1 264
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
June '24
June '240
in 0 channels
May '24
+2
in 0 channels
Get PRO
April '24
+1
in 0 channels
Get PRO
March '24
+4
in 0 channels
Get PRO
February '24
+2
in 0 channels
Get PRO
January '24
+3
in 0 channels
Get PRO
December '23
+3
in 0 channels
Get PRO
November '23
+1
in 0 channels
Get PRO
October '23
+2
in 0 channels
Get PRO
September '23
+2
in 0 channels
Get PRO
August '23
+15
in 0 channels
Get PRO
July '23
+9
in 0 channels
Get PRO
June '23
+16
in 0 channels
Get PRO
May '23
+8
in 0 channels
Get PRO
April '23
+9
in 0 channels
Get PRO
March '23
+13
in 0 channels
Get PRO
February '23
+4
in 0 channels
Get PRO
January '23
+12
in 0 channels
Get PRO
December '22
+12
in 0 channels
Get PRO
November '22
+10
in 0 channels
Get PRO
October '22
+14
in 0 channels
Get PRO
September '22
+13
in 0 channels
Get PRO
August '22
+16
in 0 channels
Get PRO
July '22
+340
in 0 channels
Get PRO
June '22
+36
in 0 channels
Get PRO
May '22
+511
in 0 channels
Get PRO
April '22
+599
in 0 channels
Get PRO
March '22
+11
in 0 channels
Get PRO
February '22
+16
in 0 channels
Get PRO
January '22
+184
in 0 channels
Get PRO
December '21
+40
in 0 channels
Get PRO
November '21
+66
in 0 channels
Get PRO
October '21
+15
in 0 channels
Get PRO
September '21
+16
in 0 channels
Get PRO
August '21
+190
in 0 channels
Get PRO
July '21
+369
in 0 channels
Get PRO
June '21
+11
in 0 channels
Get PRO
May '21
+25
in 0 channels
Get PRO
April '21
+309
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 01 June | 0 |
Channel Posts
|
|
በአላህ ፍቃድ ከነገ ሰኞ ጀምረን ፥ እስካሁን ሰለ ረመዳን ስለተዋወስናቸው ጉዳዬች ፤ ጥያቄዎችን እየተጠያየቅን፣ እራሳችንን እየፈተሽን፣ ስለ ረመዳን እንተዋወሳለን።
ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ወዳጅ፣ ጓደኞቻችሁን፣ ጋብዟቸው።
https://t.me/Abu_Umair2
| 2 | ስሁር፦
ስሁር ንጋት አከባቢ ከፈጅር አዛን አስቀድሞ የሚበላ ማንኛውም ሀላል ምግብ ወይም የሚጠጣ መጠጥ ነው። አንድ አማኝ ስሁርን ከተመገበ ከነብያችን (ሰ•ዐ•ወ) ጠንካራ ሱናዎች መሀል አንዱን ፈፅሟል ማለት ነው።
ነቢዩ (ሰ•ዐ•ወ) እንዲህ አሉ፦
* "ሱህርን ከፈጅር በፊት ተመገቡ በርሱ ላይ በረካ አለ፡፡" [ሙተፈቁን አለይህ]
* "በኛ እና በመፀሀፍት ባልተቤቶች ፆም መሀከል ያለው መለያ ፆም ነው።" [ሙስሊም]
* "በአንድ ጉንጭ ዉሃም እንኳ ቢሆን ተሰሃሩ (ስሁርን ተመገቡ)።" [አቡ ዳውድ]
* በስሁር ወቅት ተምር መመገብ ለአንድ አማኝ የተወደደ እና በላጭ የሆነ ነገር ነወ። .. "ለሙዕሚን በላጩ ስሁር ተምር ነው።" [አስ-ሰሂሃ 562]
ዘይድ ኢብን ሳቢት "ከመልዕክተኛው (ሰ•ዐ•ወ) ጋር ሱህር ከተመገብን በኋላ ፈጅር ሰገድን” ብለው ሲናገሩ ፤ "በመካከላቸው የነበረው ወቅት ምን ያህል ነበር?” ብለው ጠየቋቸው፡፡ እሳቸውም “ሀምሳ የቁርአን አንቀፆች የሚያስነበብ ወቅት ነበር"አሉ፡፡ [ሙተፈቁን አለይህ]
------------------
ኢፍጣር
“ፊጥር” የሚለው ቃል "ፈጠረ" ማለትም "ገደፈ" ከሚለው ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን ሸሪዐዊ ትርጉሙ “ጾም መግደፍ" ማለት ነው። የፊጥር ብዙ ቁጥር “ፉጡር” ነው። አንድ ፆመኛ ሰው አፉ ውስጥ አስገብቶ ትንሽ ምግብ ቢመገብ አልያ ትንሽ ውሃ ቢጎነጭ ጾሙን አፈጠረ (ገደፈ) ይባላል።
ነብዩ (ሰ•ዐ•ወ) በምን ያፈጥሩ ነበር ?
* አነስ (ረ•ዐ) ባስተላለፉት ሀዲስ ላይ ነብዩ (ሰ•ዐ•ወ) ካገኙ በተምር እሸት ፥ ተምር ካላገኙ ደግሞ ውሃ በመጎንጨት ያፈጥሩ ነበር፡፡ ( አቡዳውድ 2356 )
በረመዳን ለጉዞ የወጣ አንድ ሰው ከፈለገ የመፆም ከፈለገም የማፍጠር ምርጫ አለው። ነብዩ (ሰ•ዐ•ወ) ይህንን አስመልክቶ "ከፈለግክ ፁም። ከፈለግክ አፍጥር" ብለዋል።
* ሙሳፊር መፆሙ የማይከብደው ከሆነ በጉዞው ላይ መፆሙ በላጭ ነው። ነብዩ (ሰ•ዐ•ወ) በጉዞ ላይ የፆሙበት ተጨባጭ መረጃ አለና። የብዙሃን ዑለማዕ አቋምም ይሄው ነው።
* መፆሙ የሚከብደው ከሆነ ግን ባይፆም ይመረጣል።
* መፆሙ የሚከብደው ከሆነ እና በእርሱ ላይ ጉዳት የሚያደርስበት ከሆነ ግን መፆሙ በእርሱ ላይ ሐራም ነው። ነብዩ (ሰ•ዐ•ወ) "በጉዞ ላይ መፆም ከበጎ ስራ አይደለም" ማለታቸው እዚህ ላይ ይመጣል።
ከሁሉም በላይ አላህ አዋቂ ነው።
||
✍️ አቡ ዑመይር
የቴሌግራም Channel፦ https://t.me/Abu_Umair2 | 306 |
| 3 | አንዳንዴ አጋዥ መሆን ቀርቶ የሰውን እጅ የሚያስፈልገን ቀን ይመጣል .....
ሂራ , አራይቫል, ኡሚ, አዳል ኢትዮጵያ, የሎሚ ሜዳ አብሮ አደግ ..... ትንሹ አቡኪ በዚህ ትንሽ እድሜው ለሰዎች ለመድረስ የተሳተፈባቸው የበጎ አድራጎት ማህበራት ናቸው
ዛሬ ቀን ጥሎት በተራው እሱ የእኛን እርዳታ ፈላጊ ሆኖዋል በገጠመው የሽንት ትቦ ህመም እና የነርቭ ችግር በጳውሎስ ሆስፒታል ህክምናው እየተከታተለ ቢቆይም ከእነሱ አቅም በላይ ሆኖ ወደ ውጪ ሄዶ እንዲታከም ወስነዋል ነገር ግን ለህክምናው የሚያስፈልገው ገንዘብ እንኳን በቤተሰቡ በሰፈራችን እንኳን የማይሸፈን ሆኖብናል ከአላህ በታች እንድታግዙት በአላህ ስም ልጠይቃችሁ🤲🤲
1000481402585 አቡበከር ኸይረዲን
151196578 አቢሲኒያ ባንክ | 221 |
| 4 | 📚 كتاب:- فائدة من شهر رجب
ادرس ١
(10.1 MB) تخزين 📁
ሰለረጀብ ወር ወሳኝ ነጥቦች ክፍል አንድ ኡስታዝ ቢላል (አቡ ፈውዛን)
https://t.me/Abu_Umair2 | 290 |
| 5 | مركز الشيباني لتحفيظ القرآن الكريم والتربية الإسلاميـة
መርከዝ ሸይባኒ አዳሪ የቁርዐን ሂፍዝ እና መሰረታዊ የሸሪዓ እውቀቶች ማዕከል
ወንድም እና እህቶች መርከዝ ሸይባኒ የቁርዐን እና መሰረታዊ የሸሪዓ እውቀቶች ማዕከል በተለያዩ ቦታዎች ላይ ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህረት አይነቶች በተመላላሽ ብሎም በአዳሪ ሲያስተምር እውቀት ሲያስጨብጥ አመታቶች ተቆጥረዋል። አሁን ላይ ይህ ኢስላማዊ ማዕከል በተለያዩ ቦታዎች ሲሰጣቸው የነበረውን የቁርአን እና የሸሪዐ ትምህርት እውቀቶችን በአንድ አካባቢ ለመስጠት በማሰብ አዲስ አበባ፣ አለም ባንክ ደብረ አባይ ሰፈር ከነጃሺ መስጂድ ዝቅ ብሎ መድረሳ አቋቁሞ ትምህርት መስጠት ጀምሮ ተማሪዎችን እየተቀበለ ስለሚገኝ ሁላችሁም ሙስሊሞች ተጋብዛችኋል።
ማዕከሉ በትኩረት የሚሰጥባቸው ትምህርቶች…
* ቃዒደቱ ኑራኒያ
* ቁርአን በነዝር
* ቁርአን በሂፍዝ
* ቁርኣን ሙራጀዐ
* የኪታብ ትምህርቶች
ትምህርት የሚሰጥባቸው ፈረቃዎች
* በአዳር
* በተመላላሽ
* ከፈጅር ቡሀላ
* ከዐስር እስከ ኢሻ
ማሳሰቢያ፦ ሁሉም ፕሮግራም ሁሉንም ማህበረሰብ የሚያካትት በመሆኑ ከአዳሪ ተማሪዎች ውጭ ያለው ፕሮግራም ፆታ ወይም እድሜ አይለይም።
አድራሻ፦ አለም ባንክ ደብረ አባይ ሰፈር ከነጃሺ መስጂድ ዝቅ ብሎ
ስልክ ቁጥር፦ 0911356686
0940133817
0711101414
ቴሌግራም @merkez_sheybani | 165 |
| 6 | * በየቀኑ ኢስላማዊ ጥያቄዎች ይለቀቅበታል
* ሁሌም የቁርአን ቲላዋህ ግብዣ አለው
* ስለ ኢስላም የተለያዩ ፅሁፎች ይለቀቅበታል
* ስለ ሙስሊሞች ግለ ታሪክ ያጋራል
* አስላም እና ሳይንስን ይዳስሳል
* የሙስሊም ወንድሞች እና እህቶች ፅሁፍን ያጋራል
* ጠቃሚ ኢስላማዊ አፖችን ያስተዋውቃል ያጋራል
* የረሱል (ሰ•ዐ•ወ) ወርቃማ ንግግሮችን ይለቃል
* የሰሃቦችን ታሪክ ይተርካል
ወደ ጌታህ መንገድ በብልሃትና በመልካም ግሳጼ (በለዘብታ ቃል) ጥራ፡፡ (ሱረቱል ነህል 125)
ተቀላቀሉ ትጠቀሙበታላቹ https://t.me/Abu_Umair2 | 168 |
| 7 | No text... | 194 |
| 8 | https://vm.tiktok.com/ZM2tvG73U/ | 192 |
| 9 | No text... | 182 |
| 10 | 🔷 ከኡድሒያ ህግጋቶች
– ሸሪዓዊ ብይኑ
➲ ኡድሒያ ከፊል ዑለሞች እንደ አቡ ሐኒፋ፣ አል አውዛዒ፣ ለይስ ኢብኑ ሰዕድና ሌሎችም አቅም ባለው ሰው ላይ ግዴታ (ዋጂብ) ነው ሲሉ ሌሎች ጁሙሁሮች ደግሞ ሱና ሙአከድ ነው ይላሉ። ነገር ግን አንድ ሰው በኡድሒያ የሚገኘውን አጅር ዝም ብሎ ሊያስመልጥ አይገባም።
– የሚታረደው ከብት አይነትና እድሜው
– ለኡድሒያ የሚታረደው የከብት አይነት
– ግመል ➡️ 5 አመት የሞላውና ከዛበላይ
– በሬ ➡️ 2 አመት የሞላውና ከዛ በላይ
– ፍየል ➡️ 1 አመት የሞላውና ከዛ በላይ
– በግ ➡️ 6 ወር የሞላውና ከዛ በላይ መሆን ይኖርበታል።
↪️ ለኡድሒያ እንዳይሆን የሚከለክሉ አይቦች
➧ እውርነቱ ግልፅ የሆነ (ማየት የማይችል)
➧ ግልፅ የሆነ በሽታ ያለበት
➧ እግሩ ላይ ችግር ያለበት (ከከብቶች ጋር እኩል መሄድ የማይችል የሚያነክስ)
➧ የማይድን ስብራት ያለበት
➽ በሚታረድበት ጊዜ
➻ በሚያርድበት ጊዜ በግራ ጉኑ ማስተኛት ይኖርበታል። ኢማሙ ነወዊ በዚህ ላይ የዑለማዎች ስምምነት ይጠቅሳሉ። ወደ ቂብላ አዙሮ ማስተኛቱ የተወደደ ለመሆኑ አራቱም አኢማዎች ይስማማሉ ከሶሓቦች ዐብዱላህ ኢብኑ ዑመር ይገኝበታል። ከዛ ቢስሚላሂ አላሁ አክበር , አላሁመ ሚንከ ወለከ, ይልና ማረድ ሲጀምር ቢስሚላሂ አላሁመ ተቀበል ሚኒ ወሚን አህሊ በይቲ ይላል። የሚያርድበት ቢላዋ ስል መሆን ይኖርበታል። የሚታረደው ከብት እንዳይሰቃይ ቶሎ ማረድ ይኖርበታል። በሚታረድበት ቦታ ነው መጣል ያለበት እንጂ ጥሎ እግሮቹን ካሰሩ በኋላ እየጎተቱ ማሰቃየት አይፈቀድም።
➪ በተቻለ መጠን እላይ ከተጠቀሱት ነውሮች በተጨማሪ ምንም ነውር የሌለበት ከብት ማረድ ይኖርበታል።
– የሚታረደው ከብት መልክ
➤ ከላይ እንዳየነው ከኡድሒያ የሚከለክሉ ነውሮች አራት ናቸው። ከዛ ውጪ ኡድሒያን ወድቅ የሚያደርግ ወይም አጅር የሚያሳጣ ነውር የለም። እንደ ጥርስ መሰበርና ጆሮ በተወሰነ መልኩ መቆረጥ ወይም ጥቁር መልክ መሆኑ ኡድሒያ የሚያበላሽ አይደለም። ነገር ግን የሚወደደው መልክ የአላህ መልእክተኛ ያረዱት አይነት ቢሆን ይመረጣል። እሱም ቦቃ ይባላል። ነጭ ሆኖ ግንባሩና ጉልበቱ አካባቢ ጥቁር ያለበት እሱም አምለሕ ይባላል።
➼ አቅም ያለው ሰው የፈለገውን ያክል ከብት ገዝቶ ማረድ ይችላል። በተለይ ለሚስኪኖች በዚህ ጊዜ አረዶ ለዒዳቸው ስጋ ሰጥቶ ማስደሰት በጣም ትልቅ እድል ነው። ምንዳውም እጥፍ ድርብ ነው። አርዶ ደም ባፈሰሰ ቁጥር ወደ አላህ ይቃረባል። ድሆችን በማስደሰቱ ደግሞ ሌላ ዒባዳ ይሰራል እጥፍ ድርብ የሆነ ምንዳ።
«خِتَامُهُ مِسْكٌ ۚ وَفِي ذَٰلِكَ فَلْيَتَنَافَسِ الْمُتَنَافِسُونَ»
المطففين (26)
"ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ።"
https://t.me/bahruteka | 214 |
| 11 | 👉 የኡድሒያ ቱሩፋት
ኡድሒያ በዙል ሒጃ 10ኛ ቀን የሚታረድ እርድ ሲሆን በጣም ተወዳጅና ብዙ ቱሩፋት ያለው ዒባዳ ነው ። ኡድሒያ የገንዘብ ፣ የአካልና የቀልብ ዒባዳን አጠቃሎ የያዘ አስገራሚ ዒባዳ ነው ። አንዳንድ ዑለሞች አቅም ባለው ሰው ላይ ዋጂብ ነው የሚሉ ሲሆን ጁሙሁሮቹ ግን ሱና ሙአከድ ነው ይላሉ ።
የአላህ መልእክተኛ ኡድሒያ ስላለው ምንዳ የተናገሩትን ያየና ይህን በአመት አንድ ጊዜ የሚመጣ እንዲህ አይነት ቱሩፋት ያለውን ዒባዳ ለመተው ሞራል አይኖረውም ። የአላህ መልእክተኛ የኡድሒያን ቱሩፋት አስመልክተው እንዲህ ይላሉ : –
عن عائشة رضي الله عنها قالت : قال رسول الله – صلى الله عليه وسلم –:
" ما عمل ابن آدم يوم النحر أحب إلى الله من إهراق الدم، وإنه ليؤتى يوم القيامة بقرونها وأشعارها وأظلافها، وإن الدم ليقع من الله بمكان قبل أن يقع بالأرض، فطيبوا بها نفسا ".
قال الألباني في تحقيق مشكاة المصابيح : صحيح
እናታችን ዓኢሻ – ረዲየላሁ ዐንሃ – የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ትላለች :–
" የኣደም ልጅ የዙል ሒጃ 10ኛ ቀን ላይ ከሚሰራው ስራ ደም እንደማፍሰስ ( በአጅር የሚደርስ ) የለም ። ይህ የታረደው ከብት የቂያማ ቀን በቀንዱ ፣ በፀጉሩና በጥፍሩ ይመጣል ። ደሙ መሬት ላይ ከመፍሰሱ በፊት ቀድሞ አላህ ዘንድ ይደርሳል !!! ። በምታርዱት ነገር ነፍሳችሁ ደስ እንዲለው አድርጉ " ።
🔹 ኡድሒያ እንዲህ አይነት ምንዳ ያለው ትልቅ ዒባዳ ነው ። አጅሩ በሚወጣው ገንዘብ ልክ ነው ። የኡድሒያው ከብት በተለቀና ባማረ ቁጥር አጅሩ እየጨመረ ይሄዳል ። ስለዚህ ለኡድሒያ በምንገዛው ነገር መሰሰት የለብንም ። ደስ ብሎን መግዛት ይኖርብናል ። አላህ ከተጠቃሚዮች ያድርገን ።
http://t.me/bahruteka | 210 |
| 12 | No text... | 230 |
| 13 | አባባን ሐጅ ወስደዋቸው ነው.... ሐጁ እየተከወነ ሶፋና መርዋ መካከል የሚሮጥበት ሰአት ደረሰ። እናም ሰዎች አንዲሮጡ ነገሯቸው ....« አባባ ዱብ ዱብ በሉ » አሏቸው ...
.... «የእስማይል እናት ብትሮጥ ለልጇ ውሃ ፍለጋ ነው ፤ እኔ ምን ገዶኝ እሮጣለሁ» አሉ ይባላል ። 😊
ወላጆችን ሐጅ ለማስደረግ መቋመጥ የሁሉም መልካም ልጅ ሁሉ ምኞት ነው።ነገር ግን ሐጅ ዒባዳህ እንጅ የቱሪዝም መዳረሻ አይደለምና ልክ እንደ ሶላት አፈፃፀሙን መማርና ማስተማር ግዴታ ነው።
ብዙ ብሮችን ከስክሰህ ወላጆችን ሳታስተምር ብትወስዳቸው ኪሳራ እንጅ ትርፍ አይሆንም።
ሐጅ የምታስደርጋቸው ጀነትን በመፈለግ እንጅ መካን ለማሳየት አይደለም።ረሱለላህ ﷺእንዲህ ብለዋል፦
«ኩልል ያለ ሐጅ ጀነት እንጅ ክፍያ የለውም» (ቡኻሪይ 1773)
ኩልል ያለ ሐጅ ማለት ፦
① ከወንጀል የፀዳ
② ከይዩልኝና ይስሙልኝ የፀዳ (ኻሊስ)
③ ማእዘናቱና ዋጂቦቹ የተረጋገጡበት ማለት ነው።
ሰው ለ4ሺ ብር ደመወዝ ስራ 15 ቀን ስልጠና ይወስዳል ታድያ ክፍያው ጀነት ለሆነ ዒባዳህ እንዴት ነው ቢያንስ 15ቀን እንኳን አፈፃፀሙን የማትማረውና ወላጆችህን የማታስተምረው? ?
ከነርሱ ጋር ካዕባ ዘንድ ሰልፊ መነሳትኮ ሀጅ አይደለም ወንድሜ! ማስደሰት ከሆነ የፈለግከው በዚያው ወጪ በሌላ ነገር ማስደሰት ይቻላል።
አላህ ለኛም ለቤተሰቦቻችንም ኩልል ያለን ሐጅ ይወፍቀን!! ✍️ ismaiilnuru
Share 'አጠር ያለ የሐጅና የዑምራህ አፈፃፀም ማብራሪያ.pdf'
አጠር ያለ የሐጅና የዑምራህ አፈፃፀም ማብራሪያ በአጭሩ የተገለፀበት PDF ከታች ባለው ሊንክ ተጠቅመን ማግኘት እንችላለን። ሌሎችም ይጠቀሙ ዘንድ ሼር እናድርግ፤ የአጅሩ ተከፋይ እንሁን !!
https://t.me/Abu_Umair2 | 272 |
| 14 | ፈተና የማይቀር መሆኑና አስቀድመን ለርሷው እንድንዘጋጅ አላህ ነግሮናል። ያ ማለት ከታገስን፣ ፈተናውን በአግባቡ ካለፍን፣ ከሁላችንም ፈተና ቡሀላ ድል አለ።
* ልክ ነብዩላሂ አዩብን ከህመሙ ቡሀላ እንዳዳነው።
* ከድህነቱ ቡሀላ በሀብት እንዳንበሸበሸው።
* ከ14 የልጆቹ ሞት ሀዘን ቡሀላ ፤ በ28 የልጆቹ ሳቅ እንዳስደሰተው።
ወላሂ አትጠራጠር! አዩብ (ዐ•ሰ)ን ያስደሰተ ጌታ አንተንም ያስደስትሀል። ከችግርህ ፣ ከህመምህ፣ ከዕጦትህ ቡሀላ ይፈርጅሀል። አብደላህ ሆይ አስታውስ ወላሂ! አስታውስ አላህ (ሱ•ወ) ላንተ ቃል እንደገባልህ። አንዴም ብቻ አይደለም ቃል የገባልህ። ሁለት ጊዜ ነውና!
إِنَّ مَعَ ٱلْعُسْرِ يُسْرًا
فَإِنَّ مَعَ ٱلْعُسْرِ يُسْرًا
ይሄኔ ታፈዲያ ከድላችን፣ ከፈረጃው ቡሀላ ለሁላችንም ሁለት እድል አለን ወይ አመስግኖ ማስጨመር አልያ ክዶ ብርቱ አያያዙን መያዝ!! ምክንያቱም አላህ አዘወጀል እንዲህ ብሏልና
لَئِن شَكَرْتُمْ لَأَزِيدَنَّكُمْ ۖ وَلَئِن كَفَرْتُمْ إِنَّ عَذَابِى لَشَدِيدٌ
‹‹ብታመሰግኑ በእርግጥ እጨምርላችኋለሁ ብትክዱም (እቀጣችኋለሁ) ቅጣቴ በእርግጥ ብርቱ ነውና» በማለት ባስታወቀ ጊዜ (አስታውስ)
#የወንድም_አቡ_ዑመይር_አንዳንድ_መጣጥፎች
ከሁሉም በላይ አላህ አዋቂ ነው።
✍ አቡ ዑመይር
( ቀን, ነሐሴ 24, 2014 ) | 16 |
| 15 | No text... | 289 |
| 16 | 🚫 ማን ነው በጂሃድ የሚያዘው ?
በመጀመሪያ ደረጃ ሁሉም ሊያወቀው የሚገባው ጂሃድ በኢስላም ትልቅ ቦታ ያለው ለአላህ ተብሎ አንገት የሚሰጥበት የአምልኮት አይነት ነው ። ጂሃድ ምእራባዊያን እንደሚያስቡት አላማው ዝም ብሎ የሰው ሕይወት ማጥፋት አይደለም ። ኢስላም ጂሃድን አስመልክቶ በጣም ግልፅ መርሕ ነው ያለው ።
እንደሚታወቀው በእስልምና የአምልኮ ድንጋጌ አይነቶች በሁለት ይከፈላሉ : –
↪️ በቀጥታ ለራሳቸው ተብለው የታዘዙ በመስፈርታቸው ሁሌም የሚሰሩ ( መቅሱድ ሊዛቲሂ ) የሆኑ እንደ ሶላትና ፆምና ሐጅ የመሳሰሉ የአምኮ አይነቶች እና
↪️ በቀጥታ ለራሳቸው ተብሎ ሳይሆን ለሌላ አምልኮ መዳረሻ ተብሎ የታዘዙ ( መቅሱድ ሊጘይሪሂ ) የሆኑ
ለምሳሌ ውዱእ ማድረግ :– ውዱእ የታዘዘው በዋነኝነት ለሶላት ሲሆን ያለ ውዱእ አይሰሩም ለተባሉ የአምልኮት አይነቶችም ይሆናል ። በመሆኑም አንድ ሰው ውዱእ ማድረግ ግዴታ የሚሆንበት ሶላት መስገድ በሚፈልግ ጊዜ ወይም የፈርድ ሶላት ወቅት ሲደርስ ይሆናል ። ይህ ማለት ውዱእ በራሱ ዒባዳ ከመሆኑ ጋር ። ነገር ግን የሚፈለገው በቀጥታ ለራሱ ሳይሆን ለሌላ የዒባዳ አይነት ነው ።
እንደዚሁ ጂሃድም በቀጥታ ለራሱ ሳይሆን የታዘዘው ለሌላ አምልኮት ነው ። እሱም አላህ ለሰው ልጆች የሕይወት መመሪያ ይሆን ዘንድ ቁርኣንን አውርዷል ። ይህንን መለኮታዊ የህይወት መመሪያ የሆነው ቁርኣን ለሰው ልጆች እንዲያደርሱ መልእክተኞችን ልኳል ። ይህ መለኮታዊ የሕይወት መመሪያ የሆነው የአላህ ቃል መልእክተኞቹ ለሰው ልጅ ሊያደርሱና የሰውም ልጅ ይህ መለኮታዊ የህይወት መመሪያ ሊደርሰው መብቱ ነው ። በሱና በመብቱ መካከል የሚቆም አካል ሊኖር አይገባም አይ ብሎ በዚህ መለኮታዊ የህይወት መመሪያ በማድረሱ መንድ ላይ የሚቆም አሜኪላ ወይም ጋሬጣ በሚኖር ጊዜ ይህን ለማስወገድ ነው ጂሃድ የታዘዘው ። ከመሆኑም ጋር እንደ ሌሎቹ ህግጋቶች ሁሉ የራሱ የሆነ መስፈርቶች አሉት ። ልክ ዘካ አቅም ያለው ሰው እንደሚያወጣውና ሐጅም አቅም ያለው ሰው ሌሎች መስፈርቶችን አሟልቶ እንደሚያደርገው ሁሉ ። ጂሃድም አቅም ያለው መሪ ነው የሚያዝበት ። ኢስላም አቅም የሌለውን ዘካ አውጣ ወይም ሐጅ አድርግ እንዳላለው ሁሉ በዳዕዋ መንገድ ላይ የተጋረጠውንም አሜኪላ ለማስወገድ አቅም የሌለውን ጂሀድ አድርግ አላለውም ።
ወደ ርእሴ ስመለስ የዚህ አይነቱ ትልቅ የሸሪዓ አካል የሆነውን ጂሃድ ማን ነው የሚያዝበት ከተባለ የሙስሊም መሪ መስላሐና መፍሰዳውን አይቶ አቅሙን መዝኖ በመንገዱ ላይ የቆመውን አሜኪላ አቅም አመዛዝኖ ከሚመለከታቸው የዲኑና የሀገር ህልውና አደራ ከተጣለባቸው አጋሮቹ ጋር በመሆን የሚያዝበት ነው ።
በመሆኑም በኢስላም ጂሃድ ማንም ሰው ተነስቶ የሚያውጀው ወይም ተነሱ የሚልበት ሳይሆን በጣም ትልቅ ጥንቃቄ የሚፈልግ ነው ። ለዚህ ነው የአላህ መልእክተኛ ወሕይ እየወረደላቸውም ሙሃጅሮችንንና አንሷሮችን ያወያዩበት የነበረው ። እነ አቡበከር ዑመር በዚሁ መልኩ ትላልቅ የሙሃጅርና የአንሷር ሶሓቦችን ሰብስበው ያወያዩ የነበረው ።
በጣም የሚገርመው ዛሬ ሀገራችን ላይ ማን እንደሆኑና የት ሆነው እንደሚያዙ የማይታወቁ አካላት ጂሃድ እያወጁና ተነሱ እያሉ ነው !!!!!! ። እነዚህ አካላት ሊያውቁት የሚገባው ወይ የኢስላም ጠላት ተላላኪዎች ናቸው ። ሙስሊሞችን ለማጥቃት ይህን ምክንያት አድርገው መንቀሳቀስ የሚፈልጉ የኢስላም ጠላቶች ወይም በስሜት ፈረስ የሚጋልቡ ከጂሃጅ ስሙን እንጂ ርቀቱንና ሸሪዓዊ ብይኑን የማያውቁ ። የሚያሳዝነው እነዚህ ሙስሊሙን ወጣት ለጂሀድ ተነስ የሚሉ አካላት ሚስቶቻቸው ወይም እህቶቻቸው በየወሩ ወይም በወሊድ ጊዜ ስለሚፈሳቸው ደም ሸሪዓዊ ብይን ቢጠይቁዋቸው መመለስ የማይችሉ ናቸው ‼። ነገር ግን በተሽከርካሪ ወንበር ላይ ቁጭ ብለው ማኪያቶ እየጠጡ በኡማው ደም ላይ ፈትዋ ይሰጣሉ ። ሙስሊሞች ሆይ በፖለቲካ ወይም በመሬት ስራ የከሰሩ ማንነታቸው የማይታወቁ የኢስላም ጠላት ተላላኪዎች ተነሱ ጂሃድ ስላሉዋችሁ ወይም በእንቅፋት አለያም ትንታ ትሞታላችሁ እቺን እርካሽ ህይወት ለዲን ሰጥታችሁ በጀነት በራፍ ላይ የጀነት ሙሽራ አበባ ይዛ ብተቀበላችሁ ይሻላችኋል ‼ ብለው እያሰከሩ እንዳይነዱዋችሁ ።
የወንድምነት ምክሬ መጀመሪያ ዲናችሁን እወቁ ተማሩ ስሩበት አውቃችሁ የሰራችሁበትን እውቀት ለሌሎች በማድረስና ከሽርክና ቢዳዓ እንዲወጡ ሰበብ በመሆን በነፍሳችሁ ላይ ጂሃድ አድርጉ ይህ ለናንተ ትልቅ ጂሃድ ነው ። ስለሺርክና ቢዳዓ ሳታውቁ ስለጣሃራና ሶላት ሳታውቁ ወደ አኼራ እንዳትሄዱ ተጠንቀቁ ።
የሱና ዑለሞች ፣ ኡስታዞችና ዱዓቶች ሙስሊሙን ከእነዚህ አካላት መጠበቅና ግንዛቤ ማስጨበት ወቅታዊ ግዴታችሁ ነውና አማናችሁን ተወጡ ኡማውን ታደጉ ።
አላህ ሐቅን አውቆን የምንሰራበትና ባጢልን አውቆን የምንርቀው ያደርገን ።
https://t.me/bahruteka | 291 |
| 17 | ለአላህ ብለህ የወደድከውን ጓደኛህን፤ ለአላህ ብለህ መጥፎ ባህሪውን ጥላዉ። ግና ከእርሱ ርቀህ ብቻውን ለሸይጣን አትተው ወደ አላህ ለመመለስ ሞክር።
አንድ እጅግ የምወደው እና የማከብረው የመስጂድ ኢማም ሱዑዲ በሚኖርበት ወቅት ያጋጠመውን የአንድ ወጣት ታሪክ እንማርበት ዘንዳ ያወጋንን እንዲህ ላውጋቹ…
"ሱዑዲ የዲን ትምህርትን ከጓደኞቻችን ጋር እየተማርን በምኖርበት ሰዓት አንድ ጓደኛችን ከእኛ ተነጥሎ መልካም ያልሆነን ኑሮ ይመራ ጀመር። ሀራም ነገሮች ሁሉ መዘውተሪያው ሆኑ። መኖሪያ ቤቱ ከመስጂድ 50 ሜትር ቅርበት ላይ ሆኖ የአዛን ጥሪን እየሰማም ቢሆን እንኳን ወደ መስጂድ ለሰላት አንዴም ብቅ የማይል ሆነ።"
"በዚህ አህዋሉ ላይ ሆኖ ቀናት፣ ሳምንታት፣ ወራቶች… አለፉ። ጓደኛችን ከኛ ተነጥሎ ሀራም ነገር ላይ በመዘፈቁ፤ የጓደኛችን ሁኔታ ይበልጥ ያሳስበን ጀመር። ዛሬ ነገ ወደ ቤቱ አንድ ላይ ሄደን ጓደኛችንን ወደ መስጂድ፣ ወደ ደርስ እንመልሰዋለን ብንልም በዝንጉነታችን ጊዜዎች ነጎዱ። የወንድማችንም ሁኔታ ከትላንት ዛሬ ፥ ከዛሬ ነገ ነገ ይከፋ ጀመር።"
"አንድ ቀን መስጂድ ተሰብስበን ሳለ ዛሬ ከአስር ሰላት ቡሃል ቤቱ ሄደን እናናግረዋለን ስንል ወሰንን። የማይደርስ የለምና አሰር ሰላት ደረሰ ከሰላት ቡሃላ ከጓደኞቻችን ጋር ስንቀላለድ 15/20 ደቂቃዎች አለፉ። እኔም ተነሱ ተነሱ ጓደኛችን ቤት እንሂድ አልኳቸውና ተያይዘን እቤቱ ሄድን።"
"በሩ ላይ ደርሰን የቤቱን በር መቆርቆር ጀመርን። በአንደኛው ቁርቆራ በሩ አልተከፈተም። ሁለተኛ ቆረቆርን አሁንም እንደዛው። በሶስተኛው ቁርቆራ ከአፍታዎች በኋላ በሩ ተከፈተ። ይሄኔ ሁላችንም የተመካከርን ይመስል አንድ ላይ እኩል አልሀምዱሊላህ፣ አልሀምዱሊላህ አልን። ወደ ውስጥ ገብተንም ከሳሎኑ ቁጭ አልን።"
"ጓደኛችንም እቤቱ ተቀምጠን ሳለ እኛን ባየ ጊዜ ልክ እንደ ህፃን ልጅ ስቅስቅ ብሎ ያለቅስ ጀመር። ሁኔታውን ስናይ ደስ ብሎን ማሻአላህ ×2 ወደ አላህ ተመለሰ በቃ ×2 አልን። ይሄኔ ጓደኛችን ኑ እስኪ አንድ ነገር ላሳያችሁ አለን እና ወደ መኝታ ክፍሉ ወሰደን። በራፉ ላይ ደርሰን ወደ ውስጥ ስንመለከት ሁላችንም ባየነው ነገር ስቅስቅ ብለን አለቀስን። ምክንያቱም ያየነው ጓደኛችን እራሱ ሊያጠፋ ወንበርና አስቀምጦ ከበላዩ ገመድ አንጠልጥሎ ነበር።" ጓደኛቸው ሁኔታውን ሲያብራራ…
"እናንተ በር ላይ ቆማቹ በሩን ስታንኳኩ ይህ የምታዩት ገመድ አንገቴ ላይ ጠልቆ ነበር። መጀመሪያ ስታንኳኩ፤ ዝም ስላቸው ይሄዳሉ ብዬ ዝም አልኩ ሁለተኛኝም ስታንኳኩ እንደዛው። ሶስተኛ ላይ ስታንኳኩ ግን እስኪ ምን ሊሉ እንደሆነ ልስማቸው አልኩና፤ መጥቼ በሩን ከፈትኩላቹ።" አላህ እኒህን መልካም ወጣቶች አላሳፈራቸውም ነበርና ወጣቶቹ ጓደኛቸው ላይ ደረሱበት።
አሁን ላይ ይህ ጓደኛችን የቁርአን ሀፊዝ ነው። ሀገረ ሱዑዲ ላይ የሚገኝ አንድ መስጂድ ውስጥ ኢማም ሆኖ ሙስሊሞችን ያሰግዳል። ወጣቶች ጆሮውንም የሚሰጡት ዳዒ ሆኗል። በዚህ ሰዐት ልክ እንደሱ አይነት ሁኔታ የገጠማቸውን ሰዎች ከችግራቸው ለማላቀቅ እየተጋ ያለ ወጣት ነው።"
ከሁሉም በላይ አላህ አዋቂ ነው።
✍ አቡ ዑመይር
( ቀን, ሚያዚያ, 2015 )
ቴሌግራም፦ https://t.me/+XvB4gIKElqoyMDNk | 306 |
| 18 | የአፕልኬሽን ጥቆማ 5፦ [ Deen ]
የአፕልኬሽኑ መተግበሪያ የሚሰጠው አገልግሎት፦
1. ከማስታወቂያ ነጻ የሆነው ይህ መተግበሪያ የሰላት ወቅት ሲደርስ ሰዓት መድረሱን በድምፅ ያስታውሰናል።
- ከፈጅር እስከ ኢሻ ወቅቱን የጠበቀ የሰላት ሰዓትን ያሳውቀናል።
- በመረጥነው የሰላት ወቅት ብቻ እንዲያስታውሰን ማበበጀት ያስችለናል።
- በውስጡ የሙአዚን ኦማር ሂሻም አል አራቢ ድምጽ ተካቷል።
- የሱሁር እና ለኢፍጣር ጊዜያትን ያስታውሰናል ።
2. ቁርአን
- የመረጥነውን ሱራህ አውርደን በፈለግነው ሰዐት ያለ ኢንተርኔት ማዳመጥ ያስችለናል።
- የቁርኣንን ንባብ በሚሻሪ ራሺድ አል-አፋሲ ያስደምጣል።
- ቁርአንን በአረብኛ ብቻ ወይነረም ከትርጉም ጋር ያስነብባል። (የ23 ቋንቋዎች የቁርአን ትርጉምን ይዟል )
- በተወዳጅ ጥቅሶች ላይ ግላዊ ማስታወሻዎችን ማዘጋጀት ያስችላል።
- ይህን አፕ ለሚጠቀሙ ወዳጃቹህ በዚሁ አፕ አማካኝነት ጥቅሶችን ሼር መደራረግ ያስችላል።
3. በየቀኑ በተለያዩ የዕለት ተዕለት ርእሶች ላይ በጉዞ ላይ ሆንም በቤትችን ውስጥ በቀጥታ ከቁርኣን እና ከሳሂህ ቡኻሪ የተወጣጡ ዱዐዎችን እንድናነብ ያግዘናል።
4. በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ከቁርኣን እና ከሀዲስ መልስ ማግኘት እንችላለን።
5. ቂብላ ኮምፓስ ስላለው ቂብላ በማናቅበት አካባቢ ቂብላ ወዴት እንደሆነ ማወቅ ያስችለናል። … ተጨማሪ ሌሎች ነገሮችም ተካተውበታል።
መጠን፦ 43.1 Mb
________________
አፕልኬሽኑን በዚህ ቴሌግራም ቻናል ላይ ታገኙታላችሁ
||
https://t.me/+XvB4gIKElqoyMDNk | 240 |
| 19 | የአፕልኬሽን ጥቆማ 4፦ [ 120+ የኡስታዝ ወሒድ ዑመር ]
ለአጠቃቀም ምቹ የሆነ ኢስላሚክ አፕ ነው። የአፕልኬሽኑ መተግበሪያ የሚሰጠው አገልግሎት፦
አፑ በውስጡ አራት ማህደሮች ያሉት ሲሆን እያንዳንዱ ማህደር የራሱ የሆነ ሰፋ ያለ ማብራሪያ አለው።
ስለ ኢስላም፦
* ሰለ ሰላት
* ስለ አቂዳ
* ስለ ፊቂህ
* ስለ ተውሂድ
* ስለ ሽርክ ወ.ዘ.ተ… ይዟል።
እንዲሁም ስለ ክርስቲያን፦
* ስለ ስላሴ
* እየሱስን ጨምሮ ሰለ ነብያቶች አምላክ፣
* ሴቶች በባይብል ያላቸው ቦታ
* ስለ ነብያቶች ከበቂ ማስረጃ እና ማብራሪያ ጋር ከጥያቄዎች ጋር በብዙ አጭቆ የያዘ አፕ ነው።
መጠን፦ 3.1 Mb
______________
አፕልኬሽኑን በዚህ ቴሌግራም ቻናል ላይ ታገኙታላችሁ
||
https://t.me/Abu_Umair2 | 220 |
| 20 | የአፕልኬሽን ጥቆማ 3፦ [ Ayah ]
ለአጠቃቀም ምቹ የሆነ ሙሉ የቁርዓን አፕ ነው። የአፕልኬሽኑ መተግበሪያ የሚሰጠው አገልግሎት፦
1. 30 ጁዝ ቁርአን ከተፍሲር ጋር ይዟል።
2. ቦተውን የማናስታውሰው የቁርአን አያ ካለ ምን ሱራህ ላይ ስንተኛው አያህ ላይ እንደሆነ Search አርገን እንድናገኝ ያስችለናል።
3. ቁርአን መቅራት ካቆምንበት ቦት ላይ በየቀኑ ቁርአን መቅራታችንን እንድንቀጥል ያስታውሰናል (በፈለግነው ሰአት ሞልተን)።
4. በቀን አንደ ወሳኝ አጭር የቁርአን አያህ ያስታውሰናል። በጁምዐ ቀን ደግሞ ሱረቱል ካህፍን መቅራት እንዳለብን ይነግረናል።
5. እንዲሁም በውስጡ የሂጅሪ አቆጣጠርን ይዟል።
መጠን፦ 124 ሜጋባይት
___________________
አፕልኬሽኑን በዚህ ቴሌግራም ቻናል ላይ ታገኙታላችሁ
||
https://t.me/Abu_Umair2 | 210 |
