cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

አዲስ ምልከታ🌍

+ አዲስ የሳይንስ እይታ + አዲስ አስተሳሰብ + አዲስ እውቀት + ሃይማኖት + ፖለቲካ + ኢኮኖሚ + ሙዚቃ # የኢትዮጵያ ትንሳኤ

Show more
Advertising posts
1 636
Subscribers
+224 hours
+307 days
+17730 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
Crypto...
2441Loading...
02
እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤው በዓል አደረሳችሁ። ክርስቶስ ተንስአ እሙታን  -- ክርስቶስ ከሙታን ተነሳ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን  -- በታላቅ ኃይልና ስልጣን አሠሮ ለሠይጣን  -- ሰይጣንን አሰረው አግዓዞ ለአዳም    -- አዳምን ነፃ አወጣው ሰላም -- ሰላም እምይእዜሰ -- ከዛሬ ጀምሮ ኮነ  -- ይሁን ፍስሃ ወሰላም -- ፍስሃና ሰላም! +++++++++++++++++++ በሞቱ ሞታችንን ሲሽር በትንሣኤው ትንሣኤያችንን አወጀልን፣ አጎናፀፈን። መልካም በዓል።
2088Loading...
03
#ለቤተክርስቲያን_ብለህ ለቤተክርስቲያን ብለህ ልትቀድሳት በደምህ በአደባባይ በጥፊ ተመታህ። ንጹሕ ክርስቶስ በአዳም ጥፋት ልትወቀስ በከንቱ ልትከሰስ አመላለሱህ ከጲላጦስ ወደ ሄሮድስ ሁሉን ቻይ ሳለህ ምንም ማድረግ ሳይሳንህ በአይሁድ እጅ ተገረፍህ! ወዮ! ወሰን ለሌላት ትዕግስት ስለኛ ብለህ መከራ ተቀበልህ ምንም በደል ሳይኖርብህ አምላክ በእንጨት መስቀል ላይ ሰቀሉህ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ
2992Loading...
04
በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጓል መልክና ውበት የለውም፥ባየነውም ጊዜ እንወደ፟ው ዘንድ ደም ግባት የለውም። የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥እኛም አላከበርነውም። በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሟል እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። ርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ስለ በደላችንም ደቀቀ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በርሱ ላይ ነበረ፥በርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ትንቢተ ኢሳይያስ 53፥ 2 - 5
3635Loading...
05
ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶን/3/ ኪራላይሶን /2/ አማኑኤል ጌታ ኪራላይንሶ /2/ በጥፊ ተመታ ኪራላይሶ /2/ አለምን ሊታደግ ኪራላይሶን /2/ ተነዳ እንደበግ ኪራላይሶን /2/ አዳምን ሊፈውስ ኪራላይሶን /2/ ቆመ ከጵላጦስ ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶን/3/ ኪራላይንሶ /2/ እጁን ቸነከሩት ኪራላይሶን /2/ አጥንቱን ቆጠሩት ኪራላይሶን /2/ የእሾህ አክሊል ደፍቶ ኪራላይሶን /2/ ገዳዩን እረቶ ኪራላይሶን /2/ የሁላችን በደል ኪራላይሶን /2/ ተሻረ በእርሱ ቁስል ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶን/3/ ኪራላይሶን /2/ እጣ ተጣጣሉ ኪራላይሶን /2/ ልብሱን ተካፈሉ ኪራላይሶን /2/ ለፍርድ ተወሰደ ኪራላይሶን /2/ እንደበግ ታረደ ኪራላይሶን /2/ ለብሶ ከደም ሜዳ ኪራላይሶን /2/ ተከፈለ እዳ ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶ ኪራላይንሶ /3/ ኪራላይንሶ /2/ ሆምጣጤ አጠጡት ኪራላይሶን /2/ በገመድ ጎተቱት ኪራላይሶን /2/ በወንበዴው ፈንታ ኪራላይሶን /2/ ተሰቀለ ጌታ ኪራላይሶን /2/ ሁሉም ዘበቱበተ ኪራላይሶን /2/ በዘላለም ህየወት ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶን
2971Loading...
06
በኢንጎልስታድት ተወልዶ ያደገውና በእየሱሳውያን የምስጥር ማኅበር ትምህርት ተኮትክቶ ያደገው አዳም ዋይሻፕት የካኖን የሕግ ፕሮፌሰር ማዕርግ በ 1772 እ.ጎ.አ ተቀበለ። የእየሱሳውያን ማኅበር አባል የነበረው ዋይሻፕት የሕግ ፕሮፌሰርነት ማዕርግ ካገኝ በኋላ ግን የራሱ ነጻ የሆነ ሃይማኖታዊና ፖለቲካዊ እይታ በመያዝ ከእየሱሳውያን የምስጥር ማኅበር ራሱን አገለለ። ግንቦት 1, 1776 እ.ጎ.አ "ፐርፈክቲቢሊስት' ማኅበር መሰረተ። ይህ ማኅበር በአሁኑ ጊዜ "ኢሉሚናቲ" በመባል ይታወቃል። ዋይሻፕት የኢሉሚናቲ ማኅበር ከመሰርተ በኋላ ስፓርታክስ የሚል የምስጥር ስም መጠቀም ጀመረ። ጀርመናዊው የመደብ አልባ ስርዓተ ማህበር (communism) ርዕየተ ዓለም አመንጪ ካርል ማርክስ የኢሉሚናቲ ምስጥር ማኅበር አባል ነበር። ኢሉሚናቲ የተመሰረተበት ግንቦት 1 የመደብ አልባ ስርዓተ ማህበር (ላብ አደሮች) ቀን "May Day" በሚል ሽፋንም ይከበራል። ግንቦት 1 እ.ጎ.አ በኢሉሚናቲ ማኅበር አባላት ዘንድ ትልቅ ባዕዳዊ የሆነ ሰነ ስርዓት በማካሄድ የሚከበርበት ቀን ነው። ይህም ሰውን መስዋእት እስከማድረግ ይደርሣል። ስነ ስርዓቱ በጠቅላላ ጥንቆላና የጣኦት አምልኮ በማካሄድ ድከበራል። ኮሙኒስቶች ይህንን በዓል ለማክበር የላብ አደሮች (May Day) የሚል ሽፋን ይጠቀማሉ። እኛም ይህንን በዓል ከማክበርና ከሴራቸው መጠበቅ ይገባናል። ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ ነኝ ከጽዮን ተራራ!
3568Loading...
07
Media files
4608Loading...
08
ፍቅር የአምላክን ልጅ ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው፣ በደል የሌለበትን እንደ በደለኛ ሰቀሉት ፣ ሕይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቈጠሩት አዳምን የፈጠሩ እጆች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ፣ ወዮ ፣ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ፣ ወዮ፣ በአዳም ፊት የሕይወት መንፈስን እፍ ያለ አፍ ከሐሞት ጋራ የተቀላቀለ የኮመጠጠ መጸጻን ጠጣ፣ ወዮ፣  የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው፣ ምን ከንፈር ነው፣ ምን አንደበት ነው?  የፍቁር የጌታ ሕማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል ሕሊናም ይመታል፣ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፣ ሥጋም ይደክማል ፣  የማይሞተው ሞተ፣ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ፣ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ፤  የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት ፣ ወየው፣ ወየው፣ ወየው አማኑኤል አምላካችን፣ ወየሙ፣ ወየው፣ ወየው መድኃኒታችን ኢየሱስ፣ ወየው ወየው፣ ወየው ፡ ንጉሣችን ክርስቶስ፡ ወየው፡ ወየው ወየው ፡ ጻድቃን ከዕንጨት አወረዱት፣ ሥጋውንም ለመገነዝ ከርቤ የሚባል የጣፈጠ ሽቱንና ንጹሕ በፍታን አመጡ፤ ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው የማይሞት የማይለወጥ፣ ከድንግል ማርያም የተወለደ አቤቱ ይቅር በለን ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ፣ ቅዱስ ሕያው ፣ የማይሞት፣ የማይለወጥ፣ በዮርዳኖስ የተጠመቀ በመስቀልም  የተሰቀለ፣ አቤቱ ይቅር በለን፣ አቤቱ ይቅር በለን " ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ  "
5303Loading...
09
ሁሉን የፈጠረ፥ ሁሉን የፈጸመ፥ ሁሉንም የጀመረ፥ ሁሉን የያዘ፥ ሁሉንም የጨበጠ እግዚአብሔር። መላእክትና የመላእክት አለቆች፥ መናብርትና ሥልጣናት፥ አጋዕዝትና ኃይላት፥ ፀሐይና ጨረቃ፥ ከዋክብትም ድርገታትም የሚሰግዱለት፤ ተገዦቹና ጉልቱም ናቸውና። በሁሉ ባለጠጋ ሲሆን ራሱን ከሁሉ ደሀ አደረገ። ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው፥ እስከ ሞትም አደረሰው። አባ ሕርያቆስ
5203Loading...
10
"ሲቀርብም ከተማይቱን አይቶ አለቀሰላት፥ እንዲህ እያለ። ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ስንኳ ብታውቂ፤ አሁን ግን ከዓይንሽ ተሰውሮአል። ወራት ይመጣብሻልና፥ ጠላቶችሽም ቅጥር ይቀጥሩብሻል ይከቡሻልም በየበኵሉም ያስጨንቁሻል፤ አንቺንም በአንቺም ውስጥ የሚኖሩትን ልጆችሽን ወደ ታች ይጥላሉ፥ በአንቺ ውስጥም ድንጋይ በድንጋይ ላይ አይተዉም፥ የመጐብኘትሽን ዘመን አላወቅሽምና።" የሉቃስ ወንጌል 19 : 41-44
5142Loading...
11
📚 ድርሳነ ማሕየዊ (ይህ መጽሐፎ፦ የጌታችንን መከራውን፣ ሕማሙን፣ ስቃዩንና ሞቱን የሚያወሳ ድርሳን ሲሆን ይልቁንም በዚህ የሕማማት ወቅት ልንማጸንበት ይገባናል።) ፩- ድርሳነ ማሕየዊን በሰሞነ ሕማማት ብቻ ሳይሆን የጌታን መከራ እና ውለታ እያሰበ አርብ አርብ ቀን የሚጸልየው ‹‹በነፍሱም በሥጋውም ይከብራል፤ በመንግሥተ ሰማያትም እድል ፈንታው ጽዋዕ ተርታው ጌታችንን ከገነዙት ከኒቆዲሞስ እና ከዮሴፍ ጋር ይሆናል›› ፪- እንዲሁም ‹‹በሰባቱ ጊዜያት የሚጸልየው ሰው ቢኖር በነፍሱም በሥጋው ፈጽሞ ይከብራል፡፡ በመንግሥተ ሰማያትም እድል ፈንታው ጽዋዕ ተርታው እስከ ሰባ ዘመን ድረስ በየቀኑ የጌታውን መከራ እያሰባ ካለቀሰ ከጌታ ባለሟል ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ይሆናል›› የሚል ታላቅ ቃልኪ ኪዳን አለው፡  አራቱ ወንጌላውያንና ጌታችን የመከራውን ነገር ያስተማራቸው ኤልሳቤጥ፣ መልቴዳ እና በርዜዳ የጻፉትን ድርሳነ ማሕየዊን በመጸለይ የጌታን ሕማም ልናስብ እና ከቃል ኪዳኑ በረከት ልንሳተፍ ይገባናል፡፡ ድርሳነ ማሕየዊ ልክ እንደ ውዳሴ ማርያም ከሰኞ እስከ እሑድ የተከፋፈለ በመሆኑ ለመጸለይ አይከብድም፡፡
42411Loading...
12
አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥እጅግ ደስ ይበልሽ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥እልል በዪ እንሆ፥ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው ትሑትም ሆኖ በአህያም፥በአህያዪቱ ግልገል በውርንጫዪቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል። ትንቢተ ዘካርያስ 9፥9
3401Loading...
13
ሰላምሽ ዛሬ ነው ሰላምሽ ዛሬ ነው እየሩሳሌም ወደአንች መጥቷልና አምላክ ዘላአለም/2/  ሆሣእና በአርያም እያሉ ዘመሩ  ሕፃናት በኢየሩሳሌም  አንቺ ቤተልሄም የዳዊት ከተማ የሕዝቦችሽ ብርሃን መጣልሽ በግርማ/2 / ኪሩቤል መንበሩን የሚሸከሙለት መስቀል ተሸከመ ሊሆነን መድኃኒት /2 / የኢየሱስን ሕማም ደናግልም አይተው እያለቀሱለት ሄዱ ተከትለው /2/ 
3661Loading...
14
አንዳንዶቻችሁ flat earthን ማመን ምን ይጠቅመኛል ትላላችሁ። ነገር ግን አስፈላጊነቱ አልታያችሁም። ፍላት ኧርዝ የአምስት መቶ ዓመታትን የሳይንስ፣ የሃይማኖት፣ የፖለቲካ እና የርዕዮተ ዓለም አካሄድ የሚቀለብስ (reverse የሚያደርግ) ነው። ይህንን ነው መረዳት ያለባችሁ። በflat earth የሚያምን ሰው በኢቮሉሽን ሊያምን አይችልም። በቢግ ባንግ ሊያምን አይችልም። በፈጣሪ አለማመን አይችልም። ብዙዎች ክርስቲያን ሆነው ነገር ግን ሃይማኖታቸውን በቀጥታ የሚጻረሩትን የuniverse እና evolution ሀሳቦችን ይቀበላሉ። ሁለቱ ነገሮች (ሃይማኖት እና ኢቭሉሽን) ፍጹም ተቃራኒ እንደሆኑ አያስተውሉም፤ ማስተዋልም አይፈልጉም። ነገር ግን ጉዳዩ በሳይንስ ብቻ የሚወሰን አይደለም። ለሃይማኖት፣ ለፍልስፍና፣ ለፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ጭምር ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ ርዕስ ነው እያነሳን ያለነው። ይህን ለማስረዳት እንዲመቸን አንድ ወቅት ኦባማ የተናገረውን ንግግር ልጥቀስላችሁ፦ "My entire politics is premised on the fact that we are these tiny organisms on this little speck floating in the middle of space,"  "የፖለቲካ አስተሳሰቤ በሙሉ መሠረት የሚያደርገው፦ 'እኛ በአንዲት ዩኒቨርስ ውስጥ የምትንሳፈፍ ትንሽዬ ነጥብ ላይ የምንኖር ጥቃቅን እንስሳት ነን' በሚለው ሀሳብ ላይ ነው" አያችሁ። ዩኒቨርስ የሚባል ነገር ከሌለ፣ ምድር ዝግ አካል ከሆነች፣ እኛ በህዋ ውስጥ የምንንሳፈፍ ጥቃቅን አካላት ካልሆንን፣ የኦባማ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሙ በሙሉ ይፈራርሳል ማለት ነው። እና አንተ የምታደንቀው ፖለቲከኛ በዚህ የሚያምን ከሆነ አንተም በሱ ታምናለህ። ሁሉም ነገር አጋጣሚ ነው ብለህ ታስባለህ። ወደዚህ ዓለም የመጣሁት በዓላማ (purpose) አደለም ብለህ ወደማሰብ ትደርሳለህ። ፈጣሪህ የእውነት ዩኒቨርስን ከፈጠረ፣ ለምንድነው ፀሐይን ከምድር ይልቅ ትልቅ ያደረጋት? ፀሐይ የተፈጠረችው ለአዳም ብርሃን እንድትሆነው አደለም? የት ሀገር ነው አምፖሉ ከቤቱ ሲበልጥ ያየነው? አምፖሉ ነው ቤቱን መዞር ያለበት፣ ወይስ ቤቱ ነው አምፖሉን መዞር ያለበት? ቤቱን ተሸክሞ አንዲት ሻማን የሚዞር ሰው አይታችሁ ታውቃላችሁ? ፈጣሪ ዓለም ለመፍጠር 4 ቢሊዮን ዓመት ያስፈልገዋል? ሰባት ቀን በቂው አይደለም? እስኪ መልሱልኝ። እግዚአብሔር ዓለም የፈጠረው በሰባት ቀን ነው ወይስ በአራት ቢሊዮን ዓመት ነው? ፈጣሪ አንድ ትሪሊዮን የምድር አይነት ፕላኔቶችን ለምን ይሠራል? ምን ያረጉለታል? አንዷ ምድር አትበቃም? ይህች ምድር ላንተ ነው የተፈጠረችው? ነው ወይስ አይደለም? ላንተ ከተፈጠረች ለምን ፀሐይን እንድትዞር አደረጋት? ላንተ ከፈጠራት የዓለም ሁሉ ማዕከል መሆን አለባት ወይስ የለባትም? እግዚአብሔር የሚወድህ ልጁ ነህ ወይስ አይደለህም? መልስህ አዎ ከሆነ አንተን ለመፍጠር ቀድሞ ጦጣ እና ዳይኖሰር መፍጠር ያስፈልገዋል? በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠርክ ፍጡር ነህ ወይስ አይደለህም? ከሆንክ እንዴት ከዝንጀሮ መጥቻሁ ብለህ ታስባለህ? አእምሮ ያለው ሰው እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ። እንዳለ ነብዩ ዳዊት። እንስሳዊነት የተጠናወተውን የዘመኑን ሳይንስ ተከትለህ አትጥፋ ወገኔ።
4846Loading...
15
ይህ የምትመለከቱት በአሜሪካ ባሕር ሃይል የተሰራ "Rail Gun" የተሰኘ እጅግ አደገኛ የጦር መሳርያ ነው። መሳርያው ኤሌክትሮ-ማግኔቲዝምን በመጠቀም የሚሰራ ሲሆን ጥይቱን በ8270 feet/s ወይም 2700 ሜትር በሰከንድ በሆነ ፍጥነት መተኮስ ይችላል። ይህም Mach 8 ወይም የድምጽን ፍጥነት 8 እጥፍ እንደማለት ነው። መሳርያው እስከ 100 ማይል ማለትም 160 ኪሎሜትር ርቀት ያሉ ኢላማዎችን መምታት የሚችል ሲሆን የባሕር ሃይሉ መርከቦች ላይ ተጠምዶ ሙከራ ተደርጎበታል። ታዲያ ይህ መሳርያ ምድር ዝርግ (flat) እንደሆነች ያረጋግጥልናል። እንዴት? መልሱን ቀጥለን እንይ።
4694Loading...
16
ምድር ድቡልቡል ወይም ኳስ ቅርጽ ያላት ከሆነች፣ ካለንበት ቦታ ሆነን ወደፊት ስናይ ምድሪቱ ወደታችን እየወረደች፣ እየወረደች ትመጣለች። ከዚያም ከኛ ሙሉ በሙሉ ትሸፈናለች። ይህንን የሚያደርገው ደግሞ ክቡ ቅርጿ ነው። (ማለትም ምድር ድቡልቡል ከሆነች ያ አይነት ነገር መከሰት አለበት) በዚህም ምክንያት ከኛ እጅግ ርቀው የሚገኙ አካላት በትልቁ ይሸፈናሉ፣ አንዳንድ ነገሮችን እንዲያውም በፍጹም አናያቸውም። ምክንያቱም ከርቩ እንደ ጉብታ ሆኖ በኛና በዚያ አካል መሃል ስለሚቀመጥ። ስለዚህ ይከልለናል። ይህ የሚሆነው አይናችን በቀጥታ (እስትሬት) ያለ ነገርን ብቻ ስለሚያይ ነው። የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ብርሃን ቀጥታ መስመር ይዞ ስለሚሄድ ነው። በተመሳሳይ መልኩም፣ ከላይ ያነሳነው መሳርያ ቀጥታ መስመር ይዞ ነው የሚሄደው። ስለዚህ በሱ ስትሬት ያለ 160 ኪሎሜትር ርቆ የሚሄድን አካል ነው መምታት ያለበት። ነገር ግን ምድር ድቡልቡል ከሆነች ይህ በፍጹም ሊፈጠር አይችልም። ግሎብ ላይ ነገሮች ርቀው ሲሄዱ ምን ያህል ከኛ ይሸፈናሉ የሚለው በፎርሙላ ተሰርቶ አለ። በዚህ ፎርሙላ መሠረት 100 ማይል ወይም 160 ኪሎሜትር ርቀው የሚገኙ አካላት በ2 ኪሎሜትር ከፍታ ይሸፈናሉ። ማለትም ግሎብ ምድር ላይ 160 ኪሎሜትር ላይ ያለ አካል ለማየት ከፈለግን ያ አካል ቁመቱ 2 ኪሎሜትር መሆን አለበት፣ ምክንያቱም የምድር ከርቭ ያንን ያህል ነገሮች ስለሚሸፍን። ስለዚህ ከላይ ያለውን መሳርያ እናስበው። እንዴት ነው 160 ኪሎሜትር ያለ ታርጌት ሊመታ የሚችለው? በዓለም ላይ ከተሰሩ ነገሮች ውስጥ 2 ኪሎሜትር ቁመት ያለው ነገር የለም። ደግሞ መሳርያው ለመርከቦች ታስቦ ነው የተሰራው። ስለዚህ እንዴት ሊሰራ ይችላል? ስለዚህ ምድር ግሎብ አይደለችም ማለት ነው።
5251Loading...
17
Yuval Noah Harari: When the flood comes elite will build an ark and leave the rest to drown Harari, whose middle name happens to be Noah, has a long history of warning about the “technological Noah’s Ark” he believes is destined to save the 'elite' while leaving the rest of humanity to die in a mass casualty event.
4902Loading...
18
በአሁኑ ጊዜ ነገሮች ከመበለሻሸታቸው የተነሳ ሰዎች ስላለው ሁኔታ መናገር ሁሉ አይፈልጉም። በአደባባይ የውስጣቸውን ሀሳብ አይናገሩም ይልቁንስ ተቀባይነት ያለውን ውሸት ይዋሻሉ። ይህ ወደ ፋሺስት ስርአት መግባታችንን ነው የሚያሳየው። በፋሺዝም ስርአት ገዢው ውሸት ነው። ሰዎች በራሳቸው ፈቃድ እውነትን ከመናገር ራሳቸውን ያቅባሉ። ውሸትን ለመናገር ይፈጥናሉ። ደፍሮ እውነትን መናገር እንደ ትልቅ ወንጀል ይቆጠራል። አምላክን የመናገር ያህል ይወሰዳል። እጅግ አደገኛ ስርአት ነው። ወደዚህ ስርአት የመግባታችን ምክንያቱ ደግሞ ውሸትን የሚወዱ ሰዎች መብዛታቸው ነው። እነሱ ሲበራከቱ ለአገዛዙ መንገድን ይጠርጋሉ። የሀሳብ ፖሊስ ይሆኑታል። ከዚያ አንተ የሆነች ነገር ስትል አፍ አፍህን ይሉሃል። ሁሉም ቦታ ይህ ሲደጋገምብህ ዝም ማለትን፣ መዋሸትን እየለመድክ ትመጣለህ። ዶስቶዬቭስኪ እንዳለው ሰዎችን ላለማስከፋት ተብሎ እውነትን ከመናገር የሚታቀቡበት ጊዜ ደርሷል። ፋሺዝም ማለት ይሄ ነው። የፈጣሪ ያለህ ያስብላል።
8754Loading...
19
አሁን ያለው የሀገራችን ሁኔታ ያሳስባል። ወደ አንዱ ማጥ ገባን ብለን ስንገረም ከዛም የባሰ ሌላ ገደል ይጠብቀናል። ነገር ተበላሸ ብለን ተገርመን ሳንጨርስ ከዛም በላይ ተበላሽቶ እናያለን። ሀገሪቷ በኢኮኖሚም፣ በፖለቲካም በሁሉም ነገር እየዘቀጠች፣ እየዘቀጠች እየሄደች ነው። መንግስት ያለውን ብር በጦርነት ጨርሶታል። ከዛ ብር ሲያጥረው የኛኑ ብር ከባንክ ስናወጣና ስንልክ መቁረጥ ጀመረ። ግብር ከአቅም በላይ መጠየቅ ጀመረ... አንዱን ጦርነት ሲጨርስ ደግሞ ሌላ ጦርነት ገባ። እንደሱ ቢሆን በዚኛው ጦርነት... ምንም ምንም እንዳይተርፍ አድርጎ ቀብሮ ያዳፍነን ነበር። ሴማውያን ብሎ የሰየማቸውን ህዝቦች ተራ በተራ እያጨደ ጠራርጎ ሊያጠፋ ነበር። በሱ ቤት እግዚአብሔር የለም። እግዚአብሔር ግን መኖሩን አሳየው። ተራ ገበሬዎችን፣ የደርግ ጊዜ ክላሽ ብቻ የነበራቸው...እየተደራጁ፣ ወደ አንድ እየመጡ... ጥቁር ክላሽ፣ ዲሽቃ፣ መድፍ...እያሉ ወደ ሌላ ደረጃ እየመጡ ነው። መከላከያው ኮለኔሎችና ጄነራሎችን ጭምር እያጣ ነው... ያለውን ሃይል እና ገንዘብ ሁሉ አሟጦ ወደዛ እየላከ፣ የላከውም እየከሰመ ነው። በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን ምንም እንዳልተፈጠረ ልማት፣ ብልጽግና..ወዘተ እያለ ስብከቱ አልቀረም.. በዋናው ከተማ የአክሲዮን ገበያ፣ ካፒታል ማርኬት፣ እስታርት አፕ የመሳሰሉ ደመቅ ደመቅ ያሉ ሀሳቦችን እያሰማ ነው። የውጪ ድርጅቶች ወደ ውስጥ እንዲገቡ፣ የቴሌን የአየር መንገድን አክሲዮን እንዲገዙ፣ ጤፍ ቡና ሰሊጥ እንዲነግዱ መንገድ እየከፈተ ነው። ያ እድገት፣ ብልጽግና፣ መሰልጠንን ያመጣል ተብሎ ታስቧል። ግን ያ ለደሃው ምን ይጨምርለታል? እንኳን ደሃውን፣ ደፋ ቀና ብሎ ጉልት የሚሸጠውም አሁን ህይወቱ አደጋ ላይ ነው። እንዴት ነው ዘመናዊ ትምርህት ያልተማረ፣ የፋይናንስ እውቀት ያልቀሰመ ደሃ ከፈረንጅ ነጋዴ ጋ የሚወዳደረው? አይችልምኮ። አይመጣጠንም። ደሃውን ከድህነቱ የሚያወጣ ነገር አደለም ይሄ። ይልቅስ "ዘመናዊ ሁን ከጊዜው ጋ ተጓዝ፣ መጓዝ ካልቻልክ ትበላለህ" ነው እየተባለ ያለው። ትበላለህ በቃ። ደሃ ሆንክ አልሆንክ ጣጣው አደለም። survival of the fittest ነው። ዳርዊኒዝም በተግባር ሊተገበር ነው በቃ። አቅም ያለው ብልጥ የሆነው አምልጦ ይወጣል። ዶላርና ክሪፕቶ እየነገደ ሚሊዬነር ይሆናል። ምስኪኑ ደሃ ደግሞ በቃ በረሃብ ያልቃል። አለፍ ሲልም ባርያ ይሆናል። ሌላ outcome የለውም። በቃ ለደሃ ያለው ቦታ ይህ ነው። "ደሃ ተበደለ ፍርድ ተጓደለ" የሚለው የጥንቱ አባባል አሁን አይሰራም። "የታባቱ ለምን ድራሹ አይጠፋም" ነው የአሁኑ ፖሊሲ። በቃ ሀብታም መሆን አለብህ። ሰርተህ ለፍተህ ሊሆን ይችላል፣ ወይም ክሪፕቶ ነግደህ ሊሆን ይችላል፣ ወይ ቲክቶክ ሰርተህ፣ ወይም ደግሞ ዋሽተህ ሰርቀህ አጭበርብረህ ሊሆን ይችላል እስካልተያዝክ ድረስ... ብቻ የሆነ ነገር ይኑርህ። አንተ ታመልጣለህ። ሌላው እንደ ኖህ ዘመን ጎርፍ ቢወስደው አንተ አምልጠሃል ስለሱ አይመለከትህም። አሁን ላይ እየመጣ ያለው አስተሳሰብ እንዲህ አይነት ነው። ፈረንጆቹ ያሰቡልን የ eugenics ድግስ ሊተገበር ነው፣ ልንጠፋ...በቃ በነሱ ቤት እግዚአብሔር የለም...ደሃ ያልቃል ይጠፋል....
8033Loading...
20
📕አባቴና እምነቱ 📌የአለቃ አያሌው ታምሩ የሕይወት ታሪክ @amhbook1
5594Loading...
21
#በጌቴ ሴማኔ~~ በጌቴ ሴማኔ፣ በአትክልቱ ቦታ(2) ለእኛ ሲል ጌታችን፣ በዓለም ተንገላታ(2) አዳምና ሔዋን፣ ባጠፉት ጥፋት(2) እኛም ነበረብን፣ የዘላለም ሞት(2) መስቀል ተሸክሞ፣ ሲወጣ ተራራ(2) ይገርፉት ነበረ፣ ሁሉም በየተራ(2) ድንግል አልቻለችም፣ እንባዋን ልትገታ(2) እያየች በመስቀል፣ ልጇ ሲንገላታ(2) በአምላክነቱ፣ ሳይፈርድባቸው(2) እንዲ ሲል ፀለየ፣ አባት ሆይ ማራቸው(2) በረቂቅ ሥልጣኑ(ጥበቡ)፣ ሁሉን የፈጠረ(2) በሰዎች ተገርፎ፣ ሞተ ተቀበረ(2) ፍቅሩን የገለጸው፣ ተወልዶ በስጋ(2) ኢየሱስ ጌታ ነው፣ አልፋና ኦሜጋ(2) በመስቀል ተሰቅሎ፣ እንዲያ እየቃተተ(2) አለምን ለማዳን፣ የማይሞተው ሞተ(2) ከሞት ሊታደገን፣ በመጣልን ፈጥኖ(2) መስቀል አሸከሙት፣ ውለታው ይህ ሁኖ(2) መከራውን ሳስብ፣ ሳስታውስ ቀኑን(2) ይቆስላል ይደማል፣ ልቤ በሃዘን(2) መች ለራሱ ነበር፣ ይሁሉ መከራ(2) መስቀል ተሸክሞ፣ የወጣ ተራራ(2) ሲያጎርሱት ሚናከስ፣ ሰው ክፉ ነውና እውሩን ቢያበራ ጎባጣን ቢያቀና ጌታዬን ሰቀሉት፣ አይሁድ ጨከኑና(2) ምነው አያሳዝን፣ የአይሁድ ክፋት(2) የዝናቡን ጌታ፣ ውሃ ሲነፍጉት(2) በተንኮል በሃጢያት፣ ቀሩ እንደሰከሩ(2) ሙታን ከመቃብር፣ ተነስተው ሲያስተምሩ(2) እናታችን ሄዋን፣ ወዮ በይ አልቅሺ ያንቺን ህመም፣ ታሞ ከሞት ሊያድንሺ የህያዋን ጌታ፣ ተሰቀለልሺ(2) አዬጉድ አዬ ጉድ፣ አለም የዃላሽ(2) መድሃኒት ክርስቶስ፣ በግፍ ሞተብሽ(2) በመስቀል ተሰቅሎ፣ ስጋውን ሲቆርስ በችንካር ተወግቶ፣ ደሙንም ሲያፈስ ዋለች በመከራ፣ ድንግል(እናት) ስታለቅስ(2) ሰውነትሽ ራደ፣ ሃዘን ከበበሽ ስቃይ መከራውን፣ ዳግም ፀናብሽ ተሰቅሎ ስታይው፣ አንድ አምላክ ልጅሽ(2) ቢፈስም እንባዬ ሆኖ መንታ መንታ መች ዋጋ ይሆናል ለአንዲቱ ጠብታ ላለቀሺው ለቅሶ፣ ድንግል(እናት) የዚያን ለታ(2) ባለቀሺው ለቅሶ፣ በልጅሽ ህመም(2) ከሃጢያት ነፃሁኝ፣ ዳንኩኝ ከገሃነም(2)
6969Loading...
22
Media files
5476Loading...
23
ይህኛው የተሻለ ቅጂ ነው። ጽሑፉም የተሻለ ይነበባል ሳይዙም መጠነኛ ነው።
6111Loading...
24
መጽሐፈ አክሲማሮስ https://t.me/religious_books_lover
6569Loading...
25
crypto... and... "meme magic"
7231Loading...
26
crypto and memes...
6171Loading...
27
"ምድር ክብ መሆኗን የምናውቀው መርከቦች ከኛ እየራቁ ሲሄዱ ስለሚደበቁ ነው" የሚለው ሀሳብ ውድቅ መሆኑ በተደጋጋሚ በማስረጃ እየተረጋገጠ ነው።
7412Loading...
28
7 Rockets Hit Dome!
6582Loading...
29
#ጠፈር #firmament ምንድነው? ቋንቋ በተፈጥሮው ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ይሞታል። አንድ ቋንቋ የማደግ ደረጃ ላይ ባለበት ወቅት፣ አዳዲስ ቃላትን፣ ሀረጋትን አልፎም አገላለጾችን(expressions) እና አባባሎችንም ያዳብራል። ይህም የራሱን ቃላት በማርባት አዳዲስ ቃላት በመፍጠር አልያም ከሌሎች ቋንቋዎች በመዋስ ሊሆን ይችላል። አንዳንዴም ከሌሎች ቋንቋዎች የተቀበላቸውን ቃላት በራሱ ቋንቋ ውስጥ አቻ ቃል በመፈለግም ሊሆን ይችላል። እነዚህ ነገሮች ታዲያ፣ በሀገራችን ዘመናዊ ትምህርት ሲገባ የሀገራችን ሰው የውጪውን ዓለም እውቀት፣ ጥበብ፣ ፍልስፍና፣ ባህል ወደ ራሱ ለማዋሃድ ጥቅም ላይ አውሎታል። የዚህም ውጤት በየቦታው፣ በየትምህርት ዘርፉ እናያለን። ከተነሳንበት ርዕስ አንጻር ስናየውም፣ የሀገራችን ሰው የተለያዩ የአስትሮኖሚ ቃላትንና ሀሳቦችን በሀገርኛ ቋንቋ ለማቅረብ ሞክሯል። ከነዚህም የተቻለውን ያህል ቃላት በሀገርኛ አነጋገሮች ተክተናል። የዚህም ምሳሌ እንደ ስነ ፈለክ፣ ህዋ፣ ጠፈር፣ የመሳሰሉትን ቃላት ማንሳት እንችላለን። ታዲያ ይህን ስናይ፣ አንድ ሳናስተውል ያለፍናቸው ነገሮች ይኖራሉ። ይህም ለምሳሌ "ጠፈር" የሚለውን ቃል ብናየው፣ በተለምዶው በሳይንሱ የምናውቀውና የቃሉ ኦሪጂናል ትርጉም ምን ያህል እንደሚለያዩ ያስተዋልን አይመስልም። ቃሉን በተለምዶ የምንጠቀምበት "space" ወይም "universe" የሚሉትን ሀሳቦች ለመግለጽ ነው። ይህም ከምድር ውጪ ያለውን ሰፊ አካባቢ ሲጠቁም ነው። የቃሉ የመጀመሪያ ትርጉምስ? ይህን ቃል ከሃይማኖታዊ እይታ ስናየው የሚከተለውን ትርጉም ይዞ እናገኘዋለን፦ 1. ኦሪት ዘፍጥረት 1፥ 6-8  እግዚአብሔርም። በውሆች መካከል #ጠፈር ይሁን፥ በውኃና በውኃ መካከልም ይክፈል አለ። እግዚአብሔርም #ጠፈርን አደረገ፥ ከጠፈር በታችና ከጠፈር በላይ ያሉትንም ውኆች ለየ ፤ እንዲሁም ሆነ።  ፤ እግዚአብሔር #ጠፈርን #ሰማይ ብሎ ጠራው። ማታም ሆነ  ጥዋትም ሆነ፥ ሁለተኛ ቀን። 2. ኦሪት ዘፍጥረት 1፥14-15 እግዚአብሔርም አለ። ቀንና ሌሊትን ይለዩ ዘንድ  ብርሃናት #በሰማይ_ጠፈር ይሁኑ ፤ ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት  ለዓመታትም ይሁኑ ፤ በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር ብርሃናት  ይሁኑ ፤ እንዲሁም ሆነ። 3. ኦሪት ዘፍጥረት 1:20   እግዚአብሔርም አለ። ውኃ ሕያው ነፍስ ያላቸውን ተንቀሳቃሾች ታስገኝ፥ ወፎችም ከምድር በላይ #ከሰማይ_ጠፈር_በታች ይብረሩ። 4. መዝሙረ ዳዊት 19(20)፥1 ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ #የሰማይም_ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል። ሌሎችም ቦታዎች ላይ ይህ ቃል ተጠቅሷል። ከዚህ የምንረዳው ታድያ፣ ጠፈር ማለት ከምድር በላይ ያለ፣ አካል ሲሆን ይኸውም በሌላ አገላለጽ ሰማይ ማለት እንደሆነ ይነግረናል። ጠፈር ማለት ጠንካራ፣ ምድርን እንደጉልላት የሸፈነ፣ ብርሃናት (ማለትም ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ክዋክብት) ልክ ኮርኒስ ላይ እንዳለ መብራት እርሱ ላይ ያሉት አካል እንደሆነ ይነግረናል መጽሐፉ። ይህም በሳይንስ ከለመድነው ወጣ ያለና ተቃራኒ የሆነ ነው። በሳይንስ መሠረትም ይህ አካል የለም፣ ሊኖር አይችልም ። ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሰዎች የተለያዩ ሙከራዎችን አድርገው ይህ አካል በርግጥም እንዳለ ለማሳየት ሞክረዋል። ይህውም አነስተኛ መንኩራኩሮችን ሰርተው ላያቸው ላይ ካሜራ ከገጠሙ በሁዋላ ማምጠቅ ነው። ከዚያም መንኩራኩሩ ከአንድ አካል ጋር ይጋጫል ወይስ አይጋጭም የሚለውን ለማየት የተለያዩ ሙከራዎችን አድርገዋል። ይህንንም በቪዲዮ የምናይ ይሆናል።
6440Loading...
30
አሁን ማነው ያለ ማስረጃ ያመነው😁😁😁
6020Loading...
31
Eratosthenes never proved the curvature of the earth It is claimed that the ancient Greeks already knew that the earth is spherical and Eratosthenes with his experiment on the curvature of the earth is mentioned as the ultimate proof. Problem: On a flat earth with local, smaller sun basically the same result comes. The different angles of the shadows prove nothing but the nonexistence of the valid arguments for the globe. Eratosthenes ምድር ግሎብ መሆኗን አላሳየም። የጥንት ግሪኮች ምድር ድቡልቡል መሆኗን ያውቁ ነበር ይባላል። እና ኢራቶስቴኔስ በሙከራው የምድርን ክብነት (curve) አሳይቷል በማለት ለምድር ግሎብ መሆን እንደ ትልቅ ማሰረጃ ያቀርባሉ። ችግሩ ግን፣ ዝርግ ምድር ላይ እና ፀሐይ ቅርብ እና ከምድር አነስ ያለች ከሆነች ሙከራው ተመሳሳይ ውጤት ያመጣል። በሙከራው የተገኘው የተለያዩ እንጨቶች የተለያየ ርዝማኔ የተገኘባቸው ምድር ግሎብ መሆኗን ያሳያል ይባላል። ነገር ግን የጥላዎቹ መርዘም በዝርግ ምድር ላይም የሚታይ በመሆኑ ምድር ግሎብ ለመሆኗ ማስረጃ ሊሆን አይችልም። ስለዚህ አንዱ እንደ ማስረጃ የሚያቀርቡት ሙከራ እንኳ ግሎብን prove አያደርግም። ስለዚህ ምድር ግሎብ ለመሆኗ ምንም ማስረጃ የለም ማለት ነው😁😁😁
6240Loading...
32
ይሄን ቻናል ከጀመርኩ ወዲህ ብዙ ሰዎች አጋጥመውኛል። እውነትን ለመረዳት የሚፈልጉ እንዳሉ ሁሉ ጉዳያቸው ያልሆነም አሉ። የቀለዱ፣ ያላገጡ፣ በተለያዩ መንገድ ውይይታችን ለማጨናገፍ የሞከሩ አሉ። ብዙዙዙ ነገር ችለን አልፈናል። ይሄን ቻናል ዝጋው ምንም አያደርግልህም እስከማለት የደረሱ አሉ። የድሮውን ግሩፕ ለመዝጋት እስከደርስ ድረስ በጣም ያስቸገሩ ስዎች ነበሩ። ውይይት ግሩፑ እንደ አሁኑ ህይወት ዘርቶበት የምታዩት እነዛን ሰዎች ጠራርገን ስላወጣን ነው። ለብዙዎች flat earth ቀልድ ነው። ሌሎችም በዚህ ቻናል የሚተላለፉ ርዕሶች ለነሱ መዝናኛ ናቸው። ሰዎች አንተን እንደቲቪ ቁጭ ብለው ቢያዩ ደስ ይላቸዋል። ብቻ ብዙ ነገር አሳልፏል ይሄ ቻናል😂😂😂 እና flat earth ላይ ሲቀልዱ ሲያላግጡ ያ ሁሉ አልፎ ዛሬም ግን ሀሳቡ አልጠፋም😂😂 አንድ ነገር እውነት መሆኑን ምታቁት በዚ ነው። አዋቂ ነኝ ጥበበኛ ነኝ ያለው ሁሉ ቀልዶበት አላግጦበት ሊያጠፋው ሞክሮ ሁሉ ከዓመታትም በኋላ ሀሳቡ ካልጠፋ የሆነ እውነት አለው ማለት ነው። እና ያም አልፎ ግን አሁንም የማይቀበሉት ብዙዎች አሉ። እና አሁን ላይ ደግሞ ተቃውሞአቸውን smart በሆነ መንገድ ሊያሳዩ የሚሞክሩ አይተናል። አንዳንዶች ደግሞ በግልጽ መቀለድና ማላገጥ አይታይባቸውም ግን ረቀቅ ያለ ሀሳብ ወይም መከራከሪያ ሀሳብ አቅርበው በዛ ለማጥቃት ይሞክራሉ። በሀሳብ ደረጃ ማንኛውም ሀሳብ አይከፋም አስፈላጊም ከሆነ ለውይይት ይቀርባል። ነገር ግን በውይይት ውስጥ የተደበቀ ስድብ፣ አልያም እውነታን እያጣመሙ ለማቅረብ የሚደረጉ ነገሮች ያስቸግራሉ። "በሁለት ነገሮች መሃል correlation የለም" የሚለው የተለመደ የሳይንስ ወዳጆች ንግግር ነው። ብዙ ጊዜ conspiracy theory የሚያጋልጡ ሰዎችን የሚያጠቁበት መንገድ ነው። correlation የለም ማለት በሌላ ቃል ሁለት ክስተቶች መሃል ግንኝኙነት የለም ስለዚህ ያንተ ሀሳብ በማስረጃ አልተደገፈም ማለት ነው። በማስረጃ ካልተደገፈ ደግሞ መሠረት የለውም በቃ ተራ conspiracy ነው ማለት ነው። አጋጣሚ ነው እንዳልነው😁😁 እና በዘመናችን ደግሞ conspiracy አለማመን እንደ ስልጣኔ ነው የሚቆጠረው😁😁 ማስረጃ ያለውን ነገር ብቻ ነው ማመን ያለብህ😁😁 wall street በአይሁዶች እንደሚዘወር ማስረጃ የለህም ምክንያቱም ሁለቱ መሃል correlation የለም😁 በግሎብ ማመን ፈጣሪን እንደሚያስክድ ማስረጃ የለህም ምክንያቱም ሁለቱ መሃል correlation የለም😁 እምነት የለሽ መሆን የሞራል ዝቅጠት እንደሚያመጣ ማስረጃ የለህም ምክንያቱም ሁለቱ መሃል correlation የለም😁😁😁 የሚገርመው ግን እነዚህ ሁሉ ማስረጃ ያላቸው መሆኑን ነው😂😂😂 - wall street ውስጥ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያላቸውን ሰዎች ማንነታቸውን ብትፈትሹ አይሁድ ሆነው ታገኟቸዋላችሁ😁 -- እምነት የለሽ መሆን የሞራል ዝቅጠት ያመጣል የሚለውን ለማየት የምዕራቡን ዓለም ተመልከቱ። ምዕራባውያን እምነት የለሽነትን atheismን እንደ ፖሊሲ የፖለቲካ ስርአታቸው ውስጥ ካስገቡ በኋላ ነው ጭምልቅልቅ ያሉት። ግብረሰዶም lgbt የተስፋፋው ከዛ በኋላ ነው። - ግሎብ ማመን ፈጣሪን እንደሚያስክድ ለማየት ቲዮሪውን የሚያቀነቅኑ ሰዎችን እዩ😂 እንዳለ atheist ናቸው። Even እነ ኒውተን የግሎብ ቲዎሪ ትልቁ መሠረት የሆነውን universal gravitation ኒውተን ከፈለሰፈ በኋላ atheism እንደ ማዕበል ነው የሰፋው ይሄ በታሪክ የተቀመጠ ነው። ማንኛውም Atheist ብትጠይቁት በግሎብ ቲዎሪ የሚያምን ነው። ሰፊ ዩኒቨርስ ትልልቅ ፕላኔቶች ወዘተ ብሎ የሚያቀነቅን ነው። በተቃራኒው ሌላ የዓለም ምልከታ ወይም አረዳድ ያለው ኤቲስት ደግሞ አታገኙም። ሳይንስን የሚጠላ ኤቲስት የለም ሁለም ኤቲስት የሳይንስ አፍቃሪ ነው።😁😁 እምነታቸው እስኪመስል ድረስ😁😁 እንደውም በዛ ይፎገራሉ ብዙ ጊዜ እነዚህ ነገሮች በቂ ማስረጃ አላቸው። ጥያቄው ማስረጃውን ለማየት ፍላጎት አለን ወይ የሚለው ነው። እኛ ማየት ካልፈለግን እውር መሆን በጣጣጣም ቀላል ነው። ማስረጃውን አፍነን ይዘን ምንም ማስረጃ የለም ልንል ሁሉ እንችላለን። ማስረጃውን ባላየ አልፈን ምንም ማስረጃ የለም ልንል እንችላለን። ሰው ማስረጃ እያቀረበልን ሁሉ ሀሳቡን አጣመንበት ሀሳቡን በትነን ምንም ማስረጃ ያላቀረበ ልናስመስል ሁሉ እንችላለን። እውነትን ማመን ካልፈለግን መጥመም ቀላል ነው። ግን ያ ጥሩ አይደለም ወደ እውነት የሚመራን ቅንነት ነው። እባካችሁን ቅን እንሁን። የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል፦ እግዚአብሔር ጻድቅ ነውና፥ጽድቅንም ይወዳ፟ል ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች።   መዝሙር 11 (በኦርቶዶክሱ 10) ቁጥር 7
5391Loading...
33
እውነት ስለሆነ እውነት ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ  ዋለ ባደባባይ ሲሰደብ ሲከሰስ  የሀሰት ዳኝነት አምላክን ወቀሰው  ህይወት ሰጠን እንጂ ጥፋቱ ምንድነው/2/  ከቃሉ እብለትን ባያገኙበትም  ዝምታውን አይተው አላዘኑለትም  ባላወቁት መጠን ጠሉት ካለበደል  ጥፋቱ ምን ይሆን የሚያደርስ ከመስቀል/2/  የልቡን ትህትና ፍቅሩን ሳያስተውሉ  ቸሩ ጌታችንን አቻኩለው ሰቀሉ  እሩህሩሁን ጌታ ቸንክረው ሰቀሉት  ሞትን አስውግዶ ቢሰጣቸው ህይወት/2/  ስለ ቸርነቱ ስድብን ከፈሉት  ስለ ርህራሄው የሾህ አክሊል ሰጡት  ሀሞትና ከርቤ ሆምጣጤ ደባልቀው  መራራ አስጎነጩት ጨክኖልባቸው/2/  ፈውስን ለሰጣቸው ልባቸውን ሞልተው  አሉት ወንበዴ ነው ስቀለው ስቀለው  ከጁ በረከትን የተሻሙ ሁሉ  ይጮሁ ነበረ ይገደል እያሉ/2/
5424Loading...
34
ከመሞቱ ከጥቂት ወራት በፊት ነበር። የ world economic forum ላይ ቀርቦ ሲናገር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ክፍት አላደርግም ብሎ በጣም አሳማኝ ምክንያት አቅርቦ የተከራከራቸው። አፋቸውን ከፍተው ነው ያዳመጡት። ኢኮኖሚውን ክፍት ብናረግ በአንድ ቀን መታችሁ ባዶ ታደርጉናላቹ የናንተን ትልልቅ ድርጅቶች አይነት ልምድና እውቀት የለንም... ምንም እንደምትሰሩ ሁሉ ላናውቅ እንችላለን ነበር ያለው። መቶ በመቶ ትክክል ነበር። በሌላ ነገር ላትስማሙ ትችላላችሁ ግን በዚህ ጉዳይ ልክ ነበር።
6082Loading...
35
Media files
5727Loading...
36
ከአንዱ ርዕስ ተነስቼ ብዙ ቦታ ደርስኩ😂😂😂 ይቅርታ ቻሉት እንግዴህ
5970Loading...
37
ከነጥባችን አልወጣንም። ይህ ምሳሌ የተነሳበት ምክንያት አለው። ከላይ በጽሑፉ የተገለጸው ትልቅ ሴራ ነው። ነገር ግን ስዎች አይረዱትም። አለ ብለውም አያምኑም። በየጊዜው በዚህ ሴራ ይጠቃሉ። ሁሌ ይከስራሉ። ሁሌ ቁማሩን ይበላሉ። ይህ የተለያዩ ምክንያቶች አሉት። አንደኛው፣ ቁማር ሱስ ስለሚያስይዝ ነው። እናም ስዎች እየተበሉም ቢሆን ሱሳቸው አይተዋቸውም። ዛሬ እበላ ነገ እበላ እያሉ ዘላለም ያንኑ ነገር ይደጋግሙታል። አንዳንዶች እንደሚሉት ደግሞ በሳይንስ ሲጠና ሰዎች ሱስ የሚይዛቸው ቁማርን ከመብላት ብቻ አደለም። ከመበላትም ጭምር ሱስ ይይዛቸዋል። የሚገርም ነው። ሌላው ምክንያት ደግሞ ዋናው ነጥባችን ነው። እነዚህ ሰዎች የሚበሉበት ትልቁ ምክንያት በሴራ ስለማያምኑ ነው። አክሲዮን ገበያው በሙሉ በአጋጣሚዎች የተሞላ ነው፣ ማንም ምንም አያውቅም ብለው ስለሚያምኑ ነው። ቢሊዮነሮች ቢሊዮነር የሆኑት ከኔ የተሻለ መቆመር ስለሚችሉ ነው እንጂ ጨዋታውን ቀድመው ስለበሉት ወይም ከውስጥ መረጃ ስለተሰጣቸው ነው ብሎ አያስብም። ያው ቁማርም አድርጎ አያስበውም በርግጥ። ቢያንስ በሰው ፊት ቁማር መሆኑን አያምንም። እናም ሁሉም ነገር አጋጣሚ ነው እንጂ ሴራ አደለም ብሎ ያስባል። ከመጋረጃ ጀርባ ያሉ አካላት የሚለውን አእምሮው በፍጹም አያስበውም። በእቅድና በዓላማ ስርአቱን የሚዘውር፣ ገበያውን የሚያሽከረክር የበላይ አካል አለ የሚል እሳቤ ፈጽሞ ወደ አእምሮው አይመጣም። ያ ለምን ሆነ? ስንል ቀድሞውኑ የተመሠረተበት የዓለም እይታው ወይም ምልከታው ነው። በሱ ምልከታ ዓለም በአጋጣሚ ነው የተፈጠረችው። ሰውም በአጋጣሚ ነው ከዝንጀሮነት የወጣው (ማለትም ዝንጀሮ ሆኖ ሊቀር ይችል ነበር)። ስለዚህ ዓለም ሁሉ አጋጣሚ ናት፣ ዝብርቅርቅ ናት፣ chaos, entropy ናት ብሎ ነው የሚያምነው። ንግድ የመጣው ፈጣሪ ለመነገድ የሚያስችል አእምሮግ ስለሰጠን ሳይሆን ሰዎች ከዋሻ ነዋሪነት ወጥተው በመንደር መኖር ስለጀመሩ ነው ብሎ ነው ሚያስበው። የሰው ልጅ ባህል ያዳበረው ልክ እንደ ኢቮሉሽን በዝግመተ ለውጥ ነው ብሎ ነው የሚያምነው። በመላው ህይወቱ ይህንን አስተሳሰብና ፍልስፍና ነው የሚያራምደው። እንደ እምነት ተቀብሎታል። በዚህም ምክንያት ከበላዩ ያሉ አካላት እንደ በግ ይነዱታል። በመስመር እንዳይወጣም ይህንን የኢቮሉሽን እምነቱን በሚዲያ፣ በትምህርት፣ በመጻሕፍት ሁሉ ያዳርሱታል። በየጊዜው አዳዲስ ቲዮሪ፣ አዳዲስ መጽሐፍ፣ አዳዲስ የሚዲያ ፕሮግራም እያዘጋጁ ይህ አስተሳሰብና የዓለም ምልከታ ከሰው አእምሮ እንዳይጠፋ ማገድ ያቀብሉታል። ሰውም በዚህ ምክንያት በስጋውም በነፍሱም ተጎድቶ ከፈጣሪው ተጣልቶ ይቀራል። አሁን ደግሞ ይህ ስርአት ወደ ሀገራችንም እየመጣ ነው። የአክሲዮን ገበያን ለመጀመር የህግ ስርአቱን ጨርሰው ገበያውን ሊጀምሩት ነው። የውጪ ድርጅቶችንም ወደዚህ እያስገቡ ነው። ከዛ...ድሮም ያለችን ብር ትንሽ ናት...እሷንም አሟጠቅ ጨርሰው😂😂 ከመናጢ ደሃ ላይ ሊዘርፉ ማለት ነው😂😂😂 ከደሃ ቡሃላ ምንድነው ያለው? ወደዛ ነገር ሊያሸጋግሩን ነው። መለስ እንኳ በአቅሙ የከለከለውን ነገር ይሄኛው መንግስት ግን ተገበረው😂😂 ምናልባት መለስን የገደሉት ለዛ ይሆናል። እስካሁን ጥሩ አገልግለሃል ከዚ በላይ ግን ሀገሪቷን ክፍት ልታረግልን አልቻልክም...ስለዚህ በቃ አንተ ዞር በልና አሁን ደሞ ወጣቶቹ በተራቸው ይሞክሩ... ተብሎ ይሆናል😂😂😂
6932Loading...
38
የዚህ ዋጋ አለመታወቁ የአክሲዮን ገበያውን አንድ ትልቅ ቁማር ቤት ያደርገዋል። ቁማር ቤቶች እንደሚታወቀው ደግሞ ቁማሩን fix አስደርገው እንደሚበሉ ይታወቃል። ከዚህ በፊትም እንዳነሳነው። በእግር ኳስ ጨዋታ ላይ fix አስደርገው በሚሊይኖች የሚቆጠሩ ገንዘቦችን እንደሚበሉት ማለት ነው። የ wall streetን የአክሲዮን ገበያም ዋጋውን የሚቆጣጠሩ፣ የሁሉንም ሻጭና ገዢ ዳታ የያዙ ከመጋረጃው በስተጀርባ አሉ። እነዚህ ሰዎችም የፈለጉትን ድርጅት እያከሰሩ፣ የፈለጉትን ሀብታም እያደረጉ ይሄዳሉ። በዚህም የቱ አክሲዮን እንደሚቀንስ የቱ እንደሚጨምር ስለሚያውቁ ቁማሩን ይበሉታል። ለምሳሌ አንዱ መንገድ ይህ ነው። የአንድ ድርጅት ትርፍ በጣም ይጨምርና በጣም ብዙ ስዎች አክሲዮን ይገዛሉ። ከዛ ግን ድርጅቱ ይከስርና አክሲዮኑ በጣም ይቀንሳል። ሰዎችም ስለሚከስሩ አክሲዮናቸውን በወረደ ዋጋ ይሸጣሉ። የዚህን ጊዜ ከመጋረጃ ጀርባ ያሉት አካላት የሁሉንም ሰው አክሲዮን በዛ በሞተ ዋጋ ይገዛሉ። ከዛም ትንሽ ቆይተው ድርጅቱ ትርፍ እንዲያገኝ ይደረግና አክሲዮኑ ከልክ በላይ ይጨምራል። የዚህን ጊዜ ልሎችም ብዙ ሰዎች ያንን አክሲዮን መግዛት ይጀምራሉ። ሱስ ስለሆነባቸው😂😂። እናም አክሲዮኑን በወረደ ዋጋ የገዙት አካላት አሁን በጣም ከፍ ባለ ዋጋ ይሸጡታል። በዚህም በሚሊዮኖችና በቢሊዮኖች የሚገመት ገንዘብ ያተርፋሉ። ይህም አዙሪት ይቀጥላል።
4243Loading...
Photo unavailableShow in Telegram
Crypto...
Show all...
👍 1😁 1
እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤው በዓል አደረሳችሁ። ክርስቶስ ተንስአ እሙታን  -- ክርስቶስ ከሙታን ተነሳ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን  -- በታላቅ ኃይልና ስልጣን አሠሮ ለሠይጣን  -- ሰይጣንን አሰረው አግዓዞ ለአዳም    -- አዳምን ነፃ አወጣው ሰላም -- ሰላም እምይእዜሰ -- ከዛሬ ጀምሮ ኮነ  -- ይሁን ፍስሃ ወሰላም -- ፍስሃና ሰላም! +++++++++++++++++++ በሞቱ ሞታችንን ሲሽር በትንሣኤው ትንሣኤያችንን አወጀልን፣ አጎናፀፈን። መልካም በዓል።
Show all...
9👍 6
Photo unavailableShow in Telegram
#ለቤተክርስቲያን_ብለህ ለቤተክርስቲያን ብለህ ልትቀድሳት በደምህ በአደባባይ በጥፊ ተመታህ። ንጹሕ ክርስቶስ በአዳም ጥፋት ልትወቀስ በከንቱ ልትከሰስ አመላለሱህ ከጲላጦስ ወደ ሄሮድስ ሁሉን ቻይ ሳለህ ምንም ማድረግ ሳይሳንህ በአይሁድ እጅ ተገረፍህ! ወዮ! ወሰን ለሌላት ትዕግስት ስለኛ ብለህ መከራ ተቀበልህ ምንም በደል ሳይኖርብህ አምላክ በእንጨት መስቀል ላይ ሰቀሉህ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ
Show all...
11👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጓል መልክና ውበት የለውም፥ባየነውም ጊዜ እንወደ፟ው ዘንድ ደም ግባት የለውም። የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥እኛም አላከበርነውም። በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሟል እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። ርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ስለ በደላችንም ደቀቀ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በርሱ ላይ ነበረ፥በርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ትንቢተ ኢሳይያስ 53፥ 2 - 5
Show all...
10
ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶን/3/ ኪራላይሶን /2/ አማኑኤል ጌታ ኪራላይንሶ /2/ በጥፊ ተመታ ኪራላይሶ /2/ አለምን ሊታደግ ኪራላይሶን /2/ ተነዳ እንደበግ ኪራላይሶን /2/ አዳምን ሊፈውስ ኪራላይሶን /2/ ቆመ ከጵላጦስ ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶን/3/ ኪራላይንሶ /2/ እጁን ቸነከሩት ኪራላይሶን /2/ አጥንቱን ቆጠሩት ኪራላይሶን /2/ የእሾህ አክሊል ደፍቶ ኪራላይሶን /2/ ገዳዩን እረቶ ኪራላይሶን /2/ የሁላችን በደል ኪራላይሶን /2/ ተሻረ በእርሱ ቁስል ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶን/3/ ኪራላይሶን /2/ እጣ ተጣጣሉ ኪራላይሶን /2/ ልብሱን ተካፈሉ ኪራላይሶን /2/ ለፍርድ ተወሰደ ኪራላይሶን /2/ እንደበግ ታረደ ኪራላይሶን /2/ ለብሶ ከደም ሜዳ ኪራላይሶን /2/ ተከፈለ እዳ ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶ ኪራላይንሶ /3/ ኪራላይንሶ /2/ ሆምጣጤ አጠጡት ኪራላይሶን /2/ በገመድ ጎተቱት ኪራላይሶን /2/ በወንበዴው ፈንታ ኪራላይሶን /2/ ተሰቀለ ጌታ ኪራላይሶን /2/ ሁሉም ዘበቱበተ ኪራላይሶን /2/ በዘላለም ህየወት ኪራላይሶን ኪራላይሶን ኪራላይሶን
Show all...
👍 2 1
Photo unavailableShow in Telegram
በኢንጎልስታድት ተወልዶ ያደገውና በእየሱሳውያን የምስጥር ማኅበር ትምህርት ተኮትክቶ ያደገው አዳም ዋይሻፕት የካኖን የሕግ ፕሮፌሰር ማዕርግ በ 1772 እ.ጎ.አ ተቀበለ። የእየሱሳውያን ማኅበር አባል የነበረው ዋይሻፕት የሕግ ፕሮፌሰርነት ማዕርግ ካገኝ በኋላ ግን የራሱ ነጻ የሆነ ሃይማኖታዊና ፖለቲካዊ እይታ በመያዝ ከእየሱሳውያን የምስጥር ማኅበር ራሱን አገለለ። ግንቦት 1, 1776 እ.ጎ.አ "ፐርፈክቲቢሊስት' ማኅበር መሰረተ። ይህ ማኅበር በአሁኑ ጊዜ "ኢሉሚናቲ" በመባል ይታወቃል። ዋይሻፕት የኢሉሚናቲ ማኅበር ከመሰርተ በኋላ ስፓርታክስ የሚል የምስጥር ስም መጠቀም ጀመረ። ጀርመናዊው የመደብ አልባ ስርዓተ ማህበር (communism) ርዕየተ ዓለም አመንጪ ካርል ማርክስ የኢሉሚናቲ ምስጥር ማኅበር አባል ነበር። ኢሉሚናቲ የተመሰረተበት ግንቦት 1 የመደብ አልባ ስርዓተ ማህበር (ላብ አደሮች) ቀን "May Day" በሚል ሽፋንም ይከበራል። ግንቦት 1 እ.ጎ.አ በኢሉሚናቲ ማኅበር አባላት ዘንድ ትልቅ ባዕዳዊ የሆነ ሰነ ስርዓት በማካሄድ የሚከበርበት ቀን ነው። ይህም ሰውን መስዋእት እስከማድረግ ይደርሣል። ስነ ስርዓቱ በጠቅላላ ጥንቆላና የጣኦት አምልኮ በማካሄድ ድከበራል። ኮሙኒስቶች ይህንን በዓል ለማክበር የላብ አደሮች (May Day) የሚል ሽፋን ይጠቀማሉ። እኛም ይህንን በዓል ከማክበርና ከሴራቸው መጠበቅ ይገባናል። ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ ነኝ ከጽዮን ተራራ!
Show all...
👍 9
👍 4 1
Photo unavailableShow in Telegram
ፍቅር የአምላክን ልጅ ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው፣ በደል የሌለበትን እንደ በደለኛ ሰቀሉት ፣ ሕይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቈጠሩት አዳምን የፈጠሩ እጆች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ፣ ወዮ ፣ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ፣ ወዮ፣ በአዳም ፊት የሕይወት መንፈስን እፍ ያለ አፍ ከሐሞት ጋራ የተቀላቀለ የኮመጠጠ መጸጻን ጠጣ፣ ወዮ፣  የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው፣ ምን ከንፈር ነው፣ ምን አንደበት ነው?  የፍቁር የጌታ ሕማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል ሕሊናም ይመታል፣ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፣ ሥጋም ይደክማል ፣  የማይሞተው ሞተ፣ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ፣ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ፤  የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት ፣ ወየው፣ ወየው፣ ወየው አማኑኤል አምላካችን፣ ወየሙ፣ ወየው፣ ወየው መድኃኒታችን ኢየሱስ፣ ወየው ወየው፣ ወየው ፡ ንጉሣችን ክርስቶስ፡ ወየው፡ ወየው ወየው ፡ ጻድቃን ከዕንጨት አወረዱት፣ ሥጋውንም ለመገነዝ ከርቤ የሚባል የጣፈጠ ሽቱንና ንጹሕ በፍታን አመጡ፤ ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው የማይሞት የማይለወጥ፣ ከድንግል ማርያም የተወለደ አቤቱ ይቅር በለን ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ፣ ቅዱስ ሕያው ፣ የማይሞት፣ የማይለወጥ፣ በዮርዳኖስ የተጠመቀ በመስቀልም  የተሰቀለ፣ አቤቱ ይቅር በለን፣ አቤቱ ይቅር በለን " ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ  "
Show all...
11
ሁሉን የፈጠረ፥ ሁሉን የፈጸመ፥ ሁሉንም የጀመረ፥ ሁሉን የያዘ፥ ሁሉንም የጨበጠ እግዚአብሔር። መላእክትና የመላእክት አለቆች፥ መናብርትና ሥልጣናት፥ አጋዕዝትና ኃይላት፥ ፀሐይና ጨረቃ፥ ከዋክብትም ድርገታትም የሚሰግዱለት፤ ተገዦቹና ጉልቱም ናቸውና። በሁሉ ባለጠጋ ሲሆን ራሱን ከሁሉ ደሀ አደረገ። ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው፥ እስከ ሞትም አደረሰው። አባ ሕርያቆስ
Show all...
20👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
"ሲቀርብም ከተማይቱን አይቶ አለቀሰላት፥ እንዲህ እያለ። ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ስንኳ ብታውቂ፤ አሁን ግን ከዓይንሽ ተሰውሮአል። ወራት ይመጣብሻልና፥ ጠላቶችሽም ቅጥር ይቀጥሩብሻል ይከቡሻልም በየበኵሉም ያስጨንቁሻል፤ አንቺንም በአንቺም ውስጥ የሚኖሩትን ልጆችሽን ወደ ታች ይጥላሉ፥ በአንቺ ውስጥም ድንጋይ በድንጋይ ላይ አይተዉም፥ የመጐብኘትሽን ዘመን አላወቅሽምና።" የሉቃስ ወንጌል 19 : 41-44
Show all...
7🔥 1