G-Tutorialclass
Open in Telegram
904
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1530 days
Posts Archive
ዲቪን በተመለከተ‼️
የዲቪ ሎተሪ ቀን ለምን ዘገየ❓
በተለምዶ በጥቅምት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ለምዝገባ የሚከፈተው የዩኤስ ዲቨርሲቲ ቪዛ (ዲቪ) ሎተሪ ለ2027 ፕሮግራም ዘግይቷል።
በርካታ ግለሰቦች ዛሬ ይጀመራል ቢሉም የዩኤስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኦፊሴላዊ የምዝገባ ቀናትን ገና አላሳወቀም። የዘገየበት ምክንያት በግልጽ ባይታወቅም ለመመዝገቢያ የሚያስፈልገው የ$1 ክፍያን ለመተግበር የሚያስችል የሲስተም ዝርጋታ ሊሆን እንደሚችል ተነግሯል።
በዚህ ዙሪያ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የዘገየበትን ምክንያት ባያረጋግጡም የDV 2027 ፕሮግራም ይፋ የሚደረግበት ቀን እየቀረበ መሆኑን ገልጿል።
ቃል አቀባዩ "Diversity Immigrant Visa (DV) 2027 ፕሮግራም በቅርቡ ይፋ ይሆናል" ብለዋል።
ለዲቪ ሎተሪ 1 ዶላር የመመዝገቢያ ክፍያን የሚያፀድቅ የመጨረሻ ህግ በፌደራል መዝገብ መስከረም 16/2025 ታትሞ በዚያው ቀን ተግባራዊ መደረጉን ቃል አቀባዩ አስታውሰዋል። ይህ ክፍያ ህዝቡ መስከረም 15/2025 እንዲታወቅ ተደርጓል። “አዲሱ የመመዝገቢያ ክፍያ በምርጫ ሂደት ላይ ለሚያስፈጉ ወጪዎች ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ይመድባል። በተጨማሪም አጠያያቂ ሊሆኑ የሚችሉ ተመዝጋቢዎችን ለመበዝበዝ በሚፈልጉ ግለሰቦች የሚደረጉ ግምታዊ ምዝገባዎችን ለመቀነስ ይረዳል” ሲል ቃል አቀባዩ አብራርተዋል።
ይህ $1 የዲቪ ማመልከቻ በሚያስገቡበት ጊዜ በኤሌክትሮኒክ የክፍያ አማራጮች ወይም master card የሚከፈል ይሆናል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህ ክፍያ ወደ 25 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ እንደሚያስገኝ ገምተዋል።
አመልካቾች ዲቪ ማሸነፋቸው ሲረጋገጥ ለቪዛ አገልግሎት 330 ዶላር ይከፍላሉ።
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+4
የመሬት መንቀጥቀጥ‼️
በአፋር ኪብላቲ ረሱ ዞን ትናንት ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ከምሽት 2:00 ጀምሮ አስፈሪ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።
የመሬት መንቀጥቀጡ ከጥቅምት 1 ቀን ጀምሮ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ነው ብለዋል።
በራህሌ እና በኮናባ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በርካታ ቤቶችን፣ የውሃ ጉድጓዶችን፣ የጤና ተቋማትን፣ ትምህርት ቤቶችን እና መስጊዶችን አፍርሷል።
ከተያያዙት ምስሎች ውስጥ ሁለተኛው በቡሬ ቀበሌ በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ተራራው ሲናድ የሚታይ አቧራ ነው።
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+1
ይሄን መረጃ ሼር አድርጉት‼️
የአይን ስፔሻሊስት ሃኪሞች ሞባይል ስልክ የሚያመጣብን ጣጣ የአይን ማኩላር እርጅና እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እድሜአቸው በገፋ ሰዎች ላይ ብቻ ነበር የሚታየው።
✅አሁን ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከ30 እስከ 40 አመት የሆኑ ወጣቶች ሁሉ ‘ማኩላር ዲጀኔሬሽን’ የተባለና ወደ አይነ ስውርነት የሚያደርስ ሕመም እየተጠናወታቸው መጥተዋል ይላሉ የሲንጋፖር የአይን ሕክምና ሆስፒታል ዋና
ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ሊሊ።
✅ይሄም የሆነበት ማክንያት ብዙ ሰዎች ማታ መብራት ካጠፉ በኋላ ተንቀሳቃሽ ስልክ እየከፈቱ ያያሉ።
በጭለማ ውስጥ ወይም ጨለም ባለ አካባቢ የሞባይል ስልክን ለ30 ደቂቃ እንኳን መጠቀም መታረም የማይችል አደጋ ውስጥ የሚከት ነው።
ሕመሙም ካታራክት አይነት ሕመም ማስከተል ብቻ ሳይሆን የአይን ካንሰርም ያስከትላል።
✅ይህ ደግሞ ደግሞ መድሃኒት የሌለው በመሆኑ አይን ሲጠፋ ብቻ ቁጭ ብሎ መመልከት ነው ይላሉ
ሃኪሙ።ይህን መልዕክት ያስተላለፉት 254 የሚሆኑ የአይን ስፔሻሊት ሃኪሞች አንድ ላይ በመሆን ነው።
✅ብዙ ሰዎች ማታ አልጋቸው ላይ ሆነው መብራት አጥፍተው ወይም ፈዘዝ ባለ መብራት ተንቀሳቃሽ ስልካቸውን እንደሚጠቀሙ ስለሚታወቅ ራሳችሁን ከማይድን ሕመም ጠብቁ ብለዋል።
👉ለወዳጅም ሼር ማድረግዎን በፍፁም እንዳትረሱ።
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
እንድታውቁት‼️
TIN (ግብር ከፋይ) ቁጥር ላላችሁ በሙሉ‼️
ከዚህ ቀደም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሳይኖራችሁ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላችሁ ግብር ከፋዮች ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥራችሁን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር በአካል መሔድ ሳይጠበቅብዎ ይህን ሊንክ https://mor-migration.fayda.et በመጠቀም ማያያዝ ይችላሉ።
ይህን በማስተሳሰርዎ ፡
- ግብር በሚከፍሉበት ወቅት ጊዜዎን መቆጠብ ይችላሉ ፤
- በኦንላይን የሚሰጡ አገልግሎቶችን ቀላል እንዲሆን እና እንዳይጭበረበር ይረዳል።
ያስተውሉ፦
የግል መረጃዎ ደህንነት በእርስዎ እጅ ስለሆነ ፤ ፋይዳ ልዩ ቁጥር (FIN) በገቢዎች ለሚሰጡ አገልግሎቶች ያለምንም ችግር ማጋራት እንደሚችሉ ተቋሙ አሳውቋል።
#==========≠===========
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
በርካታ ነጋዴዎች ታስረዋል‼️
በደመወዝ ጭማሪ ሰበብ ዋጋ የጨመሩ ነጋዴዎች ላይ እስካሁን የተወሰደ እርምጃ:-
🎯የታሰሩ ነጋዴዎች-865
🎯ንግድ ፈቃዳቸው የተሰረዘ-576
🎯ንግድ ፈቃዳቸው የታገደ- 1,263
🎯ሱቃቸውን የታሸገ- 33,020
🎯የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው- 29,588 ናቸው።
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
#prettyupdate
(DV2027 LOTTERY )
ዲቪ ሎተሪ ለመመዝገብ:-
✅ለመመዝገብ ፍላጎት ላላቸው ባሉበት ሆኖ ኦንላይን ብቻ።
🔻የሚከተለውን መረጃ በማዘጋጀት ይጠብቁን:-
✍️WHAT NEED FOR REGISTER ONLINE?
✔️ፎቶው ቀለም ያለው እና ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ መነሳት አለበት.
✔️File Format: JPEG (JPG).
1. የመግቢያ መረጃ
• ስም
• ጾታ
• የተወለደበት ቀን
• የተወለድክበት ከተማ
• የተወለድክበት ሀገር
2. ፎቶ
3. የፖስታ አድራሻ
4. አሁን የሚኖሩበት አገር
5. ስልክ ቁጥር (አማራጭ)
6. ኢሜል አድራሻ
7. የትምህርት ደረጃ
8. የጋብቻ ሁኔታ
9. የልጆች ቁጥር
10. Derivative Information
(የሚመለከተው ከሆነ)
• የትዳር ጓደኛ መረጃ
• የልጆች መረጃ
መካተት ያለባቸው የትዳር ጓደኛ እና/ወይም ልጆች ካሉዎት፡-
✅ለእያንዳንዱ የትዳር ጓደኛ፡-
• የመጨረሻ / የቤተሰብ ስም
• የመጀመሪያ ስም
• የአባት ስም
• የልደት ቀን
• ጾታ
• ከተማ / የትውልድ አገር
• ፎቶግራፍ
✅ለእያንዳንዱ ልጅ፡-
• የመጨረሻ / የቤተሰብ ስም
• የመጀመሪያ ስም
• የአባት ስም
• የልደት ቀን
• ጾታ
• ከተማ / የትውልድ አገር
• ፎቶግራፍ
📆ምዝገባው በጥቅምት 16፣ 2025 ይጀምራል።
Let's get ready until then to reduce the hassle of the deadline.
Inbox👇🏻
@Mik_ye12
Thank you!
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+3
ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ‼️
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በ3 ቢሊዮን ብር የመምህራን መኖሪያ አፓርታማ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ‼️
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስረስ መለስ (ዶ/ር) እንደገለጹት በዩኒቨርሲቲው 230 መምህርንን ተጠቃሚ የሚያደርግ አፓርታማ በ3 ቢሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ግንባታው የመዝናኛና የገበያ ማዕከላትን ጨምሮ ሁለገብ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የግንባታውን ሂደት በማፋጠን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
አንድ ዶላር 148 ብር ተሸጠ‼️
አንድ የአሜሪካ ዶላር በ148 ብር ጨረታ ተሸጠ‼️
ብሔራዊ ባንክ የ150 ሚሊዮን ዶላር ውጭ ምንዛሪ ጨረታ አካሂዷል።
ባንኩ መሰል ጨረታ ሲያወጣ ለ10ኛው ዙር ሲሆን በዚህ ዙር 150 ሚሊዮን ዶላር በጨረታ ለመሸጥ አቅርቧል።
በጨረታው የአንድ የአሜሪካን ዶላር አማካይ የምንዛሪ ተመን 148.1007 ብር ሆኖ ተመዝግቧል። / 1 ዶላር በ148.1007 ተሽጧል /
ይህ አዲስ አማካኝ ዋጋ ከሁለት ወራት በፊት በ9ኛው ዙር ጨረታ ከተመዘገበው 138.2 ብር አማካይ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር፣ የ9 ብር ከ90 ሳንቲም ወይም የ 7.16 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
ዛሬ በተካሄደው የውጭ ምንዛሪ ድልድል 31 ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ጨረታው ላይ ተሳትፈው በሽያጩ ተሳትፈዋል ተብሏል።
ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያው በሚፈቅደው ጊዜ ተመሳሳይ ጨረታዎችን እቀጥላለሁ ብሏል።
#==========≠============
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+2
የቀጠለው ተቃውሞ‼️
ትናንት በመቀሌ የጀመረው የታጣቂዎች ተቃውሞ ዛሬም በአጉላዕ፣ በሀውዜን፣ በአዲግራት እና በውቅሮ ተቃውሞ እየተደረገ ይገኛል።
በዚህ የተነሳ ከአዲግራት-ውቅሮ-መቀሌ የሚወስደው መንገድ ዝግ በመሆኑ መኪኖች መንገድ ላይ ለመቆም ተገደዋል፣ጉዞ ተስተጓጉሏል ሲሉ የመቀሌ ምንጮቻችን ገልጸዋል።
ሰላማዊ ሰልፈኞቹ የደመወዝ ፣ የጥቅማጥቅምና ለቤተሰቦቻቸው መኖሪያ የሚውል የመስሪያ ቦታ ጥያቄ አንስተዋል።
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
የሶማሊላንድ አዲሱ ተመራጭ ፕሬዚዳንት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ እየመጡ ነው። ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ግብዣ የቀረበላቸው በጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ (ዶ/ር) መሆኑ ታውቋል።
ከሰሞኑ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐመድ አዲስ አበባ እንደነበሩ ይታወሳል።
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
ልጅ ለሚወልዱ 1ሚ ሩብል ‼️
በሩሲያ የወሊድ ምጣኔ መቀነሱን ተከትሎ ሀገሪቱ ቤተሰቦች ልጆች እንዲወልዱ እያበረታታች ሲሆን፤ ለዚህም ሦስት ወይም ከዚያ በላይ ልጆች ለሚወልዱ ቤተሰቦች ብዙ ጥቅማጥቅሞችን አቅርባለች፡፡ ጥቅማጥቅሞቹ የሚከተሉትን ይጨምራሉ፡-
• እስከ 1 ሚሊዮን ሩብልስ የሚደርስ የገንዘብ ጉርሻ
• መኖሪያ ቤት መገንቢያ መሬት
• ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎትና የት/ቤት ምገባ ለልጆች
• ነጻ የሕክምና አገልግሎቶች
• የመብራትና የነዳጅ ክፍያዎች ከቀረጥ ነፃና ቅናሽ
• ዓመታዊ የቤተሰብ ጉዞዎችና የእረፍት ጊዜያት
ይሄ ፖሊሲ ወደፊት ወላጅነትን ወደ ኢንቨስትመንት የሚቀይር ነው ተብሏል፡፡
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
የቤት ኪራይ‼️
የኤሌክትሪክ ክፍያ ጨምሯል በሚል ምክንያት የቤት ኪራይ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተከራዮች ቅሬታ አሰሙ‼️
በአዲስ አበባ ከተማ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጭማሪ እያሳየ የመጣዉ የቤት ኪራይ ዋጋ ንረት ስጋት እንደፈጠረባቸዉ ነዋሪዎች ይናገራሉ ። በአሁኑ ወቅት የቤት ኪራይ ጭማሪ ከማሳየቱ በተጨማሪ በምንፈልገዉ ሰፈርና ለስራ ቦታችን ቅርብ በሆኑ አከባቢዎች ላይ ቤት ማግኘት ባለመቻላችን ከፍተኛ ለሆነ የትራንስፖርት ወጪ ተዳርገናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገልፀዋል ።
ከኢኮኖሚ አቅማችን እና ከስራ ቦታችን ጋር ቅርበት ያለዉ ቤት ለማግኘት ተቸግርናል የሚሉ ቅሬታ አቅራቢዎች እንደተናገሩት የኤሌክትሪክ ክፍያ ጨምሯል በሚል ምክንያት አከራዮች ለስቶቭና ለምጣድ የምንከፍለዉን ክፍያ ከፍ አድርገዉብናል ይላሉ ። በዚህም የተነሳ በአዲስ አበባ መሀል ከተማ በሚገኙ ሰፈሮች ቤት በጣም ዉድ በመሆኑ በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸዉ ሰዎች የማይታሰብ ነዉ ሲሉ ገልጸዋል ።
የቤት ኪራይ ዋጋ ከቦታ ቦታ ልዩነት ቢኖረውም የተሻሉ ናቸዉ ከሚባሉ አከባቢዎች አንዱ በሆነዉ በጎሮ አከባቢ ስቶቭ መጠቀም የሚቻልበት አንድ ትንሽ ክፍል ቤት እስከ 5ሺህ 500 ብር እንደሚጠየቁ የሚናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ እስቶቭና ምጣድ ለመጠቀም እስከ 7ሺህ ብር እንጠየቃለን ሲሉ ገልፀዋል ።
ሌላኛዉ አስተያየት ሰጪ አንደሚሉት ከሆነ የምንጠየቀዉን ክፍያ ከፍለን እንኳን በእረፍት ቀን አብዛኛዉ ሰዉ ቤት በሚቀመጥበት ቀን ከቆጣሪ መብራት የሚያጠፉ አከራዮች መኖራቸዉን ይናገራሉ ። የቤት የዋጋ ንረት እየተባባሰ መምጣት ከፍተኛ የኑሮ ጫና አሳድሮብናል የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቸ የሚመለከተዉ አካል የዋጋ ማረጋጋት ሲራ እንዲሰራ ጠይቀዋል ።
Bisratfm
📚 JOIN :@GTutorialclass
አዲሱ የኤሌክትሪክ ታሪፍ‼️
ከጥቅምት 1 እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የታሪፍ ዝርዝር እንደሚከተለው ለመረጃ አቅርበናል።
✅ የመኖሪያ ቤት ታሪፍ
➡️ 0 - 50 ኪ.ዋ.ሰ. = 0.7571 ብር በ ኪ.ዋ.ሰ. (+0.0807 )
➡️ 51 - 100 ኪ.ዋ.ሰ. = 1.8516 ብር በ ኪ.ዋ.ሰ. (+0.1808)
➡️ 101 - 200 ኪ.ዋ.ሰ. = 3.1934 ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.2614)
➡️ 201 - 300 ኪ.ዋ.ሰ. = 4.7580ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.4597)
➡️ 301 - 400 ኪ.ዋ.ሰ. = 4.9477ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.4579)
➡️ 401 - 500 ኪ.ዋ.ሰ. = 5.0593ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.4424)
➡️ 500 ኪ.ዋ.ሰ. በላይ = 5.0990 ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.4363)
✅ ለንግድ እና ለአጠቃላይ አገልግሎት = 5.0141 (+0.4817)
✅ ለአነስተኛ ኢንዲስትሪ (380v) = 3.0889ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.2665)
✅ ለመካከለኛ ኢንዱስትሪ (15kv) = 2.4927 ብር በኪ.ዋ.ሰ. (+0.2211)
👉 የዲማንድ ቻርጅ ክፍያ ታሪፍ
➡️ ለአነስተኛ ኢንዲስትሪ = 441.28 ብር በኪዋ (+37)
➡️ ለመካከለኛ ኢንዱስትሪ = 324.34ብር በኪዋ (+27.1)
👉 የአገልግሎት ክፍያ የመኖሪያ ቤት
ለድህረ ክፍያ
✅ ከ0 - 50 ኪ.ዋ.ሰ. = 11.42 ብር (+0.23)
✅ ከ 50 ኪ.ዋ.ሰ. በላይ = 47.7ብር (+0.95)
ለቅድመ ክፍያ
✅ ከ0 - 50 ኪ.ዋ.ሰ.= 4.53 ብር(+0.17)
✅ ከ 50 ኪ.ዋ.ሰ. በላይ = 16.60 ብር (+0.32)
👉 የንግድ አጠቃላይ
✅ ለድህረ ክፍያ = 61.32 ብር(+0.19)
✅ ለቅድመ ክፍያ = 21.34 ብር (+0.41)
JOIN :@GTutorialclass
+1
ዘግናኝ የመኪና አደጋ‼️
👉እስካሁን የ10 ሰዎች ህይወት አልፏል።
ዛሬ ጥቅምት 2/2018 ዓ.ም በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በጨፋ ሮቢት ከተማ ልዩ ስሙ ጃራ ድልድይ አከባቢ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ 60 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኢት 73290 የሆነ ታታ ባስ እና ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኢት 41157 ተሳቢ መኪና ተጋጭተው በደረሰ ዘግናኝ የትራፊክ አደጋ ለግዜው ቁጥሩ ያልታወቀ የበርካታ ሰዎች ህይዎት አልፏል በርካቶች የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በጨፋ ሮቢት ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።
እስካሁን ከ10 በላይ ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን የሟቾቹ ቁጥር ሊጨምር ይችላል።
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+7
በመሬት መንቀጥቀጥ ጉዳት ደረሰ‼️
ትናንት ማታ በአፋር ሰሜናዊ ዞን በራህሌ ወረዳ፣ ቡሬ ቀበሌ እና አስጉቢ ቀበሌ አካባቢው ላይ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት በሰዎች እና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገለፁ።
👉6ሰዋች ተጎድተዋል።
👉1የአስራ ሁለት አመት ልጅ ህይወቱ አልፏል።
👉ብዛት ያላቸው ቤቶች ፈርሰዋል።
👉አጠቃላይ 43,456 ሰዋች መጠለያ አልባ ሆነዋል።
ትናንት ጥቅምት 1/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1:05 ጀምሮ በትግራይ እና በአፋር ክልል በሬክተር ስኬል 5.7 የተመዘገበ በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አዩዘሀበሻ መዘገቡ ይታወሳል።
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
አምቡላንስን ለኮንትሮባንድ‼️
በምስራቅ ሸዋ ዞን መተሐራ ከተማ በአምቡላንስ ተሽከርካሪ ታማሚ የጫነ በማስመሰል በፍጥነት ሳይረን እያስጮህ የፍተሻ ኬላ ለማለፍ የሞከረ የአንቡላስ አሽከርካሪ በውስጡ 1.3 ሚሊዮን ብር የሚገመት የኮትሮባንድ እቃ ጭኖ ሲጓዝ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ አስታውቋል።
#==========≠============
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
ብድር ለወሰዳችሁ ማስጠንቀቂያ‼️
በ #ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም አጋርነት በቴሌብር ማይክሮ ክሬዲት (እንደራስ) አገልግሎት በመጠቀም ብድር ወስደው የብድር ዕዳዎን በወቅቱ ስላልከፈሉ ያለብዎትን የብድር ዕዳ በአስቸኳይ እንዲከፍሉ በፍ/ብሔር ሕግ ቁጥር 1772 መሰረት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል።
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
+1
ውሃ ይቋረጣል‼️
"የውሃ አገልግሎት ይቋረጣል" - ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን የለገዳዲ ግድብ የጥሬ ውሃ ማስተላለፊያ ቫልቭ ቅየራ ስራ ከጥቅምት 2/2018 ዓም እስከ ጥቅምት 16/2018 ዓም ድረስ የሚከናወን መሆኑን ገልጿል።
የጥገና ስራው እስከሚጠናቀቅም በአንዳንድ የከተማዋ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ በሙሉ የሚቋረጥ ይሆናል ብሏል።
የውሃ አገልግሎት በከፊል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :-
- በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2፣ 3፣ 5፣ 8፣ 9፣ 10 እና 13
- በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 11፣ 13 እና14
- በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 7፣ 8፣ 10 እና 11
ስራው እስከሚጠናቀቅ የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ ለሙሉ ስለሚቋረጥ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ሲል ባለሥልጣኑ አሳስቧል::
#==========≠============
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
አዲሱ ደመወዝ መክፈል ተጀምሯል‼️
ከመስከረም ወር ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ ትናንት ጀምሮ ክፍያ መፈፀም የተጀመረ ሲሆን በርካታ ዩኒቨርስቲዎች መክፈል መጀመራቸውን ለማረጋገጥ ችለናል።
እስከ መስከረም 30 ጭማሪው ደመወዝ እንዲከፍል አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን ክፍያው እንዳይዘገይ አንዳንድ ተቋማት ጭማሪውን ከካዝናቸው ከፍለው ተመላሽ (Refund) እንደሚደረግላቸው አቅጣጫ ተቀምጧል። ገንዘብ የሌላቸው አንዳንድ የክልል ተቋማት እና ከተማ አስተዳደሮች "ከዚህ ቀን እስከ እዚህ ቀን ባለው ውስጥ እንከፍላለን" በሚል ለሰራተኞቻቸው እያሳወቁ መሆኑን ገልፀውልናል።
==========≠============
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
📚 JOIN :@GTutorialclass
JOIN :@GTutorialclass
ለ67 ሚሊዮን የስራ እድል‼️
በሕዝብ ቁጥር መጨመር ምክንያት ኢትዮጵያ ለ67 ሚሊዮን አዳዲስ ሠራተኞች የሥራ ዕድል ማዘጋጀት አለባት ተባለ‼️
በኢትዮጵያ እየጨመረ በመጣዉ የህዝብ ቁጥር ምክንያት በመጪዎቹ ዓመታት ለ67 ሚሊዮን የሚሆኑ አዳዲስ ሠራተኞች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ግዴታ እንደሚኖርባት አዲሱ የአለም ባንክ መረጃ አመላከተ።
ይህም በአፍሪካ ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት ከናይጄሪያ እና ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ቀጥሎ ኢትዮጵያን በሦስተኛ ደረጃ እንድትቀመጥ የሚያደርግ ከፍተኛ ፈተና ነው።
የዓለም ባንክ በሰጠው መረጃ መሠረት፣ በኢትዮጵያ በተለይም እኤአ እስከ 2050 ዓ.ም. ድረስ በ15-64 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኘው የሥራ ዕድሜ ህዝብ ቁጥር ዕድገት እጅግ ፈጣን ከመሆኑ የተነሳ ይህን ያህል ተጨማሪ የሥራ ዕድል መፍጠርን ይጠይቃል።
ተቋሙ የዚህን ፈተና መክበድ ምክንያት ሲያብራራ “የኢኮኖሚ እንቅስቃሴው አጥጋቢ አለመሆን እና ፈጣን የህዝብ ቁጥር መጨመር” መሆኑን አክሏል።
ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ፣ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ከታንዛኒያ እና ከዩጋንዳ ጋር በመሆን በአፍሪካ ከሰሃራ በታች ከሚጠበቀው አጠቃላይ የሥራ ዕድል ፈተና ግማሽ ያህሉን የሚሸፍኑ አምስቱ ሀገራት ውስጥ አንዷ ነች።
የአለም ባንክ ሪፖርት እንዳመለከተው፣ አፍሪካ ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት ለእያደገው ህዝቧ የሚፈለገውን ያህል ቋሚ ደሞዝ የሚያስገኝ ሥራ ለመፍጠር እየተቸገረች ነው። ይህም ወደ ከፍተኛ የችሎታ በታች መሥራት፣ ያለፍላጎት በግል ሥራ መተዳደር እና መደበኛ ባልሆነ የሥራ ዘርፍ መመደብ ምክንያት ሆኗል ሲል አስታውቋል።
Via Capital
==========≠============
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
