cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

⚘አትዘን لا تحۡـــــزن⚘

❆لَا تَحْزَنْ إِنَّ اللَّهَ مَعَنَا ۖ ❆ ⇘አትዘን:- <<ዛሬን የመጨረሻህ ቀንህ እንደሆነች አድርገህ ኑር ይህ አስተሳሰብና የህይወት አመለካከት ካለህ የቀረችህን ትንሽ ጊዜ ሀዘንና ቁጭት እንዲሰርቅህ አትፈቅድለትም >> ☞ ♡ዶ/ር ዓኢድ አል_ቀርኒ♡ https://t.me/joinchat/AAAAAELvlw_o9x05C8m61A ❥•••

Show more
Advertising posts
9 924
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-16830 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Show all...
TikTok · አልበራሂን

Check out አልበራሂን's video.

Show all...
አልበራሂን on TikTok

አፉታ #muslim #ሙስሊምች🇪🇹 #habeshatiktok #ሃበሻቲክቶክ #ሃበሻሙስሊም #habeshamuslim🧕 #brother #ወንድም

🥰ተጀመረ   ተጀመረ   ተጀመረ  🥰 #የአባቴ_ሚስት❤️ በቃ ወሬ አላበዛም furqan tube ብቻ ያለ ቀጥታ ከባለ ታሪኳ የተወሰደ💔 ልብ የሚሰብር አሳዛኝና😓 አስተማሪ የሆነ ድንቅ ታሪክ ነው መቼስ እንድታምኑኝ ወላሂ ምናምን አልልም ገብታቹ ብቻ አንብቡት አስተማሪ ታሪክ ነው። ✨OPEN ✨የሚለውን ስትነኩ ወደ ታሪኩ ይወስዳቹኋል አታስምሉኝ ከሌለ leave አርጉ🤦
Show all...
🍂ይ🀄️ላ🀄️ሉን🍂
✨✨OPEN✨✨
እንኳን ለ 1,444ኛው የዒዱል አድሓ በዓል አላህ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!! ጌታ አላህ ዒዱን የተባረከ፣ የመደሰቻ፣ ምስኪኖችንም የማስደሰቻ ቀን ያድርግላችሁ። ዒዱኩም ሙባረክ፣ ተቀበለላሁ ሚንና ወሚንኩም
Show all...
አረፋህ ሊመን አረፈህ! ነገ ቤት የማፅጃ ወይ መጋረጃ የማውረጃ ቀን አይደለም። የኢድ ሸመታም ሆነ የመዝናኛ እንዲሁ! ነገ አላህ የሰማይ ባለሟሎች ላይ በአረፋ ሰዎች የሚኩራራበት፤ የሰው ልጆች ከእሳት በገፍ ነፃ የሚባሉበት ከሁሉ በላይ ዱአዎች በሙሉ ተቀባይነት የሚያገኙበት እለት ነው። ለይለቱል ቀድር ባትታወቅ የውሙ አረፋ ትታወቃለች። በለይለቱል ቀድር መላእክት ቢወርዱ በአረፋ አላህ (እሱን በሚመጥን አወራረድ) የሚወርድበት ነው! ነገ አላህ በጊዜ ፀጋ ላጣቀማችሁ አንድ to do list ላካፍላችሁ ጠዋት ከፈጅር በፊት ከለይሉ ጥቂቱን መስገድ፣ ስሁር መመገብ እና ኢስቲግፋር ማብዛት! ከሰላት በኋላ ቀጥታ ተክቢራ መጀመር ከዛም ፀሀይ እስክትወጣ ቁርአን፣ተህሊል፣ተህሚድ በአጠቃላይ በዚክር ማሳለፍ(አዝካረ ሰባህ ሳይረሳ) ፀሀይ ስትወጣ የፀሃይ መውጣትን ሰላት እዛው ከመስገጃችን ሳንነሳ በመከወን ከረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ሀጅ የማድረግን ምንዳ እንዲጎናጸፍ ለቀን ኢባዳ ያግዘናል ብለን ካሰብን መጠነኛ እኝቅልፍ እንተኛ። ስንነሳ በትንሹ 4 ረክኣ ሰላተ ዱሃ እንስገድ! ከሰአት ከዝሁር ሰላት በኋላ ቁርዐናችንን እንቀራለን። የአረፋ ኹጥባ(ከመስጂደ ነሚራህ የሚተላለፈውን) መልእክት በጥብቅ መከታተል ልባችንን ሊያረጥብ የሚችል መፅሐፍ ወይም ቪድዮ እየተመለከትን እራሳችንን እናርጥብ! ከአስር በጥሎ እንዲሁ በቁርአን እና በዚክር መግሪብ 1 ሰአት አቅራቢያ እስኪቀረው ማሰለፍ! የእለቱ ወሳኝ ሰአት ይህ ነው። የተሰበረ የሚጠገንበት፤ የታመመ የሚፈወስበት፤ ተስፋ የቆረጠ ተስፋው ነፍስ ሚዘራበት ድንቅ ሰአት! ዱኣ!!! ዱኣ ብቻ! በዚህ ቀን ከእሳት ነፃ አለመባል ኪሳራ ነው። ምኞት ኖሮን ምኞታችንን ሳናሳካ መቅረት ቂልነት ነው! ነገ አላህ አልመረጥንም እና እየተመለከታቸው ከሚኮፈስባቸው ጌታቸውን ለማላቅ በነጭ ተውበው ከአረህማን ድግስ ከሚታደሙት አልሆንም! "አረፋ ተራራ ላይ መቆም ያልቻለ አላህ ያሳወቀው ድንበር ላይ ይቁም ሙዝደሊፋ ላይ ማደር ያልቻለ በአላህ ትእዛዝ ላይ ይደር...ያቀርበዋልና! ሚና ላይ እርዱን መከወን ያልቻለ ምኞቱን ይረድ! ከፍ ይላልና። ወደ ቤቱ በርቀት ምክንያት መድረስ ያልቻለ ከደም ስሩ ቅርብ ወደ ሆነው የቤቱ ጌታ ይከጅል!" ኢብኑ ረጀብ እርቅ ይበጀናል! Huzeyfa Sultan
Show all...
አልበራሂን ኢስላማዋ የኦንላይን ትምህርት ቤት የአላህ ሰላም እዝነትና በረከት በናንተ ላይ ይስፈን።አልበራሂን ኢስላማዊ ትምህርት ቤት በልዩ መጠሪያው አንፎ ጊቢ በአካል ከሚሰጠው የትምህርት ፕሮግራም በተጨማሪ የትምህርት ማህደሩን በማስፋት የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በኢንተርኔት ኢስላማዊ ትምህርቶችን ባሉበት ሆነው መማር ለሚሹ ሙስሊም ወንድምና እህቶቻችን ለማድረስ ቀን ከሌት እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው። በዚህኛው ዙር ምዝገባ ውስን ተማሪዎችን ብቻ መዝግቦ ለማስተማር ዝግጅቱን ያጠናቀቀ ሲሆን በዋናነት የቁርአን ንባብ ትምህርት ላይ ትኩረት በማድረግ ጎን ለጎን ደግሞ ለልጆችና መሠረታዊ ኢስላማዊ እውቀትን ለሚሹ ወንድምና እህቶች ስድስት መሠረታዊ የዲን ትምህርቶችን ማለትም ዓቂዳ፣ሀዲስ፣ፊቂህ፣አዳብና አኽላቅ፣አዝካር፣የሲራ ትምህርቶችን ለመስጠት ዝግጅቱን ጨርሷል። ትምህርቱ በዋናነት የሚሰጥባቸው የሞባይል መተግበሪያዎች(applications) የሚከተሉት ናቸው፦ -ዙም(zoom) -ቴሌግራም(telegram) -አይኤሞ(imo) -ዋትሳፕ(whats app) ማሳሰብያ ፦አልበራሂን ኢስላማዊ የትምህርት ተቋም ለትርፍ የተቋቋመ ድርጅት ሳይሆን ሙስሊሙን ኡማ ለማገልገልና በእውቀት የታነፃ ትውልድን ለማፍራት እያለመ የሚተጋ ተቋም ነው።ይህን ትልቅ እቅድ ለማሳካት በሚያደርገው ሂደት ላይ አገልግሎቱን በመስጠት የሚያገኘውን ፋይናንስ ሙሉ ለሙሉ ለዳዕዋ፣ለመድረሳ፣ለኡስታዞች ክፍያና ለሌሎች ዘርፈ ብዙ ኢስላማዊ ስራዎች በአላህ ፍቃድ የሚያውል መሆኑን በደስታ እንገልፃለን። ኑ የጋራ ነጋቻንን በጋራ እንገንባ! ስልክ ቁጥር +251943829274 +251912104750 እንዲሁም አልበራሂን ኢስላማዊ ጀመዓን ተቀላቅለው የበኩሎን ኢስላማዊ አሻራን ለማሳረፍ በቴሌግራም አድራሻችን ይቀላቀሉን👇 https://t.me/alberahin1 https://t.me/alberahin1
Show all...
አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላህ የማስታወቂያው ቪድዮ ነው ሃሳብ ካላችሁ አካፍሉኝ
Show all...
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ እርሶ ከቁርዓን ጋር ይተዋወቃሉ? የቂርዓቶ ደረጃንስ ማሻሻል ይፈልጋሉ?እነሆ የምስራች በመላው አለም ለምትገኙ ለቁርዐንና ለሀዲስ ትምህረት ፈላጊዎች በሙሉ አልበራሒን ኦንላይን ቁርአን የቦታ ርቀት ሳይገድባቹ ቁርዐንን ባላቹህበት ቦታ አስተካክሎ ለመቅራት ልዩ የኦንላይን ቁርዐን ፕሮግራም አዘጋጅቷል።በተጨማሪም ለርሶና ለልጆችዎ በመልካም ልዩ ትምህርት (ዓቂዳ፣አኽላቅ፣አዝካር፣ ሲራ እና ሀዲስ) የትም መሄድ ሳይጠበቅባቸው በኦንላይን የዘመኑን ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም ትምህረት ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል።  ፈጥነው ይመዝገቡ እርሶ እኛ ጋር ሲቀሩ ከወጪ ቀሪ የሚገኘው ትርፍ ሙሉ ለሙሉ ኢስላማዊ ስራዎችን ብቻ በመስራት ላይ ላለው አልበራሒን ጀመዓ የሚውል መሆኑ  በደስታ እንገልፃለን!ኒያ ካሎት የኸይር ስራ ተቋዳሽም  ኖት ስልክ ቁጥር +251967936098 በኢንቦክስ👇👇 @Ba_Alewi ግሩፑን ይቀላቀሉ👇👇👇 https://t.me/+5c5NKMc7F75hNDQ0
Show all...
በዝቅታ ውስጥ ሆኜ የመመራትን ብርሃን ሳልኖር ወርጃለሁ።የእድሜ ፈተና ይሁን ምን ልናገረው አልችልም።ማንን ጩኼ ተጣርቼ ካለሁበት አዘቀት እንደሚያወጣኝ ባውቅም አቅሙና ተነሳሽነቱ የለኝም።አዎ ቆሞ የሚሄድ ሁሉ ሰው ከተባለም እኔም ሰው ነኝ።የማንነቴ መለኪያ ሚዛን የለውም።የማውቀው አንድ ነገር እያጠፋውና እየጠፋው እንደሆነ ነው።መዳረሻየን ሳስበው ስጋት መላ ሰውነቴን ደጋግሞ ይነዝረኛል።አውቆ የተኛ ሲጠሩት አይሰማም እንደሚባለው አውቆ የሞተ የሚባል ብሂል አለመኖሩን ሳስብ ግርምት ይጭርብኛል።ከኔ ውጪ እኔን እንደኔ የሚያውቅ ተራማጅ ፍጡር እንደሌለ አቃለሁ።ሁለት ጥሪዎች አካሌን በየእለቱ በየደቂቃው በየሰኮንዱ ይጠሩታል።ለሁለቱም አቤት እላለሁ። ሃጥያት ፈሳሽ ቁስ አካል ይዞ ባህር ቢሆን ኖሮ የእኔ ብቻ ወንጀል የምድርን ሰው የሚያሰምጥ ይመስለኛል። ።ይሄ ቅኔ ሳይሆን እኔ ነኝ።አሁንም መዳኔን ወይም መስጠሜን ሳላውቅ በአንድ ጥሪ አድማሱን በሚሞላ ልክ እጣራለሁ ለኔ ሳይሆን ለናንተ ዱዓ አደርጋለሁ ያአላህ ከአንተ በሚያርቅ ወንጀል ወንድሞቼን አትፈትናቸው።መልዓኩ ተቀብሎ ላንተም አምሳያው እንዲልልኝ እሻለሁ።በመልካም ዱአችሁ አትርሱኝ። اللهم صلي على نبينا محمد
Show all...