አብርሆት
Open in Telegram
ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23
Show more3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 738
የኢትዮጵያ ቀንን" ስለመዘከር..
"ኩሽ" የሚለውን ወደ ዕርዕ/ግሪክ/ ሲተረጉሙ " ኢትዮጵያ " አሉት አይደለም የተባለው ? በዚህ ጊዜ ነው በፀሃይ መቃጠላችን የነገሩን ፤ መክሰላችንን ያረዱን፣መጥቆራችንን ያበሰሩን፤ የተቃጠለ ፊት ወይም በፀሃይ የጠቆረ ፊት ያላቸው ብለው ተረጎሙታ። ወቸ ጉድ ፡እሺ ባክህ....ከዚህ ጊዜ በፊትስ፡እነ ሆሜር፣እነ ሄሮዱተስ ማን ይሉን ነበር ? " ኢይቶፒያ" ምን ለማለት ? "ታላላቆች፤ መልካቸው ያማረ ፣ ቅኖች፣ በጎ አድራጊዎች፣ ሸበላዎች (ተንኮልና ወሬኛነት በቅርብ ነው የመጣብን ባይዘዌ ☺...እያሉ የዚችን ምድር ነዋሪዎች ሲገልጿቸው እኮ ነው ።
የምድር ሁሉ ቋንቋ አንድ በነበረበት ጊዜ ፣ የቋንቋዎች ሁሉ እናት ቋንቋ፣ ፈጣሪ ከፍጡሮቹ ጋር በተነጋገረበት ቋንቋ "እንቅዮጳዝዮን" ስትባል ቆየችና ቀስ በቀስ " ኢትዮጵግዮን " መባል ጀመረችና በመሀል ቤት ተሰረቀች። ከዚያ በኋላማ ለሌላ ግልጋሎት ሲጠቀሙበት ኖረው ብንፈልግ ፣ብንፈልግ ፣ብንዳስስ አጣነው። በመጨረሻ "ኢትዮጵ" ሆኖ አገኘነው።
አሃ ብለን ስንመረምር ፡ ኢት ምንድነው "ስጦታ " ፡ ዮጵ ደግሞ "ብጫ ወርቅ ወይም እንቁ" ግዮን? "ፈሳሽ ወንዝ" በጥቅል " ኢትዮጵግዮን"...አጠቃላይ ምን ይሆናል ? .."የግዮን ወርቅ ስጦታ"..በድሮው "ኢትኦጵግዮን" ፡ ከዚያ በፊትስ "እንቅዮጳዝዮን"..ባጭሩ በሁሉም ቋንቋ ትርጉሙ ይኸው ነው። ለወደፊት ልጅ ስወልድ ያገራቸውን ስም ስነግር እንዳይበዛባቸው "ኢትዮጵ" ብዬ እነግራቸዋለሁ። ከፍ ሲሉ "ኢትኦጵግዮን" እላቸዋለሁ ። ለአቅመ ማገናዘብ ሲደርሱ "እንቅዮጳዝዮን" ብዬ እነግራቸዋለሁ። ፀሀይ ለፀሀይ ሳይሆን እንዲንከራተቱ ሳይሆን በነፋሻማ አየር ዘና ብለው ወርቅ እንዲፈልጉ ፤....
ሚስጥር የሆነች አገር..አስቡት እስኪ፡ በፈጣሪ እጅ ተፅፎበት ለሙሴ የተሰጠው ፅላት እዚህ ነው። የኢየሱስ ግማደ መስቀል አንድ አካል እዚህ ነው። በአፍሪካ የመጀመሪያው መስጂድ ነው፧ የመጀመሪያው መንፈሳዊ ዜማና ሽብሸባ እዚህ ነው፧ ነብዩ መሀመድ ወገኖቻቸውን የላኩት እዚህ ነው፧ የራሷ የሆነ ፊደል ያላት ፣ የራሷ ብቻ የሆነ ጤፍ የተባለ ምግብ የሚሆን ሰብል የሚበቅልባት፡ እንጀራ በወጥ የሚበላባት ልበል ይ ሆ ን !
....
#ኢትዮጵያ
#ኢትዮጵ# ኢትኦጵግዮን# እንቅዮጳዝዮን
💚💛❤️
3 738
Fear Ethiopians!! They ask you what you do for a living so አየር ላይ calculate ይደረግልሀል what level of respect to give you...
ጠንቀቅ በል አባቴ 😂
we Eth ልዩ ነን ስንል በአመክንዮ ነው
3 738
ድህነት ግን ራስን በማሳነስ በሽታ እንድንሰቃይ አድርጎናል። አሁን ደሀ ነን ማለት ከውድድሩ ውጪ ነን ማለት ግን አይደለም ። ከስልጣኔ በመሸመም ምን ጊዜም አናሸንፍም ...ለመጋፈጥ ፥ደረጃና ሕይወትን ለማሻሻል ግን #እልህ ያጠነከረው ሞራል ያስፈልገናል ። ይህች ዓለም ደሞ ለዚህ ምቹ ናት..
በህይወት ላይ አንዳችም ቋሚ ነገር የለም! በህይወት እንቅስቃሴ ውስጥ ብቸኛው ቋሚ ነገር ለውጥ ብቻ ነው..በዚች አለም የተሸነፈ እንዳሸነፈ ፥ ያሸነፈ ደግሞ ሁሌ ተኮፍሶባት የሚኖርባት አይደለችም። አሁንን፣ዛሬን የሚዘውሯት ባደጉ አገሮች ምድብ የተመደቡት ለረሀብ፥ለእርዛት፥ለስደት ፥ለመከራ የተጋለጡ ነበሩ ፤ በሕብረት ፣ በጥረት ክንድ ግን አስተማማኝ ኢኮኖሚ ገንብተዋል" it will get worse before it gets better" እንዲሉ ። እኛ አፍሪካውያን በግል ችሎታችን የመመፃደቂያው ዘመን አርጅቶ ገርጅፎብናል...ቶሎ ብለን ወደ ጋራ ጨዋታ (Collective game ) መጀመር አለብን ። አንዱ ለሌላው መኖር ሲጀመር የሕይወት ውጤቷም የዘለቄታ ድል ይሆናል ።
በሕብረት ክንድ ለውጥ ማምጣት..ማሳያውም#የኛው_የአባይ_ግድብ ነው..
#Congrats
#ተስፋ
#ኢ ት ዮ ጵ ያ
#ItsMyDam
💚💛❤
3 738
ፋይናንስ አድሚንስትሬሽን
➡️የት ደረጃ ፡ ዲግሪ /ዲፕሎማ
➡️የስራ ልምድ ፡ 1አመት እና ከዛ በላይ
➡️ደሞዝ ፡ በስምምነት
➡️የስራቦታ ፡ አ.አ ገርጂ
➡️ ፆታ : ሴ/ወ
➡️አስቸኳይ
ስልክ
➡️0900004491
➡️011-8-63-40-11
3 738
አብርሆት ፡
"ምክንያት/አመክንዮ እንደ ሸርሙጣ ናት" ይላል ማርቲን ሉተር። ሸርሙጣ አንዴ ከነጩ
ጋር ትተኛለች ፤ ሌላ ግዜም ከጥቁሩ ጋር ወይም ከቢጫው ጋር። አመክንዮም እንዲሁ
ናት― ትለዋወጣለች። በአንድ አጋጣሚ እና አውድ ምክንያታዊ የሆነ በሌላው ላይሆን
ይችላል። ከሚለዋወጠው የሰው ልጅ ንቃተ ህሊና ጋር አብሮ ይጎለምሳል እንጂ ረግቶ
አይቀመጥም።
የተለያዩ ወይም የሚጣረሱ አመለካከቶች በተለያየ ዘመን እኩል ዋጋ ወይም ተቀባይነት
የሚያገኙት ከዚሁ መሰረታዊ የምክንያት ማደሪያ ተቀያያሪነት ወይም ሸርሙጣነት
የተነሳ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ እምነት/faith አይቀያየርም። በዘመናት ርዝመት፣ በቦታ ርቀት
አይወሰንም ፣ አይለወጥም። ይህም እምነት ከነፍስ ፤ ምክንያት ደግሞ ከአእምሮ/ስጋ
ስለሆነ ነው። ከሰው ልጅ ውስጥ የማይለወጠው ነፍሱ ብቻ ነው። በዚህም ነፍስ
"የማትንቀሳቀሰዋ አንቀሳቃሽ" ትባላለች። የማይንቀሳቀስ ነገር ደሞ ፅኑ ነው።
ምክንያት ግን ከአእምሮ ወይም ከስጋ ይነሳል። አእምሮ ደግሞ የሀሳብ ማደሪያ ነው።
ሀሳብ በባህሪው ተለዋዋጭ ነው። አሁን ያሰብነውን ኋላ፣ ዛሬ ያሰብነውን ነገ እርስ
በእርሱ የሚጣረስ ሊሆን ይችላል። ስጋም በማያቋርጥ ተለዋዋጭ ሂደት ውስጥ
ያልፋል።የስጋ መሰረት ሕዋስ ወይም ሴል ነው። ሕዋስ ደግሞ ይወለዳል፣ ያድጋል ፣
ይሞታል። ስለዚህ ከህዋስ/ከስጋ የሆነን ነገር ፍፁም እውነት ብለን መቀበል
አንችልም። ይህ ማለት ታዲያ ምክንያታዊነት አያስፈልግም ማለት ሳይሆን እምነትን
በአመክንዮ ማስረዳት አይቻልም። ወይም ደግሞ ነፍስን በስጋ መነፅር መመርመር
ፈፅሞ አይቻልም ።
ይኼ አሁን ከላይ ያወራሁላችሁ ሁሉ አመክንዮን ተከትዬ የፃፍኩት ስለሆነ እውነት
ላይሆን ይችላል ማለት ነው።
3 738
ፍልስፍና በፈላስፎች እይታ (፩)
📖📜📜📜📖
"ፍልስፍና ምንድነው?" የሚለው ጥያቄ በርካታ ፈላስፋዎችን በልዩነት ያፈላሰፈ ጉዳይ ነው። ይሁን እንጂ ሁሉም ፈላስፋዎች በፍልስፍና ባህሪ ላይ የሰጡት ትርጉም ሰፊ ልዩነት ያለው ነው።
፧
ለምሳሌ ፦
❇️ ለሶቅራጥስ ፍልስፍና የነፍስ ማንነትን ለመኖር ስጋን መግደል ማለት ነው። በሶቅራጥስ ሌላ ትርጉም አለማወቅን ማወቅ ፍልስፍና ነው።
❇️ የፕሌቶ ፍልስፍና ትርጉም ከስሜት ደረጃ የዘለለ የነፍስ እውነታ ለመረዳት የሚያስችል የሁለተኛ ደረጃ ግንዛቤ ነው።
❇️ ለአርስቶትል ፍልስፍና የሁሉም ጥናቶች አባት የሆነ ጥቅል ሳይንስ ነው። በሌላኛው ትርጉሙ አርስቶትል ፍልስፍናን ሲገልፀው የመገረም ወይም የመደነቅ ስሜት የሚፈጥረው የማወቅ ጉጉት ማለት ነው።
❇️ ፍልስፍና ለካርል ማርክስ የለውጥ ሂደት ነው።
፧
በአጠቃላይ በፍስፍና ባህሪ ላይ የተሰጡት ትርጉሞች በስፋትም በልዩነትም ሊታዩ የሚችሉ ቢሆንም በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል ።
አንደኛው የትርጉም አማራጭ ፍልስፍናን በራሱ እውቅት አድርጎ የሚወሰድ ሲሆን፤ ሁለተኛው ትርጉም አማራጭ ፍልስፍናን እውቀት ሳይሆን የእውቀት መንገድ አድርጎ የሚወሰድው ነው።
📜📜📜
📖 የመጀመሪያው የትርጉም አማራጭ በማንኛውም ጉዳይ ላይ በማንኛውም መልኩ የሚፈጠር አስተሳሰብ በራሱ ፍልስፍና አድርጎ የሚወሰድ ነው። ይህ ትርጉም አጠቃላይ የአለማትን እውነት አሳብና ስሜት አዋቅሮ በማንኛውም የአስተሳሰብ ቅርፅ መፍጠርን መሰረት የሚያደርግ ስነ ኑባራያዊ ውክልና (Metaphysical make up) ግንባታ ላይ የሚያተኩር ነው።
፧
ለምሳሌ ፦ መሬት ክብ ናት ወይም መሬት ጠፍጣፋ ናት የሚለው የመሬትን እውነታ በአስተሳሰብ የመወከል ጉዳይ በመሆኑ ይህ በራሱ ፍልስፍና እንደሆነ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።
📜📜📜
📖 በሁለተኛው የትርጉም አማራጭ ፍልስፍና በራሱ አስተሳሰብ ሳይሆን አስተሳሰብ የመፍጠር ሂደት ነው። በዚህ መሰረት መሬት ክብ ናት የሚለው አሳብ በራሱ አስተሳሰብ ሳይሆን የማሰብ ሂደት ነው። በዚህ መልኩ የሚወሰደው የፍልስፍና ትርጉም ፍልስፍና ማለት ማወቅ ሳይሆን የማወቅ ሂደት፣ አስተሳሰብ ሳይሆን የማሰብ ሂደት፣ ጥበብ ሳይሆን የጥበብ መንገድ እና የመሳሰሉትን የመጠየቅና ምላሽ የመፈለግ፣ የመጠራጠር ወዘተ ሂደቶችን የሚያመላክት እንደሆነ ሊወሰድ ይችላል። ...
ይቀጥላል...
ምንጭ ፦ ኢትዮጵያዊው ኦሾ ፌስቡክ ገጽ
እንዲሁም " የፍልስፍና አጽናፍ " መጽሐፍ
@abrhott @abrhott @abrhott
3 738
#ሳይኮሎጂ እንደሚለው
ሴቶች በተሻለ መንገድ ያጭበረብራሉ እንዲሁም ምክንያቶች አላቸው (ወንዶች ዝም ብለው ያደርጉታል እና ሲያዙ ሊያብራሩት አይችሉም)
3 738
"አንዳንድ ነገሮች አሉ አስር ግዜ ተጠይቀው ፤ አስር ግዜ ተመልሰው ፤ አስር ግዜ የሚጠየቁ "
ወንድም ጋሼ:- ሰለሞን ዴሬሳ
@thyselfphilosophy
@thyselfphilosophy
# ተቀላቀሉን
3 738
"አንዳንድ ነገሮች አሉ አስር ግዜ ተጠይቀው ፤ አስር ግዜ ተመልሰው ፤ አስር ግዜ የሚጠየቁ "
ወንድም ጋሼ:- ሰለሞን ዴሬሳ
@thyselfphilosophy
@thyselfphilosophy
# ተቀላቀሉን
3 738
"አንተ ከምታውቀውና ከምታምነው በላይ ሌላ ማንነት አለህና እሱን ፈልገህ አግኝ"
💗
በሰው ልጅ ተፈጥሮ ውስጥ የምናገኘው አንድ አስቸጋሪ ባህርይ ቢኖር ለማንኛውም ድርጊቱ ወይም ጥፋቱ ኃላፊነቱን ወስዶ ወይም ተቀብሎ በሕይወት ለመቀጠል ድፍረት ማጣቱ (መነጠቁ) ነው:: ድርጊቱ ብቻ ሳይሆን በማንነቱም ቢሆን ኃላፊነትና ሸክሙን በአምላኩ፣ በቅዱሳኑ፣ በመምህራኑ ወይም ሌላ በሚያምንበት ነገር ላይ ጥሎ የእነሱን ይቅርታ ወይም ምህረት በመፈለግ ይጠመዳል:: ከዚህም የተነሳ ሕይወቱን የጭንቀትና የመከራ ብሎም የፍርሃት አድርጎ ከመቀበል በዘለለ ሌላ አማራጭ የሌለው ተስፋ ቢስ ፍጡር አስመስሎታል። እነሆ በማንኛውም የሕይወት አቅጣጫችን ዙሪያ ለምንፈፅማቸው ድርጊቶች ይቅርታና ምህረት ከምንለምንበት ፍርሀት ተሻግረን በራስ ፀንቶ ወደመቆም ድፍረት የሚወስደንን መንገድ እንቃኛለን።
በርካታ አሳባውያን የሚስማሙበት አንድ የሰው ልጅ የማንነቱ እውነት ቢኖር የፈፀመውን ማንኛውንም ድርጊት አምኖበትና ፈቅዶ መሆኑን ከመቀበል ይልቅ እንደስህተትና ኃጢአት በመቁጠር በንስሀና ይቅርታ ራሱን ቀፍድዶ በሌሎች ፊት የመቆሙ ጉዳይ ነው:: ይኸ ብቻም አይደለም:: የሰው ልጅ መከራ ምንጩም ሆነ ምክንያቱ ይኸው ስህተት ወይም ኃጢአት በማለት የሚፀፀትበትን ድርጊት በኃላፊነት ከመሽከም ይልቅ ወደሌላው ትከሻ ማሽጋገሩ ነው:: ነገር ግን የአንተን (የሰው ልጅ) ኃጢአትም ሆነ መከራ አልያም ጭንቀት የሚሽከም (የሚወስድ) ሌላ ማንም እንደሌለ ደግሞ ብትረዳ ጭንቀትህን ለማስወገድ የመጀመሪያውን እርምጃ እንደወሰድህ ይቆጠራል:: ከአንተ ከራስህ በቀር አንተን ተክቶ ፃድቅ ወይም ቅዱስ የሚያደርግህ ሊኖር አይችልምና:: ነገር ግን በድርጊትህ ምክንያት ከሚፈጠርብህ የኃጢአተኛነት ጭንቀት ወይም የቅድስና እርካታ ይልቅ ኃላፊነቱን ራስህ ብትወስድና ሕይወትን እንደነበረች በማስቀጠል (ወደኋላ ዞረህ ሳትመለከታት) በጉዞህ ብትቀጥል ያን ጊዜ በእውቀት መንቃት ለመጀመርህ ማረጋገጫ ይሆናል:: ኃጢአትም ሆነ ቅድስና ብለህ የምትጠራውን ነገር አንተ ለብቻህ እንደፈፀምከው ካመንክ ስለምን ምህረትም ሆነ በረከትን ፍለጋ ወደሌላ ትመለከታለህ?
እዚህ ላይ የሰው ልጅ የዘወትር ሃሣቡ፣ ጭንቀቱና ፍርሃቱ በሕይወት ውስጥ በአንዳች አጋጣሚ አምኖበት ከፈፀመው ድርጊቱ የሚመነጭ ለመሆኑ የሚካድ አይደለም:: በመሆኑም ዛሬ የሚያጋጥምህን መከራ ትናንት ተሳስቼ ፈፀምኩት ከምትለው ድርጊት (በአንተ ቋንቋ 'ኃጢያት') የተነሣ እንደመጣብህ እያሰብክና ይኸው ምክንያትህ በሚያተርፍልህም ጭንቀት ሕይወትን አስቀያሚ አድርገህ በመመልከት ልትቀጥል አይገባም:: ኃላፊነትና ነጻነት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው! የሰው ልጅ ለማናቸውም ድርጊቱ ሌሎች ኃላፊነቱን ወስደው የሚቆሙለትና የሚሸከሙለት እንዳሉ በማመኑ ዘወትር የሚከተላቸውን "አዳኞቹን" (saviors) በፀፀት፣ በልመናና በንስሀ ከፊታቸው መቅረቡን ተለማምዶታል። ከዚህም የተነሳ ፈጣሪውን ብቻ ሳይሆን ፈጣሪውን ወክለው በምድር ላይ የተገለጡትን ሁሉ በመከተል የእነሱን ፈቃድና ትዕዛዝ ፈፃሚ ሆኖ በመቅረቡ አንድ ቀን በራሱ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ የፈፀመው ድርጊት "ኃጢአት" ቢኖር እንኳን ከእነሱ ምህረትና ይቅርታ ለማግኘቱ እርግጠኛ እስከሚሆን ድረስ ህይወቱን በጭንቀት መግፋቱ አይቀሬ ይሆናል:: በመሆኑም "የሰው ልጅ ይኸንና ያንን አታድርግ፤ እኔን ተከተል፤ እኔን እመን... እኔም አድንሃለሁ፤ እኔ ጠባቂህ ነኝ ወዘተ በሚለው የተስፋ ትዕዛዝና ቃላቸው የታመነባቸውን እየተከተለ የራሱን ማንነት ግን ለመጣል ተገዷል::
💗
ሀይለጊዮርጊስ ማሞ(ጲላጦስ)
3 738
🌿" የምትናገሩት ከሀሳቦቻችሁ ጋር ሰላም መፍጠር ሲያቅታችሁ ነው ። በልባችሁ ውስጥ ባለው ጭር ያለ ስፍራ መኖር ሳትችሉ ስትቀሩ፣ በከናፍሮቻችሁ ውስጥ ትኖራላችሁ
ንግግርም አቅጣጫን የሚያዛንፍ ጊዜ ማሳለፊያ እና መደሰቻ ነው ...እናም በአብዛኛው ንግግራችሁ(ወሬያችሁ) ውስጥ የማሰብ ችሎታችሁ በከፊል ይሞታል ። ሃሳብስ በህዋ ላይ እንደምትበር ወፍ አይደለምን ?
በፍርግርግ ብረት በተሰራ የቃላት መረብ ውስጥ ከተዘጋባትስ ክንፎቿን ትዘረጋ እንደሆን እንጂ ልትበር ትችላለችን...?
በእናንተ መካከል ለብቻቸው መሆንን በመፍራት ወሬኞችን የሚፈልጉ አሉ ። ምክንያቱም የብቸኝነት ፀጥታ ለአይኖቻቸው እርቃኑን የቀረውን ራሳቸውን አጋልጦ ያሳያቸዋልና ሁሌ ከእሱ ለመሸሽ ይፈልጋሉ...ደግሞም ሳያውቁት ወይም ቀደም ብለው ሳያስቡበት የሚያወሩ እና በዚህ ንግግራቸው ራሳቸው እንኳን የማያውቁትን እውነት ገልጠው የሚያሳዩም አሉ...
በውስጣቸው እውነትን የያዙ ፣ ነገር ግን በቃላት የማይናገሩትም አሉ ። እንደዚህ ባሉት ሰዎች ልብ ውስጥ የእውነት መንፈስ ዜማ በሚደረድር ትርታዊ ፀጥታ ውስጥ ይኖራል...
ጓደኞቻችሁን በመንገድ ዳር ወይም በገበያ ቦታ ስታገኙዋቸው በውስጣችሁ ያለው መንፈስ ፣ ከናፍራችሁን ያንቀሳቅስ ፤ ምላሳችሁንም ይምራ ። የጽምፆቻችሁ ድምፅም ለጆሮዋቸው ጆሮ ይናገር..የወይንን ጣዕም ሁሌ እንደሚያስታውስ ሁሉ ፣ የጓደኞቻችሁ ነፍስ የልባችሁን እውነት ጠብቆ ያቆያል አይደለምን? ቀለሙ(ጣዕሙ) በተረሳ ጊዜ ግን ዕቃውም አይታወስም ። "
ካህሊል ጂብራን -
3 738
ቴዎድሮስ:- ከጥያቄው እና ከመልሱ ለፍልስፍና የቱ ይቀርባል?
ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ:- ጥያቄው። እንደውም ፍልስፍና የጥያቄ ሳይንስ ነው ሊባል ይችላል የተወሰኑ ድባቦችን አድማሶችን የቱንም ጉዳይ የቆምክበትን ሀሳብ ሁሉ እንድትጠይቅ ነው የሚያደርግህ። ሁሉም መልስ እና ውጤት ሊገኝ የቻለው በመጀመሪያ ጥያቄ ማንሳት ስለተቻለ ነው ለዚህም ነው በፍልስፍና ጥያቄው የመልሱን ያህል ዋጋ አለው መባሉ። ፍልስፍና በቃ አለቀ የሚባል መልስ የለውም መልሱንም ይጠይቃል ራሱ የጠየቀውንም የሚጠይቅ ነው። ፍልስፍና የማይወዳቸው አንድ፣ሁለት፣ሶስት ነገሮች አሉ። እንደውም ጠላቶቹ በላቸው።
#ፍልስምና ✍በቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
~~~~~~~~~~
...........ይቀጥላል.........
3 738
#የቀጠለ
ሄዶኒዝም በአሪስቲፐስ ይጀመር እንጂ ያገነነው ኢፒኪዩረስ ነው።
ለኢፒኪዩረስም ብቸኛው ጥሩ ነገር ደስታ ፤ መጥፎ ነገር ደግሞ ስቃይ እና ሀዘን ሲሆን የነገሮችም ጥሩነት እና መጥፎነት መመዘን ያለብን በሚያስገኙልን የደስታ መጠን ላይ ብቻ በመመስረት ነው።
፡
ደስታ ደግሞ አካላዊ እና መንፈሳዊ ፍላጎቶቻችን ሲሟሉ የሚሰማን ስሜት ነው። ነገር ግን ሁሉንም ፍላጎቶቻችንን በፈለግነው ግዜ እና መጠን ማሟላት ስለማንችል ፍላጎቶቻችንን መመርመር እና መቆጣጠር ያስፈልጋል።
፡
ኤፒኩረስ ፍላጎቶቻችንን በሶስት ይከፍላቸዋል
1)ተፈጥሯዊ አስገዳጅ :- ምግብ ልብስ መጠለያ የመሰላሉት
2)ተፈጥሯዊ አስገዳጅ ያልሆኑ :- ወሲብ ጓደኝነት ጥበብ እና ፍልስፍና
3)ተፈጥሯዊም አስገዳጅም ያልሆኑ :- የቅንጦት እቃዎች ፤ ዝና እና ስልጣን ፤ ሀብት
፡
ኢፒኪዩረስ እነዚህ በሶስተኛ ደረጃ ከተቀመጡ ማለቂያ አልባ ፍላጎቶች በመራቅ ውስን በሆኑት ተፈጥሯዊ ፍላጎቶቻችን
ላይ ብቻ ትኩረት እንድናደርግ እና ከአካላዊ / ደመነፍሳዊ ፍላጎቶቻችን እኩል ለአእምሯችን ሰላም እና እርጋታ ትኩረት እንድንሰጥ ያሳስበናል።
፡
በሌላ በኩል እግዜርን መፍራትም ሆነ ገነትን መመኘት ከንቱ ነው የሚለን ኢፒኪዩረስ ለፈጣሪ አለመኖር እንደማሳያ ከሚነሱ መከራከሪያዎች አንዱን በዚህ መልኩ ትቶልን አልፏል
፡
እግዜር መጥፎ ነገርን/ሰይጣንን ማጥፋት ይፈልጋል ግን አይችልም?
ስለዚህ ሁሉን ቻይ አይደለም።
፡
ይችላል ግን አይፈልግም?
እንደዛ ከሆነ ክፉ ነው
፡
ከፈለገም ከቻለም
መጥፎ ነገር እንዴት ሊኖር ቻለ?
፡
ካልፈለገም ካልቻለም
ለምንድነው እግዜር የምንለው/የምናመልከው?
ይቀጥላል
@abrhott
3 738
🌿" የምትናገሩት ከሀሳቦቻችሁ ጋር ሰላም መፍጠር ሲያቅታችሁ ነው ። በልባችሁ ውስጥ ባለው ጭር ያለ ስፍራ መኖር ሳትችሉ ስትቀሩ፣ በከናፍሮቻችሁ ውስጥ ትኖራላችሁ
ንግግርም አቅጣጫን የሚያዛንፍ ጊዜ ማሳለፊያ እና መደሰቻ ነው ...እናም በአብዛኛው ንግግራችሁ(ወሬያችሁ) ውስጥ የማሰብ ችሎታችሁ በከፊል ይሞታል ። ሃሳብስ በህዋ ላይ እንደምትበር ወፍ አይደለምን ?
በፍርግርግ ብረት በተሰራ የቃላት መረብ ውስጥ ከተዘጋባትስ ክንፎቿን ትዘረጋ እንደሆን እንጂ ልትበር ትችላለችን...?
በእናንተ መካከል ለብቻቸው መሆንን በመፍራት ወሬኞችን የሚፈልጉ አሉ ። ምክንያቱም የብቸኝነት ፀጥታ ለአይኖቻቸው እርቃኑን የቀረውን ራሳቸውን አጋልጦ ያሳያቸዋልና ሁሌ ከእሱ ለመሸሽ ይፈልጋሉ...ደግሞም ሳያውቁት ወይም ቀደም ብለው ሳያስቡበት የሚያወሩ እና በዚህ ንግግራቸው ራሳቸው እንኳን የማያውቁትን እውነት ገልጠው የሚያሳዩም አሉ...
በውስጣቸው እውነትን የያዙ ፣ ነገር ግን በቃላት የማይናገሩትም አሉ ። እንደዚህ ባሉት ሰዎች ልብ ውስጥ የእውነት መንፈስ ዜማ በሚደረድር ትርታዊ ፀጥታ ውስጥ ይኖራል...
ጓደኞቻችሁን በመንገድ ዳር ወይም በገበያ ቦታ ስታገኙዋቸው በውስጣችሁ ያለው መንፈስ ፣ ከናፍራችሁን ያንቀሳቅስ ፤ ምላሳችሁንም ይምራ ። የጽምፆቻችሁ ድምፅም ለጆሮዋቸው ጆሮ ይናገር..የወይንን ጣዕም ሁሌ እንደሚያስታውስ ሁሉ ፣ የጓደኞቻችሁ ነፍስ የልባችሁን እውነት ጠብቆ ያቆያል አይደለምን? ቀለሙ(ጣዕሙ) በተረሳ ጊዜ ግን ዕቃውም አይታወስም ። "
ካህሊል ጂብራን -
3 738
የጥንታዊው ግሪክ ፍልስፍና informative ሳይሆን formative ነበር። ማን ፈጠረን ይሄንንስ እንዴት ማወቅ እንችላለን ምናምን ከሚል መላምታዊ ፍልስፍና(speculative philosophy) በላይ እንዴት መኖር አለብን ለሚለው ኢቲካል እና ተግባራዊ ጥያቄ ቅድሚያ ይሰጣልና። ለዚህም ይመስላል እንደሄዶኒዝም ስቶይሲዝም እና ሲኒሲዝም የመሳሰሉ ምግባር ላይ ያተኮሩ ፍልስፍናዎች 2000 አመታትን ተሻግረው ሳይንስ ሊመልሰው ያልቻለውን የሞራል ጥያቄ ለመመለስ እኛ ጋር የደረሱት።
፡
ሄዶኒዝም
፡
የሰው ልጆች ሁሉ ሩጫ የመጨረሻ ግቡ ምንድን ነው?ገንዘብ/እውቀት/ስልጣን የምንሰበስበው ፤ ሚስት አግብተን ልጆች የምንወልደው ፤ ቤተክርስቲያን ሄደን ገንዘብ የምንመፀውተው ባጠቃላይ ሁሉንም ነገር የምናደርገው ደስታን እና እርካታን ፍለጋ ነው አደል?
፡
በራሱ ጥሩ የሆነ ብቸኛ ነገር ደስታ ነው ፤ሌላው ሁሉ ወደ ደስታ የሚወስደን መንገድ ነው ይላሉ ሄዶኒስቶች።
፡
ግን ምን አይነት ደስታ?
፡
የሄዶኒዝም ፍልስፍና መስራች አሪስቲፐስ ይህን ሃሳብ የወሰደው ከሶቅራጥስ ሲሆን ለሶቅራጥስ የህይወት ግብ ደስታ ነው። ነገር ግን እንደሶቅራጥስ አስተምህሮ ደስታ የምናገኘው ምክንያታዊ የሆነውን አዕምሮዋችንን ተጠቅመን እውነትን / ጥበብን በመፈለግና በማሰላሰል ሲሆን ለአሪስቲፐስ ግን እውነተኛ ደስታ የምናገኘው አካላዊ ፍላጎቶቻችንን በማርካት ብቻ ነው። እርቦህ የሚጣፍጥ ምግብ ስትበላ ፤ አሪፍ ወይን ስትጠጣ ፤ የምትወዳትን ልጅ እቅፍፍፍፍፍፍፍ ስታደርግ(ያቺ ሞመንት)ይሄ ብቻ ነው እውነተኛ (ልንክደው የማንችለው) ደስታ ሌላው አጉል መራቀቅ ነው።
፡
"አሁንን አጣጥማት ፣ ዛሬን ተደስተህ ኑርባት ፤ ምናልባትም ነገ ላይኖር ይችላል።"
ይቀጥላል
@abrhott
3 738
የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የት ደርሷል ?
By : EPA
- የኮርቻ ግዱቡ 99 በመቶ ደርሷል፤
- የጎርፍ ማስተንፈሻው ወይም ጎርፍ መከላከያ 97 በመቶ፤
- የኃይል ማመንጫዎች ግንባታ 84 በመቶ ተጠናቋል፤
- አጠቃላይ የሲቪል ስራው ዛሬ ላይ 91.4 በመቶ ተጠናቋል፤
- የኤሌክትሮ ሜካኒካልና የብረታ ብረት ስራዎች 54 በመቶ ተሰርቷል
- አጠቃላይ የህዳሴው ግድብ ግንባታው 79 በመቶ ደርሷል፤
ለግድቡ ከ2003 ዓ.ም እስከ መጋቢት/2013 የተሰበሰበ ገንዘብ መጠን ምን ያህል ነው ?
- ከሀገር ውስጥ ቦንድ ግዢና ልገሳ...13,762,030,021.64
- የዲያስፖራ ቦንድና ልገሳ...1,068,349,251.54
ልዩ ልዩ ገቢዎች… 333,454,551.80
- ጠቅላላ ድምር ... 15,163,833,824.98
ከሀምሌ 2012- መጋቢት 2013 የተሰበሰበ ገንዘብ ፦
- የአገር ውስጥ ቦንድ ሽያጭና ስጦታ ….1,322,448,847.53
- የውጭ አገር ዲያስፖራ ቦንድ ሽያጭና ስጦታ… 61,553,943.51
- በኢ/ኤ/ኃይል የስጦታ አካውንት ገቢ የሆነ /GERD LOCAL Grant… 10,750,690.98
- ከፒን ሽያጭ ገቢ የሆነ/… 392,750.00
- ከ8100 አጫጭር የሞባይል መልእክት አገልግሎት...88,764,422.00
- ጠቅላላ ድምር፡- 1,483,910,654.02
Video : Ethiopian Electric Power (Jul 28/2020)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
3 738
#ዓድዋ_የምኒልክ_እጅ_ሥራ !!!
በIsho Bir
…ምኒልክን ልትጠላው ትችላለህ፤ ደግሞም ልትወደው ትችላለህ። ነገር ግን ምኒልክ ተራ ስብዕና እንዳልነበረ ለመረዳት አይከብድም።
… ምኒልክ ውስብስብ ሰው ነው። ረቂቅ ነው። ደግሞ አድማጭ ነው።
… ምኒልክ እንደ ገሞራ እሳት የሚፋጅ ነው። ደግሞ እንደ ምንጭ ውኃ ገር ነው። ሚኒልክ ሀገር መመስረት፣ ግዛት ማስተዳደር ያውቃል። ተራ የታሪክ ሰው አይደለም። ጉልህ ነው።
… የምኒልክን ነገር ለማጉላት ብዬ ከሌሎች ማወዳደር አልፈልግም። ዳግሞም ማሳነስ ሊሆን ይችላል።
… ውጫሌ ውል የዓድዋ ጦርነት መነሻ ነው ይላሉ። ፈፅሞ ስህተት ነው። የዓድዋ ጦርነት መነሻ የበርሊኑ የቅኝ ገዢዎች ውል ነው።
… አውሮጳ አፍሪካን ለመቀራመት የተስማማው በበርሊን ስምምነት ነው። ያን ለማስፈፀም አውሮጳውያን በውድም፣ በውልም፣ በግድም አድርገውታል። በውል ወደ ቅኝ ግዛት የገቡ ብዙ ናቸው።
… ጣሊያን ለምኒልክ የውጫሌን ውል ስታቀርብለት፣ ምኒልክ ሳይገባው ቀርቶ፣ ተሸውዶ፣ ወይ ገር ሆኖ ነው ማለት ደካማ የታሪክ ተማሪ ከመሆን የሚመጣ ነው።
…የውጫሌ ውል የተፈረመው አፄ ዮሐንስ በሞቱ በ 10 ቀናት ውስጥ ነው። የዓድዋ ጦርነት የተካሄደው ደግሞ አፄ ዮሐንስ ከሞቱ ከ 7 ዓመት በኋላ ነው።
… ምኒልክ የውጫሌን ውል በመፈረም የራሱን ጉልበት እስኪያጠናክር ግዜ መግዣ ነው ያደረገው። ሚኒልክ ከፍ ለማለት ዝቅ ማለትን ያውቃል።
… እንደ ጣይቱ የሚፋጅ እሳት፣ እንደ ልብ ወዳጁ ራስ መኮንን የረጋ ውኃ ብቻ ቢሆን፣ ሀገርም አይሠራም፣ መንግሥቱንም አያፀናም ነበር።
… ውጫሌ በተፈረመበት ወቅት ምኒልክ፣ ብዙ ጠላቶች ነበሩት። ተጨማሪ ጠላት ጣሊያንን ማድረግ ስላልወደደ የፈረመው ነው።
… የውጫሌ ውል ኖረ አልኖረ ጣሊያን እንደሁ ኢትዮጵያን መውረሯ እንደማይቀር የሚታወቀውማ፣ የትግራይና የኤርትራን መኳንንት ጥሩ አድርጋ ስትክድ በማየት ነው። ምኒልክ ግን ጦርነቱን ቢያንስ እሱ በመረጠው ግዜ እንዲሆን ማድረግ ችሏል።
… ሚኒልክ ሁሉን ያዳምጣል። በቅንም ይረዳል። ዓላማውን አይስትም። ብልሃተኛም ነው።
… የአምባላጄ ጦርነት፣ የመቀሌ ከበባን በአሸናፊነት ሲያልፍ፣ በምኒልክ ውሳኔ የሚቆጡ ብዙ ነበሩ። ጣሊያኖችን ቢማርክም መልሶ እንደውም ከመጋዣ (ፈረስና በቅሎ ) ጋር ላካቸው እያሉ የሚወቅሱት ነበሩ። ምኒልክ ግን ጦርነት የሚገጥምበትን ቦታ እየመረጠ ነበር። የሱ መኳንንት የሚያውቁትን ምኒልክ ጠፍቶት አይደለም። ከባድ ስትራቴጂስት ስለነበረ ነው።
… ምኒልክ ያሰለፈውን ኃይል ያውቀዋል። ከቴድሮስ እስከ ራስ ውቤ፣ ወርቂትና ተዋበች፣ እስከ ዮሐንስና ጎበና የነበሩ ጦርነቶችን፣ በአይኑ ያየና የሰለጠ ንጉሥ እና ብልህ ጦርነት አዋቂ ነው።
… የቻይናው ታዋቂ የጦር ጀነራል - ሱን ሱ " ኃይል እንዳለህ ስታዉቅ፣ ደካማ ምሰል" ያለውን ምኒልክ ፈፅሞታል።
… ጣሊያን ዓድዋ ላይ የዘላለም ውርደት እስክትከናነብ በዚህ የሚኒልክ ብልጠት ተሸውዳለች። ምኒልክም ዓድዋ እስኪደርስ ድረስ የሚፋጅ ነብር መሆኑን ደብቆ ቆይቷል።
… አምስት ወር የተደረገ ጉዞ፣ የስምንት ሰዓት አጭር ጦርነት የሆነው፣ በዚህች አስደናቂ የምኒልክ ብልሃት ነው።
… ምኒልክ ያደረጋቸው ነገሮች፣ የፈፀማቸው ታሪኮች፣ የሰበሰባቸው ሸንጎዎች፣ የወሰናቸው ውሳኔዎች በእርግጠኝነት የምኒልክን ልህቀት የሚያገኑ ናቸው።
… ዓድዋ - በምኒልክ ተመርጦ፣ በምኒልክ ታቅዶ፣ በምኒልክ ተመርቶ፣ የተፈፀመ ጀብዱ ነው።
… ለዚያም ነው ምኒልክ የሀገር መሪ ብቻ ሳይሆን ሀገር መሥራች ነው የሚባለው።
… ከዚህ መለስ ስላለው የታሪክ ፋይዳ፣ ውጤት፣ ጥቅምና ጉዳት እንነጋገር እንጂ ሁነቱ ዳግም ላይመለስ፣ በምኒልክ ተፈፅሟል ።
***
ይገርምሃል ሸዋ !!!
💚💛❤️
#ዓድዋ_125
#የኢትዮጵያውያን_ድል
#የጥቁር_ህዝብ_ኩራት
#ኢትዮጵያ
