Bible verses
Open in Telegram
" ቃልህ ለጕሮሮዬ ጣፋጭ ነው፤ ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ።" (መዝሙረ ዳዊት 119:103) Bible_verses
Show more1 381
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 381
1ኛ ዜና መዋዕል 4
10፤ ያቤጽም፦ እባክህ፥ መባረክን ባርከኝ፥ አገሬንም አስፋው፤ እጅህም ከእኔ ጋር ትሁን፤ እንዳያሳዝነኝም ከክፋት ጠብቀኝ፡ ብሎ የእስራኤልን አምላክ ጠራ፤ እግዚአብሔርም የለመነውን ሰጠው።
1 381
ኦሪት ዘዳግም 33
29፤ እስራኤል ሆይ፥ ምስጉን ነህ፤
በእግዚአብሔር የዳነ ሕዝብ እንደ አንተ ማን ነው?
እርሱ የረድኤትህ ጋሻ፥
የከፍተኛነትህም ሰይፍ ነው።
ጠላቶችህም ይገዙልሃል፤
አንተም ከፍታቸውን ትረግጣለህ።
1 381
ትንቢተ ኢሳይያስ 46:9 ፤ እኔ አምላክ ነኝና፥ ሌላም የለምና የቀድሞውን የጥንቱን ነገር አስቡ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ እንደ እኔም ያለ ማንም የለም።
1 381
ትንቢተ ሆሴዕ 14
5፤ ለእስራኤልም እንደ ጠል እሆነዋለሁ፤ እንደ አበባም ያብባል፥ እንደ ሊባኖስም ሥሩን ይሰድዳል።
6፤ ቅርንጫፎቹም ይዘረጋሉ፥ ውበቱም እንደ ወይራ፥ ሽታውም እንደ ሊባኖስ ይሆናል።
1 381
2ኛ ሳሙኤል 3
1፤ በሳኦል ቤትና በዳዊት ቤት መካከል ብዙ ዘመን ጦርነት ሆነ፤ የዳዊት ቤት እየበረታ፥ የሳኦል ቤት ግን እየደከመ የሚሄድ ሆነ።
1 381
1ኛ ሳሙኤል 30
6፤ ስለ ወንዶችና ስለ ሴቶች ልጆቻቸው የሕዝቡ ሁሉ ልብ ተቈጥቶ ነበርና ሕዝቡ ሊወግሩት ስለ ተናገሩ ዳዊት እጅግ ተጨነቀ፤ ዳዊት ግን በአምላኩ በእግዚአብሔር ልቡን አበረታ።
1 381
የሐዋርያት ሥራ 27
24፤ እርሱም፦ ጳውሎስ ሆይ፥ አትፍራ፤ በቄሣር ፊት ልትቆም ይገባሃል፤ እነሆም፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር የሚሄዱትን ሁሉ ሰጥቶሃል፡ አለኝ።
25፤ ስለዚህ እናንተ ሰዎች ሆይ፥ አይዞአችሁ፤ እንደ ተናገረኝ እንዲሁ እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና።
1 381
የሐዋርያት ሥራ 4
16፤ የታወቀ ምልክት በእነርሱ እጅ እንደ ተደረገ በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ ሁሉ ተገልጦአልና፥ እንሸሽገው ዘንድ አንችልም፤
1 381
ትንቢተ ኢሳይያስ 46
9፤ እኔ አምላክ ነኝና፥ ሌላም የለምና የቀድሞውን የጥንቱን ነገር አስቡ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ እንደ እኔም ያለ ማንም የለም።
10፤ በመጀመሪያ መጨረሻውን፥ ከጥንትም ያልተደረገውን እነግራለሁ፤ ምክሬ ትጸናለች ፈቃዴንም ሁሉ እፈጽማለሁ እላለሁ።
1 381
ኦሪት ዘፍጥረት 32
10፤ ለባሪያህ ከሠራኸው ከምሕረትህና ከእውነትህም ሁሉ ትንሽ ስንኳ የማይገባኝ ነኝ፤ በትሬን ብቻ ይዤ ይህን ዮርዳኖስን ተሻግሬ ነበርና፥ አሁን ግን የሁለት ክፍል ሠራዊት ሆንሁ።
1 381
የዮሐንስ ወንጌል 15
13፤ ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም።
ኢየሱስ ብቻውን ከፍሎታል
Happy Easter ❤️🙏
1 381
መዝሙረ ዳዊት 40
1፤ ቆይቼ እግዚአብሔር ደጅ ጠናሁት፥
እርሱም ዘንበል አለልኝ ጩኽቴንም ሰማኝ።
2፤ ከጥፋት ጕድጓድ ከረግረግም ጭቃ አወጣኝ፥. እግሮቼንም በድንጋይ ላይ አቆማቸው፥ አረማመዴንም አጸና።
3፤ አዲስ ዝማሬን ለአምላካችን ምስጋና በአፌ ጨመረ፤
ብዙዎች ያያሉ ይፈሩማል፥
በእግዚአብሔርም ይታመናሉ።
