en
Feedback
Sadat_Text_Posts

Sadat_Text_Posts

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Sadat_Text_Posts

Channel Sadat_Text_Posts (@sadattextposts) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 10 532 subscribers, ranking 18 731 in the News & Media category and 3 222 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 532 subscribers.

According to the latest data from 04 March, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -85 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 March, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

10 532
Subscribers
No data24 hours
-207 days
-8530 days
Posts Archive
ማን ነው የከፋው? አንዳንድ ሰዎች መውሊድ በኢስላም የሌለ የፈጠራ መንገድ ነው፡፡ መውሊድ ሸር ነው፡፡ ኸይር ቢሆን ኖሮ አላህ እና መልክተኛው ይደነግጉልን ነበር፡፡ ሰሃባዎች፣ ታቢእዬች፣ አትባኡ ታቢኢን፣ አራቱ አኢማዎች ፉቀሃዎች (አቡ ሀኒፋ፣ ኢማሙ ማሊክ፣ ኢማሙ ሻፊኢይ፣ ኢማሙ አሕመድ)፣ ሙሐዲሶች (ቡኻሪ፣ ሙስሊም፣ ነሳኢ፣ አቡ ዳውድ ኢብን ማጃእ…..) ያውቁት ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ ምርጦች አያውቁትም ሲባሉ እሺ አናከብርም ፈጠራ ስለሆነ ከማለት ፋንታ “በሳቸው መወለድ ሰይጣን እና ወሃቢ ብቻ ነው ያለቀሱት” ሲሉ እየተደመጡ፣ ሲፅፉም እየታዩ ነው፡፡ እውነታው በነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) መወለድ የመካ ሙሽሪኮች አልተቆጡም ነበር፡፡ የመካ አጋሪያን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ከነብይነት በፊት “ሙሐመዱል አሚን (ታማኙ ሙሐመድ)” እያሉ ነበር የሚጠሯቸው፡፡ ነብይ ሆነው “ህዝቦቼ ሆይ! ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ የለም በሉ ትድናላችሁ” ሲሉ የመጀመሪያው ጠላታቸው በሳቸው መወለድ አይደለም ሊቆጣ ተደስቶ የነበረው አቡ ለሃብ “እልም ያድርግህ ለዚህ ነው ወይ የሰበሰብከን” ሲል ግልፅ ጥላቻውን ይፋ አደረገ፡፡ ከዛም አጋሪያን ታማኙ ሙሐመድ እንዳላሉ “ድግምተኛ፣ እብድ፣ አባትና ልጅን የሚለያይ፣ ገጣሚ….” እያሉ ይሰድቧቸውና ስማቸውን ያጠፉ ጀመር፡፡ አለ የሚባል ሁሉ ፈተና ደረሰባቸው፡፡ ጥያቄ አለኝ ሰሃባዎች መውሊድን አላከበሩም ነበር ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ስለሚጠሉ ወይንም በሳቸው መወለድ ስለተናደዱና ስለበሸቁ ነበርን? በፍፁም፡፡ ሰሃባዎች ማለት በጣም ስነስርኣት ያላቸው ትውልድ ነበሩ፡፡ አደለም መልክተኛው በህይወት እያሉ መልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከሞቱም በኋላ የሳቸውን ትእዛዝ ታዘው ለሁለት አገር ድል በቅተዋል፡፡ ዛሬ ይህ ኡመት አላህ ካዘነለት ውጭ ሱና እንከተል እየተባለ ወደ ቢድኣ ይሮጣል፡፡ ይህም ኡማዋ ላለበት ውርደት ሰበብ ሆኗል፡፡ አላህ የሳቸውን ሱና አጥብቀው፣ የሱናን ባንዲራ ከፍ አድርጎው ለድል ከሚጎናፀፉት ያድርገን፡፡ ዛሬ ዛሬ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንደገለፁት “የማይሰሩትን የሚናገሩ፣ ያልታዘዙትን የሚሰሩ” ሰዎች ማየት የተለመደ ሆኗል፡፡ እንዲህ አይነት ሰዎችን ከቻልን በእጃችን እንድናስቆም፣ ካልቻልን በምላሳችን እንናገር፣ ካልቻልን በቀልባችን እንድንጠላ ነግረውናል፡፡ አላህ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) መወለዳቸውን ሳይሆን መላካቸውን ነው ፀጋ፣ ልገሳ ብሎ የጠራው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል لَقَدْ مَنَّ ٱللَّهُ عَلَى ٱلْمُؤْمِنِينَ إِذْ بَعَثَ فِيهِمْ رَسُولًا مِّنْ أَنفُسِهِمْ يَتْلُوا۟ عَلَيْهِمْ ءَايَٰتِهِۦ وَيُزَكِّيهِمْ وَيُعَلِّمُهُمُ ٱلْكِتَٰبَ وَٱلْحِكْمَةَ وَإِن كَانُوا۟ مِن قَبْلُ لَفِى ضَلَٰلٍ مُّبِينٍ አላህ በምእምናን ላይ ከጎሳቸው የኾነን፤ በእነርሱ ላይ አንቀጾቹን የሚያነብ፣ የሚጠራቸውም፣ መጽሐፍንና ጥበብን የሚያስተምራቸውም የኾነን መልእክተኛ በውስጣቸው በላከ ጊዜ፤ በእርግጥ ለገሰላቸው፡፡ እነርሱም ከዚያ በፊት በግልጽ ስህተት ውስጥ ነበሩ፡፡ እኛ እዚህ ዲን ላይ ያለን ድርሻ መከተል ብቻ ነው፡፡ መጨመር እና መቀነስ ለእሳት ይዳርጋል፡፡ አላህ ኢድ እና አረፋን እንድናከብር እንደ ደነገገልን መውሊድን እንድናከብር ቢያዘን እንሰራ ነበር፡፡ ነገር ግን የሃይማኖቱ ባለቤት አላህ አላዘዘንም እኛም ስነስርኣት ይዘን ሰይጣን የሚያመጣልንን ወጥመድ አንቀበልም ብለን ይሀው በሱና ላይ ሰሃባዎች በነበሩበት መንገድ ላይ ፀንተናል፡፡ አልሐምዱሊላህ፡፡ ሰይጣን በነብዩ ውዴታ ስም አላህ ያላዘዘውን እንዳያሰራን ወጥመዶቹን ጠንቅቀን እንወቅ፡፡ ነሷራች ኢሳን (አለይሂ ሰላም) ያመለኩት ወደውት እንጂ ጠልተውት አይደለም፡፡ ስለዚህ የአላህ ባሪያ የሆኑትን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ስንወድ አላህና መልክተኛው ያዘዙንን ብቻ በመታዘዝ ከከለከሉን በመራቅ ብቻና ብቻ ነው፡፡ አላህ እና መልክተኛው ያላዘዙንን ሰርተን “ለነብዩ ያለኝን ውዴታ ለመግለፅ ነው” ብንል ምክንያት አይሆነንም፡፡ አይደለም መልክተኛውን አላህን መውደዳችን እንኳን የሚረጋገጠው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) በመከተል ነው፡፡ መከተል ሲባል የሰሩትን በመስራት የከለከሉትንና ያልሰሩትን ከመስራት በመራቅ፡፡ የአላህ ሰላትና ሰላም በመልክተኛ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸውና ሐቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡ አሚን፡፡ https://t.me/SadatTextPosts

ቆት ብቻ ከሰፈሩ ፀሐፊዎች በተሻለ ምስክርነታቸው ሚዛን የሚደፋ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ሙዞፈር ፃድቅ እንኳ ቢሆን፣ አይደለም እንጂ መውሊድ በሱ የተጀመረ ቢሆን እንኳ ይሄ ከቢድዐነት አያወጣውም፡፡ ከነቢዩ- ﷺ - ህልፈት በኋላ ስድስት መቶ አመታት ዘግይቶ የሚጀመር አዲስ ፈሊጥ ጥመት እንጂ ፈፅሞ ፅድቅ ሊሆን አይችልም፡፡ እምነታችን ከቁርኣንና ከሐዲሥ የሚቀዳ እንጂ እንደ ክርስትና ማንም እየተነሳ አዳዲስ ነገሮችን የሚለጥፍበት አይደለም፡፡ Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) የቴሌግራም ቻናል። ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ። https://t.me/IbnuMunewor

መውሊድ በማን ተጀመረ? በሙዞፈር ወይስ በ“ፋጢሚያ” ሺዐ? ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ሰሞኑን አሕባሾች መውሊድን በማስተዋወቅ ላይ ተጠምደው እያየን ነው። ከሚያነሷቸው ነጥቦች አንዱ መውሊድ “ታላቅ ዓሊም፣ ተቂይ፣ ሷሊሕና ጀግና በነበሩት” ንጉስ ሙዞፈር ነው የተጀመረው የሚል ነው። ሙዞፈር የሞተው ከ812 አመት በፊት በ630 ሂጅሪያ ነው። ሰዎቹ ሙዞፈር ላይ ችክ የሚሉት እጅግ አፈንጋጭ በሆኑት “ፋጢሚያ” ሺዐዎች ነው የተጀመረው የሚለውን ለመሸሽ ነው። እርግጥ ነው መውሊድ የተጀመረው በሙዞፈር ነው ያሉ አሉ። ሌሎች ደግሞ የለም ትንሽ ቀደም ብሎ በሸይኽ ዑመር አልመላ (571 ሂ.) ነው የሚሉም አሉ። ሁለቱም ሃሳቦች ግን በማንም - እደግመዋለሁ - በማንም ቢጠቀሱ ፈፅሞ ስህተት ናቸው፡፡ ምክንያቱም ከዚያ በፊት እንደተጀመረ የሚያሳዩ ተጨባጭ ማስረጃዎች አሉና፡፡ ማስረጃ ከቀረበ በኋላ ለማንም ሙግት እጅ አንሰጥም፡፡ ለሐቅ እጅ ለሚሰጡ፣ ከመንጋዊ አስተሳሰብ አግልለው ህሊናቸውን ለሚያከብሩ ሰዎች ብቻ ማስረጃዎቹን አሰፍራለሁ። 1. ኢብኑል መእሙን (587 ሂ.):— በታሪክ ድርሳናት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ መውሊድ ተጠቅሶ የተገኘው በኢብኑል መእሙን ስራ ነው። የኢብኑል መእሙን አባት የ“ፋጢሚያ” ንጉስ ከፍተኛ ባለሟል ነበር። የታሪክ ፀሐፊው አልመቅሪዚ (845 ሂ.) ኢብኑል መእሙንን በማጣቀስ በ517 ሂጅሪያ የተካሄደውን መውሊድ አስመልክተው እንዲህ የሚል መረጃ አስፍረዋል፡- “የ‘ፊጢሚያ’ ገዢዎች በዓላትና ለተገዢዎቻቸው ነገሮችን ሰፋ የሚያደርጉባቸው እንዲሁም ችሮታ የሚበዘባቸው ዓውደ-አመታት” ካሉ በኋላ እንዲህ ይላሉ፡- ለፋጢሚያ ገዢዎች በአመቱ ውስጥ በዓላትና ዓውደ አመታት አሏቸው። እነሱም … የዓሹራእ ቀን፣ የነብዩ- ﷺ - ልደት ቀን፣ የዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ ረዲየላሁ ዐንሁ ልደት ቀን፣ የሐሰን የልደት ቀንና የሑሰይን የልደት ቀን (ሰላም በነሱ ላይ ይሁንና)፣ የፋጢመቱ ዘህራእ ዐለይሃ ሰላም ልደት ቀን፣ ስልጣን ላይ ያለው ገዢ የልደት ቀን፣ … የገዲር ዒድ (የሺዐዎች ነው)” እያሉ ይዘረዝራሉ። ከውስጣቸው የፋርስ መጁሳዎች፣ የሺዐና ከክርስትና ደግሞ እንደ ገና እና ትንሳኤ ያሉ በዓላት የተካተቱበት ሲሆን ባጠቃላይ 28 በዓላት ናቸው የተዘረዘሩት። [አልመዋዒዝ ወልኢዕቲባር ቢዚክሪል ኺጦጥ ወል ኣሣር፡ 1/436] መውሊድ ከምን አይነት በዓላት ጋር እንደተጀመረ ተመልከቱ። በሌላ ኪታባቸው ላይም “በረቢዐል አወል ላይ (የ“ፋጢሚዮቹ” ንጉስ) ሌሊት ላይ በጎዳናዎችና መንገዶች ላይ ጧፎች እንዲበሩ ያስገድድ ነበር” ይላሉ። [ኢቲዒዙል ሑነፋእ፡ 2/48] ሌላ ቦታ ደግሞ “ረቢዐል አወል ላይ የነብዩን - ﷺ - ክቡር ልደት መፈፀም ብሄራዊ ልምድ ሆኖ ቀጠለ” ይላል። [ኢቲዒዙል ሑነፋእ፡ 3/101] ልብ በሉ! ይህንን መረጃ የሰጠን ኢብኑል መእሙን የሞተው መውሊድን ጀመረ የሚባለው ንጉስ ሙዞፈር ገና በተሾመ በአመቱ ነው፡፡ እያስተዋላችሁ!! 2. ኢብኑ ጡወይር (617 ሂ.):— ሌላኛው መውሊድን ከ“ፋጢሚዮች” ጋር በማያያዝ የጠቀሰው ጥንታዊ የታሪክ ፀሐፊ ኢብኑ ጡወይር ነው። ኢብኑ ጡወይር ለነዚህ “ለፋጢሚያ” መንግስት ፀሐፊ ሆኖ አገልግሏል። ኋላ በሶላሑዲን አልአዩቢ ሲደመሰሱም በአይኑ ተመልክቷል። በዚህኛው ስርኣትም ውስጥ ዳግም አገልግሏል። በ“ፋጢሚያዎች” መንግስት ስለሚዘጋጀው መውሊድና ስለተትረፈረፈ ምግቡ “ኑዝሀቱል ሙቅለተይን ፊ አኽባሪ ደውለተይን” በተባለ ኪታቡ ላይ በዝርዝር አትቷል። “ማን ያውራ የነበረ፣ ማን ያርዳ የቀበረ” ይላል ያገራችን ሰው። ለናሙና ያክል ቀንጨብ ላድርገው፡- ذكر جلوس الخليفة في الموالد الستة في تواريخ مختلفة، وما يطلق فيها، وهي مولد النبي صلى الله عليه وسلم، ومولد أمير المؤمنين علي بن أبي طالب، ومولد فاطمة عليها السلام، ومولد الحسن، ومولد الحسين عليهما السلام، ومولد الخليفة الحاضر “ኸሊፋው በተለያዩ ጊዜያት በስድስቱ መውሊዶች ላይ የሚያደርጋቸውን መሰየምና ምን ተብለው እንደሚታወቁ ማውሳት፡- እነሱም የነብዩ- ﷺ - መውሊድ፣ የአሚረል ሙእሚኒን ዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ መውሊድ፣ የፋጢማ ዐለይሃ ሰላም መውሊድ፣ የሐሰን መውሊድ፣ የሑሰይን - ዐለይሂመ ሰላም - መውሊድና የዘመኑ ኸሊፋ መውሊድ ናቸው፡፡ …” [ኑዝሀቱል ሙቅለተይን፡ 217-219] 3. አሕመድ ብኑ ዐሊይ አልቀልቀሸንዲ (821 ሂ.):— ስለ “ፋጢሚያ” መሪዎች ጉባዔ ሲያወሩ “ሶስተኛው ጉባዔ በረቢዐል አወል ወር 12ኛ ቀን ላይ በነብዩ - ﷺ - መውሊድ ላይ የሚኖረው ጉባዔ ነው” ካሉ በኋላ ዝርዝር አፈፃፀሙን ይተርካሉ፡፡ [ሱብሑል አዕሻ፡ 3/576] ስናጠቃልል የመውሊድ በዓል ጀማሪዎች “ፋጢሚያ” ሺዐዎች እንደነበሩ ለጥርጣሬ ቀዳዳ የማይሰጡ መረጃዎች አሉን ማለት ነው፡፡ ልብ በሉ! የመጨረሻው የ“ፋጢሚዮች” ንጉስ አልዓዲድ ሊዲናህ የሞተው በ 567 ሂጅሪያ ነው፡፡ ሱፍዮች “መውሊድ ጀመረ” የሚሉት ሙዞፈር የተሾመው ደግሞ ከ 19 ዓመታት በኋላ በ586 ሂ. ነው፡፡ ይህንን ተጨባጭ ታሪካዊ መረጃ እያየ “አይኔን ግንባር ያርገው” የሚል ካለ ሰርቲፋይድ ቂላቂል ነው፡፡ መውሊድ በሺዐዎች እንደተጀመረ የሚጠቁሙ ግልፅ ማስረጃዎች እየቀረቡ እያዩ “እከሌ እንዲህ ብለዋል” “እንቶኔ እንዲህ ብለዋል” እያሉ ነገር መዘብዘብ እራስን መሸወድ ብቻ ነው፡፡ “ሙዞፈር ነው የጀመረው” ያሉት እንደ ሲዩጢ ያሉ የኋለኛው ዘመን ሰዎች ከመሆናቸውም በላይ ያጣቀሱት ተጨባጭ ማስረጃ የለም፡፡ በነገራችን ላይ እነዚህ መውሊድ በሙዞፈር ነው የተጀመረው የሚሉ አካላት ኢብኑ ከሢርን ሲያጣቅሱ ማየት የተለመደ ነው፡፡ ኢብኑ ከሢር የሙዞፈርን መውሊድ ከመጥቀሳቸው ውጭ “ጀማሪ ነው” አላሉም፡፡ መቅሪዚ እንደጠቀሱት እነዚህ የሺዐዎቹ መውሊዶች ኋላ ላይ ለተወሰኑ ጊዜያት ተቋርጠው ነበር፡፡ [አልመዋዒዝ ወልኢዕቲባር፡ 1/432] ኋላ ላይ በተተካው የ“ፊጢሚዮቹ” ንጉስ አልኣሚር ቢአሕካሚላህ (524 ሂ.) ነው የተጀመሩት፡፡ ልብ በሉ! ይህ ዳግም የተጀመረው መውሊድ እራሱ ከሙዞፈር መውሊድ በዓል ብቻ ሳይሆን ከራሱ ሙዞፈር መወለድም የቀደመ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ሱፍዮች መውሊድን ጀመረ የሚሉትን ሙዞፈርን ቅዱስ አድርገው የሚጠቅሱት ወይ ታማኞች ስላልሆኑ ነው፡፡ ወይ ደግሞ በሰውየው ላይ የቀረቡ ሂሶችን ያልተመለከቱ ናቸው፡፡ አብዛኞቹ የሚያደርጉት ለገበያቸው የሚሆናቸውን እየመረጡ ማቅረብ ነው፡፡ ንጉሱ በከፊል የታሪክ ፀሐፊዎች ከመወደሱም ጋር የሰላ ሂስ የሰነዘሩበትም አሉ፡፡ አንድ ምሳሌ ልጥቀስ፡- ያቁት አልሐመዊ ይባላሉ፡፡ በ626 ሂ. የሞቱ ታዋቂ የታሪክ ምሁር ናቸው፡፡ ሙዞፈርን አስመልክተው እንዲህ ይላሉ፡- “የዚህ ሰውየ ባህሪ እርስ በርሱ የሚቃረን ነው፡፡ እሱ ሲበዛ በዳይ፣ ህዝቦቹ ላይ ጨካኝ እንዲሁም አግባብ ባልሆነ መልኩ ገንዘቦችን የሚወስድ ነበር፡፡ ይህ ከመሆኑ ጋር ለድሃዎች የሚቸርና ለእንግዶች በብዛት የሚሰድቅ ነበር፡፡ እጅግ በርካታ ገንዘቦችን አፍስሶ ከከሃዲዎች እጅ ምርኮኞችን ነፃ ያወጣ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ባለቅኔው እንዲህ ይላል፡- ‘ልክ እንደዚያች ወጥ ረገጥ በብልቷ ነግዳ ለበጎ ስራ የምትሮጥ መስሚያ ካለሽ ወዮ ላንቺ! ምፅዋትሽ ይቅር ይልቅ አትዘሙቺ፡፡’ ” [ሙዕጀሙዑል ቡልዳን፡ 1/138] ያቁት አልሐመዊ ከሙዞፈር ጋር አንድ ዘመን የኖሩ በመሆናቸው ዘግይተው መጥተው ስለ ንጉሱ አድና

photo content

photo content

ሰኞ እና መውሊድ? መውሊድ አክባሪዎች “ነብዩ ﷺ ሰኞን የተወለዱበት ቀን ስለሆነ ፆመዋል፡፡ ይህም መውሊድን (ልደታቸውን) ለማክበር ማስረጃ ነው፡፡” ይላሉ፡፡ በአላህ ፍቃድ እና እገዛ ማስረጃ ብለው ያቀረቡት፣ ማስረጃ መሆን እንደማይችል በሰፊው እንየው፡፡ ነብዩ (ﷺ) ሰኞን ቀን እንደሚፆሙ በትክክለኛ ሀዲሶች ተረጋግጧል፡፡ የሚከተሉትን ሀዲሶች እንይ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ሰኞን ለምን እንደሚፆሙ ተጠየቁ፣ እሳቸውም “በዛ ቀን ተወለድኩ፣ እናም መለኮታዊ ራእይም በዛው ቀን መጣልኝ” ሰሂህ ሙስሊም 1162 በሌላ ዘገባ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ አሉ “ስራዎች ሰኞ እና ሀሙስ (ወደ አላህ) ይወጣሉ፡፡ ስራዬ ፆመኛ ሆኜ እንዲቀርብልኝ እፈልጋለሁ” ቲርሚዚ 747 ከነዚህ ሁለት ሀዲሶች የምንማራቸው ትምህርቶች እንደሚከተለው ይቀርባሉ 1.) የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ሰኞን የፆሙት ለሶስት ምክንያቶች ነው a. የተወለዱበት ቀን ስለሆነ፣ b. ቁርኣን ለእሳቸው የወረደበት ቀን ነው፣ c. ስራዎችም ወደ አላህ የሚወጡበት ቀን ስለሆነ እና እሳቸው ስራቸው ፆመኛ ሆነው እንዲወጣላቸው ስለፈለጉ፡፡ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) የፆሙት ከላይ በተጠቀሱት ሶስት ምክንያቶች እንጂ ሰኞን ስለተወለዱበት ብቻ አልነበረም፡፡ 2.) ከዚህ ሀዲስ ሰሃባዎች አመት ጠብቀው በረቢአል አወል የነብዩን (ﷺ) ልደት ማክበርን አልተረዱም፡፡ ሰሃባዎች ደግሞ ለኢስላም በጣም ቅርብ፣ ኢስላምን ጠንቅቀው አዋቂዎች እና ኢስላምን ከማንም በላይ የተረዱ ከመሆናቸውም ጋር “መውሊድ” የሚባል በአል አያከብሩም ነበር፡፡ 3.) ታቢኢን በመባል የሚታወቁት የሰሃባ ተማሪዎች ከዚህ ሀዲስ መውሊድ የሚባል በአል አለ ብለው አልተረዱም፡፡ 4.) አራቱ ታላላቅ የፊቂህ ኢማሞች አቡ ሀኒፋ፣ ኢማሙ ማሊክ፣ ኢማሙ ሻፊኢ እና ኢማሙ አህመድ ይህን ሀዲስ እያወቁ፣ ሀዲሱን መውሊድ (የነብዩን ልደት) ማክበር ይቻላል ለሚል ማስረጃ አልተጠቀሙትም ፡፡ 5.) በዚህ ሀዲስ የተገደበው አምልኮ ፆም ነው፡፡ ስለዚህ ፁሙ፡፡ ከዚህም አትለፉ፡፡ ዲኑ ገር ነው፡፡ ነብዩ (ﷺ) የሰሩትን እንስራ ያልሰሩትን አንስራ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ይገርማሉ ሀዲስን ትርጉሙን ያዛባሉ፣ ይጠመዝዙታል ለምን ሲባል ቢድኣን ለማንገስ፡፡ እኛ ከሰሃባዎች በላይ አላህን አዋቂ፣ ፈሪም፣ አላህ ዘንድ እውነተኞችም አይደለንም፡፡ እኛ ከሰሃባዎች በላይ ነብዩ (ﷺ) አንወድም፣ አናከብርም፣ መስዋትም አልሆንም፡፡ ስለዚህ አደብ አድርገን እንቀመጥ፡፡ እንዲህ አይነት ጥፋቶችን ስናጋልጥ እናንተ በእድሜ ከጠገቡት ታላላቅ ኡለማዎች፣ ሙፍቲዎች፣ ዶክተሮች፣ ኡስታዞች ትበልጣላችሁን? ሲሉ ይጠይቃሉ መልሱም ቀላል ነው እነዚህ እናንተ ኡለማ ብላችሁ የምትከተሏቸው ሶዎች ከሰሃባዎች አላህን በመፍራት፣ አላህ እና መልክተኛውን በመውደድ፣ በእውቀት ይበልጣሉን? አይበልጡም ስለዚህ ሙፍቲም፣ ዶክተርም፣ ኡስታዝም፣ ሙነሺድም፣ ድቤ መቼም አርፈው ይቀመጡ፣ ዲን አይበጥብጡ፡፡ ኡማውን አይከፋፍሉ፡፡ ሺርክ እና ቢድኣን አያንግሱ፡፡ አላህ ከሺርክ፣ ከቢድኣ፣ ከዘረኝነት የፀዳ እውነተኛ አንድነት ይስጠን፡፡ https://t.me/SadatTextPosts

photo content

photo content

photo content

አሹራ የሚሆነው ቀን ቅዳሜ ነው። የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የሚቀጥለው አመት ከደረስኩኝ 9ኛውንም ቀን እፆማለሁ ብለው ነበር። ስለዚህ ጁመአ እና ቅዳሜን በመፆም የአላህን ምህረት እንከ
አሹራ የሚሆነው ቀን ቅዳሜ ነው። የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የሚቀጥለው አመት ከደረስኩኝ 9ኛውንም ቀን እፆማለሁ ብለው ነበር። ስለዚህ ጁመአ እና ቅዳሜን በመፆም የአላህን ምህረት እንከጅል።

አንድ ሴት አግብታ የፈታች ስለሆነች፣ ልጆች ስላላት፣ አንድን ወንድ በእድሜ ስለበለጠችው አትገባም አይባልም ፡፡ እንዲህ አይነቷ ሴትም ነውረኛ አትባልም፡፡ ብትባል ኖሮ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያገቧት ኸዲጃ የሴቶች ቁንጮ፣ እሷንም ጨምሮ ሌሎች ሚስቶቻቸው የምእመናን እናቶች ነውረኛ በተባሉ ነበር፡፡ እንዲህ አይነቷን ሴት ያገባ ነውር እንደሰራ ሊታይ አይገባም፡፡ ቢባል ኖሮ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያገቧቸው ሴቶች ከአኢሻ ውጭ ሁሉም ባል የሞተባቸው፣ አግብተው የፈቱ ነበሩ፡፡ ውዱ ነብይ ከነ ሚስቶቻቸው ታላቅ ተምሳሌቶቻችን ናቸው፡፡

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

ዘካተል ፊጥር ዘካተል ፊጥር ማለት ረመዳን ወር ተፁሞ ሊፈጠር 2 ቀን ሲቀረው አንስቶ የኢድ ሰላት እስኪሰገድ ድረስ ከተምር፣ ከገብስ ሀገሪቱ ላይ ከሚመገቡት ምግብ አንድ ቁና ለሚስኪን የሚሰጥ የምግብ አይነት ነው። መለኮታዊ ራእይ የሚወርድላቸው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በሚበላ ምግብ አውጥተው አሳይተውናል። የቤቱ አባወራ በእርሱ ስር የሚተዳደሩ ሰዎችን ቆጥሮ ሊያወጣላቸው ይገባል። የቤት ሰራተኛ ደሞዝተኛ ስለሆነች የራሷን እራሷ ነው ማውጣት ያለባት። እኛ የሳቸውን ፈለግ እንከተል። የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ይህንን አምልኮ በመፈፀም ወደ አላህ እንቃረብ። አላህ መጨረሻችንን ያሳምርልን። ፅናት ይስጠን።

photo content