cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

hanny❤tube

"ያ አላህ ለሰጠኸኝ ፀጋ ሁሉ አመሰግንሀለው በፍጥረታትህ ስፍር ቁጥር ልክ ምስጋና ይገባህ" ለማንኛውም ጥያቄ ወይም አስተያየት @hilarious28

Show more
Advertising posts
789
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-4430 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የወንጀል ብዛት ያጎበጠኝ ባሪያህ ነኝ።  ረህመትህን ከጅዬ ሁሌ አነባለሁ፡፡ እንደ ሰማይ የራቀኝ ኢማኔ እንዲመለስልኝ ወዳንተ አለቅሣለሁ፡፡ ተራቁቻለሁና የኢማን ልብስ አልብሠኝ፤ ደክሚያለሁና በተወኩል ካስሚያ ደግፈኝ፡፡ ሸብቻለሁና በተቅዋ ካባ አጊጠኝ፡፡፡ ያ ረብ! @hannyTube
Show all...
Repost from ABX
የወንጀል ብዛት ያጎበጠኝ ባሪያህ ነኝ። ረህመትህን ከጅዬ ሁሌ አነባለሁ፡፡ እንደ ሰማይ የራቀኝ ኢማኔ እንዲመለስልኝ ወዳንተ አለቅሣለሁ፡፡ ተራቁቻለሁና የኢማን ልብስ አልብሠኝ፤ ደክሚያለሁና በተወኩል ካስሚያ ደግፈኝ፡፡ ሸብቻለሁና በተቅዋ ካባ አጊጠኝ፡፡፡ ያ ረብ! https://t.me/MuhammedSeidAbx
Show all...
ጥቂት ሰዓታትን ብቻ ፆመንለት ብዙ ለሚመነዳን አላህ ምስጋናው ይብዛ። @hannyTube
Show all...
እነሆ ከእንኳን አደረሳችሁ ወደ እንኳን አደረሳችሁ ተሸጋገርን። ለዚህ መድረስም ትልቅ መታደል ነው። ለረመዷን መድረስም፣ ጀምሮ በሰላምና ጤና መጨረስም ግዙፍ ፀጋ ነው። ሲመጣ በበረከቱ መምጣት ተደሰትን። ሲወጣ የጌታችንን ትዕዛዝ የቻልነዉን ያህል በመፈፀማችን፣ ትሩፋቱ መልካም ይሆናል ብለን በማሰባችን ተደሰትን። ሥራ ከኛ ዉጤት ከአላህ ነው። እሱ የመልካም ሠሪን ምንዳ ቅንጣት ታክል አይዘነጋም። @hannyTube
Show all...
#ረመዳን 24 وَٱلَّذِينَ هُمْ لِأَمَٰنَٰتِهِمْ وَعَهْدِهِمْ رَٰعُونَ እነዚያም እነርሱ ለአደራዎቻቸውና ለቃል ኪዳናቸው ጠባቂዎች፡፡ ይህ አንድ ሰው ሙዕሚን ለመሆን ከሚያሟላቸው መስፈርቶች አንዱ ነው። አማኝ ሰው የሰውን አደራ አይበላም። ቃል ለመግባትም አይቸኩልም ከገባ ግን ለመፈፀም ይቻኮላል።                መልካም የኢባዳ ቀን😍😍 @hilarious28
Show all...
ረመዷን - 21 *** ኢዕቲካፍ ከዱንያ ግርግርና ሁካታ በመራቅ ለቀናት አሊያም ለሰዓታት በተለያዩ የአምልኮ ተግባራት መስጊድ ዉስጥ የመቆየት ሁኔታ ነው፡፡ ዓላማው ወደ አላህ መቅረብ፣ ቀልብን ማለስለስ፣ ኢማንን ማደስ፣ በመንፈስ ከፍ ማለት ነው፡፡  ለሁሉም ነገር የተሻለ ጊዜ አለው። ለኢዕቲካፍ ይበልጥ ተመራጩ ጊዜ እነኚህ አሥር ቀናት ናቸው። ይህንኑ በማሰብ ባሮች ወደ አላህ መስጊድ ይመጣሉ። አሁን አሁን ላይ ብዙ መስጊዶች ላይ ኢዕቲካፍ ይደረጋል፡፡ ጉጉቱ እንዳለ ሆኖ ስህተቶችም ሲፈፀሙ ይስተዋላል። ኢዕቲካፍ ዓላማው ይሳካና ትርፍም ይገኝበት ዘንድ ጥንቃቄ ይፈልጋል፡፡ * ኒያ ይቀድማል፤ ኒያችሁን አሳምሩ፣ ሰው ስለገባ ብቻ አትግቡ፣ * ሙሉ ትኩረታችሁን ዒባዳ ላይ ብቻ አድርጉ፣ * ዱንያን እዉጭ ትታችሁ ግቡ።  መንፈሳዊ ስኬትን አስቡ፣ * ራሳችሁን ፈትሹበት፣ ዉስጣችሁን እዩበት፣ የጥሞና ጊዜ አድርጉት፣ * በአምልኮ ወደ አላህ ይበልጥ ለመቃረብ አጋጣሚ ነዉና ተለወጡበት። * ሱቃቸዉንና ስልካቸዉን ሁሉ ዘግተው ኢዕቲካፍ የሚገቡ  ደጋግ ባሮች አሉ፣ * ዱንያዊ ወሬዎችንና ወጎችን ይራቁ፣ * የግድ ለሆነ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከመስጊድ አትውጡ፣ *  ቁርኣን፣ ዚክር፣ ዱዓ፣ ሶላትና ሶለዋት አብዙ። አስታውሱ - ኢዕቲካፍ * እንቅልፍ ሲለጥጡ የሚዉሉበት አጋጣሚ አይደለም፣ * ሶሻል ሚዲያ ላይ ተጥደው የሚያሳልፉበት ቦታም መሆን የለበትም፣ *  ኢዕቲካፍ ነኝ ብለው ለዚህም ለዚያም አይለፍፉ፣ አላህ ያሉበትን ቦታና ሁኔታ ያውቃልነሰ፣ * የሀሜት ቦታ፣ ወሬ መሰልቀጫ፣ ምግብ ማማረጫ  ቦታም እንዳይሆን ይጠንቀቁ። * ቁጭ ብለው በስልክ የመነገጃ መድረክም አያድርጉት። ኢዕቲካፍ ለትልቅ ዓላማ ነዉና የተደነገገወ በአግባቡ እንጠቀምበት። ባረከሏሁ ፊኩም @hannyTube
Show all...
Repost from ABX
ረመዷን - 21 *** ኢዕቲካፍ ከዱንያ ግርግርና ሁካታ በመራቅ ለቀናት አሊያም ለሰዓታት በተለያዩ የአምልኮ ተግባራት መስጊድ ዉስጥ የመቆየት ሁኔታ ነው፡፡ ዓላማው ወደ አላህ መቅረብ፣ ቀልብን ማለስለስ፣ ኢማንን ማደስ፣ በመንፈስ ከፍ ማለት ነው፡፡  ለሁሉም ነገር የተሻለ ጊዜ አለው። ለኢዕቲካፍ ይበልጥ ተመራጩ ጊዜ እነኚህ አሥር ቀናት ናቸው። ይህንኑ በማሰብ ባሮች ወደ አላህ መስጊድ ይመጣሉ። አሁን አሁን ላይ ብዙ መስጊዶች ላይ ኢዕቲካፍ ይደረጋል፡፡ ጉጉቱ እንዳለ ሆኖ ስህተቶችም ሲፈፀሙ ይስተዋላል። ኢዕቲካፍ ዓላማው ይሳካና ትርፍም ይገኝበት ዘንድ ጥንቃቄ ይፈልጋል፡፡ * ኒያ ይቀድማል፤ ኒያችሁን አሳምሩ፣ ሰው ስለገባ ብቻ አትግቡ፣ * ሙሉ ትኩረታችሁን ዒባዳ ላይ ብቻ አድርጉ፣ * ዱንያን እዉጭ ትታችሁ ግቡ። መንፈሳዊ ስኬትን አስቡ፣ * ራሳችሁን ፈትሹበት፣ ዉስጣችሁን እዩበት፣ የጥሞና ጊዜ አድርጉት፣ * በአምልኮ ወደ አላህ ይበልጥ ለመቃረብ አጋጣሚ ነዉና ተለወጡበት። * ሱቃቸዉንና ስልካቸዉን ሁሉ ዘግተው ኢዕቲካፍ የሚገቡ ደጋግ ባሮች አሉ፣ * ዱንያዊ ወሬዎችንና ወጎችን ይራቁ፣ * የግድ ለሆነ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከመስጊድ አትውጡ፣ *  ቁርኣን፣ ዚክር፣ ዱዓ፣ ሶላትና ሶለዋት አብዙ። አስታውሱ - ኢዕቲካፍ * እንቅልፍ ሲለጥጡ የሚዉሉበት አጋጣሚ አይደለም፣ * ሶሻል ሚዲያ ላይ ተጥደው የሚያሳልፉበት ቦታም መሆን የለበትም፣ * ኢዕቲካፍ ነኝ ብለው ለዚህም ለዚያም አይለፍፉ፣ አላህ ያሉበትን ቦታና ሁኔታ ያውቃልነሰ፣ * የሀሜት ቦታ፣ ወሬ መሰልቀጫ፣ ምግብ ማማረጫ ቦታም እንዳይሆን ይጠንቀቁ። * ቁጭ ብለው በስልክ የመነገጃ መድረክም አያድርጉት። ኢዕቲካፍ ለትልቅ ዓላማ ነዉና የተደነገገወ በአግባቡ እንጠቀምበት። ባረከሏሁ ፊኩም https://t.me/MuhammedSeidAbx
Show all...
ረመዷን (20) ከዐስር በኋላ አንድ ማዕድ ነበረን፣ እስከ መግሪብ ድረስ የሚዘልቅ። ከተራዊሕ በኋላም አንድ ማዕድ ነበረን፣ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ የሚረዝም። ከሱብሒ በኋላም ሌላ ማዕድ ነበረን፣ እስኪነጋ ድረስ የሚቆይ። ረመዷን የቁርኣን ወር ነዉና እነኚህ በቀን ዉስጥ የቁርኣን መማማሪያ ማዕዶቻችን ነበሩ።  በዚህ መልኩ መስጂዶች በቡድን ቡድን ሆነው ቁርኣንን በሚማማሩ ሐለቃዎች ይደምቃሉ። የዛሬዉን ሳይሆን የድሮዉን ነው የማወራችሁ። አላህ ይዘንልህ ሙሐመዱ፤ ምን ሆነህ ነው እንዲህ የደከምከው!። ሰብሰብ ብሎ ተቀምጦ ቁርኣንን በዙር ማንበብ በርካታ ፋይዳዎች አሉት። ያላወቁትን ለመማር፣ ያጠፉትን ለማስተካከል ያግዛል። ለማስተዋልና ለማስተንተንም ይጋብዛል። በአላህ ቤት ዉስጥ ቁርአንን ስብስብ ብሎ ማንበብና መማማር አላህ ዘንድ ያስወድዳል፣ የዉጭና የዉስጥ ሰላም ይሰጣል፣ የአላህን እዝነት ያስገኛል፣  በመላእክት ያሰከብባል፣ በላዕላዩ ዓለም ያስወድሳል። የ20ኛ ቀን ፀሐይ እየጠለቀች፣ የረመዷን 21ኛው ቀን ገባሁ እያለ ነው። አላህ ረሃብ ጥማታችሁን፣ ድካማችሁን ሁሉ ይቁጠር። @hannyTube          @hilarious28
Show all...
ረመዷን 20 በርግጥ ትናንት ነበር አላህ ሆይ ለረመዷን አድርሰን ብለን ስንማፀን የነበረው። ዛሬ ስለ ዐሽረልአዋኺር እያወራን ነው። 10ቱ ወሳኝ የረመዷን የመጨረሻ ቀናት። ጌታዬ ሆይ ሁሌም የእዝነትህ ከጃዩች ነን። ለባሮችህ እዘንልን። @hannyTube
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.