አብርሆት
Open in Telegram
ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @bellalsina @ThomB23
Show more3 738
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 738
ቶምዬ ይሄን ሰውዬ አየኸው : ታቀዋለህ? ብላ ጠየቀችኝ ወ/ሮ ወርቅነሽ (ና ቁጭ ብለህ ስማው በሚል ትዛዝ በሚመስል ቃና
እኔም ቀጠል አረኩና እንዴ ኤርሚ፣ኤርሚን እንዴት ታቀዋለህ ትይኛለሽ አልኳት...
ተግባሩን ሰምተህ ካልተገበርክ ማወቅ ብቻውን ምን ሊፈይድ 'አለችኝ
ግዴታ እንደሱ ሀብታም መሆን አለብኝ ‘ ብዬ ጠየኩ
አይይ እኔስ እሱን አልነበረም የፈለኩት ደሞ ሀብታም ብትሆንስ ምናለ : ማን ይጋደምልህ እንጂ
አንድ ቀን አይቀርም : ጠብቂ ‘ አልኳት ጢሜን ላመል እየነካካሁ
በቀን አንዴ ነው የምበላው ‘ እያለ ነው ስማው እስኪ አለችኝ...
ሂድ እንግዲህ አለ ሰውዬው : ሲሰክስ ነው ባክሽ
እና ደሞ ከኔ ህይወት ጋ ምን ያገናኘዋል ‘አልኳት
ነገሩን እንዳልሰማ ሆና ' ትላንት ዘይት ስንት ነበር ገዝተህ የመጣኸው
950"አልኩ
እና በቀን 3ቴ ሆድህን መቀብተት ያዋጣል’ አለችኝ
አንድ ቀን እንኳ ግዛ ብላኝ የማታቅ : ትላንት ግዛና ና ማለቷ ነገሩን ልታለማምደኝ እንደሆነ ሳስብ ገረመኝ...እና አሁን እራት የለም? አልኳት።
እንደ ኤርሚ ጀምረናል : ዳይ ወደ እንቅልፍ
እረ እማዬ እርቦኛል አቀልጂ..
ጥላኝ ስትነሳ አየኋት..አመርራለች ማለት ነው...
አንተ መላጣ ሰውዬ እግዜር ይልህ...አንተ ዥል መንግስት ደሞ በርትተህ ደግስ...
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው የተሾሙት የአቶ መስፍን ጣሰው አያት ስም ግን ማን ሆነ?🤭
3 738
በዚህ በኛ ዘመን የሰው ልጅ ዋጋ ክቡር መሆኑ በተለይ በአፍሪካ ምድር እምብዛም አይታወቅም ። ከሰሞኑ ከወደ አፍሪካ ምናልባትም ብቸኛዋ በሚያስብል ሁኔታ ለአንድ ህፃን ህይወቱን ለማትረፍ ከወደ ሞሮኮ የሰማነው ነገር አጃኢብ ያስብላል። ዜናውንም የኛ አገር ባለስልጣኖችን፣ሚዲያዎች ጭምር በሰፊው ሲያራግቡት በሰማን ጊዜ ወቸ ጉድ ለአንድ ሰው እንዲህ ማሽቃበጥ አሁን ምን ይሉታል ብለን ተሳለቅነ። ምን እናርግ በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ ለምንኖረው (እለት ከእለት ሰው በሚጨፈጨፍባት ምድር ባላዩ በልሰሙ በሚታለፍባት አገር እንዲህ ያለ ዜና መስማት፣የሰውን ክብርን ከረሳን ለሰነባበትነው ህዝቦች ብዙም ባያስጨንቀው አይገርምም...። )
የአንድ ሰው ዋጋ ምን ያህል ክብር እና ዋጋ እንዳለው የሞሮኮ ሕዝብና መንግስት ለአለም ህዝብ በላይቭ አሳይተውናል። 4ቀን ሙሉ በተደረገ ታላቅ መረባረብ ከገባበት ጉድጓድ መውጣት ቢችልም ህይወቱ ግን መትረፍ አልቻለም።
እኛጋስ ?የኛ ህዝብ እና መንግስትስ?
እዚህ እኛጋ ደሞ በዘር እና በማንነታቸው ላይቭ ሪከርድ እየተደረገ እየታረዱ፣ከማህፀን ተተልትለው ራሱ የሰው ልጅ የሰው ልጅ እስካይመስል ድረስ እንደ አውሬ እየተበሉ፣በጅምላ እየተቀበሩ ባልሰማ ባላየ ያለፈ ህዝብ እና መንግስት አሁን እንዲህ ስለ ሰው ሀገር ሰው ሲውለበለብ ስሰማ ለምንድነው ብለህ ትጠይቃለህ?የኛ አገር ሰው ነፍስ ለምን ይሆን የሚያስጨቀን? ሀዘንን ከሃዘን ማወዳደሩ መልካም ባይሆንም እኛ አገር በሰፊው ዜና የሚሰራልህ ወይ ችግኝ ስተክል ነው ወይ ደሞ መናፈሻ ስታስመርቅ ነው።እረ እየ ሞትኩ ነው ድረሱልኝ ብትል ግን፥ለምን ድፍት አትልም ከሞትክም እንደቆሻሻ በአንድ ጉድጓድ እንቀብርሃለን አትረብሸን ይሉሃል...
ስለ መናፈሻ እድሳት፤ ስለ ችግኝ ማጠጣት እለት እለት የሚነግሩን እለት ከእለት የሚሞተውን ሰው እንደምን ብንንቀው፣ቢንቁት እንደምን ቢረክስባቸው ይሆን?
እረኛው በጎቹን ለተኩላው አሳልፎ ሰቷቸዋልና በጎችህን እግዜር ሆይ ጠብቃቸው...።
3 738
#SafaricomEthiopia : አለም አቀፍ የቴሎኮም አገልግሎት አቅራቢ የሆነው ኩባኒያችን ሳፋሪኮም ለኢትዮጲያዊያን የቴሌኮም አገልግሎቶችን በዝቅተኛ ዋጋ ለማቅረብ በስራላይ ይገኛል በዚህ ቴሌግራም ቻናላችን የጀመርነው የሽልማት መርሃግብርም እንደቀጠለ ነው በዚህ ሳምን ባጋራው ሊንክ 1500 ሰዎች ወደ ቻናሉ እንዲቀላቀሉ ያደረገው የሬድ ትእግስቱ ከሀዋሳ የ45 ሺህ ብር እጅግ በጣም ዘመናዊ አይፎን 13 ፕሮማክስ ስልክ ተሸላሚ ሆኗል :: እርሶም ይህን ፁሁፍ ለሰላሳ ጓደኞቾ ያጋሩ ይሸለሙ እንዲሁም ብዙሰዎች ከጋበዙ የ80 ሺህ ብር እጅግ ዘመናዊ አፕል ላፕቶፕ ይሸለማሉ :: ፁሁፉን በጉሩፖችና በቡድኖች ካገሩ የመሸለም እድሎ በእጥፍ ይጀምራል :: እንድንተዋወቅ አዲስ ኔትወርክ እየገነባን ነው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ : በዚህ ሊንክ https://t.me/+M6DMoKl8mvVmYWY0 ጆይን ያድርጉ ፁሁፉን ያጋሩ ይሸለሙ ::
3 738
ይሄ አዲሱ የፖሊሶች ዩኒፎርም ግን......."ና" ሲለኝ የባንክ ዘበኛ መስሎኝ አንተ እራስህ ና ብዬው ምኔን እንደነካኝ እንጃ ዲስኬን አንሸራተተው😔😔😔
3 738
የአዳነች አቢየቢየ ንግግር አሁን አ እንዴ የገባኝ ጎበዝ... ጠቅላያችንን ‘’ሲደናበር ነው አሸዋ የገባበት : ከፈለጋችሁ ማስረጃ አለኝ በሀውልት መልክ አሰርቼ ከትውልድ ትውልድ አስተላልፈዋለሁ’’ ማለቷ ነው ለካ። በኮማንድ ፖስት ትተየቅልን....☹️😅
3 738
..... የአፍሪካ መሪዎች አብዛኞቹ ማለት ይቻላል ሀገራቸውን ቤተ ሙከራ ያደርጉታል። ባለስልጣንን ባሻቸው ጊዜ ሲቀይሩ፣ሲሾሙ ጊዚያቸውን ይፈጃሉ። ትንሽ ደሞ ለቢሮክራሲያቸው አልመች ያለውን : በእውቀትም ሆነ በህዝብ ቅብሉነት ከነሱ ሻል ያለውን ባለስልጣንንማ ወይ ሸቤ ወይ ደሞ 40ክንድ አርቀዎ ይወረውሩታል። አዲስ የፖለቲካ ሃሳብ ነው፥ ይህ የፖለቲካ ሃሳብ ለአገሪቱ ወሳኝ ነው፥ ከዚህ ሃሳብ ውጪ ወደ ውጪ የሚል በሚመስል ዲስኩር ቋቅ እስኪልህ ድረስ ሆድህን ይነፉቷል...
ምናልባት የፖለቲካውን ሃሳብ አልተቀበልኩትም : ልክ አይመስለኝም : ለአገራችንም አይጠቅምም ያለውን ባለስልጣንም ሆነ activist በስማም ወወልድ በዚህ በዛ : በዚህ በዛ ብለው ወይ እስር ቤት ወይ ሞት ወይ ደሞ በሆነ በሆነ ነገር አርገው ከጨዋታው ሜዳ ውጪ አርገውህ ራስህን ታገኘዋለህ.... እና ምን ልልህ ነው ጌታው አሁን ከላይ ያልኩህ ሁሉ የአፍሪካ መሪዎች በትንሹ መገለጫቸው ነው። የሆነ እንደሆነስ... እናማ ከሰሞኑ እንዴት የአገር ትላልቅ የጦር መሪዎች ገና ጦርነቱ ይለቅ አይለቅ ሳይታወቅ ያለ ሙያቸው እንዴት ዲፕሎማት ይሆናሉ ብሎ የሚጠየቅ አለ አሉ...ወንድሜ ያለህበት ምድር Africa መሆኑን ረሳኸው መሰለኝ.. . በአፍሪካ ምድር በሙያው ሞገስ እና ክብር ባገኘበት ሲሰራ ያየኽው አለ ወይ? በትምርት አለም ለአቅመ Diploma እንኳ ያልደረሰውን Diplomat ሲደረግ እንጂ...(this is Africa ብሮ እሺ Dr ስለሺንስ ግን ለምን Diplomat አረጉት" እያልክ ደሞ አትጃጃል...ስለሺም ቢሆን አገልገግሎቱን ጨርሷል። ምርጫውን እነደሆነ አሸንፎላቸዋል..ህእ..ምን ሊሰራላቸው አገር ያስቀምጡት ብለህ...ይልቅ ሳልረሳው Birbirssa Gooroo ማለቴ ፒያሳ ላይ ያየኋት ልጅ...😅
.
በነገራችን ላይ ይህ ፖስት ከእኔ እውቅና ውጪ የተፖሰተ መሆኑን ልብይለዋል። ☹️
3 738
..... የአፍሪካ መሪዎች አብዛኞቹ ማለት ይቻላል ሀገራቸውን ቤተ ሙከራ ያደርጉታል። ባለስልጣንን ባሻቸው ጊዜ ሲቀይሩ፣ሲሾሙ ጊዚያቸውን ይፈጃሉ። ትንሽ ደሞ ለቢሮክራሲያቸው አልመች ያለውን : በእውቀትም ሆነ በህዝብ ቅብሉነት ከነሱ ሻል ያለውን ባለስልጣንንማ ወይ ሸቤ ወይ ደሞ 40ክንድ አርቀዎ ይወረውሩታል። አዲስ የፖለቲካ ሃሳብ ነው፥ ይህ የፖለቲካ ሃሳብ ለአገሪቱ ወሳኝ ነው፥ ከዚህ ሃሳብ ውጪ ወደ ውጪ የሚል በሚመስል ዲስኩር ቋቅ እስኪልህ ድረስ ሆድህን ይነፉቷል...
ምናልባት የፖለቲካውን ሃሳብ አልተቀበልኩትም : ልክ አይመስለኝም : ለአገራችንም አይጠቅምም ያለውን ባለስልጣንም ሆነ activist በስማም ወወልድ በዚህ በዛ : በዚህ በዛ ብለው ወይ እስር ቤት ወይ ሞት ወይ ደሞ በሆነ በሆነ ነገር አርገው ከጨዋታው ሜዳ ውጪ አርገውህ ራስህን ታገኘዋለህ.... እና ምን ልልህ ነው ጌታው አሁን ከላይ ያልኩህ ሁሉ የአፍሪካ መሪዎች በትንሹ መገለጫቸው ነው። የሆነ እንደሆነስ... እናማ ከሰሞኑ እንዴት የአገር ትላልቅ የጦር መሪዎች ገና ጦርነቱ ይለቅ አይለቅ ሳይታወቅ ያለ ሙያቸው እንዴት ዲፕሎማት ይሆናሉ ብሎ የሚጠየቅ አለ አሉ...ወንድሜ ያለህበት ምድር Africa መሆኑን ረሳኸው መሰለኝ.. . በአፍሪካ ምድር በሙያው ሞገስ እና ክብር ባገኘበት ሲሰራ ያየኽው አለ ወይ? በትምርት አለም ለአቅመ Diploma እንኳ ያልደረሰውን Diplomat ሲደረግ እንጂ...(this is Africa ብሮ እሺ Dr ስለሺንስ ግን ለምን Diplomat አረጉት" እያልክ ደሞ አትጃጃል...ስለሺም ቢሆን አገልገግሎቱን ጨርሷል። ምርጫውን እነደሆነ አሸንፎላቸዋል..ህእ..ምን ሊሰራላቸው አገር ያስቀምጡት ብለህ...ይልቅ ሳልረሳው Birbirssa Gooroo ማለቴ ፒያሳ ላይ ያየኋት ልጅ...😅
.
በነገራችን ላይ ይህ ፖስት ከእኔ እውቅና ውጪ የተፖሰተ መሆኑን ልብይለዋል። ☹️
3 738
someone ask me about my relationship…
And My relationship is like my car.
I don't have a car🙍🏽♂️😅
3 738
The best time to argue 🗣 with a woman is when she's applying make up 💄, you will not hear a single word 😂
3 738
ከሃበሻ People በጣም ከሚያስገርሙኝ ነገሮች...
፩ : እረ ማን የሌለ አምሮብሻል ስትለው "እረ ባክሽ ምን ያምርብኛል አታየኝም እንዲህ ገርጥቼ...ይልሃል። ምናለበት አመሰግናለሁን ብንለምድ
፪ : እረ ማን ልብስህ ያምራል በጣም፥ የት ነው የገዛሻት ስትለው ‘ ህ ስንት እንዳወጣሁበት አታቅም:የሚገርምህ ልብሱ ብቻውን ነው በመርከብ ተጭኖ የመጣው’..ብሎ ሆድህን በጉራ ይነፋሃል።...ምናለ እውነት ብናወራ፣እና ደሞ ያምራል ብቻ ብለን ዝም ብንልስ ከየት ይግዛው ስንት ይግዛው ምናገባን😑
፫ : የሆነች ቺክ ጋር ስቴድ ድንገት ከታየህ(ምናልባት ቦታ ጠፍቶባት እያሳየሃት ይሆናል:ከዛ በነጋታው አንዱ ጀለስህ ይመጣና.."እረ ከባድ ሰው ከባድ ሰው " ይልና ሞቅ ያለ ሰላምታ ከሰጠህ በኋላ: ውስጥ ውስጡን ነው ኣ የምታጫውቺው፣አንተ ሚስጥረኛ የሆንክ ልጅ የማትያዝ መስሎህ ነው ኣ ምናምን ይልሃል
፬ : ምንድን ነው የምሰራው ይሉሃል : ከዛ አየር ላይ ምን አይነት level of respect እንደሚገባህ Calculate ይደረግልሃል...
፭ :መብራት ድንገት ሲጠፋብን...ከቆጣሪ መልሶ ሊሆን ይችላል እ አምፖል ተቃጥሎ ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰብ የለ ወዲያውኑ ውጪ ወተው የጎረቤት መብራት መጥፋት እና አለመጥፋቱን ቼክ ያደርጋሉ...(ቆይ አሁን ይሄ ምን አይነት ምቀኝነት ነው ግን በዋቃ
3 738
ከሃበሻ People በጣም ከሚያስገርሙኝ ነገሮች...
፩ : እረ ማን የሌለ አምሮብሻል ስትለው "እረ ባክሽ ምን ያምርብኛል አታየኝም እንዲህ ገርጥቼ...ይልሃል። ምናለበት አመሰግናለሁን ብንለምድ
፪ : እረ ማን ልብስህ ያምራል በጣም፥ የት ነው የገዛሻት ስትለው ‘ ህ ስንት እንዳወጣሁበት አታቅም:የሚገርምህ ልብሱ ብቻውን ነው በመርከብ ተጭኖ የመጣው’..ብሎ ሆድህን በጉራ ይነፋሃል።...ምናለ እውነት ብናወራ፣እና ደሞ ያምራል ብቻ ብለን ዝም ብንልስ ከየት ይግዛው ስንት ይግዛው ምናገባን😑
፫ : የሆነች ቺክ ጋር ስቴድ ድንገት ከታየህ(ምናልባት ቦታ ጠፍቶባት እያሳየሃት ይሆናል:ከዛ በነጋታው አንዱ ጀለስህ ይመጣና.."እረ ከባድ ሰው ከባድ ሰው " ይልና ሞቅ ያለ ሰላምታ ከሰጠህ በኋላ: ውስጥ ውስጡን ነው ኣ የምታጫውቺው፣አንተ ሚስጥረኛ የሆንክ ልጅ የማትያዝ መስሎህ ነው ኣ ምናምን ይልሃል
፬ : ምንድን ነው የምሰራው ይሉሃል : ከዛ አየር ላይ ምን አይነት level of respect እንደሚገባህ Calculate ይደረግልሃል...
፭ :መብራት ድንገት ሲጠፋብን...ከቆጣሪ መልሶ ሊሆን ይችላል እ አምፖል ተቃጥሎ ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰብ የለ ወዲያውኑ ውጪ ወተው የጎረቤት መብራት መጥፋት እና አለመጥፋቱን ቼክ ያደርጋሉ...(ቆይ አሁን ይሄ ምን አይነት ምቀኝነት ነው ግን በዋቃ
3 738
Sign up for Coinbase using my link and we can each get ETB 494.13 in Bitcoin https://www.coinbase.com/join/EBJTE2?src=ios-link
3 738
🌼መስቀል በዐል ስጦታ ከ ዳሽን ባንክ 🌼 እስከመስከረም 17 የሚቆይ
ለ ቴሌግራም ቻናላችን ተከታይዎች!
ዳሽን ባንክ ለዕድለኞች መልካም ዜና ይዞ መጥቷል
#የ 600 ሚሊዮን ትርፍ #ያጋሩ ይሸለሙ
https://t.me/dashen_banketh
እንኳን ደስ አላቸችሁ ዳሽን ባንክ ሀብት 600 ሚሊዮን ምክንያት በማድረግ በባንካችን ፕሬዝዳንት እስከ መስከረም_5 ብቻ የሚቆይ #የቴሌግራም_ገፅ ማነቃቂያ የሚሆን ሽልማቶች ተዘጋጅቷል።
https://t.me/dashen_banketh
ባልነው መሰረት የያጋሩና ይሸለሙ ውድድር አሸናፊዎቻችን በአስገራሚ ስጦታዎች
ለመሸለም ተዘጋጅተናል! የእንኳን ደስ አላችሁ
https://t.me/dashen_banketh
ያስተውሉ ዕጩ ለመሆን መጀመርያ በጥንቃቄ ያንብቡ
‼️ለመሸለም ይህንን መንገድ ተከተሉ
1.መጀመርያ ከታች ባለው ማስፈንጠርያ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇👇
https://t.me/dashen_banketh
🌻1ኛ ሽልማት ለ500 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 50,000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!
https://t.me/dashen_banketh
🌻2ኛ ሽልማት ለ200 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 30,000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!
https://t.me/dashen_banketh
🌻3ኛ ሽልማት ለ100 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 20,000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!
https://t.me/dashen_banketh
🌻4ኛ ሽልማት ለ50 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 10,000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!
https://t.me/dashen_banketh
🌻5ኛ ሽልማት ለ25 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 5000 ብር አሸናፊ
https://t.me/dashen_banketh
ቤቶ በመሆን ሀብታም ይሁኑ ለ ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር በማረግ የገንዘብ ተሸላሚ ይሁኑ!!!!👇👇
https://t.me/dashen_banketh
ሁሌም አንድ እርምጃ ቀዳሚ!
3 738
🌼Happy new year to ya'll🌼 and Happy Mother's Day to all of you that found pharmacies closed today🤣
3 738
I Commented on her Status: Happy New Year..
She Replied: Same to You..
I Edited the Comment to "I Love You" 😎
3 738
የአዲስ አመት ጭውውት ያመጣው መዘዝ...
ቤቱን ፀዳ ፀዳ አድርገው እስኪ፡ በቃ ሁልጊዜ መቀመጥ ምንድን ነው። በአል ደርሷል ፡ በአል በአል አስመስለው ቤቱን...
እረ በስማም በይ እማዬ፡ ምን ሆነና ነው የማፀዳው ...
ምን ሲሆን ነው ላንተ ለማፅዳት የምትነሳሳው ፡ ለስሙ ኢንጅነር ነህ ..
በርግጥ እኔ ምንም ቢሆን ለማፅዳት አልነሳሳም 😃
እረዲያ ለዛ ቢስ ፡ በቃ ለዛህ ተሟጦ አለቀ ..
አለቄ እንዴ ☺
አይይ እ ፡ አይ ለዛ ማጣት። ምናለ ፀጉርህን እንኳ ብትቆረጠው ፡ የአበደ ሰው መስለህ..አሁን አንተ የኔ ልጅ ነህ፡ ውይ ውይ..
ለዛውም በጣም የምትወጂው ልጅ ነኛ ☺
መስሎህ ነው..
በመሀል የኩኩ ሰብስቤ ዘፈን ከጆሮዬ ገብቶ ኖሮ አብርያት ማንጎራጎር ጀመርኹ...
አበባዬ እዮሀ
እዮሀ አበባዬ
መስከረም ጠባ
ጓዜን ጠቅልዬ ወዳገሬ ልግባ
መጨረሻ ላይ ምን እንዳለች ሰማሀት ወይ ጨብራራው..
አዎ ፡ ጓዜን ጠቅልዬ ወዳገሬ ልግባ ነው ያለችው ። ለውጪ ሀገር ላሉት ነው የሚሰራው መልክቱ..ምነው ግን ጠየቅሽኝ ?
አንተም እኮ እንደዛው ነህ ...
እንደዛው ማለት
የውጪ ሀገር ሰው ነህ ..
እመስላለኋ ፡ እኔ ያንቺ ልጅ አየሻ ☺😃
ዘፋኟ እንዳለችው ለምን ጓዝህን ጠቅልለህ አትወጣልኝም..
ቀልድሽ አይጠገብም እኮ ማሚ ☺
በ2014 ከቤቴ ለመውጣት ተዘጋጅ፡ ቀልድ ከመሰለህ ሲደርስ ቀኑ ታየኛለህ ...
የምርሽን ነው እንዴ
አልመለሰችልኝም..እሺ ቤቱን ላፅዳ..አሁንም ዝም...መበላት ይልሀል ይሄ ነው...☺
የምትወዱኝም የማትወዱኝም ከቤት መባረሬ ነውና ጎዳና ወጥቼ ሚኒ ባስ ታክሲ ተከራይቼ ፡ "እኔነኝ ደራሽ ለወገኔ እኔነኝ" የሚለውን ዘፈን ፡ መሰልቸት የሌለበት ግን በሁነቶች ብዛት የሰለቸኝን ዘፈን ከፍቼ በተለያዩ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ሳላስጮህባችሁ በግዜ እርዱኝ...አይ ካላችሁኝ ግና ፡ አንድ degree የተመረኩበትን photo ፡ አንድ ላንጋኖ እና Hike ሳረግ የተነሳሁትን፡ በጎን ደሞ በግብድዬ ብርድልብስ ተጠቅልዬ የተነሳሁትን አንድ ላይ በባነር አሰርቼ መደንቆራችሁ ነው...አስቡት አስኪ''እኔ ነኝ ደራሽ ለወገኔ ፣ ዘራ የበረሮ መጥፊያ ፣ በዚህ ደሞ እየሱስን ተቀበል ፤ በዚህኛው የመኪኖች ክላክስ፡ የኑሮው ጩኸትም ሳይረሳ " መደንቆራችሁም እማይደል ...
አስቡበት ☺!
3 738
የኢትዮጵያ ቀንን" ስለመዘከር..
"ኩሽ" የሚለውን ወደ ዕርዕ/ግሪክ/ ሲተረጉሙ " ኢትዮጵያ " አሉት አይደለም የተባለው ? በዚህ ጊዜ ነው በፀሃይ መቃጠላችን የነገሩን ፤ መክሰላችንን ያረዱን፣መጥቆራችንን ያበሰሩን፤ የተቃጠለ ፊት ወይም በፀሃይ የጠቆረ ፊት ያላቸው ብለው ተረጎሙታ። ወቸ ጉድ ፡እሺ ባክህ....ከዚህ ጊዜ በፊትስ፡እነ ሆሜር፣እነ ሄሮዱተስ ማን ይሉን ነበር ? " ኢይቶፒያ" ምን ለማለት ? "ታላላቆች፤ መልካቸው ያማረ ፣ ቅኖች፣ በጎ አድራጊዎች፣ ሸበላዎች (ተንኮልና ወሬኛነት በቅርብ ነው የመጣብን ባይዘዌ ☺...እያሉ የዚችን ምድር ነዋሪዎች ሲገልጿቸው እኮ ነው ።
የምድር ሁሉ ቋንቋ አንድ በነበረበት ጊዜ ፣ የቋንቋዎች ሁሉ እናት ቋንቋ፣ ፈጣሪ ከፍጡሮቹ ጋር በተነጋገረበት ቋንቋ "እንቅዮጳዝዮን" ስትባል ቆየችና ቀስ በቀስ " ኢትዮጵግዮን " መባል ጀመረችና በመሀል ቤት ተሰረቀች። ከዚያ በኋላማ ለሌላ ግልጋሎት ሲጠቀሙበት ኖረው ብንፈልግ ፣ብንፈልግ ፣ብንዳስስ አጣነው። በመጨረሻ "ኢትዮጵ" ሆኖ አገኘነው።
አሃ ብለን ስንመረምር ፡ ኢት ምንድነው "ስጦታ " ፡ ዮጵ ደግሞ "ብጫ ወርቅ ወይም እንቁ" ግዮን? "ፈሳሽ ወንዝ" በጥቅል " ኢትዮጵግዮን"...አጠቃላይ ምን ይሆናል ? .."የግዮን ወርቅ ስጦታ"..በድሮው "ኢትኦጵግዮን" ፡ ከዚያ በፊትስ "እንቅዮጳዝዮን"..ባጭሩ በሁሉም ቋንቋ ትርጉሙ ይኸው ነው። ለወደፊት ልጅ ስወልድ ያገራቸውን ስም ስነግር እንዳይበዛባቸው "ኢትዮጵ" ብዬ እነግራቸዋለሁ። ከፍ ሲሉ "ኢትኦጵግዮን" እላቸዋለሁ ። ለአቅመ ማገናዘብ ሲደርሱ "እንቅዮጳዝዮን" ብዬ እነግራቸዋለሁ። ፀሀይ ለፀሀይ ሳይሆን እንዲንከራተቱ ሳይሆን በነፋሻማ አየር ዘና ብለው ወርቅ እንዲፈልጉ ፤....
ሚስጥር የሆነች አገር..አስቡት እስኪ፡ በፈጣሪ እጅ ተፅፎበት ለሙሴ የተሰጠው ፅላት እዚህ ነው። የኢየሱስ ግማደ መስቀል አንድ አካል እዚህ ነው። በአፍሪካ የመጀመሪያው መስጂድ ነው፧ የመጀመሪያው መንፈሳዊ ዜማና ሽብሸባ እዚህ ነው፧ ነብዩ መሀመድ ወገኖቻቸውን የላኩት እዚህ ነው፧ የራሷ የሆነ ፊደል ያላት ፣ የራሷ ብቻ የሆነ ጤፍ የተባለ ምግብ የሚሆን ሰብል የሚበቅልባት፡ እንጀራ በወጥ የሚበላባት ልበል ይ ሆ ን !
....
#ኢትዮጵያ
#ኢትዮጵ# ኢትኦጵግዮን# እንቅዮጳዝዮን
💚💛❤️
