HPPPDSO BID INVITATION (የሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት የመንግሰት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት ጨረታ ማስታወቂያ)
Open in Telegram
የሐረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት የመንግሰት ግዘዥናንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሰጪ ጽ/ቤት በጋዜጣ የሚወጡትን ጨረታ ማስታወቂያዎችን ለሁሉም አቅራቢዎች መረጃው በፍጥነት ተዳራሸ ለማድረግ የተቀረፀ የጽ/ቤቱ የቴለግራም ሚዲያ ነው
Show more433
Subscribers
+124 hours
+37 days
-430 days
Posts Archive
Good job🙏 The purpose of Media is all about informing through different platform about news, features, current affairs programmes, public service announcements,magazine and other forms of programming ON TIME.
sadaasa 9/2016 Beeksisa caalbaasii bitta Gaazeexaa addis zaman gubatti bahe turee caalbaasi Koodii PPPDSo/015
/2016 bitta meeshaa HDPE,PIPE and Fiting sirni baninsa caalbaasii Guyyaa arra Gaafa 25/3/2016 iddoo dorgomtoonni /bakka bu’oonni fi qaamni dhimmi ilaalatu argamanitti galma waajjirichaati sa’aa 4:15 Cufuun/ Saamsuun fi sa’aa 4:30 banuun sirni baniinsa caalbaasii raawwatamee xumuramee jira.
ህዳር 9/ 2016 አዲስ ዘመን ወርጊብቲ ለአይቤ ዚወጠኣ ዊኻቦት ዚርረ ኮድ PPPDSo/015/2016 ዚ HDPE, PIPE and Fiting መህዋች ዊኻቦት ዚርረ መክፈት ሔራው ሆጂ አያም 25/3/2016 ሒንጫይ አትጋፈሪያችዋ ዩጠቅሰዩ ቃማች ዚትረኸቡ አታይ መክተበ ጋርዞ ገልመቤ 4፡15 መቆፈልቤ ዋ 40 ፡ 30 ቤ መክፈትቤ ዚርረ መክፈት ሄራው ተኸመለማ ተሄለደ ፡፡
በዛሬው እለት በቀን 25/3/2016 የቀድሞ የተቃማችን ሃላፊ አቶ ያህያ አብዱረሂም ከአዲሱ ተሻሚ ከአቶ አብዱልባሲጥ አቡበከር ጋር ርክክብ በማካሄድ ከተቃሙ የማኔጅመንት አባላት ጋር ትውውቅ ፈፅመዋል
ህዳር 9/2016 በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ወቶ የነበረው የሽያጭ ጨረታ ኮድ PPPDSO/010/2016 የህክምና እቃዎች ግዥ ጨረታ አከፋፈት ስነ ስርኣት በዛሬው እለት በቀን 24/3/2016 ተወዳዳሪዎች/ተወካዮች በተገኙበት በጽ/ቤ አዳራሽ 4 ፡ 15 በማሸግ እና 4 ፡ 30 በመክፈት የጨረታ መክፈት ስነ ስርኣቱ ተጠናቋል፡፡
አቶ አብዱልባሲጥ አቡበከር የመንግስት ግዥ ንብረት ማስወገድ አገልግሎቸት ሰጪ ጽ/ቤት ሃላፊ ለሆነው ተሹመዋል መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንልህ እንመኛለኘን
ለታለመለት አላማ የሚስማማ ውጤታማ የእቃዎች ዝርዝር ፍላጎት መግለጫን (specification ) እንዴት ማዘጋጀት ይችላል? 🌟
ውጤታማ የእቃ ፍላጎት መግለጫን (specification ) ማዘጋጀት በመንግስት ግዥ ሂደት የተሳካ ውጤቶችን የማረጋገጥ ወሳኝ ገጽታ ነው። የዕቃ ፍላጎት መግለጫዎችን (specification ) ከግዥ ዓላማዎች ጋር በማጣጣም፣ በአፈጻጸም ላይ የተመሰረቱ መመዘኛዎችን በማጉላት፣ የጥራት ደረጃዎችን በማካተት፣ ከመጠን በላይ ገዳቢ መስፈርቶችን በማስቀረት፣ አቅራቢዎችን በማሳተፍ እና ቀጣይነት ያለው የማሻሻያ ባህልን በመቀበል የመንግስት መስሪያቤቶች ለታለመላቸው ዓላማ ተስማሚ የሆኑ ዕቃዎችን ለመግዛት አቅማቸውን ያሳድጋል። ውጤታማ ዝርዝር መግለጫዎች ለገንዘብ የተሻለ ዋጋ ማበርከት ብቻ ሳይሆን የመንግስት መስሪያቤቱን ፍላጎት የሚያሟሉ እና ሰፋ ያሉ የህብረተሰብ አላማዎችን ለማሳካት የሚረዱ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን እቃዎች ለመግዛት ያስችላል። ነገር ግን በቂ ያልሆነ ወይም በደንብ ያልተዘጋጁ የእቃ ፍላጎት መግለጫን (specification ) ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶች፣ የዋጋ መጨናነቅ እና በመጨረሻም የግዥ አፈፃፀም የታቀዱትን አላማዎች አለማሳካት ያስከትላል። ይህ ጽሑፍ ዝርዝር ፍላጎት መግለጫዎችን ከተፈለገው ውጤት ጋር ማመጣጠን አስፈላጊ መሆኑን ያጎላል፣ ውጤታማ ዝርዝር መግለጫዎችን ለማዘጋጀት መመሪያ ይሰጣል፣ እና በመንግስት ግዥ ሂደት ለአላማ ተስማሚነት ቅድሚያ የመስጠት ጥቅሞችን ያጎላል።ለበለጠ መረጃ ሊንኩን ይጫኑ፡ https://hppdso.gov.et
የ2016 በጀት አመት የአለም የፀረ - ሙስና ቀን በሐረሪ ክልል የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አ/ሰጪ ጽ/ቤ ሰራተኞች ተከበረ
በአለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ እና በክልላችን ለ18ኛ ጊዜ "ሙስና የጋራ ጠላታችን ነውና በጋራ እንታገል" በሚለው መፈክር በሐረሪ ክልል የመንግስት ግዥ እና ንብረት ማስወገድ አ/ሰጪ ጽ/ቤ ሰራተኞች የተከበረ ሲሆን በእለቱ በመድረኩ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የ ጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ያህያ አብዱረሂም እንደገለፁት "ሙስና የጋራ ጠላታችን ነውና በጋራ እንታገል" የሚለው መሪ መፈክር የሚያሳየው ሙስናን የመከላከል ስራ ለአንድ ወገን የሚተው ሳይሆን የሁሉንም ዜጎች ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ እያንዳንዳችን ግዴታችንን መወጣት ይጠበቅብናል ካሉ ቡሃላ አክለውም ሙስና የሀገር ሀብትን በማባከን ዜጎችን የሚያባላና ከውጭ ወራሪ ኃይል የበለጠ ጠላት መሆኑን በማብራራት ሙሰኞች ላይ በተግባር እና ከልብ እንድንታገል በመጠየቅ እና ቀጥሎ በሚቀርበው የስልጠና ማኑዋል ላይ ሰፊ ተሳትፎና ውይይት እንድታደርጉበት በተለይም የመንግስት ግዥ ተጋላጭ ከሆኑ ሴክተሮች መሀል አንዱ ስለሆነ የስልጠና ማኑዋሉን ከተቃማችን አንፃር በመውሰድ ሰፊ ውይይት ማድረግ ይጠበቅባቹኃል በማለት መድረኩን ከፍተዋል፡፡
በመቀጠል አቶ ዩሱፍ አብደላ የ2016 የአለም የፀረ - ሙስና ቀንን ለማክበር የተዘጋጀውን የስልጠና ማኑዋል በስፋት በማቅረብ ሰራተኞቹ ሰፊ ውይይት አካሄደውበታል፡፡
ከክልሉ የስነ ምግባርና የፀረ - ሙስና ኮሚሽን የተገኙት ከፍተኛ ባለሞያዎች ወ/ት ሰኣዳ መሀመድ እና ሌሎች ባለሙያዎች በበኩላቸው የተለያዩ የጥናት ውጤቶችን በማቅረብ ልዩ ልዩ መረጃዎችን በስፋት በማቅረብ ሰራተኞቹን አወያይተዋል፡፡ በተለይም አንድ ሰራተኛ ተጨባጭ ጥቆማን በመስጠቱ ብቻ ከስራ ላይ ተባሮ ከሆነ ኮሚሽኑ ሰራተኛውን ወደ ስራ ለመመለስ ሙሉ ስልጣን እንዳለው በማንሳት ሁሉም ሰው ወደ ትግሉ እንዲቀላቀል እና የንብረት ማስመዝገብ ግዴታን እንዲወጣ ጠይቀዋል ፡፡
በመጨረሻም ከሰራተኞቹ ለተነሳው ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና ሀሳቦች ከመድረኩ ላይ መልስ እና ማጠቃለያ በመስጠት ተጠናቀቀ።
ዘጋቢ የጽ/ቤ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር
17/3/2016
