ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
Open in Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Show more1 720
Subscribers
-124 hours
-47 days
-1430 days
Posts Archive
Naked as we came,
Naked we will go.
No Nation.
No Race.
No Sex.
No Chains.
Liberty's taste so sweet
As there is nothing to hold back
The true self.
No labels.
No expectations.
Oneself and oneself only.
#DailySay
@storyteller_rh
'ጉራ ብቻ'
(በታመነ መንግስቴ)
ያው የማከብረው ወዳጀ መምህር ሀብታሙ አለማየሁ አንድ ማስፈንጠሪያ(Link) ላከልኝ።Egypt Independant የተሰኘ ገፀ ድር ጉራ ተሸክሟል።"ኢትዮጵያ እና ግብፅ ጦርነት ቢገጥሙ ማን ያሸንፋል?" ዓይነት የሰይጣን ንፅፅር ውስጥ ለመግባት ሲንደረደር የአገሩ ርዕሰ ብሔር አብደል ፈታህ አል ሲሲ የአየር ኃይል መኮነኖቻቸውን "ለየትኛውም የአገር ውስጥ ወይም የድንበር ባሻገር ተልዕኮ ተዘጋጁ"እያሉ ማሟሟቃቸውን ወሽክቷል።
ይቀጥልና የግብፁ ውጭ ጉዳይ ምሉክ ሳሚ ሽኩሪ ስለ እኛው አቻቸው አቶ ገዱ ዓረፍተ ነገሮች"ጠብ አጫሪነትና"እና "አበሳጭነት" መናገራቸውን ፅፏል።ከዚያም ከዓለም ዐቀፉ የጦር መሳሪያ ሃይል ድረገፅ አገኘሁት ያለውን የኢትዮጵያና ግብፅ ንፅፅሮሽ ያስቀምጣል።ለአብነት፦
ሀ.የግብፅ ዓለም ዓቀፍ የጦር አቅም ዘጠነኛ ሲሆን የኢትዮጵያ 60ኛ ተብሏል።
ሁ.የግብፅ ዓመታዊ የጦር ኃይል ገንዘብ ድልድል(በጀት) 11.2 ትዕልፊት(ቢሊዮን) ሆኖ የኢትዮጵያው 350 አዕላፍ(ሚሊዮን) ተገምቷል።
ሂ.የግብፅ ወታደሮች ቁጥር 920ሺ ተገምተው የእኛዎቹ 160ሺ ላይ ተቀምጠዋል።
እንግዲህ ነፃነትን ለ2ሺህ ዓመታት ተነፍጋ በቱርክ፣እንግሊዝ፣ሮማ፣ፋርስ፣እና ኢትዮጵያ ስትገዛ በኖረችውና ነፃነትን በማታውቀው አገረ ግብፅ ያለ የሚመስለው 'Egypt Indepndant' የፃፈውን እንመነውና ወደ እኛ ጉዳዮች እንምጣ፦
'ከነገራችን ጋር' የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ምሉክ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የያዙት መንገድ አይከፋም።ግብፅን እንደማንፈራትና በተለይ በሁለት እጆቿ ልታፍስ መቃጣቷን መቃወማቸው ያስመሰግናቸዋል።_ ሰውየው ደመ ሞቃት ስለመሆናቸው ራሳቸው ለዘመን መፅሔት በሰጡት ቃለ ምልልስ ውስጥ አንብቤያለሁ።
ቢሆንም ከዘመን አይሽሬው የኢትዮጵያ ላዕከ መንግስት(Diplomat) አክሊሉ ሃብተወልድ ጋር የሚነፃፀር ብልጠት ያስፈልጋል።አክሊሉ በማስታወሻቸው እንደፃፉልን ኤርትራን ለማስመለስ ባደረጉት እልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ ረፍት አልባ ሆነው ለህመም ሳይቀር ተዳርገዋል።የዚያኔ ኢትዮጵያን በስም እንኳ በደንብ ከማያውቋት አገራት መሪዎች ጋር በፈጠሩት መልካም ግንኙነት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የኤርትራን ወደ ኢትዮጵያ መቀላቀል ደግፈው እጅ እንዲያወጡልን አድርገዋቸዋል።
ጋሽ አክሊሉ ሃብቴ ዛሬ "የጥቁር እንቁ" የምንለውን የጋምቤላ ምድር ወደ እናት አገሩ የመለሱት በጥበብ ነው።ኦጋዴንን፣የባቡሩን ባለቤትነት፣ ኢትዮጵያን ራሷን ያስረከቡን በከፍተኛ የተግባቦት ብቃት ነው።ከእነ አቶ ገዱ ይሄ እና ከዚህ በላይ ይጠበቃል።
የእኛ ትውልድ ሃውልት የህዳሴ ግድብ ነው።ግብፅ "ጦርነት" የምትለው 'ጉራ ብቻ' ነው።ምክንያቱም ዘመኑ አይፈቅድማ! የምወደው ነገራተሰብ(ጋዜጠኛ) ዮርዳኖስ አበበ እንደሚለው "በዚህ ዘመን በአንድ ጦርነት የሚመጣን ኪሳራ 20 ዓመት አይመልሰውም።" ጦርነቱ ከሆነም እንዲሁ በጉራ ደረጃ እና የአገር ውስጥ ባንዳዎቻችንን በመመልመል ነው።ስለዚህ ለጊዜው በአጥንት መናከሱን ትተን ወደ ጅቡ መጮህ አለብን።
ጅቡ ብዙ ነው።እነ አሜሪካም የእኛን ጉዳይ ለራሳቸው ይፈልጉታል።ያ ታላቅ ሰው-አክሊሉ ሃብቴ እንደፃፉት"ሁሉም ለየራሱ ጥቅም እንጅ በፖለቲካ 'ጀስቲስ'(ፍትሕ) እንደሌለ የታወቀ ነው።"
በዚህም ተባለ በዚያ እኛ መራብ አንፈልግም።ግዮን ኢትዮጵያን "ይከብ" ዘንድ በአምላኩ ታዝዟል።አሁንም ጋሽ አክሊሉ ሃብቴ ኦጋዴንን ሊነጥቋቸው ለቋመጡ እንግሊዞች"ሳንዋጋና ሳንሸነፍ ልትወስዱት አትችሉም!" እንዳሏቸው እኛም "ሳንዋጋና ሳንሸነፍ የዓባይን ግድብ ውሃ ሙሌት ልትከለክሉን አትችሉም!" ብለናል።
"ጉራ ብቻ'' የለቀቀብኝን ገፀ ድር ማስፈንጠሪያ እነሆ፦https://egyptindependent.com/is-an-egypt-ethiopia-war-an-option-a-comparison-between-the-egyptian-and-ethiopian-armies/
. . .
ደሞ እንደ መስቀል ወፍ እንደ አደይ አበባ
ህይወት እንደሚያድስ መስከረም ሲጠባ
እናፍቃታለሁ እንደ ህጻን ልጅ
አትሂድብኝ የትም አትውጣ ከደጅ. . .
. . . እንደ ናርዶስ ሽቶ እንደ ፈዋሽ ጸበል
ማነው ያልተመኛት የኔናት የማይል
የትም ዞራ ውላ ስትመለስ ድንገት
ያጣል መሸሸጊያ አይኔ የሚገባበት
ማን ለምን ይላታል ማን አለ ጠያቂ
የቱ ሽማግሌ የትኛው አዋቂ. . .
ሲያምረኝ - ምትናፈቅ
I woke up this morning and figured I'd call you
In case I'm not here tomorrow
I'm hoping that I can borrow a piece of mind
I'm behind on what's really important
My mind is really distorted
I find nothing but trouble in my life
I'm fortunate you believe in a dream
This orphanage we call a ghetto is quite a routine
And last night was just another distraction
Or a reaction of what we consider madness
I know exactly what happened
You ran outside when you heard my brother cry for help
Held him like a newborn baby and made him feel
Like everything was alright
And a fight he tried to put up, but the type
Of bullet that stuck had went against his will ...
Kendrick Lamar - Sing About Me, I'm Dying of Thirst
Rap is a complex mix of
influences, including
elements of speech , prose,
poetry, and song . Learn to
rap by listening to the
masters, learning rhythms,
and practicing your own
lyrics. There are no
shortcuts, and you won't
sound like Kendrick Lamar
overnight – but if you put in
the hard work, you'll be
rewarded.
https://www.facebook.com/Ethio-Rap-Game-ERG-481719268940791/?ref=page_internal
____ልቤ_____
የሰላምን ፡ ጣዕም ፡ እረሳው: ልቤም ፡ አመፃን ፡ ወደደች፤
የእረፍትን ፡መልክ ፡ ዘነጋው: ነፍሴም ፡ ረብሻን ፡ ፈለገች።
_______❤____________
ህሊናዬ ፡ ግን ፡ ይለኛል : ይህ ፡ መንገድ ፡ ያንቺ ፡ አይደለም፤
አይኔ ደግሞ ፡ ይፈልጋል: ያያል ፡ ግን ፡ ሚታይ ፡ የለም፤
________❤___________
ልቤ ፡ አመፃን ፡ ወደደች ፡ ማን ፡ ይልቃል ፡ ከጉልበቷ፤
ነፍሴም ፡ ረብሻን ፡ ፈለገች ፡ማን ፡ ይልቃል ፡ ከልኬቷ፤
_______❤__________
የሚገስፅ ፡ የሚመልስ ፡ የሚወቅስ ፡የሚያቃና፤
የተቻለው ፡ የሚቻለው ፡ ካንተ ፡ በቀር ፡የለምና፤
የፈሰሰ ፡ የእንባ ፡ ሳቅ ፤
የሚመስል ፡ የሀዘን ፡ስላቅ፤
የቆሰለ ፡ የፈውስ ደም፤
የሚመስል ፡ድኖ የሚያም፤
የተደበቀውን ፡ሚስጥሬን፤
እንድታውቀው ፡መሰበሬን፤
ምነግርበት ፡ ቃል ፡የለኝም፤
ቃል ፡ ባወጣም፡ አታምነኝም።
_____❤__________
ታውቀኝ ፡ እንደው፡ፊቴን ፡ አልፈህ ፡ ተመልከተኝ፤
ታዝን ፡ እንደው ፡ ሳቄን ፡ትተህ ልቤን እየኝ።
_____❤__________
ልቤ፡ አመፃን ፡ ወደደች፤
ነብሴም ፡ ረብሻን ፡ ፈለገች፤
የሚወቅስ ፡ የሚያቃና ፤
ካንተ ፡ በቀር ፡ የለምና፤
ፈገግታዬን ፡ ሳቄን ፡ ትተህ፤
ተመልከታት ፡ ልቤን ፡ መተህ።
________❤____________
እኔ ርብቃ ሲሳይ በሰኔ እሮብ 10 ቀን ፃፍኩኝ😁@beyoubegoodbehappy
Power of Art: Performance and Collaborative Expressions
Art isn't just for aesthetics. They say that it is art together with science that allows a society to move forward by asking stronger questions. This time, we are seeing art in its core as a powerful means of starting dialogue and communication. We hope you enjoy tonight’s conversations. And don’t forget to message us your questions and feedback.
Special thanks to Mulugeta Gebrekidan, Va-bene, and John Herman for making this session possible.
Openly share your individual views and opinions. The session has been recorded and streamed live and due to the depth of the topics, this session will not be suitable for children. Watch the full conversation on Facebook by clicking here: facebook.com/Tibeb2020/videos/1135392696830915/
Copyright/photo credits - pIAR [Perforcraze INTERNATIONAL ARTIST RESIDENCY]
የኤቶዮጵ መጽሐፍ ደራሲ ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አዕምሮ እና ሌሎች አስራስድስት ወጣትና አንጋፋ ደራሲያን በሕብረት ሆነው በጉራማይሌ የአጻጻፍ ስልት በብዕር ቅባት አእምሯችሁን ሊያዋዙ ይኸው ሰብሰብ ብለው " አቦል " በተሰኘ ዳጎስ ባለ ድርሳን መጥተዋል ::
የአብሮነት ውልድ ልጃቸውን " አቦል " ብለው ጠርተውታል፡፡
ያንብቡት ::
ለቴልግራም @jafbok
ለዌብሳይታችን www.jaferbooks.com
መገኛ :- ለገሃር ኖክ ነዳጅ ማደያው አጠገብ ተወልደ ሕንጻ ስር ::
Bibliographic information
Title Together in a Sudden Strangeness: America's Poets Respond to the Pandemic
Editor Alice Quinn
Publisher Knopf Doubleday Publishing Group, 2020
ISBN 0593318714, 9780593318713
Length 208 pages
https://bit.ly/2N8CbVT
ከጥያቄሽ ሁሉ እኔን ደስ የሚለኝ
"ትወደኛለህ ወይ"? ብለሽ ስጠይቂኝ
አዉ እወድሻለሁ አዉ እወድሻለሁ
ጠይቂኝ ግዴለም
አንድ ሺ አመት መሉ
አዎ'ወድሻለሁ ብልሽ አይደከመኝም
:
:
:
ከጥያቄሽ ሁሉ እኔን የሚጨንቀኝ
ቃል የሚቸግረኝ
"እንደምን?" ስትይኝ
እንደምን ልበልሽ
እንደ ፅጌረዳ?
እሱ'ኮ ውበቱ ነው እስኪፈነዳ
እንደምን ልበልሽ እንዳደይ አበባ
ባመት እንደሚታይ መስከረም ሲጠባ
የለም የለም
እንደሱም አይደለም
ከምሽት ጨረቃ ከማለዳ ፀሀይ ትደምቂያለሽ በጣም
ያለም ውዱ ሽቶ የገላሽን ጠረን ፈፅሞ አይወክልም
የምወደው ሁሉ ምን በቃል ቢሞሸር አንቺን አያክልም
እርግጥ ነው የቤተስኪያን ዜማ
ቅዳሴ ስሰማ ልቤ ይሸፍታል
ላንቺ ያለኝ ስሜት ግን ከዚህም ይለያል
እባክሽ የኔ አለም
ሰማይና ምድር እንደሚያልፉ እያወቅሽ
እንደምን አትበይኝ እንደምን ልበልሽ
ምንም ስለሌለ ላንቺ "እንደ" የምለው
አንቺን የምወድሽ አንዳንቺ ብቻ ነው
ዳግም ተካ
#ግጥምሲጥም #ዳግም_ተካ
ምታት ምታት አለኝ፤ እራስ እራሴን
ከፍ ዝቅ አረገኝ፤ አንጀት አንጀቴን
ዞር ዞር እላለው፤ እንደነኩት መሪ
ጎንበስ ጎንበስ እኔው፤ ደርሶ እንደአፋሪ
ቅልሽልሽ ቅልሽልሽ ፤ ቂም እንዳረገዘ
ድንብርብር ድንብርብርብር፤ ሰርቆ እንደተያዘ
መሀል አየት ፤ ጥግ ለየት
ድንገት ፍክት፤ ወድያው ጥፍት
ደሞ ልስልስ፤ ከዚያ ውል'ፍት
አይቶ ክስስ፤ ሰምቶ ምልስ
አውቆ መርሳት፤ ጥሎ ማንሳት
ይህን መንካት ፤ ያን ማንኳኳት
ትቶ መተው፤ ቂሎ ማቄል
ስሎ ማሾል፤ ስቶ ማ'ሴት
እንዲህ እንዲያ፤ እንዲያ እንዲህ
እዚህ እዚያ ፤ እዚያ እዚህ
እኔን ያደርገኛል፤ እኔ አደርገዋለው
ዛሬ ይሆነኛል፤ ዛሬን ሆነዋለው
ነገን ይተወኛል፤ ትላንትን ትቻለው።
ዛሬ
ዛሬ ይሆነኛል፤ ዛሬን ሆነዋለው
ነገን ይተወኛል፤ ትላንትን ትቻለው።
ርብቃ ሲሳይ @Ribki
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊ_ቅዳሜ #ርብቃ_ሲሳይ
Fate isn't exclusively mine,
Like everyone here I gotta wait in line,
Fate doesn't happen to me,
Stumbling along the lines of fear and boldness,
I happen to it,
Fate isn't biased,
"Resigning to my fate" is hoax,
Fate is where you decide to go,
Fate is who you decide to be,
Fate isn't exclusively yours,
One fate wasn't designated for you,
Fate doesn't happen to you,
Along the lines of taking chances,
You happen to it,
"Accepting your fate" is a hoax,
Nothing is given,
With fate, we're always taking,
Not what is predeterminedly ours,
Not what has been written and left to the dust,
With fate, we're always taking,
Taking segments to draw our own line.
@cannotthinkofstgcool
ውስጥ አገር
የተቀደደ አገር ሲጥፉት ቢጋፋ
ድንብርብሩ ድንበር እያደር ባይሰፋ
ባቆመችህ ቦታ እግርህን ደግፋ
ደረትህን ገልብጠህ
ወደልብህ ዙረህ
ጥሩአንባህን ንፋ
ህዋስ ሳለህ ስውር ኗሪ ደቂቅ ፍጡር
ምንነትህ እንኳን ለዓለም ላንተም ምስጢር
ዛፍ አይደለህ አትነቀል
ወይ መልሰህ አትተከል
ከስንቱ ጋር በስንቱ አጀብ
‘ምትታጀብ
ከስንቱ ጋር ለስንቱ አጀብ
‘ምታጅብ
ስንት ለሊት ስንት መዓልት ስንትስ ዘመን
ካለ ትዕይንትህ ‘ምትተውን
‘አገሬ መሬት ነው ወንዝና ተራራ
አገሬ ባህል ነው ምግብና ጭፈራ
አገሬ ሰዉ ነው ኦሮሞና አማራ’
ከማንም ሳትወግን
ማንንም ሳትጠራ ማንንም ሳትፈራ
ይቻልህ እንደሆን ከቆምክባት ቦታ
አገርህን ስራ
ከምትመታው ልብህ አንድ የደም ጠብታ
ከመዋደድ ፀጋም ቆንጥረህ በእርጋታ
ሰላም አፀድ መሃል ውስጥህ አኑራታ
በክብር በሞገስ ሰንደቅህን ተክለህ
ከአይምሮ ባርነት ሰዉን ነፃ አውጥተህ
ከዓለም ሰመመን ሁሉን ቃል አንቅተህ
ባልጠፋ ሸማኔ ባልቸገረ ፈታይ ድሪቶን አትስፋ
ኑር እንጂ አብርተህ
የተቀደደ አገር ሲጥፉት ቢጋፋ
ድንብርብሩ ድንበር እያደር ባይሰፋ
ባቆመችህ ቦታ እግርህን ደግፋ
ደረትህን ገልብጠህ
ወደልብህ ዙረህ
መለከትህን ንፋ
‘ማንነህ?’ ሲልህ ያኔ ሰው ሞኙ ወገኔ
ስም አማኝ ዘመዴ
እኔ ማለት አንተው እራስህ ነኝ ብለህ
ንገረው በዘዴ
ሰይፈ ተማም 2009
ለባይተዋር ክንፎች
(ከቴዎድሮስ ካሳ)
አያልቅም ቅዠቱ ደርዝ አለዉ ሌሊቱ
ለአንድ ባለቅኔ
መኖር ሁለት ነዉ ሁለት ክዋኔ
አንድ
የፀሀይ ነበልባል የፀሀይ ወጋገን
ከተቀመጠበት ደርሳ እንደምትልሰዉ
እንደምትዳስሰዉ
ረዥም ቀሚሷን እንደሚዳስሳት
በነበልባል ቃሉ ቅኔ እያለበሳት ።
፥
ሁለት
ጠልፋ ከምስታስቀር የናፍቆት ኩሬ ላይ
በመዳፏ ጨልፎ
ሁልጊዜ መጠጣት ህመሙን ቢያብሰዉ
ወደ ጥልቁ ባህር ጠልቆ እንደገባ ሰዉ
የፀሀይን ነጠብጣብ አይችልም መጠጣት
ይንጠራራል እንጅ አንድ'ዜ ሊዉጣት ።
ቴዎድሮስ ካሳ
፥
በጥልቀት ወደ ግጥሙ ባህር ያደላል ። በእርሱ ስራዎች ዉስጥ መንፈሳዊ ልዕልናዎች ጎልተዉ ይወጣሉ ። ዉበት ፣ እምነት ፣ እዉነት ፣ ፍቅር እና የፈጣሪ ሁለንታ አፅንኦት ተሰጥቷቸዉ ይዳሰሳሉ ። ግጥሞቹ የማንንም ቤት ባይዳስሱ ይወዳል ፥ ይልቁኑ በራሳቸዉ ቁመት የደረሱበትን አሻግረዉ እንዲያዩ ይለቃቸዋል ።
ተወልዶ ያደገዉ ደሴ ነዉ ። ግጥም ዉስጥ ጠልቆ የገባዉ ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ እያለ ነዉ ። ዩኒቨርሲቲዉ ሳይኾን እድሜየ ነዉ እሳት ዉስጥ የገባዉ ባይ ነዉ ። አዲስአበባ ከመጣ በኃላም በብዙ መዉጣት ባይፈልግም በ ግጥማዊት ቅዳሜ ( poetic Saturday ) @poeticsaturday አንዳንድ ስራዎቹን አቅርቧል ። አሁን ላይ አዲስ የግጥም ቤት ለመስራት እየሰራ ይገኛል ።
ስራዎቹን በፌስቡክ ገፁ ( ቴዎድሮስ ካሳ ) ላይ መከታተል ይቻላል ።
Agar (By Liyou Libsekal)
I remember a yellow scarf fashioned every which way and beautiful bones that peaked at the cheeks.
Mounted proud “young mother” in eyes mourning a daughter left behind
Families don’t speak of shame and hindsight lives in layers.
She was pieces of you strolling tall, slender and curved but you were with me as she cocooned and rolled and stretched. Always in a flowered dress, always drenched in fate
you sit, a lakeside lullaby a picture of youth then, and forever and forever I gnaw on whether you knew near the end
but with age as authority, we lived in darkness why expect more in death?
My anger lives in layers un-abandoned, if only for my sake.
https://www.ethiobeauty.com/article/ethiopian-poet-liyou-libsekal-wins-the-2014-african-poetry-prize
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
