en
Feedback
Sadat_Text_Posts

Sadat_Text_Posts

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Sadat_Text_Posts

Channel Sadat_Text_Posts (@sadattextposts) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 10 532 subscribers, ranking 18 731 in the News & Media category and 3 222 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 532 subscribers.

According to the latest data from 04 March, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -85 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 March, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

10 532
Subscribers
No data24 hours
-207 days
-8530 days
Posts Archive
እባካችሁ ዘካ የምትሰጡ ወገኖች! ~~~ ህዝብን በተለያዩ መንገዶች ዲን እያስተማሩ ያሉ (በደዕዋ፣ በቁርኣን፣ በተድሪስ፣ ወዘተ ላይ የተሰማሩ) አቅመ ደካማ መሻይኾችን፣ ዱዓቶችን በዘካችሁ አትርሷቸው። ወላሂ አፍ አውጥተው ችግራቸውን የማይናገሩ ነገር ግን ዲን ለማስተማር ጊዜያቸውን በመስጠታቸው የተነሳ የሰቀቀን ህይወት የሚገፉ ብዙ ናቸው። በተለይ በዚህ ዘመን ደግሞ የኑሮ ጫና በየጊዜው ይበልጥ እየከበደ ነው። እነሱ የህዝባቸው ኣኺራ አሳስቧቸው እንደሌሎች መስራት፣ መነገድ፣ መለወጥ ሲችሉ ዱንያቸውን መስዋእት አድርገው የችግር ህይወት ሲገፉ እንዴት ውለታቸው ይዘነጋል? እንዴትስ ዋጋቸው ይቃለላል? ለነሱ ውለታ መዋል ለዲን ውለታ መዋል ነው። እንዲያውም ለማህበረሰባችንም ውለታ መዋል ነው። ከጎናቸው የሚቆም አጋር ሲያገኙ ይበልጥ የመስራት ሞራል ያገኛሉ። እናም ዘካ የሚመለከታችሁ ወገኖች ሆይ! እባካችሁ እባካችሁ በየአካባቢያችሁ ተመልካች ያጡ መሻይኾችን፣ ኡስታዞችን፣ የቁርኣን አስተማሪዎችን፣ የመስጂድ ኢማሞችን፣ ሙአዚኖችን የአቅማችሁን ያክል አትርሷቸው።

ተራዊህ ላይ ቁርዓን መቅራት የማይችሉ ወንድም እና እህቶች እንደ ሱረቱል ኢኽላስ ያሉ በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡ قُلْ هُوَ ٱللَّهُ أَحَدٌ «አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው፡፡ ٱللَّهُ ٱلصَّمَدُ «አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ «ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡» وَلَمْ يَكُن لَّهُۥ كُفُوًا أَحَدٌۢ አጫጭር ሱራዎችን መቅራት ይችላሉ፡፡ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይህችን ሱራ አስመልክቶ የቁርዓንን አንድ ሶስተኛ ናት ብለዋል፡፡ https://t.me/SadatTextPosts

photo content

እንኳን ለተከበረው ታላቁ የረመደን ወር አደረሰን። የአላህ ባሪያዎች ሆይ! የሚከተሉትን ነገሮች ነፍሴንም እናንተንም አደራ ልላችሁ እወዳለሁ 1) አደራ በተውሒድ ላይ፣ አደራ ሺርክን በመራቅ ላይ አላሁ ሱብሃነሁ ወተኣላ "እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! ፆም በናንተ ላይ ተደንግጓል…" ነው ያለው። ያመናችሁ ሰዎች የሚለው ላይ አስምሩበት። የተበላሸ እምነት፣ ተውሒድን የሚፃረር ሺርክ እኛ ላይ ካለ አላህ ብንፆምም አይቀበለንም። 2) አደራ በሱና ላይ፣ አደራ ቢድአ (በዲን ላይ አዲስ መጤ ጉዳዮችን) በመራቅ ላይ በረመዳን አብዛኛው ሰው በስሜት ተነስቶ ያልተደነገጉ አምልኮዎችን መፈፀም ይፈልጋል። የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) "የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ ነው (አላህ አይቀበለውም)።" ብለዋል 3) አደራ በሰላት ላይ ሰላት ታላቅ አምልኮ ነው። ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሰለትን የተወ ከሃዲ እንደሆነ ተናግረዋል። ለአለማቱ ጌታ በስግደት ያልተደፋች ፊት ምንኛ በደለኛ ናት። ሰላትን ትቶ መፆም በሀይማኖት ላይ መቀለድ ነው። 3) አደራ ቅርኣንን በመቅራት፣ በመስማት ላይ፣ 4) አደራ በቸርነት ላይ የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ቸር ነበሩ ይበልጥ ቸር የሚሆኑት ደግሞ በረመዳን ወር ነው። በግማሽ የተምር ፍሬ ሰደቃ ነፍሳችሁን ከእሳት አድኑ የሚል ታላቅ ሃይማኖት አላህ ሰጥቶናል። አላህ በሰላም ፆመን፣ መስጂዶቻችን ድጋሚ ተከፍተው፣ ተውሒድና ሱና የበላይ ሆኖ ሺርክ እና ቢድአ የበታች ሆነው ለማየት ያብቃን። https://t.me/SadatTextPosts

ስልጤኛ አባባል "ይሽላን ሰብ የደለ ነገ የገገከ ጋር በር ይደላን።" ትርጉሙ "የሚያውቅ ሰው የሳተ እለት የራሱን ቤት በር ይስታል" https://t.me/SadatTextPosts

photo content

መንዙማ ቁጥር 4 ስለዚህ ርእስ መደጋገም ለምን አስፈለገ? በድምፅ ፋይል የተደገፈ።

ሷሊሕ እና ሙስሊሕ ~~~~~~~~~~ ☘️ "ሰዎች ሷሊሖችን (ደጋጎችን) ይወዳሉ። ☘️ ሙስሊሖችን (አራሚዎችን) ግን ይጠላሉ። 🎋 🌴 ነብዩ ‏ﷺ ከመላካቸው በፊት ሷሊሕ ስለነበሩ ህዝብ ዘንድ የተወደዱ ነበሩ። 🌴 አራሚና ነቢይ ሲሆኑ ግን ጠሏቸው። "ደጋሚ"፣ "ዋሾ"፣ "እብድ" አሏቸው። 📌 አራሚ የሆነ ሰው ሰዎችን ከነፍሶቻቸው ብልሽት ሊያወጣቸው ስለሚታገል ከስሜቶቻቸው ቋጥኝ ጋር ነው የሚላተመው። 📌 ሷሊሕ ግን እራሱን በመጠበቅ ላይ ነው የሚብቃቃው።" 📚 ከሸይኽ ዐብዱለጢፍ ኣሊ ሸይኽ፣ የሰዑዲያ ኢስላማዊ ጉዳዮች ሚኒስትር የትዊተር ገፅ የተወሰደ‏ ኢብኑ ሙነወር https://t.me/IbnuMunewor

photo content

"የቦረናው ደግዮ እርዱኝ አባብዬ" የሚለው የክህደት ንግግር ላይ መልስ ለመስጠት ውጭ ሀገር ተምሮ መምጣት፣ ብዙ ኪታቦችን መቅራት፣ ዶክተር፣ ሸይኽ፣ ኡስታዝ መባል አይጠይቅም። የኢስላም አስኳል የሆነውን፣ በቀን 17 ጊዜ በትንሹ "አንተን ብቻ እናመልካለን። በአንተም ብቻ እንታገዛለን።" የሚለውን ማወቅ ብቻ ከበቂ በላይ ነው። https://t.me/SadatTextPosts

photo content

photo content

photo content

"የመንሃጅ ግልፅነት እና በዳዕዋ ላይ ያለው አስተዋፅኦ"፤ ከአረብኛ ወደ አማርኛ የተመለሰ የሸይኽ ሙሐመድ ረምዛን አልሃጂሪ ድንቅ ሙሓዶራ ሲሆን በ15 ገፆች ተርጉሜ በ pdf ፋይል አቅርቤዋለሁ። አንብበው ይጠቀሙበት። ሌሎችንም ያስጠቅሙበት።

ከማንም ጋር በገባበት ልንገባ፣ በወጣበት ልንወጣ የህይወት ዘመን ውል የለንም። መንሃጅ ያገናኘናል። መንሃጅ ይለያየናል። መንሃጅ ከለያየን ከትላንት ቀርቶ ከዛሬ ወዳጅም ጋር እንለያያለን። መንሃጅ ካገናኘን ዛሬ ከምንርቃቸው አካላት ጋር እጅ ለእጅ ተያይዘን እንጓዛለን። መለኪያችን የሰለፊያ መንሃጅ ብቻ ነው። ትላንት አንድ የነበርን የተለየናቸው አሉ። ትላንት ተወጋግዘን ዛሬ ከልብ የምንወዳቸው ብዙ ናቸው። አላህ በሰለፊያ ላይ ያፅናን። @IbnuMunewor

photo content
+1

ኢኽዋን፣ ከኮሮና የባሰ ቫይረስ ~~~~~~~~~~ ኢኽዋን ለሙስሊሙ ዓለም ከኮሮና ቫይረስ የከፋ በሸታ ነው። ሊቢያ ዛሬ ለገባችበት ማጥ የአንበሳውን ድርሻ የሚወስዱት እነ ቀርዷዊ ናቸው። ለጋዳፊ ጠባቂዎች “ግደሉት! የሱ ደም በኔ ጫንቃ ላይ ነው” እያለ በእልቂት ማሺኑ አልጀዚራ እሳት ሲያቀጣጥል ነበር። ዛሬ ለሊቢያ ተቆርቋሪ መስለው ያለቅሳሉ። የሚያለቅሱት ለኩርሲዋ ነው። በሙስሊሙ ዓለም እስካሁን ያለው የኮሮና ሞት መዝገብ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ኢኽዋኖች ካደረሱት የበዛ አይደለም። ከዚህ የከፋው ግን የሙስሊሞችን ዐቂዳ በመበከል እና እንዳይስተካከል ደንቃራ በመሆን ያላቸው ሚና ነው። ይሄ በርግጠኝነት በኮሮና ከሚደርሰው አደጋ የከፋ ሙሲባ ነው። የሙስሊሞችን ዐቂዳ መበከል፣ ከብልሹ እምነት እንዳይወጡ እንቅፋት መሆን ከኮሮናም የባሰ ሙሲባ ነው። ኢኽዋን ከሃገራት ለኢስላም ይበልጥ የምትቀርበውን፣ ከዑለማእ ለሱና ይበልጥ የሚቀርቡትን ነው ከሌሎች በተለየ ጠላት የሚያደርጉት። እስኪ የሺዐ እምነት ተከታዩዋ ኢራን ላይ ሲዘምቱ አይታችኋል? በዚህ ሰዓትኮ በኢራን ከ64 ሺ ህዝብ በላይ በቫይረሱ ተይዞ፣ 4 ሺህ አካባቢ ሞቷል። በርካታ ሚኒስትሮች በቫይረሱ ተይዘዋል፣ ሞተዋል። የበድሩ ሑሴንን ትኩረት የሳበው ግን የሳዑዲ ነው። የዛሬው የበድሩ ሑሴን ፅሑፍ የዚህ ኢኽዋናዊ ቫይረስ አንድ ነፀብራቅ ነው። (አቡበክር አሕመድም ተመሳሳይ ነገር እንደለጠፈ ዘግይቼ አይቻለሁ።) ጥቂት ንግግሮቹን እንመልከት፡- 1. “ከሳውዲ ንጉሳዊ ቤተሰቦች 150 አሚሮች በኮሮና ቫይረስ እንደተጠቁና የሪያዱ ገዥ ፅኑ ህሙማን ክፍል እንደገቡ ኒውዬርክ ታይምስ ውስጥ አዋቂዎችን ጠቅሶ ዘግቧል” ይላል። መልስ፡- በመጀመሪያ፡- ምንን እንደሚያጣቅስ ተመልከቱ። የከሃዲ ጋዜጣ፣ ያ ደግሞ ካልተረጋገጠ ምንጭ! የሳዑዲያ ጠላቶች ስለ ሳዑዲ ክፉ የሚናገር ካገኙ ከሰይጣንም ቢሆን ወሬ ለመቀበል አያመነቱም። እንጂ ጋዜጣው የሚያወራው ስለ ቱርክ ቢሆን ኖሮ ተጨባጭ መረጃ ቢያቀርብ እንኳን ከቁም ነገር አይቆጥሩትም ነበር። ሁለት፡- እውነት ንጉሳዊ ቤተሰቦች በዚህ ወረርሺኝ ተይዘው ከሆነም ወረርሺኝ ለአማኝ የአላህ ረሕመት ነው። የታገሰ ሸሂድነትን ይታደልበታል። በርግጥ እናንተ ዘንድ ሙስሊሞች ላይሆኑ ይችላሉ። በተረፈ ንጉሳዊ ቤተሰቦች ማለት የህዝቡ አካል ናቸው። እውነት ከሆነ ህዝቡ ላይ የደረሰ ነው የደረሰባቸው። ምንም የሚደንቅ ነገር የለም። እነሱ ቀርቶ ከዑለማዎችንም በቫይረሱ የተያዙ አሉ። 2. “ምናልባት የየመን ንፁሃን ደም መፍሰስ፣ የታላላቅ ዑለማዎች የግፍ እስርና ስቃይ ማብቂያው ተዳርሶ ይሆን? …” ይላል በድሩ ሑሴን። መልስ፡- አንድ፡- ለየመን ንፁሃን ተቆርቁራችሁ አይደለም። የየመን ንፁሃን በሑሢ ሺዐዎች ሲገደሉ፣ መሳጂድ ሲጠቁ፣ ኢራን ላይ ሱንዮች ሲሰቀሉ ኢኽዋን ሺዐዎችን አይኮንንም። ደግሞም ደዩሦች ሆናችሁ እንጂ ከኢራን ጋር እየተመሳጠረ የህዝቡን ዐቂዳ ለመበከል ሰርክ የሚሰራን አንጃ ጥላችሁ ሳዑዲ ላይ አትዘምቱም ነበር። ለየመን ትላንትም ዛሬም ከማንም በላይ ከጎናቸው ያለችው ሰዑዲያ ነች። ለዚያም ነው ከኢኽዋን በቀቀኖች ውጭ ያለው እጅግ በርካታ የየመን ህዝብና የሱና ዑለማዎች ዛሬም ድረስ የሳዑዲን ዘመቻ የሚደግፉት። ኢኽዋኖች የየመንን ጉዳይ የሚያስጮሁት ለሙስሊሞች ተጨንቀው እንዳልሆነ ከሚያጋልጣቸው አንዱ የቱርክ መንግስት በሶሪያዋ ኢፍሪን ጭፍጨፋ ሲያደርስ ዝም ማለታቸው ነው። ሁሉንም ነገር በቡድናዊ ስሌት የሚመለከቱ የደም ነጋዴዎች ናቸው። እንጂ ቱርክ ውስጥ የባለፈውን የመፈንቅለ-መንግስት ድራማ ተከትሎ ስንት ፍጅት፣ ስንት እስር፣ ስንት ማፈናቀል ነው የደረሰው? ከፈትሑላህ ጎለን ጋር ንክኪ አላቸው በሚል 32 ሺህ ህዝብ ታስሯል። ከመንግስት ተቋማት ብቻ 60 ሺህ ህዝብ ከስራው ተፈናቅሏል። እነ በድሩን ግን ይሄ አያስጨንቃቸውም። ሁሉንም ነገር የሚመለከቱት በኢኽዋን መነፅር ነዋ!! ሁለት፡- “የታላላቅ ዑለማዎች የግፍ እስርና ስቃይ” የሚለው እነ ሰልማነል ዐውዳንና መሰሎቻቸውን ማለቱ ነው። እንጂ እነ ፈውዛንን፣ እነ ዐብዱል ሙሕሲን አልዐባድን፣ ወዘተ አይደለም። እነዚህ ታላላቅ ዑለማዎች ኢኽዋኖች ዘንድ የመንግስት ቅጥረኞች ሲሆኑ የፊትና ማሽኖቹ እነ ሰልማኑል ዐውዳ ግን እውነተኛ ዑለማዎች ናቸው። ኢኽዋንኛ ከኮሮና የከፋ ከአካል ይልቅ ልብን የሚገድል ቫይረስ!! እንጂ እነ ሰልማነል ዐውዳ ማለት ከሰዑዲያ አልፈው ለአለም ሙስሊሞች አገር አፍራሽ አስተሳሰብ የሚያሰራጩ መርዝ ናቸው። ሶስት፡- ሳዑዲ ውስጥ በቫይረሱ የተያዘው እስካሁን ድረስ 3 ሺህ አካባቢ ነው። ሙገሳ ብቻ የምትሰፍሩላት ቱርክ ግን ከ38 ሺህ ህዝብ በላይ በቫይረሱ ተጠቅቶ ከ800 በላይ ሞቷል። መነፅሩ ግን አገር እየመረጠ ነው የሚያሳየው። 3. “ምናልባት የየመን ንፁሃን ደም መፍሰስ፣ የታላላቅ ዑለማዎች የግፍ እስርና ስቃይ #ማብቂያው_ተዳርሶ_ይሆን? …” የሚለውንና ከኮሮና በኋላ “ዓለማችን ከኮሮና በፊት የነበራት ገፅታ የሚኖራት አይመስልም” የሚለውን ንግግሩን አስተውሉ። ፍላጎቱን ነው እየገለፀ ያለው። የሰዑዲያ አገዛዝ ይወድቃል እያለን ነው። አላህ አያሳካላችሁ። ደግሞም ሸሪዐ አፍራሽ አስተሳሰብ እያራመዳችሁ አይሳካላችሁም። ሸይኹል አልባኒን አላህ ይማራቸውና “ኢኽዋ ባለህበት ሂድ እንደተባለ ወታደር ነው” ይላሉ። ባሉበት እንጂ ወደፊት የለም። ከተመሰረቱ 92 አመታቸው። ለሙስሊሙ ኡማ ዋይታን አተረፉ እንጂ የትም አይደርሱም። **************************************** በነገራችን ላይ ይሄ ሸፍጠኛ አካሄዳቸው በተለያዩ አለማት የሚገኙ ኢኽዋኖችን የሚያመሳስላቸው በሽታ ነው። በቅርቡ ጣልያን በኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ክፉኛ ስትመታ የተለያዩ ሃገራት እርዳታ ሲያቀርቡላት ነበር። ከነዚህ ሃገራት ውስጥ አንዷ ግብፅ ናት። ይህንን የግብፅ እርዳታ ተከትሎ የአልጀዚራው ጋዜጠኛ ኢኽዋኒው አሕመድ መንሱር እንዲህ ብሎ በትዊተር አሰራጨ፡- “በአብዛኞቹ የግብፅ ክልሎች የኮሮና ቫይረስ ከመስፋፋቱና በህክምና ቁሳቁሶች እጥረት የተነሳ ሃኪሞች ቅሬታዎችን በሚያሰሙበት ጊዜ ሲሲ ግን ህዝቡ እየሞተ የህክምና እርዳታ የያዘ አውሮፕላን ለጣልያን በመላኩ ይጎረራል። … የግብፅ ህዝብ ከዚህ ቡድን ተገላግሎ ሃገሩን የሚመልስበትና ይህ ቀልድ የሚያከትምበት ጊዜ አልቀረበም?” ይላል። ከዚያስ? ቱርክ ለጣልያን እርዳታ ስትልክ ግን እንዲህ ነበር ያለው፡- “አውሮፓ ለጣልያን ጀርባዋን በሰጠችበትና የኖቭል ኮሮና ቫይረስን ብቻዋን እንድትጋፈጥ በተወችበት ጊዜ ቱርክ ግን በርካታ ቶን አስቸኳይ የህክምና ቁሳቁሶች እርዳታ ለጣልያን ልካለች። ይሄ የሚያረጋግጠው የኮሮና ቫይረስ የሃገራትን የፖለቲካ ካርታ፣ ቃል-ኪዳንና የርስ-በርስ ግንኙነቶችን እንደሚቀይር ነው። ከኮሮና ቫይረስ በኋላ የዓለም ቅርፅ ምን የሚሆን ይመስልሃል?” ይህ እንግዲህ የቱርክን እርዳታ ተከትሎ የአልጀዚራው “በድሩ ሑሴን” የሰጠው ሃሳብ ነው። በአንድ እራስ ሁለት ምላስ!! ሁሉንም ነገር በቡድናዊ መነፅር ነው የሚመለከቱት። እንጂ ቱርክ እራሷ የህክምና ቁሳቁስ እጥረት ገጥሟታል። የቫይረሱ ስርጭትም የግብፅን 24 እጥፍ ያክላል። ኢኽዋኒው ግን ሌሎች ላይ እንደሚዘምተው ቱርክ ላይ የሚዘምት እንዳይመስልህ። እነዚህ ሃይማኖትን ለቡድናዊ ትርፍና ለፖለቲካ ስልጣን መንጠላጠያ የሚጠቀሙ የደም ነጋዴዎች ናቸው። (የአሕመድ መንሱርን ንግግር ከስር ያገኙታል።)

photo content

photo content

ሰይጣናዊ መንገድ? በድምፅ ማስረጃዎች የተደገፈ። https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2387