ሐዲስ በአማርኛ
Open in Telegram
📚ይህ እለታዊ ሶሒሕ የሆኑ ሐዲሶች የሚለቀቁበት ቻናል ነው። አስተያየት ወይም መልእክት ካለዎት በ @HadithAmharic_bot ይላኩ።
Show more2 590
Subscribers
-224 hours
+57 days
-1530 days
Data loading in progress...
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '24
+6
in 0 channels
November '24
+6
in 0 channels
Get PRO
October '240
in 0 channels
Get PRO
September '24
+30
in 0 channels
Get PRO
August '24
+12
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 1 channels
Get PRO
March '240
in 0 channels
Get PRO
February '240
in 0 channels
Get PRO
January '240
in 0 channels
Get PRO
December '230
in 0 channels
Get PRO
November '230
in 0 channels
Get PRO
October '23
+33
in 0 channels
Get PRO
September '23
+41
in 0 channels
Get PRO
August '23
+31
in 0 channels
Get PRO
July '23
+54
in 0 channels
Get PRO
June '23
+43
in 0 channels
Get PRO
May '23
+32
in 0 channels
Get PRO
April '23
+62
in 0 channels
Get PRO
March '23
+63
in 0 channels
Get PRO
February '23
+26
in 0 channels
Get PRO
January '23
+50
in 0 channels
Get PRO
December '22
+44
in 0 channels
Get PRO
November '22
+38
in 0 channels
Get PRO
October '22
+57
in 0 channels
Get PRO
September '22
+56
in 0 channels
Get PRO
August '22
+46
in 0 channels
Get PRO
July '22
+57
in 0 channels
Get PRO
June '22
+75
in 0 channels
Get PRO
May '22
+84
in 0 channels
Get PRO
April '22
+162
in 0 channels
Get PRO
March '22
+46
in 0 channels
Get PRO
February '22
+73
in 0 channels
Get PRO
January '22
+54
in 0 channels
Get PRO
December '21
+44
in 0 channels
Get PRO
November '21
+34
in 0 channels
Get PRO
October '21
+54
in 0 channels
Get PRO
September '21
+60
in 0 channels
Get PRO
August '21
+98
in 0 channels
Get PRO
July '21
+82
in 0 channels
Get PRO
June '21
+72
in 0 channels
Get PRO
May '21
+124
in 0 channels
Get PRO
April '21
+208
in 0 channels
Get PRO
March '21
+99
in 0 channels
Get PRO
February '21
+61
in 0 channels
Get PRO
January '21
+95
in 0 channels
Get PRO
December '20
+3 482
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 20 December | 0 | |||
| 19 December | +1 | |||
| 18 December | 0 | |||
| 17 December | +1 | |||
| 16 December | 0 | |||
| 15 December | +4 | |||
| 14 December | 0 | |||
| 13 December | 0 | |||
| 12 December | 0 | |||
| 11 December | 0 |
Channel Posts
عَنْ أَبِي قَتَادَةَ رضي الله عنه ، قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم:
[ صِيَامُ يَوْمِ عَاشُورَاءَ أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ ]
📚رواهُ مسلم
🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸
ከአቢ-ቀታዳ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው የአላህ መልዕክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:-
[ የዐሹራን ቀን መጾም ከርሱ በፊት (ያለፈውን) አመት ወንጀል ያስሰርዛል ብዬ ከአሏህ እከጅላለሁ። ]
📚ሙስሊም ዘግበውታል።
●የሙሐረም ወር 10ኛው ቀን እለተ ዐሹራእ በመባል ይታወቃል።
የዘንድሮ (የ1445 ዓ.ሂ) ዐሹራእ የሚሆነው የፊታችን ጁሙዐ ሐምሌ 21/2015 ነው:: ከፊቱ ወይም ከኋላ መጾም ተገቢ ነው።
🤲አላህ ይወፍቀን
🔖ሐዲስ በአማርኛ:
Telegram: t.me/HadithAmharic
Instagram: instagram.com/HadithAmharic
FB: fb.com/HadithAmharic
| 2 | عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ :
قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّم
" أَفْضَلُ الصِّيَامِ بَعْدَ رَمَضَانَ شَهْرُ اللَّهِ الْمُحَرَّمُ
وأفضل الصلاة بعد الفريضة صلاة الليل "
📚 رواه مسلم
🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸
የአላህ መልዕክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡-
“ከረመዷን በኋላ በላጩ ጾም የአላህ ወር ሙሐረም ነው፣ ከግዴታ ሶላት በኋላ በላጩ ሶላት የሌሊት ሶላት ነው።”
📚[ሙስሊም ዘግበውታል።] | 445 |
| 3 | 🕋የጁሙዐ ቀን ሱናዎች🕌
1-ነቢዩ(صلى الله عليه وسلم)ላይ ሶለዋት ማውረድን ማብዛት
2- 📖 ሱረቱ–ከህፍን መቅራት
3-🚿 ሸዋር መውሰድ
4-👚 ካለው ሻል ያለውን ልብስ መልበስ
5-🦷ሚስዋክ መጠቀም(ጥርስን መፋቅ)
6-🌹 ሽቶ መቀባት
7-🌅 ወደ መስጂድ አበክሮ መሄድ
8- ወደ መስጅድ በግር መሄድ
9-📿 ከጁሙዐ ሶላት ቡሃላ 4 ረከዓ(2+2) መስገድ
10- ዱዓ ተቀባይነት ያላትን ሰዓት መጠባበቅ
🔖ሐዲስ በአማርኛ: | 1 523 |
| 4 | تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
ዒድ ሙባረክ!! 🎉 | 348 |
| 5 | عن أبي قتادة الأنصاريِّ رضي الله عنه أن النبي صلى الله عليه وسلم قال:-
[ صِيَامُ يَوْمِ عَرَفَةَ أَحْتَسِبُ عَلَى الله أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلهُ وَالسَّنَةَ الَّتِي بَعْدَهُ ]
📚 رواه مسلم
🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸
ከአቢ-ቀታዳ አል-አንሷሪ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:-
[የዐረፋን ቀን መጾም ከርሱ በፊት (ያለፈውን) አመት እና ከርሱ ቡሃላ(የሚቀጥለውን) አመት ወንጀል ያስሰርዛል ብዬ ከአሏህ እከጅላለሁ።]
📚ሙስሊም ዘግበውታል።
📆 የዐረፋ ቀን(ዙልሒጃ 9ኛው) ነገ ነው።
🔖ሐዲስ በአማርኛ:-
Telegram: https://t.me/HadithAmharic
Instagram: https://instagram.com/HadithAmharic | 495 |
| 6 | አስሩን የዙልሒጃ ቀናት እንዴት እናሳልፍቻው?
1-እውነተኛ ተውበት ማድረግ
እነዚህንም ሆነ ሌሎች የዒባዳ ቀናትን ለመቀበል ከሰራናቸው ወንጀሎች በመጸጸት ወደ አላህ መመለስ አለብን። አላህ እንዲ ብሏል:-
{ ምእምናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ) ተጸጸቱ።﴿ [ሱረ አል-ኑር፣31]
2- ቀኖቹን በአግባቡ ለመጠቀም ቁርጠኛ መሆን
በዙልሒጃ 10 ቀናት ውስጥ ልዩ ትኩረት ሰጥተን አላህ በደነገጋቸው ኢባዳዎች ለማሳለፍ ከወዲሁ ራስን እና ያግዘናል ያልነውን ነገሮች በሙሉ ማዘጋጀ ተገቢ ነው።
አላህ እንዲ ብሏል:- {እነዚያም በኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፤ አላህም በእርግጥ ክበጎ ሠሪዎች ጋር ነው።﴿[ሱረቱ አል-ዐንከቡት፣69]
3- ከወንጀል መራቅ
የአላህን ተእዛዛት መፈጸም ወደርሱ እንደሚያቃርብ ሁሉ የከለከላቸውን እና እርም ያደረጋቸውን ነገሮች መዳፈር ከርሱ መራቅን እና ከእዝነቱ ለመባረር ምክንያቶች ናቸው።
🕋 አስሩ የዙልሒጃ ቀናት ያላቸው ደረጃ
1-አላህ ሱብሓነሁ ወተዓላ በነዚህ ቀናት ምሏል
አላህ በሆነ ነገር ሲምል የዛን ነገር ትልቅነት እና ደረጃ ያመለክታል፤ አላህ በትልቅ ነገር እንጅ አይምልም። አላህ እንዲህ ብሏል:-
﴾በጎህ እምላለሁ።በዐሥር ሌሊቶችም።﴿
[አል-ፈጅር፣1-2]
ኢብን ከሢርን ጨምሮ አብዛኞች ሙፈሲሮች እንዳሉት ‘አስሩ ሌሊቶች’ የዙልሒጃ የመጀመሪያዎቹ ናቸው።
2-አላህ በርሱ ውስጥ እሱን ማውሳትን የደነገገባት “የታወቁ ቀናት” መሆናቸው።
አላህ እንዲህ ብሏል:-
﴾በታወቁ ቀኖችም ውስጥ ከማለዳ እንሰሳዎች በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ፣ (ይመጡሃል)﴿
[አል-ሐጅ፣28]
ኢብን ዐባስ እንዳሉት የታወቁ ቀኖች የተባሉት የዙሒጃ የመጀመሪያዎቹ አስሩ ቀኖች ናቸው።
3- ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከዱንያ ቀኖች በላጭ መሆኗን ተናግረዋል
ከዐብደላህ ቢን ዐባስ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው ነቢዩ( ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:-
[ከነዚህ አስርት(ከዙልሒጃ የመጀመሪያዎቹ) ቀናት ይበልጥ አላህ ዘንድ በውስጣቸው የሚሰሩ መልካም ስራዎች ተወዳጅ የሚሆኑበት ቀን የለም።] ብለው ሲናገሩ ሶሐቦች፡- ”የአላህ መልእክተኛ ሆ! በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን?“ በማለት ጠየቁ፤ ነብዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም):- [ (አዎን!)ነፍሱንና ንብረቱን ይዞ የወጣ፣ ከዚያም አንዱንም ይዞ ያልተመለሰ ሰው ካልሆነ በስተቀር፣ በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን(አይበልጥም።)] አሉ። (አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።)
4- በአስሩ ቀናት ውስጥ የዐረፋ ቀን አለ።
ዐረፋ ከዙልሒጃ የዘጠነኛው ቀን ነው። አላህ ﴾ ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ። ለናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ﴿የሚለውን አያህ ያወረደበት፣ወንጀሎች የሚማሩበት፣ የአላህ ባሮች ከእሳት ነጻ የሚባሉበት ቀን ነው።
5- በአስሩ ቀናት ውስጥ የእርድ ቀን (ዒደል-አድሐ) አለ።
የዙሒጃ አስረኛው የውመነሕር(የእርድ ቀን)የዒድ ቀን ነው። ከቀናቶች ሁሉ ታላቅ ቀን ነው። ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:-(አላህ ዘንድ ከቀናት ሁሉ ትልቁ የእርዱ(ዒደል-አድሐ) ቀን ነው።(አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።)
6-ዋና ዋና የዒባዳ አይነቶች በነዚህ ቀናት ውስጥ ተሰብስበው ይገኛሉ።
ኢብን ሐጀር(አላህ ይዘንላቸው እና) እንዲህ አሉ:- “የዙልሒጃ አስሩ ቀናት ልዩ የሆኑበት ምክንያት ዋና ዋና የአምልኮ አይነቶች እነሱም:ሶላት፣ ጾም፣ ሶደቃ እና ሐጅ በውስጧ ስለተሰበሰቡ ነው። ይህ(ስብስብ) በሌሎቹ ውስጥ አይገኝም።”
🕋በአስሩ የዙልሒጃ ቀናት ውስጥ ከሚሰሩ ታላላቅ ዒባዳዎች:- ሐጅ እና ዑምራ፣ ጾም፣ ሶላት፣ ዚክር እና ደቃ ማብዛት ይገኙበታል።
🔖ሐዲስ በአማርኛ:-
Telegram: t.me/HadithAmharic
Instagram: instagram.com/HadithAmharic
FB: fb.com/HadithAmharic | 466 |
| 7 | No text... | 383 |
| 8 | عن ابن عباس رضي الله عنهما، عن النبي صلى الله عليه وسلم قال:
[ ما مِن أيَّامٍ العملُ الصَّالحُ فيها أحبُّ إلى اللَّهِ من هذِهِ الأيَّام يعني أيَّامَ العشرِ ، قالوا : يا رسولَ اللَّهِ ، ولا الجِهادُ في سبيلِ اللَّهِ ؟ قالَ : ولا الجِهادُ في سبيلِ اللَّهِ ، إلَّا رَجلٌ خرجَ بنفسِهِ ومالِهِ ، فلم يرجِعْ من ذلِكَ بشيءٍ]
📚رواه أبو داوود
🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸
ከዐብደላህ ቢን ዐባስ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው ነቢዩ( ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:-
[ከነዚህ አስርት(ከዙልሒጃ የመጀመሪያዎቹ) ቀናት ይበልጥ አላህ ዘንድ በውስጣቸው የሚሰሩ መልካም ስራዎች ተወዳጅ የሚሆኑበት ቀን የለም።] ብለው ሲናገሩ ሶሐቦች፡- ”የአላህ መልእክተኛ ሆ! በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን?“ በማለት ጠየቁ፤ ነብዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም):- [ (አዎን!)ነፍሱንና ንብረቱን ይዞ የወጣ፣ ከዚያም አንዱንም ይዞ ያልተመለሰ ሰው ካልሆነ በስተቀር፣ በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን(አይበልጥም።)] አሉ።
📚አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።
🔖ሐዲስ በአማርኛ:-
Telegram: https://t.me/HadithAmharic
Instagram: https://instagram.com/HadithAmharic | 463 |
| 9 | عن أسامة بن شريك رضي الله عنه قال: قال النبي ﷺ:
[ما كرهت أن يراه الناس , فلا تفعله إذا خلوت ]
📚رواه ابن حبان
🌸«::::::::::::::::» «:::::::::::::::»🌸
ከኡሳማ ቢን ሸሪክ (አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተላለፈው ነቡዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–
[ ሰዎች ካንተ እንዲያዩት የምትጠላውን ነገር አንተ ብቻህን ስትሆን አትስራው።]
📚ኢብን ሒባን ዘግበውታም | 518 |
| 10 | 🕋የጁሙዐ ቀን ሱናዎች🕌
1-ነቢዩ(صلى الله عليه وسلم)ላይ ሶለዋት ማውረድን ማብዛት
2- 📖 ሱረቱ–ከህፍን መቅራት
3-🚿 ሸዋር መውሰድ
4-👚 ካለው ሻል ያለውን ልብስ መልበስ
5-🦷ሚስዋክ መጠቀም(ጥርስን መፋቅ)
6-🌹 ሽቶ መቀባት
7-🌅 ወደ መስጂድ አበክሮ መሄድ
8- ወደ መስጅድ በግር መሄድ
9-📿 ከጁሙዐ ሶላት ቡሃላ 4 ረከዓ(2+2) መስገድ
10- ዱዓ ተቀባይነት ያላትን ሰዓት መጠባበቅ
🔖ሐዲስ በአማርኛ: | 417 |
| 11 | عن ثوبان رضي الله عنه أن رسولُ الله صلى الله عليه وسلم قال:
[ من صام رمضان وستا من شوال فقد صام السنة ]
📚رواه إبن حبان
🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸
ከሠውባን(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–
[ ረመዷንን እና ከሸዋል ስድስት ቀን የፆመ ሰው በእርግጥ አመት ፆመ።]
📚ኢብን ሒባን ዘግበውታል።
🔖ሐዲስ በአማርኛ:-
Telegram: https://t.me/HadithAmharic
Instagram: https://instagram.com/HadithAmharic | 495 |
| 12 | 🌾 ስለዘካተል-ፊጥር አጭር ማስታወሻ🌾
1⃣ ትርጉም:- ዘካተል-ፊጥር(ሶደቀተል-ፊጥር):- የረመዷንን ወር ፆም በመጨረስ ግዴታ የሚሆን ሶደቃ(ምጽዋት) ነው።
2⃣ የመደንገጉ ሒክማ(ጥበብ)
💡ለፆመኛው ሰው በረመዳን ፆም ላስገኛቸው ያልተገቡ እና ውድቅ ንግግሮች ማጥሪያ
💡ለሚስኪኖች በጎ ለመዋል እና የዒድ ቀን ከልመና እንዲብቃቁ ማድረግ
💡የዒዱን ቀን ደስታ አብሮ ለመጋራት
💡አላህ የረመዷንን ፆመ ለመጨረስ ስላበቃን ለአላህ ምስጋናን የምንገልፅበት
3⃣ ሑክሙ(ሸሪዐዊ ድንጋጌው)
✔️ዘካተልፊጥር መስጠት ግዴታ ነው።
ከዐንደላህ ቢን ዑመር(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው እንዲህ አለ:-
"የአላህ መልዕክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘካተል-ፊጥርን ግድ አደረጉ። ከተምር አንድ ዘንቶ፣ ወይም ከገብስ አንድ ዘንቶ(ግድ አደረጉ)። ሙስሊም የሆኑ ባሪያም ጨዋም ላይ፣ ሴትም ወንድም ላይ፣ ትንሽም ትልቅም ላይ (ግድ አደረጉ)። ሰዎች ወደ(ዒድ) ሶላት ከመውጣታቸው በፊት እንድትሰጥም አዘዙ።"(ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል።)
4⃣ ግዴታ የሚሆንባቸው ሰዎች
▫️የዒድ ለሊት እና ቀን ለራሱ እና በርሱ ላይ መቀለብ ግዴታ ከሚሆኑበት ሰዎች ቀለብ በላይ ያለው ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።
5⃣ ማውጣት ግድ የሚሆነው ከማን ነው?
✅ ከራሱ እና በርሱ ስር ላሉ የሚቀልባቸው ሰዎች(እንደ ሚስቶች፣ ልጆች...)
✅ ሆድ ውስጥ ላለ ጽንስ ማውጣት የተወደደ ነው።
6⃣ የሚወጣው ምንድን ነው?
✔️ዘካተል-ፊጥር የሚወጣው በአካባቢው በአብዛኛው ለምግብነት ከሚውል እህል ነው።
✅ የእህሉን ዋጋ በገንዘብ ቀይሮ መስጠት አያብቃቃም።
7⃣ የሚወጣው የእህል መጠን
✨ ለእያንዳንዱ ሰው አንዳንድ ዘንቶ
ዘንቶ:- በመካከለኛ ሰው እጅ አራት እፍኝ🤲 የሚይዝ መስፈሪያ ነው።
8⃣ ለማን ነው የሚሰጠው?
🔖 በሚያወጣው ሰው አገር ላሉ ደሀ እና ሚስኪኖች
9⃣ ⏰የሚወጣበት ጊዜ
📍በላጩ ጊዜ የዒድ ቀን ጧት ከዒድ ሶላት በፊት ነው።
📍ከዒድ አንድ ወይም ሁለት ቀን ቀደም ብሎ መስጠት ይቻላል።
🕌 ከዒድ ሶላት ቡኃላ ማዘግየት አይፈቀድም።
🔖ሐዲስ በአማርኛ:-
Telegram: https://t.me/HadithAmharic
Instagram: https://instagram.com/HadithAmharic | 813 |
| 13 | عن ابن عمر رضي الله عنهما قال:
"فرَض رسول الله صلى الله عليه وسلم زكاة الفطر صاعًا من تمرٍ، أو صاعًا من شعيرٍ، على العبد والحر، والذكر والأنثى، والصغير والكبير من المسلمين، وأمر بها أن تؤدى قبل خروج الناس إلى الصلاة"
📚رواه البخاري ومسلم
🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸
ከዐንደላህ ቢን ዑመር(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተወራው እንዲህ አሉ:-
"የአላህ መልዕክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘካተል-ፊጥርን ግድ አደረጉ። ከተምር አንድ ዘንቶ፣ ወይም ከገብስ አንድ ዘንቶ(ግድ አደረጉ)። ሙስሊም የሆኑ ባሪያም ጨዋም ላይ፣ ሴትም ወንድም ላይ፣ ትንሽም ትልቅም ላይ (ግድ አደረጉ)። ሰዎች ወደ(ዒድ) ሶላት ከመውጣታቸው በፊት እንድትሰጥም አዘዙ።"
📚ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል።
ዘንቶ:- በመካከለኛ ሰው እጅ አራት እፍኝ🤲 የሚይዝ መስፈሪያ ነው።
✔️ዘካተል-ፊጥር የሚወጣው በአካባቢው በአብዛኛው ለምግብነት ከሚውል እህል ነው።
🔖ሐዲስ በአማርኛ:-
Telegram: https://t.me/HadithAmharic
Instagram: https://instagram.com/HadithAmharic | 654 |
| 14 | عن عائشةَ رضِيَ اللهُ عنها أنَّ رسولَ الله صلَّى الله عليه وسلَّمَ قال:
[ تَحرُّوا لَيلةَ القَدْرِ في الوَتْر من العَشرِ الأواخِرِ من رمضانَ]
📚رواه البخاريُّ
🌸«::::::::::::::::» «:::::::::::::::»🌸
ከዓኢሻ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተላለፈው የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–
[ ለይለተል-ቀድርን ከረመዳን መጨረሻዎቹ አስርት ቀናት ጎዶሎ ለሊቶች ውስጥ (መገጠምን) ፈልጉ።]
📚ቡኻሪ ዘግበውታል።
ሐዲስ በአማርኛ: https://t.me/HadithAmharic | 653 |
| 15 | عن أبي هريرة رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:
[ مَن يَقُمْ ليلةَ القَدْرِ إيمانًا واحتسابًا، غُفِرَ له ما تَقدَّمَ من ذَنبِه ]
📚متفق عليه
🌸«::::::::::::::::» «:::::::::::::::»🌸
ከአቢ-ሁረይረህ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እንደተላለፈው የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–
[ ለይለተል-ቀድርን በአላህ አምኖ፣ ምንዳን ከአላህ ከጅሎ የሚቆም ሰው ከወንጀሉ ያለፈው ይማርለታል።]
📚ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል።
ሐዲስ በአማርኛ: https://t.me/HadithAmharic | 480 |
| 16 | عن عبد الله بن عمر رضي الله عنهما قال: كان رسول الله صلى الله عليه وسلم إذا أفطر قال:
[ ذَهَبَ الظَّمَأُ، وَابْتَلَّتِ الْعُرُوقُ، وَثَبَتَ الْأَجْرُ إِنْ شَاءَ الله]
📚 رواه أبو داود
🌸«::::::::::::::::::» «:::::::::::::::::»🌸
ከዐብደላህ ቢን ዑመር (አላህ ከሁለታቸውም ስራቸውን ይውደድላቸው) እንደተወራው የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሲያፈጥሩ(ፆም ሲፈቱ) እንዲህ ይሉ ነበር:-
"ዘሀበዝ-ዞመኡ ወብተል-ለቲል ዑሩቁ ወሠበተል-አጅሩ ኢንሻ አላህ"
ትርጉሙ:-
[ ጥሙ ተወገደ የደም ሰሮችም ረጠቡ በአላህ ፍቃድ ምንዳውም ፀደቀ።]
📚አቡ-ዳውድ ዘግበውታል።
🔖ሐዲስ በአማርኛ:-
Telegram: https://t.me/HadithAmharic
Instagram: https://instagram.com/HadithAmharic | 536 |
| 17 | 1- ስለበሽተኛ ሰው ጾም መፍታት
2- ጾም ለመፍታት የሚያበቃ በሽታ ምን ሲሆን ነው?
3- በበሽታ ያፈጠረ ሰው ምን ማድረግ አለበት?
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
1⃣ ስለበሽተኛ ሰው ጾም መፍታት
በሽተኛ ሰው በረመዷን ጾም መፍታት ይችላል።
وَمَن كَانَ مَرِيضًا أَوْ عَلَىٰ سَفَرٍ فَعِدَّةٌ مِّنْ أَيَّامٍ أُخَرَ ۗ يُرِيدُ اللَّهُ بِكُمُ الْيُسْرَ وَلَا يُرِيدُ بِكُمُ الْعُسْرَ وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ [٢:١٨٥]
[በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነም ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን (በልኩ) መጾም አለበት፡፡ አላህ በእናንተ ገሩን (ነገር) ይሻል፡፡ በእናንተም ችግሩን አይሻም፡፡ ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩትና ታመሰግኑት ዘንድ (ይህን ደነገግንላችሁ)፡፡(ሰረቱል-በቀራ 2፡185)
2⃣ ጾም ለመፍታት የሚያበቃ በሽታ ምን ሲሆን ነው?
1-በጾም ምክንያት በሽታው የሚጨምር ከሆነ
2- በጾም ምክንያት መሻሩ የሚዘገይ ከሆነ
2- የሚጎዳውና እና ከጾመ ለሞት የሚዳርገው ከሆነ(መፍታት ግዴታ ነው።)
✅ ከጾም ጋር መቋቋም የሚቻሉ እና ጉዳት የማያደርሱ ቀላል በሽታዎች(እንደ ቀላል ራስ ምታት፣ ጉንፋን፣ የጥርስ ህመም…) ጾምን ለመፍታ በቂ ምክንያት አይሆኑም።
3⃣ በበሽታ ያፈጠረ ሰው ምን ማድረግ አለበት?
ሀ- የሚሽር በሽታ ከሆነና ከሻረ ያፈጠረውን ቀኖች ያክል ቀዷ(ማካካሻ)መጾም አለበት።
ለ-የማይሽር በሽታ(እንደ ስኳር በሽታና የመሳሰሉት) ከሆነ:- በረመዷኑ ወር ቀኖች ብዛት ያክል ለሚስኪኖች ምግብ ማብላት አለበት። በየቀኑ ወይም ሁሉንም አንድ ጊዜ ማብላት ይችላል።
https://t.me/HadithAmharic | 819 |
| 18 | عن أبي هريرة رضي الله عنه أن النبيَّ صلى الله عليه وسلم قال:-
[ مَن لم يَدَعْ قول الزُّور والعملَ به والجهلَ، فليس للهِ حاجةٌ أن يَدَعَ طعامه وشرابه]
📚رواه البخاري
🌸«::::::::::::::::» «:::::::::::::::»🌸
ከአቢ-ሁረይረህ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸው) እንደተወራው የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–
[ የሀሰት ንግግርን፣ በርሱ መስራትን እና የቂል ተግባርን ያልተወ ሰው ምግቡንና መጠጡን ከመተዉ አላህ ጉዳይ የለውም። ]
📚ቡኻሪ ዘግበውታል።
https://t.me/HadithAmharic | 607 |
| 19 | عن عمرو بن العاص رضي الله عنه أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال:-
[ فصلُ ما بين صيامنا وصيام أهل الكتاب، أَكْلةُ السَّحَر ]
📚رواه مسلم
🌸«::::::::::::::::» «:::::::::::::::»🌸
ከዐምር ቢን አል-ዓስ(አላህ ስራቸውን ይውደድላቸው) እንደተወራው የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–
[ በኛ ፆም እና በመጽሐፍ ባለቤቶች ፆም መካከል ያለው ልዩነት የሱሕር ምግብ ነው።]
📚ሙስሊም ዘግበውታል።
https://t.me/HadithAmharic | 726 |
| 20 | عن عبد الله بن عمرو أن رسول الله - صلى الله عليه وسلم - قال :
[ الصيام والقرآن يشفعان للعبد ، يقول الصيام : أي رب إني منعته الطعام والشهوات بالنهار فشفعني فيه ، ويقول القرآن : منعته النوم بالليل فشفعني فيه ، فيشفعان ]
📚رواه البيهقي في شعب الإيمان
🌸«::::::::::::::::» «:::::::::::::::»🌸
ከዐብደላህ ቢን ዐምር (አላህ ስራቸውን ይውደድላቸው) እንደተወራው የአላህ መልእክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ:–
[ ፆም እና ቁርኣን የቂያማ እለት ለባሪያው አማላጅ ይሆናሉ። ፆም ይላል :- ጌታዬ ሆይ! በቀን ምግብ እና ስሜት ከልክየዋለሁ እና አማልጅነቴን ተቀበለኝ። ቁርአንም ይላል:- በለሊት እንቅልፍ ከልክየዋለሁ እና አማልጅነቴን ተቀበለኝ። አማልጅነታቸው ተቀባይነት ያገኛል።]
📚በይሀቂይ ዘግበውታል(ሹዐቡል-ኢማን)
https://T.me/HadithAmharic | 1 073 |
