cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Jesus channel

@Jesuscan ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2 : 5 @Jesuscan

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
212
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

#ድግስ 👪በሀገራችን ባህል አንድ ሰው ሲደግስ፥ ብዙ ሰው ማለቴ ቤተሰብ፣ ዘመድ አዝማድ፣ ጓደኛ፣ ከቅርብ ጎረቤት አንስቶ እሩቅ ሀገር ያለ ደስታህ ደስታዬ ነው ብሎ የሚያስብ ወዳጅ ሁሉ ይተጋገዛል ይተባበራል፥ ቢችል ገንዘቡን ባይሆንለት የደስታ መግለጫ መልዕክቱን ይልካል፤ ደስታህ ደስታዬ ነው እንኳን ደስ አለክ ይለዋል፤ ክብር በሚሰጥበት መንገድ ሁሉ ለደጋሹ ያለውን ክብር ያሳየዋል፤ ታድያ እንደምታውቁት የድግስ ጣጣ ብዙ ነውና ሲደገስ፥ ይጠነሰሳል፣ ይወቀጣል፣ ይፈጫል፣ ይቦካል፣ ይጋገራል፣ ይወጠወጣል...ምኑ ቅጡ የማይደረግ የለም፥ ድግሱን ለማሳመር ብዙ ዋጋ ይከፈላል፡፡ ማለት የፈለኩት የኢየሱስ ክርስቶስን ህይወት የተካፈላቹ ወንድሞቼ እህቶቼ ምንም እንኳን መደገስ መልካም፥ ከደጋሹ ጋር መተባበርና ከጎኑ መቆም ይበልጥ መልካም ቢሆንም፥ ሳታውቁትና ሳይገባቹ የጠላትን ጥንስስ እየጠነሰሳቹ፣ የክፋዎችን ደባ እየወቀጣቹ፣ ክፋ ሀሳብ እየፈጫጩና እያቦካቹ፣ የክፋትን እንጀራ እየጋገራቹ እንዳትገኙ ተጠንቀቁ #ንቁ ስል በጌታ ፍቅር አሳስባችኋለሁ፡፡ "#የክፋዎች ድግስ ሞቅ ደመቅ የሚለው ቅኖች ባለማወቅ፥ ደጎች በሞኝነት ሲያጅቡት፥ ይሄን ትብብር ያየ ሁሉ ሁኔታውን ሲያራግበው ነው፡፡" የጌታን ማዕድ ተካፍለን፥ በጠላት ገበታ ተገኝተን እንዴት ደስ ልንሰኝ እንችላለን??? #ታድያ እንደኔ ከአብርሃምና ከይስሐቅ ከያዕቆብም ጋር በመንግሥተ ሰማያት መቀመጥንና ቅዱሱ ግብዣ ላይ መገኘት የምትናፍቁ ሁሉ፥ ከጌታ የተቀበላችሁትን ንፁሁን ነጭ ልብስ እዚህም እዚያም እያላቹ ማንም የወጠወጠውን ወጥ ለመብላት ብላቹ የምታቆሽሹት አይመስለኝም፡፡ “ከውሾች ተጠበቁ፥ ከክፉዎችም ሠራተኞች ተጠበቁ፥ ከሐሰተኛም መገረዝ ተጠበቁ።”—ፊልጵስዩስ 3፥2 ⁶ እንግዲህ ጌታ ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ተቀበላችሁት እንዲሁ በእርሱ ኑሩ፤ ⁷ በእርሱ ተተክላችሁና ታንጻችሁ፣ እንደ ተማራችሁት በእምነት ጸንታችሁ፣ የተትረፈረፈ ምስጋና እያቀረባችሁ ኑሩ። ⁸ በክርስቶስ ላይ ሳይሆን፣ በሰዎች ልማድና በዚህ ዓለም መሠረታዊ ሕግጋት ላይ በተመሠረተ ፍልስፍናና ከንቱ ማግባቢያ ማንም ማርኮ እንዳይወስዳችሁ ተጠንቀቁ። ⁹ የመለኮት ሙላት ሁሉ በአካል በእርሱ ይኖራልና፤ ¹⁰ እናንተም የገዥነትና የሥልጣን ሁሉ ራስ በሆነው በክርስቶስ ሙሉ ሆናችኋል። ቆላስይስ 2 (አ.መ.ት) ¹⁶ በክርስቶስ ያለውን መልካሙን ኑሮአችሁን የሚሳደቡ ሰዎች ክፉን እንደምታደርጉ በሚያሙበት ነገር እንዲያፍሩ በጎ ሕሊና ይኑራችሁ። ¹⁷ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲህ ቢሆን፥ ክፉ ስለ ማድረግ ሳይሆን በጎ ስለ ማድረግ መከራን ብትቀበሉ ይሻላችኋልና። [1ኛ ጴጥሮስ 3] በሚገባ አስቡበት!!! የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን @jesuschanne @jesuschanne @jesuschanne
Show all...
ሕይወት ከዘላለም አንፃር ሕይወትህን ከዘላለም አንፃር ኑር። ሕይወትን ከዘላለም አንፃር እስካልኖርክ ድረስ ህይወት ትርጉም የለሽ ትሆንብሀለች።የዘላለሙ ጌታ ለዘላለማዊነት ፋጥሮሀል።ይህ ደግሞ ታላቅ ሚስጥር ነው።ዘላለማዊነት እስከ እለተ ሞትሕ የምትኖረው አለም ሳይሆን ከሞት ማዳ ያለ ዘላለማዊነት ነው።ይህ እውነት ሲገባሕ እያንዳንዶ እርምጃህ ትርጉም ያለው ይሆንልሀል።ለዚህ ነው ሀዋርያው ጳውሎስ የልቦናችሁ አይኖች ይበሩዘንድ በአብ ፌት እበረከካለሁ ሚለው ፤ ይህ ሲሆን የመጥራቱ ን ተስፋ በመረዳት።ሕይወትን ከዘላለም ተስፋ አንፃር መኖር ትጅምራለህ።"ከዘላለም አንፃር ስትኖር ለህይወት የምትሰጠው ፋይዳ ይቀየራል"ሪክዋርን ትክክለኛው የሕይወትህ ዓላማ ጅማሮው ከዘላለም አንፃር መነሻውን እስካላገኘ ግብህ ምድራዊ እና ምድራዊ ቢቻ ነው።
Show all...
😍😍😍 አንተ ፅኑ ሀያል 😍😍😍 👌"አሁን ራሳቹን እያያቹት እንዳላቹት እግዚአብሔር ፈፅሞ እያያቹ አደለም እግዚአብሔር የሚያያቹ ጅማሪያቹ ላይ ቆማቹ ፍፃሚያቹን እየተመለከተ ነው ፤ ለዛ ነው አንተ ፅኑ ሀያል ብርቱ ሰው የሚልህ " 👌"እንደሚያይህ ራስራህን ማየት፣እንደሚልህ ለራስህ መናገር ጀምር " 👌የጌዴዎን የስኬት ሚስጥር ይሄ ነው 👌የአዲስ ኪዳን ጌዴዎን አንተ አንቺ ነሽ 🤷‍♂ @ambassadorlife 🤷‍♂ 🤷‍♂ @ambassadorlife 🤷‍♂ ለአስተያየት 👉 @bereketteshome
Show all...
part two 😍😍😍😍 ፆም 😍😍😍😍 ስለ ፆም አስደናቂ መገለጥ #በበረከት_ተሾመ 👌"ኢየሱስ እንደምንፆም እርግጠኛ ነበር !! " 👌" እግዚአብሔር ሁሉንም ቢወድም ለሁሉም እኩል ሞገስ ግን አይሰጥም " 👌 " እግዚአብሔር የተወደድክ የሚልህ ከሌላው እሱ ሲበልጥብህ ነው !!" Part- 2 @ambassadorlife @ambassadorlife ለአስተያየታችሁ 👉 @bereketteshome
Show all...
part one 😍😍😍😍 ፆም 😍😍😍😍 ስለ ፆም አስደናቂ መገለጥ #በበረከት_ተሾመ 👌"ኢየሱስ እንደምንፆም እርግጠኛ ነበር !! " 👌"ቃል ማንበብ እና ፀሎት የሌለበት ፆም የምግብ አድማ ነው!" 👌 "በቁስ አለም ውስጥ የምናደርገው ነገር ሁሉ በመንፈስ አለም ላይ የሚፈጥረው ነገር አለ !!" Part-1 @ambassadorlife @ambassadorlife ለአስተያየታችሁ 👉 @berekerteshome
Show all...
#ኦሮሞ_ስማ #አማራ_ስማ #ትግሬ_ስማ #ደቡብ_ስማ #ኢትዮጵያውያን_ስሙ ፊልጵስዩስ 2:2-4 "2፤ በአንድ አሳብ ተስማሙ፥ አንድ ፍቅር አንድም ልብ አንድም አሳብ ይሁንላችሁ፤ 3፤ ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ፥ ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር፤ 4፤ እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ።" ©በረከት ተሾመ #ሼር @AMBASSADORLIFE
Show all...
"ከመተወን ወደ መሆን መለወጥ አለበት ፍቅራችን " ዮሐንስ 13፥35 " እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ።" 1 ዮሐንስ 3:18 " ልጆቼ ሆይ፥ በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት አንዋደድ።" ©በረከት ተሾመ #ሼር @AMBASSADORLIFE
Show all...
ህያው እግዚአብሔርን!!✋ ይሄን ሰምተህ እንደነበራቹ ሆናችሁ አትቀጥሉም ። ስሙት 😊 ሮሜ 12፥2 "የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ #በልባችሁ #መታደስ #ተለወጡ #እንጂ #ይህን #ዓለም #አትምሰሉ ።" ©በረከት ተሾመ #ሼር @AMBASSADORLIFE
Show all...
ሮሜ 12፥ 1 "እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው።" ®በረከት ተሾመ @AMBASSADORLIFE
Show all...