሲረሁ) በጉንያ ኪታባቸው ላይ ስለነዚህ ውድ ቀናት ውብ አስገራሚ ነገሮችን ከትበዋል። መዋሲሞች (ልንጠቀምባቸው የሚገቡ ቀናት) ሲመጣ የምቃኘው ውድ ኪታብ ነው። ጥቂቱን ለዚህ ለሊት ላካፍላችሁ። አላህ (ሱወ) በእነዚህ ውድ ዐሥር ቀናት ዐሥር ተዓምራትን አስቀምጧል ተብሏል ይላሉ። ① የዕድሜ በረከት ② የገንዘብ (ንብረት) መፋፋት ③ የቤተሰብ ጥበቃን የማግኘት ④ የወንጀል ምሕረት ⑤ የምንዳ መነባበር ⑥ በሞት ወቅት ከሚፈጠር ሰከራት መግራራት (ነፍስ አልወጣ ስትል ከሚፈጠር ችግር መጠበቅ) ⑦ ለጨለማ ብርሃን ማግኘት ⑧ የመልካም ሥራ ምንዳዎች ሚዛን ላይ መክበድ ⑨ ከችግሮች መዳን ¹⁰ ከፍተኛ ደረጃን መጎናጸፍ እነዚህ ታላላቅ ተዓምራት የተደገሱበት ውድ ቀናት ናቸው ይሉናል ዐሪፎቹ። እነዚህን ቀናት በዋናነት በልብ ጥራት መቀበል ያስፈልጋል። በማለት ኪታቡ ሌላም የዐሪፎችን ውብ ተጅሩባቶች (ልምዶች) ይጨምርልናል። ተጅሩባቶች ማለት በሸሪዓው እንደ ግዴታ የማይታይ ግና በታማኝነት ከዑለሞቹ በመውሰድ መለማመድ እንዳለብን ዑለሞቹ ያስተምራሉ። "በእነዚህ ቀናት ለመሳኪኖች ሰደቃ መለገስ ለነብያቶችና ለሩሱሎች የመለገስ ያህል ነው፣ አንድ ሕመምተኛ የዘየረ ሰው የአላህን ወዳጅ ወሊዮች እንደዘየረ ነው፣ አንድን ጀናዛ የሸኘ የሹሓዳዎችን ጀናዛ እንደሸኘ ነው፣ አንድን አማኝ ያለበሰ ሰው አላህ ከእርሱ በኾነ ነገር ያለብሰዋል፣ ለአንድ ወላጅ አልባ ልጅ ያዘነና የተንከባከበ ሰው በዕለተ ትንሳኤ በዐርሹ ጥላ ሥር ያስጠልለዋል፣ የዒልም መጃሊስ ላይ የተቀማመጠ ሰው የነብያትና የሩሱሎች መጃሊስ ላይ እንደተቀማመጠ ይቆጠርለታል።" ሲሉ የቀናቱን ውድነት እነርሱ በተረዱበት ተግባራዊ ዕይታ ለኡመቱ ሰንደው አስተላልፈውታል። ዐረፎቹ የጘይብ (የሩቅ) ነገር የገባቸው ምርጦች እንዲህ ይላሉ መን የራ ዐይባ ላ ዩራ ጘይባ [ነውር የሚመለከት ሰው ጘይብ አያይም] ጉድ እኮ ነው ♥ ይህ የኢማን ዐለም ዐይናችንና አዕምሮኣችን በሚታዩና በሚነበቡ ዐለሞች ተሞልቶ የወረቀት ዕውቀት ላይ ብቻ ቀርተን መረዳት ይጠናል።እንደውም የወረቀት ዕውቀት የልብ ዕውቀት ካልተከተለው የሚያስከትለው የነፍሲያ በሽታ ከባድ ነው። ከላይ እንዳነሳሁት አይነት የገውሶቹ ኩቱቦች የያዙት ጉድ የሚገባችን ልባችንን ለመክፈት ስንነይት ነው። በእነዚህ ቀናት የምንለማመደውም ልብን ለመከፈት የሚያግዙ ሥራዎችን በመነየት ነው። ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች ውጭ ልብን ከተንኮልና ራስን ካለማወቅ ለመራቅ በአንጻሩ ደፍሮ ራስን በመመርመር መቆየት ኸይርን እንድንረዘቅ ያደርጋል። ከዚሁ ጎን ለጎን ዚክርና ሰለዋት፣ ቁርኣንና በጥልቀት ማሰብ ላይም እንሰንብት። ተውፊቁን ይስጠና፣ ያስረዳንም ♥ አላህ ዐረፎቹን የምንረዳበት የኢማን ዐቅም ይለግሰን ♥ ጁመአ ነው በዱዓችሁ ♥
273
17
No text...
213
18
May-31-2024.m4a
234
19
‹‹መሞትህ ነው›› አሉት ገጠሬውን። ‹‹ከዝያ የት ነኝ?›› ብሎ ጠየቀ። ‹‹እጌታህ ዘንድ›› ቢሉት... ‹‹ታድያ መልካም ሁላ ተሱ ዘንዳ ይገኝ የለ! ምን አስፈራኝ!›› #ተስፋ ‹‹ዱዓው ተቀባይ የሆነን ሰው ታውቃለህ›› ብለው ጠየቁት። ‹‹አላውቅም፤ ግና ዱዓን የሚቀበል ጌታ አውቃለሁ›› አላቸው። #እምነት ሰሓቢዩ ዘንዳ አንዱ መጥቶ ጠየቀ፦‹‹ቂያም ቀን ማን ነው ሞጋቻችን?›› ‹‹አላህ›› ሰሐቢዩ መለሰ። ‹‹እንግዲህ ድነናላ!›› ብሎት ሄደ። #ጥልቅ_ተስፋ ወጣቱ ሞት አፋፍ ላይ ሁኖ ሲያጣጥር እናት ታለቅሳለች፦‹‹እማ! የቂያም ለት ሂሳብ ተሳሳቢዬ አንች ብትሆኚስ፤ ምን ታደርጊኛለሽ? ›› ጠየቃት። ‹‹ስለማዝንልህ ይቅር እልሃለኋ!›› ‹‹ካንቺ በላይ ወደሚያዝንልኝ ጌታ እየሄድኩ ነው'ና አታልቅሺ›› #ፍቅር Anuman
287
20
ፍትህ እና ፍርድ በጀሊሉ ችሎት... ሙሳ (ዐ.ሰ) አንድ ቀን ከአላህ ጋር እያወራ ሳለ አላህን እንዲህ ብሎ ጠየቀው፦ "ጌታዬ እስቲ ያንተን ፍትህ እና ያንተን ፍርድ አሳየኝ?" አላህም፦ "አንተ እኮ ችኩል እና ማትታገስ ነህ እንዴት አድርጌ ላሳይህ" ብሎ መለሰለት። ሙሳም፦ "ባንተ እገዛ ትዕግስት አደርጋለሁ" አለው። አላህም፦ "እንዲህ እንዲህ ... የሚባል ቦታ የውሀ ምንጭ አለ። እዛች ቦታ ማንም እንዳያይህ ተደብቀህ ችሎታዬንና ውስጥ አዋቂነቴን ዝም ብለህ ተከታተል" አለው። ሙሳም (ዐ.ሰ) እዛች ምንጭ ጋ ደረሰና ምንጯ አጠገብ ማንም በማያየው መልኩ እንዲት ዛፍ ላይ ወጥቶ ቁጭ አለ። ከዚያም አንድ ፈረሰኛ ምንጯ ጋ መጣና ፈረሱን አቁሞ ውሀ ጠጣ። በዛውም በአንድ ከረጢት 1000 ዲናር አጠገቡ አስቀመጠና ትንሽ ጋደም አለ። ከትንሽ እረፍት በኋላ ፈረሰኛው ያስቀመጠውን 1000 ዲናር ረስቶ ጉዞውን ጀመረ። ይህ ሁሉ ሲሆን ሙሳ በትኩረት እየተከታተለ ነው። ብዙም ሳይቆይ አንድ ልጅ መጣና ከምንጩ ጠጣና ሊሄድ ሲል ያ ፈረሰኛ ረስቶ የሄደውን 1000 ዲናር አየ። በጣም ተደስቶ ይዞት ሄደ። ልክ ልጁ አከባቢውን ለቆ እንደሄደ አንድ ማየት የተሳነው ሽማግሌ መጣ። ከምንጩ ጠጥቶ ውዱእ አደረገና እዛው ሰግዶ ጋደም አለ። ልክ ይህ ሽማግሌ ጋደም እንዳለ ያ የቅድሙ ፈረሰኛ ዲናሩን አስታውሶ ሲጋልብ መጣ። ቦታው ላይ ሲደርስ ሽማግሌው ተኝቷል ፈረሰኛውም ሽማግሌውን ቀሰቀሰውና፦ "አሁን እዚህ ጋ ውሀ ጠጥቼ 1000 ዲናር ረስቼ ሄጃለሁ። ካንተ ሌላ ማንም እዚጋ አልመጣም ስለዚህ ንብረቴን አሁን አምጣ" አለው። ሽማግሌውም፦ "ልጄ እኔ እንደምታየኝ እውር ነኝ ምንም ማየት አልችልም ታዲያ እንዴት አድርጌ እወስዳለሁ?" አለው። ፈረሰኛውም በጣም ተናደደ እየዋሸውም እንደሆነ ገመተ። ከዚያ ጎራዴውን አወጣና፦ "ንብረቴን ምትመልስ ከሆነ መልስ አይ ካልክ በዚህ ሆድህን እተረትረዋለሁ" ሲለው... ሽማግሌው ማልቀስ ጀመረ። ሙሳ (ዐ.ሰ) ይህን ሁሉ በትዕግስት እየተከታተለ ነው፡፡ ትዕግስቱ ሲሟጠጥ የጌታውን ቃል በማስታወስ ባለበት ይፀናል። ከዛ ፈረሰኛውም በያዘው ጎራዴ የሽማግሌውን አንገቱን ቀነጠሰለት። ከዚያም ልብሱን አገለባብጦ ሲፈትሽ ምንም ሊያገኝ አልቻለምና ትቶት ሄደ። ከዚያም አላህም እንዲህ አለ፦ " አንተ ሙሳ ይህ የኔ ፍትህ እና የኔ ፍርድ ነው፡፡" ሙሳም፦ "ጌታዬ ትዕግስቴ ተሟጥጦ አልቋል አንተ ጥበበኛ ነህ እስቲ አስረዳኝ" አለው አላህም፦ "እኔ ውስጥ አዋቂ ነኝ አንተ የማታውቀውን አውቃለሁ። ቅድም መጥቶ የፈረሰኛውን ንብረት የወሰደው ልጅ የራሱን ሀቅ ነው የወሰደው። ምክንያቱም የልጁ አባት! እዛ ፈረሰኛው ዘንድ ተቀጥሮ ሰርቷል ፈረሰኛውም የላቡን ከልክሎታል። ስለዚህ ልጁ የወሰደው የአባቱን ሀቅ ነው። "እውሩ ሽማግሌ ደሞ ድሮ አይኑ ከመጥፋቱ በፊት የዛን ፈረሰኛ አባት ገድሎት ስለነበር። ፈረሰኛው የአባቱን ገዳይ እንዲበቀልለት አድርገናል። "ያ ሙሳ! ለሁሉም ሀቁን አድርሰናል። አንዱ ፍትሀችን ሲሆን አንዱ ደሞ ፍርዳችን ነው። እኛም የጥበበኞች ሁሉ ጥበበኛ ነን አለው። ሱብሀን አላህ!!!
266