en
Feedback
HPPPDSO BID INVITATION (የሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት የመንግሰት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት ጨረታ ማስታወቂያ)

HPPPDSO BID INVITATION (የሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት የመንግሰት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት ጨረታ ማስታወቂያ)

Open in Telegram

የሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት የመንግሰት ግዘዥናንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት በጋዜጣ የሚወጡትን ጨረታ ማስታወቂያዎችን ለሁሉም አቅራቢዎች መረጃው በፍጥነት ተዳራሸ ለማድረግ የተቀረፀ የጽ/ቤቱ የቴለግራም ሚዲያ ነው

Show more
433
Subscribers
+124 hours
+37 days
-430 days
Posts Archive
ነሀሴ 16/ 2015 አዲስ ዘመን ወርጊብቲ ለአይቤ ዚወጠኣ መሴመ ዚርረ ኮድ PPPDSo/001/2016 ኺድመ ዚሰጡ ቁጢ ቁጢ ሲቢላች ፣ ፌሮ ዋ ስታፋ ሲቢላች፣ ሲቢላ ታንከራች፣ ጀነሬተራች፣ ሚኢ ዪዚምጊ ሞተር ዋ የሸራ ዪሰፊ መኪና (ሲንጀር) መሴመ ዚርረ መክፈት ሔራው ሆጂ አያም 3/13/2015 ሒንጫይ አትጋፈሪያችዋ ዩጠቅሰዩ ቃማች ዚትረኸቡ አታይ መክተበ ጋርዞ ገልመቤ 4፡00 መቆፈልቤ ዋ 40 ፡ 30 ቤ መክፈትቤ ተኸመለማ ተሄለደ ፡፡

ውድ ደንበኞቻችን፣ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ማክሰኞ ነህሴ 16/2015  አመት የተለያዩ ያገለገሉ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች አስመልክቶ ንብረት ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ መውጣቱን ይታወሳል። *** በዚሁ መሰረት የሽያጭ መለያ ቁጥር ሐረ-ን.ሽያጭ /001/2016 የጨረታ መክፈቻው ስነ ስርዓት አርብ ጳጉሜ 03/2015  ከጠዋቱ  4:00 ተዘግቶ በእለቱ በ4:30 ላይ በጽ/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ የሚካሔድ መሆኑን  ስንገልጽላችሁ በደስታ ነው። ****" በንብረት ሽያጭ ጨረታ ላይ ለመሳተፍ ያለዎትን ፍላጎት እናደንቃለን * ከፍተኛ ጥራት ባላው አገልግሎት  እርስዎን ለማገልገል ዝግጁ ነን ።            መልካም ምኞት,

ውድ ደንበኞቻችን ነሀሴ21/2015 አመት በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ ** የሀረሪህዝብ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት ለ2016 በጀት አመት የተዘረዘሩትን እቃዎችእና ተያያዥ አገልግሎቶች  በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። 1.  ተጫራቾች ከላይ የተጠቀሱትን እቃዎች ለማቅረብ ተጫራቹ ሕጋዊ አግባብነት ያለው የንግድ ዘርፍን የሚመለከት የታደሰ የንግድ ፈቃድና የዘመኑን ግብር የከፈሉበት ግብር መክፈያ ቁጥር// ሰርተፊኬት ያላቸው፣ የቫት ተመዝጋቢ የሆነ፣ ከገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ የምዝገባ ፍቃድ እንዲሁም ሌሎችንም ከስራው ጋር ተያያዥነት ያላቸው ሰነዶችን ኮፒ በማድረግ ከጨረታ መልስ መስጫ ጋር ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፡፡ 2.  ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ለ60 ቀናት ይሆናል፡፡ 3.  ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ /Bid bond/፣ሲፒኦ /cpo/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በሐ/ክ/መ የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት ስም  በማሰራት ማቅረብ አለባቸው፡፡ 4.  የጨረታ ሰነዱ የተዘጋጀው በአማረኛ ቋንቋ ነው። በጨረታው መሳተፍ የሚፍልግ ተጫራች የግዥ መለያ ቁጥር PPPDSO/001/16 እና PPPDSO/002/16 ጨረታ ሰነዶቹን  በጽ/ቤቱ ግዥ ፋይናንስና ንብረት ስራ ክፍል የማይመለስ  ለእያንዳንዱ ብር 500/አምስት መቶ ፣ የማይመለስ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡ 5.  ተጫረቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መዝጊያ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ የጨረታ ሰነዱን ለዚሁ በተዘገጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡ 6.  የግዥመለያቁጥር PPPDSO/001/2016የጨረታውአይነት ባለሁለት ኢንቨሎፕ ሲሆን ተጫረቾች የጨረታ መመሪያ መሰረት በማድረግ የመወዳደሪያ ጨረታሰነዳቸውን ቴክኒካል እና ፋይናንሺያል ሰነዳቸውን ለየብቻ በማሸግ ለእያንዳንዳቸው አንድ ኦሪጅናል እና አንድ ኮፒ አድረገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ 7.  የግዥ መለያ ቁጥርPPPDSO 001/2016የቴክኒካል ሰነድ በ03/01/2016 ቀን ከጠዋቱ  በ4:15 ተዘግቶ ፤ በ4:30ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት አዳራሽ ይከፈታል፡፡ 8.  የግዥ መለያ ቁጥርPPPDSO/002/2016 የጨረታው አይነት ባለአንድ  ኢንቨሎፕ ነው፡፡ ተጫረቾች የጨረታ መመሪያ መሰረት በማድረግ የመወዳደሪያ ጨረታ ሰነዳቸውን ቴክኒካል እና ፋይናንሺያል ሰነዳቸውን አንድ ላይ አብሮ በማሸግ አንድ ኦሪጅናል እና አንድ ኮፒ አድረገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ 9.  የግዥ መለያ ቁጥርPPPDSO/002/16 የቴክኒካል እና ፋይናንሺያል ሰነድበ04/01/2016 ቀን ከጠዋቱ  በ4:15 ተዘግቶ ፤ በ4:30ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት አዳራሽ ይከፈታል፡፡ 10.  ከላይ የተጠቀሱት  ቀናት በአል ወይም ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል ፡፡ 11.   የበለጠ ለመረዳት በስልክ ቁጥር 0256660169 ወይም 0256590017 በመደወል ማነጋገር ይቻላል፡፡ 12.   ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 13.  ጨረታው የሚከፈትበትና ለማብራሪያ ጥያቄ  ዓላማ  የሚያገልግል  አድራሻ ስልክ 0256660169/ 0256590017 14.  ጨረታው የሚከፈትበት ቦታ፡ የሀረሪ ህዝብ ክልል የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ጽ/ቤት አሚር ሀቦባ ስታዲየም ፊት ለፊት (የድሮ ስታዲየም) በሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት Web site http//hppdso.gov.et https:t.me//hppds2 https://WWW.facebook.com/hppdso

ማክሰኞ ነህሴ 16/2015 በኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣ ንብረት ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ በሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት በመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት በሽያጭ መለያ ቁጥር ሐረ-ን.ሽያጭ /001/2016 የተለያዩ ያገለገሉ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች ፣ ፌሮና ስታፋ ብረቶች፣ የብረት ታንከሮች፣ ጀነሬተሮች፣ የውሃ መሳቢ ሞተር እና የሸራ መስፊያ መኪና (ሲንጀር) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታዉ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት ዉስጥ ዘዉትር በስራ ሰዓት በመቅረብ የጨረታ ስነዱን በጽ/ቤቱ ቢሮ ቁጥር 03 መግዛት ይችላሉ፡፡ 1. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በ/መ/ግ/ን/አ/ሰጪ ጽ/ቤት የሽያጭ መለያ ቁጥር ሐረ-ን.ሽያጭ/001/2016 ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላል፡ 2. ተጫረቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መዝጊያ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ ዘዉትር በስራ ሰዓት በጨረታ ዶክመንት ዉስጥ በተጠቀሰዉ መስሪያ ቤት ድረስ በመሄድ የሚወዳደሩባቸውን ንብረቶችን መመልከት ይችላሉ፡፡ 3. ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸዉ ንብረት እቃዎች ጠቅላላ ዋጋ በመነሻ ዋጋ 5% የሚሆነዉን ጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና/ Bid Bond/ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ /CPO/ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሚያቀርቡት ከጨረታ ሰነድ ጋር በማያያዝ በፖስታ በማሸግ ለጨረታ በተዘጋጀዉ ሳጥን ዉስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል ፡፡ (የሚዘጋጀዉ / CPO/ በሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት በመንግስት ግዢ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት ስም መሆን አለበት)፡፡ 4. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ ሲያቀርቡ በታሸገ ፖስታ ሆኖ በፖስታው ላይ የተጫራቾች ሙሉ ስም፣ፊርማ እና አድራሻ በማይለቅ ቀለም በመፃፍ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ 5. ተጫራቾች ከመጫረቻ ሰነድ ጋር ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ማስረጃዎች እድሜው 18 አመትና ከዚያ በላይ የሆነ ፣ ማንነቱን የሚገልፅ መታወቂያ ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፡፡ 6. የሽያጭ መለያ ቁጥር ሐረ-ን.ሽያጭ/001/2016 ጳጉሜ 03/2015 ቀን ከጠዋቱ በ4:00 ተዘግቶ ፤ ጳጉሜ 03/2015 በ4:30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት ይከፈታል፡፡ 7. የጨረታው አሸናፊ የሽያጭ ውል ከተዋዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ቀናት ውስጥ ያሸነፈባቸውን ንብረቶች ጠቅላላ ክፍያ በመፈፀም ማንሳት ይኖርበታል፡፡ 8. ተጫራቾች ያሸነፉትን ንብረት በሚወስዱበት ወቅት የማጓጓዣ ክፍያዎች ተጫራች የሚሸፍን ይሆናል፡፡ 9. የበለጠ ለመረዳት በስልክ ቁጥር 0256660037/0256590017 በመደወል ማነጋገር ይቻላል፡፡ ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ጨረታው የሚከፈትበት አድራሻ፤የሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት አሚር ሀቦባ ስታዲየም ፊት ለፊት አዳራሽ የተሟላ መረጃ እና የንብረት ፎቶ ለማግኘት   ሊንኩን ይጫኑ http://hppdso.gov.et

የግዥ እቅድ አላማዎች ########### ሰላም ለሁላችሁም!  በዛሬው ውይይት ስለ አንድ በጣም አስፈላጊ ርዕስ እንነጋገራለን ። ርእሱም " የግዥ እቅድ አላማዎች"  የሚል ነው  ። የግዥ እቅድ አላማዎች የሚከተሉት ናቸው፡- 1. የወጪ ቁጠባ እና የአፈፃፀም ብቃት የላቀ እንዲሆን ለማድረግ፡- የግዥ ዕቅድ ዋና ዓላማዎች አንዱ ወጪ ቆጣቢነትን ማሳካት እና የአፈጻጸም ቅልጥፍናን ማሳደግ ነው።  ግዢዎችን በጥንቃቄ በማቀድ, ድርጅቶች ወጪዎችን ለማመቻቸት, ሂደቶችን ለማቀላጠፍ እና አጠቃላይ አፈፃፀምን ለማሻሻል እድሎችን መለየት ይችላሉ. 2. የውድድር አድማሱን ለማስፋት፡- የግዥ እቅድ ማውጣት አላማው ለአቅራቢዎች ፍትሃዊ እና ክፍት ዕድሎችን በማረጋገጥ የውድድር አድማሱን ለማስፋት ነው።  ይህ ተወዳዳሪ አካባቢን ለማስተዋወቅ፣ ፈጠራን ለማበረታታት እና ለገንዘብ ምርጡን ዋጋ ለማግኘት ይረዳል። 3. የተቀናጀ እና ፍትሃዊ የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት፡- የግዥ እቅድ ማውጣት የተቀናጀ እና ፍትሃዊ አሰራርን ለመዘርጋት ያለመ ነው።  ይህም የግዥ ተግባራት ግልፅ፣ ወጥነት ያለው እና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ መከናወናቸውን ያረጋግጣል፣ ይህም ፍትሃዊነትን የሚያጎለብት እና ለሁሉም አቅራቢዎች እኩል እድል የሚሰጥ ነው። 4. የባለድርሻ አካላት አመኔታ ለማሳድ፡- ውጤታማ የግዥ እቅድ ማውጣት ዓላማው ባለድርሻ አካላት በግዥ ሂደቱ ላይ ያላቸውን እምነት ለማሳደግ ነው።  ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትን እና የስነምግባር አሠራሮችን በማክበር ድርጅቶች በህብረተሰቡ፣ በአቅራቢዎች እና በውስጥ ሰራተኞች መካከል በባለድርሻ አካላት መካከል መተማመን እና መተማመን መፍጠር ይችላሉ። 5. ግልጽነትና ተጠያቂነት ለማስፈን፡- የግዥ ዕቅድ በግዥ ሂደት ውስጥ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን ያለመ ነው።  ይህ ግልጽ ሰነዶችን, ግልጽ ግንኙነትን እና ደንቦችን እና ፖሊሲዎችን ማክበርን ያካትታል.  ግልጽነት እና ተጠያቂነት ሙስና፣ አድሎአዊነት እና ኢ-ሥነ ምግባራዊ ድርጊቶችን አደጋ ለመቀነስ ይረዳል። 6. በአካባቢ ልማት ውስጥ የአቅራቢዎች ተሳትፎ ለማሳደግ፡ የግዥ እቅድ አላማው የሀገር ውስጥ አቅራቢዎችን በግዥ ሂደት ውስጥ እንዲሳተፉ ለማበረታታት ነው።  የአካባቢ ልማት አላማዎችን በማገናዘብ እና ለሀገር ውስጥ አቅራቢዎች እድሎችን በመስጠት ድርጅቶች ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለስራ እድል ፈጠራ እና ለአካባቢው ማህበረሰብ ዘላቂ ልማት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማድረግ ያስችላቸዋል። በአጠቃላይ የግዥ ዕቅድ ወጪ ቁጠባን ማስፈን፣ ውድድርን ማስተዋወቅ፣ ፍትሃዊነትን ማረጋገጥ፣ የባለድርሻ አካላትን መተማመን ማሳደግ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ማስፈን እና የአካባቢ ልማትን መደገፍ ነው።  እነዚህ ዓላማዎች በጋራ ውጤታማ እና ቀልጣፋ የግዥ ልምዶችን ለማበርከት አስተዋፅኦ ያደርጋል  ።

     የሀረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት ባለበጀት መንግስት መ/ቤቶች  የ2016 በጀት ዓመት የግዥ ፍላጎታቸው እና ዕቅዶቻቸውን እንዲያቀርቡ ተጠየቀ። * የሐረሪ ክልል የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ስጪ ጽህፈት ቤት ሀላፈ  አቶ ያህያ አብዱራሂም እንደገለፁት  ለክልሉ የመንግስት ተቋማት የጋራ መገልገያ ዕቃዎችን እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸውን እቃዎች በእቅድ በውቅቱ ለመግዛት ፍላጎት፥  እንዳለው አስታውቋል።  የግዥ ሂደቶችን ወቅታዊና ቀልጣፋ ለማድረግ ሁሉም የክልሉ ባለበጀት መ/ቤቶች የ2016 በጀት ዓመት የግዥ ፍላጎታቸውን በየሩብ ዓመቱ እቅድ እንዲከፋፈሉ ጠይቋል።  እነዚህ እቅዶች በተረጋገጡ በጀቶች ታጅበው በተመደበው የጊዜ ገደብ ውስጥ  መቅረብ አስፈላጊ ነው። **** ይህ አስቀድሞ እቅድን የማዘጋጀት ዘዴ የጽ/ቤቱን  የግዥ ሂደቶችን በእቅድ በመምራት ና በመተግበር የሚፈለጉትን እቃዎችና አገልግሎቶች በወቅቱ ለማግኘት  ያስችላል ።  ይህንን ሂደት በማክበር ፅህፈት ቤቱ የግዥ ስራዎችን ለማቀላጠፍ እና አጠቃላይ ቅልጥፍናን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ገልፃል። **** የክልሉ ባለበጀት መንግስት መ/ቤቶች  ይህንን ጥያቄ በማክበር የ2016 በጀት ዓመት የግዥ ፍላጎታቸውና ዕቅዳቸውን በወቅቱ  እንዲያቀርቡ አሳስበዋል። ይህም ከ መንግስት ተቋማት እና በጽ/ቤቱ መካከል ውጤታማ ቅንጅት እና ትብብርን ያመቻቻል። ***"" ግዥን በእቅድ በመምራት እና በጋራ በመስራት  ለመንግስት ተቋማት የግዥ ፍላጎት በብቃት እና በፍጥነት እንዲሟሉ ማድረግ እንችላለን ብሏል። http://hppdso.gov.et ዘጋቢ የጽ/ቤቱ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ጽ/ቤቱ የ2015  በጀት አመት አፈፃፀም  ሪፖርት  እና የ 2016 በጀት አመት እቅድን ገመገመ፡፡ **** የሀረሪ ክልል የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ጽ/ቤት የ2015 በጀት አመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሞ የ2016 በጀት አመት እቅድ ቀርቦ አቅጣጫ ተስጥቶበታል። ** በግምገማውና በውይይት መድረኩ ላይ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ያህያ አብዱረሂም በጽህፈት ቤቱ የተገኙ ስኬቶችንና ውጤቶችን አመልክተዋል። **** እንደ አቶ ያህያ አብዱረሂ ገለፃ ጽህፈት ቤቱ የብር 326 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሚያወጡ የተለያዩ የጋራ መገልገያ ዕቃዎችን በማዕቀፍ ስምምነቶች እና በስትራቴጂካዊ ግዥዎች ግዥ በተሳካ ሁኔታ ፈፅሟል።  በተጨማሪም በንብረት አወጋገድ ለመንግስት ብር 13.8 ሚሊዮን ገቢ አስገኝተዋል።  እነዚህ ስኬቶች ጽሕፈት ቤቱ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል። * ጽህፈት ቤቱ የመንግስት ግዥዎችን  የቅሬታ አሰራር በመዘርጋት ለቅሬታዎች ፍትሃዊ ምላሽ በመስጠት ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ለመንግስት እንዲቆጥቡ አድርጓል። ለላቀ አፈፃፀም ዕውቅና በ2015 በጀት ዓመት 8 ሰራተኞች የምስክር ወረቀትና የፋይናንስ ማበረታቻ ተሰጥቷቸዋል።  በተጨማሪም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ንቁ ተሳትፎ ያደረጉ ሁለት ሰራተኞችም እውቅና ተሰጥቷቸዋል። በውይይት መድረኩ ላይ አቶ ሄኖክ ግርማ የ2015 በጀት አመት የአፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን አቶ ዚያድ አርጋው ሰራተኞች ለ2016 በጀት አመት ሊከተሏቸው የሚገቡ መርሆዎችን አካፍለዋል። በመጨረሻም የጽ/ቤቱ ኃላፊው በውይይት መድረኩ ላይ የተነሱ ሀሳቦችን በማጠቃለል በበጀት አመቱ የተስተዋሉ ጥንካሬዎችን በማንሳት ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት ለቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አቅርበዋል። http://hppdso.gov.et የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት