G-Tutorialclass
Open in Telegram
904
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1530 days
Posts Archive
ባንኮቹ ምን ገጠማቸው❓‼️
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን መርሳ ከተማ ከትናንት በስተያ ማክሰኞ መስከረም 27/2018 ዓ.ም የመርሳ ቅርንጫፍ የሆኑት አቢሲንያ ፤አዋሽ፤ዳሽን፤አማራ፤ሂጂራ፤ቡና እና ዘምዘም ባንኮች ከቀኑ 10:00 ሰዓት ላይ በተመሳሳይ ሰዓት በታጣቂዎች ዝርፊያ መፈፀሙን የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገልጸዋል።
ዳሽን ባንክ ላይ ብቻ ከ5 ሚልዮን ብር በላይ ሳይወሰድ እንዳልቀረ የገለፁልን ሲሆን ከሌሎች ባንኮች አጠቃላይ ምን ያህል ብር እንደተወሰደ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም።
==========≠============
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
ደመወዝ‼️
አዲሱ የፖሊስ አባላት የደመወዝ ስኬል ከላይ ተያይዟል።
==========≠============
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
የዩኒቨርሲቲ ምደባ‼️
የዩኒቨርስቲ ምደባ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤
የዩኒቨርስቲ ምደባችሁን በእነዚህ ሊንኮች ማየት ትችላላችሁ👇👇
Website: https://student.ethernet.edu.et
Telegram bot: @moestudentbot
==========≠============
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+1
ደብዳቤው‼️
#ኢትዮጵያ #ኤርትራ እና #ህወሓት"ጦርነት ሊከፍቱብኝ በቅንጅት እየሰሩ ነው" ስትል ከሰሰች፤ በወልዲያ በተፈጸመው ጥቃት ተሳትፈዋል አለች‼️
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኤርትራ መንግሥትና ህወሓት “ፅምዶ” በተሰኘ አዲስ ጥምረት “ኢትዮጵያን ለመውጋት” እየሰሩ ነው ሲል ከሰሰ። በተጨማሪም በቅርቡ በአማራ ክልል ወልዲያ ከተማን ለመያዝ በፋኖ ሀይሎች በተፈጸመ ጥቃት ውስጥ ሁለቱ ተዋናዮች ተሳትፈዋል ሲልም ገልጿል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዎን ጤሞቲዎስ (ዶ/ር) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ለሆኑት አንቶኒዮ ጉተሬዝ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም. በጻፉት ደብዳቤ፤ “በኤርትራ መንግሥትና በህወሓት አንጃ መካከል ያለው ቅንጅት ባለፉት ጥቂት ወራት ይበልጥ ግልጽ ሆኗል” ብለዋል።
ሚኒስትሩ በደብዳቤው ቅንጅቱ “በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት ለመክፈት በንቃት እየተዘጋጀ ነው” ሲሉ ገልጸው፤ ሁለቱንም ተዋናዮች “የግጭቱን አድማስ ለማስፋት እንደ ፋኖ ያሉ ታጣቂ ቡድኖችን በገንዘብ በመደገፍ፣ በማሰባሰብ እና በመምራት” ከሰዋል።
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
🚨 አስደንጋጭ ዜና‼️
ከ60 ሚሊየን ብር በላይ ለመዝረፍ የሞከሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ!
በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ በሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በተከሰተው አስከፊ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሰለባ ለሆኑ ዜጎች ከተሰበሰበው የድጋፍ ገንዘብ ላይ ከ60 ሚሊየን ብር በላይ ለመዝረፍ የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የዞኑ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አስታወቀ።
* አደጋው በደረሰባቸው ወገኖች ህይወትና ችግር ለመበልጸግ ያሰቡት ተጠርጣሪዎች፣ ለተጎጂዎች የተሰበሰበውን 60,276,383 ብር ከጎፋ ዞን አደጋ ስጋት አካውንት ለመውሰድ ሞክረዋል።
* ገንዘቡን ለመዝረፍም ቀደም ሲል ቮይድ በተደረገ የቼክ ቁጥር (42221123) አስመስለው በማሳተም ሙከራ አድርገዋል።
* የወንጀል ሙከራው የተጋለጠው ከአዲስ አበባ ንግድ ባንክ ሸገር ቅርንጫፍ ለጎፋ ዞን አስተዳደር በተደረገ ፈጣን ጥቆማ ምክንያት ነው።
* በጥቆማው መሠረትም ከአዲስ አበባና ከክልል ፖሊስ ጋር በመተባበር፣ ገንዘቡ ሳይወጣ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል።
የዞኑ መንግሥት ኮሙኒኬሽን፣ ሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ የለገሰውን ድጋፍ 'ወደ ኪሴ ገብቶ ካልበለጸግኩ' በሚል አስተሳሰብ የተጠመዱ አካላት ያሰቡት "አስነዋሪና ስብዕና የጎደለው ተግባር" አለመሳካቱን ገልጿል።
Via አሐዱ
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ‼️
ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የ Remedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን እናሳውቃለን።
1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን።
2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
➡ በዚህ መሠረት የተፈጥሮና ማህበራዊ ሳይንስ ለወንድ 216/600፣ ለሴት 204/600፣ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር ሁለቱም ፆታ 198/600፣ለአይነ ስውራን 165/600 ሆኗል ።
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+1
ሰበር❗ኢትዮጵያ ደብዳቤ ላከች‼️
👉ኢትዮጵያ ኤርትራ ላይ እርምጃ እንደምትወስድ አስጠንቅቃለች።
በባለፈው በሰኔ ወር ከተላከው ደብዳቤ በተጨማሪ ኢትዮጵያ በውጪ ጉዳይ ሚኒስትሯ በኩል ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኤርትራን በማስጠንቀቅ October 2/2025 የአቤቱታ ደብዳቤ አስገብታለች።
ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የተላከው ደብዳቤ “የኤርትራ መንግስት ህወሃትን ጨምሮ ሌሎች በክልል የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎችን እየደገፈች የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እየተዳፈረች መሆኑንና ኢትዮጵያም ይህን በሉዓላዊነቷ ላይ የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለማስቆም ህጋዊ፣ሞራላዊ እና ተፈጥሯዊ መብቷን ትጠብቃለች” ማለቱን ከሆርን ሪቪው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር የተገለለችበት መንገድ ህጋዊ ባለመሆኑ ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት ለመሆን ያነሳችውን ጥያቄ አሁንም አቋሟን እንደማትቀይር አቋሟን በግልፅ ለተባበሩት መንግሥት ድርጅት አሳውቃለች።
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+1
ፈተናው መቼ ይሰጣል❓❓❓
የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያው ዙር ብሔራዊ የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ በቀን መስከረም 26/2018 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተላከ ሰርኩላር፥ የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተናው ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይገልጻል።
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
English Lesson
Exercise I.10
1. We should work out our environmental problem so that we will have a better future.
2. My grandmother tried to get up on her own, but the sofa was too low for people of her age.
3. Let me put on my clothes well before rushing towards a taxi.
4. The plane takes off the land half past 2:00, so we are expected to check in one hour time.
5. The sounds of both the storm and fireworks made people get freighted and go out the building through the backdoors.
6. He sleeps without trouble while the laundry machine is working. This is impossible for me. I have to turn off it before going to bed.
Exercise II
It is not easy to sleep in a noisy place. You may be interrupted now and then.
Environmental campaigners have (1) called for a ban on traffic in the city center. This (2) resulted in pollution levels were found to be dangerously high for two years running. The campaigners' plans to (3) turn into the city center a car-free zone have (4) met with support from city residents. Campaign spokesman Derek Shields said: 'Closing the city center to traffic would (5) result in lower carbon emissions and make the city a more pleasant place to live. It's time for the city authorities to (6) step in and address this problem.'
Note the small change to 5 to be consistent with the overall text.
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
ለወንዶች የወሊድ ፈቃድ‼️
በደቡብ አፍሪካ አባቶች ከእናቶች እኩል የወሊድ እረፍት ተፈቀደላቸው
"ለደቡብ አፍሪካ የወደፊት አባቶች ፈር ቀዳጅ እርምጃ ነው"
#Ethiopia | የደቡብ አፍሪካ ሕገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ሁሉም ወላጆች እኩል የወሊድ እረፍት እንዲኖራቸው ወሰኗል።
ውሳኔው ትልቅ ውሳኔና ለፆታ እኩልነትና የቤተሰብ መብት ግዙፍ አሸናፊነት ተደርጎ ተወስዷል።
በቀደመው ሕግ እናቶች የአራት ወር የወሊድ ፈቃድ ያላቸው ሲሆን፤ አባቶች ደግሞ 10 ቀናት ብቻ ይሰጣቸው ነበር።
የአገሪቱ ሕገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ባሳለፈው ውሳኔ፣ ሕጉን ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ያለው ሲሆን፤ ለአባቶች አድሎአዊ ነው ብሏል። በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ሁለቱም ወላጆች እንደፈቀዱ የሚጠቀሙበት እኩል የወሊድ እረፍት እንዲያገኙ በይኗል።
'ሲንግል ዳድስ ኔትወርክ' የተባለ ድርጅት መስራች የሆኑት ሴትምቢሶ ፓኪቲ፤ "ይህ ለእኩልነት፣ ለቤተሰብ ደኅንነትና ለደቡብ አፍሪካ የወደፊት አባቶች ፈር ቀዳጅ እርምጃ ነው" ብለዋል።
እ.ኤ.አ በ2023 የአገሪቱ የታችኛው ፍርድ ቤት፣ የአገሪቱ ሁለት ሕጎች የተወሰኑ ክፍሎች ፍትኃዊነት የጎደላቸው መሆናቸውን እንዳገኘና የበርካታ የቤተሰብ መብቶችን የሚጥሱ ናቸው ብሏል።
ከፍተኛ ፍርድ ቤት የወሊድ ፈቃድና የሥራ አጥ ጥቅማ ጥቅሞችን ማግኘትን በተመለከተ ለወላጆች ፍትኃዊ አለመሆኑን ወስኗል።
ጉዳዩ በብቸኝነት በሴቶች ላይ የሚጣለውን ማኅበረሰባዊ ጫና ፍትኃዊ ለማድረግ በወጠኑ በሁለት ጥንዶች፣ በፆታ እኩልነት ኮሚሽንና በሌሎችም ወደ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን፤ የወላጅነት ኃላፊነት የጋራ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል።
ቢቢሲ
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+1
የኤርትራ አመራሮች‼️
የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ዛሬ ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል፡፡
ከሰሞኑ horn review "ኢትዮጵያ ለኤርትራ የሰጠችውን የሀገርነት እውቅና ማንሳት አለባት፣ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት እውቅና ለማንሳት አለምአቀፍ ህጎች እንዳሉ እንዲሁም የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በማቅረብ" ረዘም ያለ ፅሁፍ ማሰራጨቱን ተከትሎ የኤርትራ አመራሮችን ክፉኛ ያበሳጨ ይመስላል፡፡
ይህን ተከትሎ የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስቴር አቶ የማነ ገብረመስቀል "ነጻነታችንን ከኢትዮጵያ በስጦታ አልተረከብንም ኢትዮጵያን አሸንፈን ያገኘነው ነው ብለዋል፡፡ የኤርትራ ሉዓላዊነት እውቀና መሰጠት የነበረበት በ1940 ቢሆንም አሜሪካ እና ሌሎች ሀገራት በቀጠናው የነበራቸው ፍላጎት ሌላ በመሆኑ ሳይሳካ ቀርቷል ብለዋል።
ኢትዮጵያ እንደተባለው የምታደርግ ከሆነ እኛም ከ1952 እስከ 1993 እ.ኤ.አ ኢትዮጵያ ለወሰደችብን ሀብትና ንብረት በቢሊየን ዶላር የሚቆጠር ካሳ እንጠይቃለን ብለዋል፡፡ለዚህም የኢራቅ እና ኩዌትን ታሪክ አጣቅሰዋል፡፡
በፅሁፉ የኢትዮጵያ ሰራዊትን ሲዋጉ በተለይ በመንደፈራ፣በምፅዋና በአሰብ እንዴት እንዳሸነፉና ከኢትዮጵያ በኩል ምን ያህል ሰራዊት እንደተበተነ፣እንደቆሰለ፣እንደሞተ እና እንደተማረከ በቁጥር ለማስቀመጥ ሞክረዋል።
በተያያዘ ዜና ከሰሞኑ የኤርትራ ወታደራዊ አመራሮች ከኢትዮጵያ ጋር በተዋጉባቸው በእያንዳንዱ ግንባር በመሄድ የጦርነቱን ሂደትና አሰላለፍ ምን ይመስል እንደነበር ለሰራዊታቸው አመራሮች እና መኮንኖች የጦርነት ትንታኔ ሲሰጡ ታይተዋል።
(አዩዘሀበሻ)
==================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
Repost from Ayu Zehabesha-Official አዩ ዘሀበሻ
+1
የኤርትራ አመራሮች‼️
የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ዛሬ ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል፡፡
ከሰሞኑ horn review "ኢትዮጵያ ለኤርትራ የሰጠችውን የሀገርነት እውቅና ማንሳት አለባት፣ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት እውቅና ለማንሳት አለምአቀፍ ህጎች እንዳሉ እንዲሁም የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በማቅረብ" ረዘም ያለ ፅሁፍ ማሰራጨቱን ተከትሎ የኤርትራ አመራሮችን ክፉኛ ያበሳጨ ይመስላል፡፡
ይህን ተከትሎ የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስቴር አቶ የማነ ገብረመስቀል "ነጻነታችንን ከኢትዮጵያ በስጦታ አልተረከብንም ኢትዮጵያን አሸንፈን ያገኘነው ነው ብለዋል፡፡ የኤርትራ ሉዓላዊነት እውቀና መሰጠት የነበረበት በ1940 ቢሆንም አሜሪካ እና ሌሎች ሀገራት በቀጠናው የነበራቸው ፍላጎት ሌላ በመሆኑ ሳይሳካ ቀርቷል ብለዋል።
ኢትዮጵያ እንደተባለው የምታደርግ ከሆነ እኛም ከ1952 እስከ 1993 እ.ኤ.አ ኢትዮጵያ ለወሰደችብን ሀብትና ንብረት በቢሊየን ዶላር የሚቆጠር ካሳ እንጠይቃለን ብለዋል፡፡ለዚህም የኢራቅ እና ኩዌትን ታሪክ አጣቅሰዋል፡፡
በፅሁፉ የኢትዮጵያ ሰራዊትን ሲዋጉ በተለይ በመንደፈራ፣በምፅዋና በአሰብ እንዴት እንዳሸነፉና ከኢትዮጵያ በኩል ምን ያህል ሰራዊት እንደተበተነ፣እንደቆሰለ፣እንደሞተ እና እንደተማረከ በቁጥር ለማስቀመጥ ሞክረዋል።
በተያያዘ ዜና ከሰሞኑ የኤርትራ ወታደራዊ አመራሮች ከኢትዮጵያ ጋር በተዋጉባቸው በእያንዳንዱ ግንባር በመሄድ የጦርነቱን ሂደትና አሰላለፍ ምን ይመስል እንደነበር ለሰራዊታቸው አመራሮች እና መኮንኖች የጦርነት ትንታኔ ሲሰጡ ታይተዋል።
(አዩዘሀበሻ)
==================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ልዩነት ❗❗
1. ⛽ ነዳጅ (Crude Oil/Petroleum) ምንድነው?
ነዳጅ (ድፍድፍ ዘይት) ከጥንት የባሕር ውስጥ ሕይወት ቅሪት የተገኘ ፈሳሽ የቅሪተ አካል ነዳጅ ነው። ከማጣራት በኋላ ለተለያዩ ነገሮች ይውላል። ዋና ዋናዎቹ፡-
*ቤንዚን (Gasoline): ለመኪናዎች
*ናፍጣ (Diesel): ለትላልቅ ተሽከርካሪዎች እና ጄኔሬተሮች
*ኬሮሲን እና የአውሮፕላን ነዳጅ
ፕላስቲኮችና አስፋልት ለመሥራት ግብዓት ነው።
2. የተፈጥሮ ጋዝ (Natural Gas) ምንድነው?
በአብዛኛው ሚቴን (Methane) ከተባለ ጋዝ የሚሰራ ሲሆን፣ እንደ ነዳጅ ሁሉ ከጥንታዊ ሕይወት ቅሪት የተፈጠረ ነው።
ለኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች
ለቤቶች ማብሰያ እና ማሞቂያ
ለኢንዱስትሪዎች እና እንደ የተሽከርካሪ ነዳጅ (CNG)፣ለማዳበሪያ (Fertilizer) ማምረቻ ወሳኝ ግብዓት ነው።
🇪🇹 ኢትዮጵያ ይፋ ያደረገችው የትኛውን ነው?
የሀገራችን የኃይል ስትራቴጂ ትልቁ ትኩረት በሶማሌ ክልል ኦጋዴን ተፋሰስ የሚገኘው የተፈጥሮ ጋዝ ላይ ነው።
✅ ኢትዮጵያ በቅርቡ ወደ ምርት እያስገባች ያለችው ዋነኛው የተፈጥሮ ሃብት: የተፈጥሮ ጋዝ ነው!
የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ (LNG) ፕሮጀክት፡ በቅርቡ በካሉብ አካባቢ የተፈጥሮ ጋዝን ለሀገር ውስጥ ፍጆታና ለኢንዱስትሪ የሚሆን ፈሳሽ ጋዝ (LNG) የሚያመነጨው ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ተመርቆ ሁለተኛው ተጀምሯል።
ይህ የተፈጥሮ ጋዝ የማዳበሪያ ፋብሪካዎችን ለመገንባት እንደ ወሳኝ ግብዓት ያገለግላል። ይህም ሀገሪቱ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር አውጥታ ከውጭ የምታስገባውን ማዳበሪያ በሀገር ውስጥ ማምረት እንድትችል ትልቅ በር ይከፍታል።.
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+1
#አሜሪካ #ኢትዮጵያ ለምትገነባው ግዙፍ አውሮፕላን ማረፊያ ድጋፍ ለማድረግ ማቀዷ ተሰማ‼️
ይህም የአፍሪካ ቀንድ የትራምፕ የመጀመሪያው ትልቅ ተነሳሽነት ነው ተብሏል።
አሜሪካ በኢትዮጵያ በ10 ቢሊዮን ዶላር ለሚገነባው የአፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገባች። ይህም የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአፍሪካ ቀንድ የመጀመሪያው ትልቅ የቢዝነስ ተነሳሽነት ተደርጎ ተወስዷል።
የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ቀደም ብሎ በኢትዮጵያ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ሀገሪቱ ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኝነቷን አስታውቀዋል።
እንደ ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ ዘገባ፣ ቡሎስ የአሜሪካ የዓለም አቀፍ ልማት ፋይናንስ ኮርፖሬሽን በፕሮጀክቱ እንደሚሳተፍ እና ከቦይንግ ጋር በመተባበር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በአፍሪካ ባሉ ሌሎች ሥራዎች ላይ እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።
Business insider
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
አዲሱ የደመወዝ ስኬል‼️
አዲሱ የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ስኬል ከላይ ተያይዟል። ይህ የደመወዝ ማሻሻያ ከተያዘው መስከረም ወር ጀምሮ የሚፈፀም ይሆናል፣የመስከረም ወር ክፍያው በ back payment በጥቅምት ወር ይፈፀማል።
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
የሞባይል ባንኪንግ ላይ ያነጣጠረ አዲስ የአንድሮይድ ቫይረስ መከሰቱ ተነገረ‼️
"ክሊዮፓትራ" የሚል ስያሜ የተሰጠዉ የሞባይል ባንኪንግ ላይ ያነጣጠረ አዲስ የአንድሮይድ ቫይረስ መከሰቱን የሳይበር ደህንነት ስጋቶች ላይ የሚሰራዉ ክሌፊስ #Cleafy’s ቡደን አሳወቀ።
የዚህ ቫይረስ መከሰት በሞባይል ባንኪንግ ስጋት እድገት ዉስጥ ከፍተኛ የሚባል ለዉጦች እየተከሰቱ መሆናቸዉን ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
በክሌፊስ ቡድን አማካኝነት በነሃሴ ወር መጨረሻ የተለየዉ ይህ ቫይረስ በአውሮፓ የፋይናንስ ተቋማት ላይ ባነጣጠሩ መጠነ ሰፊ ዘመቻዎች ዉስጥ ጥቅም ላይ እንደዋለ ተገልጿል።
"ክሊዮፓትራ" የተራቀቀ የባንክ ትሮጃን ቫይረስ የመረጃ መንታፊዎች በርቀት ሆነዉ የተደበቀ ምናባዊ ኔትዎርክ ስርዓትን በመጠቀም ለጥቃት ሰለባ የሆኑ መሳሪያዎችን መቆጣጠር የሚያስችላቸዉ መሆኑ ተነግሯል።
ይህ አጥፊ ሶፍትዌር ከገሃዱ ዓለም የማጭበርበር ሙከራዎች ጋር ቁርኝት የፈጠረ ሲሆን ለጥቃት ኢላማ የተደረጉ አካላት መሳሪያዎቸዉን ቻርጅ ሲያደረጉ እንዲሁም ብዙም ክትትል አይደረግበትም ብለዉ በሚያስቡት ምሽት ላይ ጥቃቶች በጥንቃቄ እንደሚሰነዝሩ ታዉቋል።
የደህንነት ባለሙያዎች ቫይረሱ ለወደፊቱ የዘርፉ ስጋቶች ማሳያ ሆኖ ሊያገለግል እንደሚችል ያስጠነቀቁ ሲሆን ይህም የፋይናንስ ተቋማትን ላይ ያለዉ የስጋት ደረጃ ከፍ እንደሚያደርገዉ ጠቁመዋል።
የቫይረሱ መከሰት ለፋይናንሺያል ተቋማት እና ፀረ-ማጭበርበር ቡድኖች፣ ከስታቲክ ትንታኔ በላይ የሆኑ ስራዎችን እንደሚጠበቅባቸዉ ያሳየና በመጠቀሚያ መሳሪያዎች ላይ የሚከሰቱ የባህሪ ለዉጦች ላይ ክትትል ማድረግ እንዲሁም የስጋት ማሳወቂያ መፍትሄዎችን መተግበር ወሳኝ መሆኑን ተገልጿል።
======
💎📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
2027 ዲቪ ለመሙላት‼️
ከዚህ በኋላ የዲሺ ሎተሪ ወይም የግሪን ካርድ ሎተሪ ለመሙላት ለመመዝገቢያ 1 ዶላር የሚያስከፍል ሲሆን የዲቪ ሎተሪ የደረሰው ግለሰብ ለቪዛ አፕልኬሽን 330 ዶላር የሚከፍል ይሆናል።
ይህ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው ከመጪው October 16/2025 ጀምሮ ነው። ዲቪ ሎተሪ ለመሙላት ክፍያ ሲጠየቅ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የ2027 ዲቪ ሎተሪ በፈረንጆቹ ከጥቅምት ወር እስከ ህዳር ድረስ መሙላት ይቻላል።
ክፍያው የሚፈፀመው በ e-paymet ነው። ውጤት ማየት የሚቻለው may 2026 ነው።
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+1
Update❗❗
በአማራ ክልል ምንጃር አረርቲ ማሪያም ቤተክርስቲያን በተፈጠረው አደጋ የሟቾች ቁጥር 40 መድረሱን የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገልፀዋል።
የጎን አጥንታቸው የተሰበረ፣አይናቸው የጠፋ...ሌላም ጉዳት ያስተናገዱ እጅግ በርካታ ናቸው።
አሳዛኝ አደጋ፣አሳዛኝ ጠባሳ😥
ለመላው የምንጃር ህዝብና ለተጎጂ ቤተሰቦች መፅናናትን እንመኛለን።
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
በግሸን ሌቦች ተያዙ‼️
በግሸን ደብረከርቤ አመታዊ በዓል ላይ ከህዝቡ ስልክ እና ገንዘብ ሲሰርቁ የነበሩ ሰዎች እጅ ከፍንጅ ተይዘው ታስረዋል።
አንድ ግለሰብ ስምንት ስልኮችን እንዲሁም ገንዘብ ሰርቆ በፀጥታ ኃይሎች እጅ ከፍንጅ ተይዞ በአስቸኳይ ፍርድ የእስር ትዕዛዝ ተላልፎበታል።
አዩዘሀበሻ
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት‼️
ትምህርት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤትን ከ300 ወደ 297 ዝቅ አድርጓል፡፡
ሚኒስቴሩ እንደገለጸው ÷ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ተማሪዎች ወደቀጣይ የትምህርት ደረጃ ለመዛወር 50 በመቶና ከዚያ በላይ ማምጣት እንዳለባቸው ይደነግጋል።
በዚህ መሰረትም በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና አማካይ ውጤታቸው 49 ነጥብ 50 እስከ 49 ነጥብ 99 በመቶ ያመጡ ተማሪዎች ወደ 50 በመቶ እንዲጠጋጋ መወሰኑን አመልክቷል፡፡
ውሳኔውን ተከትሎም 49 ነጥብ 5 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ዝቅተኛውን 50 በመቶ የማለፊያ ነጥብ እንዳሟሉ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ስለሆነም 49 ነጥብ 5 እና በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመግባት መማር እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ አረጋግጧል፡፡
===================
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
