AL–JUED DAAWA አል–ጁድ ደዕዋ
Open in Telegram
AL–JUED DAAWA አል–ጁድ ደዕዋ «በብዕርህ መጣራት ባትችል በሰዎች ብዕር ተጣራ» ሀሳብ አሰተያየት ካለዎት ⇙ @AlJUDDAEWA_bot
Show more1 486
Subscribers
-124 hours
-27 days
-1730 days
Posts Archive
📚 ይህ ፎቶ ብዙ ነገር ይናገራል… ❤️
እነዚህ የምትመለከቷቸው ልጆች ባለፈው ዓመት የሙፍቲ ዳውድ የበጎ አድራጎት ድርጅት የትምህርት ድጋፍ ያገኙ ተማሪዎች ናቸው። 📚🎒✏️
ያኔ በእጃቸው የነበረው ደብተር ብቻ አልነበረም…
ተስፋ ነበር።
ደስታ ነበር።
የመማር ፍላጎት ነበር።
የነገ ህልም ነበር። ❤️
ዛሬም እንደገና ወደ አዲሱ የትምህርት ዘመን እየገባን ነው።
ለ2019 ዓ.ል. የትምህርት ዘመን በ6ኛ ዙር የትምህርት ድጋፋችን 1,000 አቅመ ደካማና የቲም ተማሪዎችን ለመድረስ ዝግጅታችንን ጀምረናል።
💰 የአንድ ተማሪ ፓኬጅ — 1,000 ብር ብቻ!
እርስዎ የምትሰጡት 1,000 ብር ብቻ ሊመስል ይችላል፤ ለአንድ ተማሪ ግን የትምህርት ጉዞውን በተስፋ ለመጀመር ትልቅ ስጦታ ነው።
🤲 ዛሬ አንድን ተማሪ እንደግፍ
📚 ደብተር እንስጠው።
✏️ እስክሪብቶ እንስጠው።
❤️ ተስፋ እንስጠው።
ለአንድ ተማሪ፣ አንድ ሺህ ብር፣ አንድ ትልቅ ተስፋ!
📚 “አንድም ተማሪ ከትምህርት ገበታ አይርቅም!”
🏦 የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች
♢ ንግድ ባንክ: 1000388115444
♢ ኦሮሚያ ባንክ: 1493281700001
♢ ሒጅራ ባንክ: 1001097420001
♢ ዘምዘም ባንክ: 0019001920101
♢ አቢሲንያ ባንክ: 227989898
♢ አዋሽ ባንክ: 01425412116600
♢ ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ: 1000085221616
#አንድም_ተማሪ_ከትምህርት_ገበታ_አይርቅም
#አንድ_ተማሪ_1000_ብር
#1000_ተማሪዎች
#የትምህርት_ድጋፍ
#አንድ_ተማሪ_አንድ_ተስፋ
#ሙፍቲ_ዳውድ_የበጎ_አድራጎት_ድርጅት
#በጎ_አድራጎት
#EducationForAll
#SupportAStudent
በ1977 ዓ.ል. በነበረው አስከፊ የድርቅ ዘመን፣ አንድ አባት ሁለት ሕፃናት ልጆቹን ከድርቅ ሺሽት ይጓዝ ነበር። አንዱን እጁን ይዞ፣ ሌላኛውን እሽኮኮ አድርጎ…
ረጅም ጉዞ፣ ረሃብና ድካም ተደማምረውበት በመንገድ ዳር ካለች ዛፍ ሥር አረፈ። ያቺ የዛፍ ጥላ ግን ለአባታቸው የመጨረሻ የእስትንፋስ ማረፊያ ሆነች።
አባታቸው በዛፏ ሥር ሕይወቱ አለፈ። ምሽቱ ሲቃረብ፣ እሽኮኮ ተደርጎ የነበረው ልጅ የአባቱን ራስ እየዳበሰ፦
“አባ… መሸ… ጂቡ ሳይመጣ እንሂድ…” እያለ ያለቅስ ነበር ይባላል። 😢
ይህ ታሪክ የትናንት ብቻ አይደለም።
የዛሬም ማስጠንቀቂያ ነው።
ዛሬ ያለንበት ወቅትም እጅግ አስፈሪ ነው። ዝናብ ጠፍቷል፣ ድርቅ እየተስፋፋ ባለበት በዚህ ጊዜ፣ ወደ አላህ ተመልሰን ምሕረትን መለመን አለብን።
🌧️ ነገ ለ4ኛ ጊዜ ሶላተል ኢስቲስቃ ለመስገድ ጥሪ ቀርቧል።
📍 ኹለፋዑ ራሺዲን ግቢ
⏰ ጧት 2፡30
እባካችሁ በሰዓቱ ተገኝተን፣ በአንድነት ቆመን፣ እጃችንን ወደ ሰማይ አንስተን አዛኙን ጌታችንን እንለምን። 🤲
“አላህ ሆይ! የኃጢአታችንን ማረን፣ ምሕረትህን አውርድልን፣ ዝናብህን ለግሰን።”
🤲 አላህ ሆይ! ምድራችንን የሚያለመልም፣ ሕይወታችንን የሚያድን የበረከት ዝናብ አውርድልን። አሚን! 🤲🌧️
አንድም ተማሪ ከትምህርት ገበታ አይርቅም!
ዘንድሮም ለ6ተኛ ዙር ለ1,000 ተማሪዎች
እርሰዎም ለነገ ብሩህ ልጆች ድጋፍ ያድርጉ
የአንድ ተማሪ ፓኬጅ — 1,000 ብር
🏦 የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች
♢ ንግድ ባንክ: 1000388115444
♢ ኦሮሚያ ባንክ: 1493281700001
♢ ሒጅራ ባንክ: 1001097420001
♢ ዘምዘም ባንክ: 0019001920101
♢ አቢሲንያ ባንክ: 227989898
♢ አዋሽ ባንክ: 01425412116600
♢ ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ: 1000085221616
#አንድም_ተማሪ_ከትምህርት_ገበታ_አይርቅም
#ሙፍቲ_ዳውድ_የበጎ_አድራጎት_ድርጅት
#SupportEducation #BackToSchool
አንድም ተማሪ ከትምህርት ገበታ አይርቅም!
ሙፍቲ ዳውድ የበጎ አድራጎት ድርጅት፣ “አንድም ተማሪ ከትምህርት ገበታ አይርቅም!” በሚል መሪ ቃል፣ ለ2019 ዓ.ል. የትምህርት ዘመን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ የማሰባሰብ ሥራውን ዛሬ ጀምሯል።
ይህ በጎ ተግባር 6ኛ ዙር ሲሆን፣ በዚህ ዙር 1,000 አቅመ ደካማና ወላጅ አልባ ተማሪዎችን በደብተር፣ በእስክሪብቶ እና በሌሎች አስፈላጊ የትምህርት ቁሳቁሶች ለመደገፍ አቅደናል።
የአንድ ተማሪ ፓኬጅ — 1,000 ብር
ይህንን ታላቅ ተግባር ለማሳካት የሚያስፈልገውን ወጪ በተለያዩ የሶሻል ሚዲያ አማራጮች ከህብረተሰቡ ለማሰባሰብ ዝግጅታችንን አጠናቀናል።
እንደ ሁልጊዜውም፣ በዚህ በጎ ተግባር ከጎናችን እንደምትቆሙና አብሮነታችሁ እንደማይለየን በሙሉ እምነት እንጠብቃለን። 🤲
📚 ደብተር — ትምህርቱን ያስቀጥላል።
✏️ እስክሪብቶ — ህልሙን ይጽፋል።
❤️ የእኛ ድጋፍ — ተስፋውን ያበራል።
🤲 ለ1,000 ተማሪዎች የተስፋ ብርሃን እንሁን!
ዛሬ የምትሰጡት 1,000 ብር ለአንድ ተማሪ የትምህርት በርን ይከፍታል። 🌱📚
🏦 የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች
♢ ንግድ ባንክ: 1000388115444
♢ ኦሮሚያ ባንክ: 1493281700001
♢ ሒጅራ ባንክ: 1001097420001
♢ ዘምዘም ባንክ: 0019001920101
♢ አቢሲንያ ባንክ: 227989898
♢ አዋሽ ባንክ: 01425412116600
♢ ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ: 1000085221616
#አንድም_ተማሪ_ከትምህርት_ገበታ_አይርቅም
#ሙፍቲ_ዳውድ_የበጎ_አድራጎት_ድርጅት
#የትምህርት_ድጋፍ
#EducationForAll
#SupportEducation
#BackToSchool
#HelpAStudent
የነቢዩ ﷺ ልጆች
ነቢዩ (ﷺ) 11 ሚስቶችን ቢያገቡም ልጅ ያገኙት ከሁለቱ ከኸዲጃ ቢንት ኹወይሊድ እና ከማሪያ ቢንት ሸምዑን አል-ቂብጢያ ብቻ ነው።
ልጆቻቸው 7 ሲሆኑ 4 ሴት 3 ወንዶች ናቸው። ከኢብራሂም በቀር ሁሉም የተወለዱት ከኸዲጃ ነው።
ነቢዩ ﷺ በህይወት እያሉ ከፋጢማ በቀር ሁሉም ሞተዋል። ፋጢማም ከነቢዩ በኋላ ስድስት ወራት ቆይታ አርፋለች። የሁሉም ልጆቻቸው ዕድሜ ከ30 በታች ነው።
ለትረካ እንዲመች ከወንዶቹ ጀምረን በቅደም ተከተል ሲቀመጡ የሚከተሉት ናቸው፦
🟣 ቃሲም
♦ ከኸድጃ የተወለደ
♦️ የተወለደው በመካህ ከነቢይነት 9 ዓመታት ቀድሞ ነው።
♦️ የመጀመሪያ ልጃቸው ሲሆን አበል ቃሲም ተብለው ይጠሩ ነበር
♦ የሞተው ነቢዩ ﷺ በነቢይነት ከመላካቸው በፊት ነው
♦️ ቃሲም ከመሞቱ በፊት ለፈረስና ግመል ግልቢያ ደርሶ እንደነበረ ይነገራል።
(ዛድ አል-መዓድ 1/100)
🟣 ዐብዱላህ
♦ ከኸድጃ የተወለደ
♦ የተወለደው ከነቢይነት በፊት ነው። ነቢዩ ﷺ ስሙን ያመጡለት በአባታቸው እንደሆነ ይነገራል።
♦️ የሞተው በነቢይነት ዓመት በመካህ ነው።
♦ ዕድሜው 4
♦️ ዐብዱላህ በሞተ ጊዜ ቁረይሾች ነቢዩ ﷺ ወንዶች ልጆቻቸውን ስላጡ ❝ዘሩ ተቋረጠ❞ አሏቸው። አላህም ❝ጠይህ እርሱ በእርግጥ ዘሩ የተቆረጠው ነው፡፡❞ የሚል አንቀፅ አወረደ።
(አል-ከውሰር 3)
🟣 ኢብራሂም
♦ ከማሪያ አል-ቂብጢያ የተወለደ
♦️ የተወለደው በ8 ሒጅራ መዲና ሲሆን ነቢዩ ﷺ ❝ወንድ ልጅ ተወለደልኝ። ስሙንም በአባቴ ኢብራሂም አልኩት።❞ አሉ።
(ሙስሊም 2315)
♦ ኢብራሂም የሞተው ገና በልጅነቱ ሲሆን የጡት ጥቢውንም አልጨረሰም ነበር። ነቢዩም ﷺ ❝በጀነት የሚያጠቡት አሉ።❞ አሉ።
(ቡኻሪይ 3255)
♦️ ኢብራሂም መዲና ተወልዶ መዲና የሞተ ብቸኛ ልጃቸው ነው።
🟣 ዘይነብ
♦ ከኸድጃ የተወለደች
♦️ የተወለደችው በመካህ ሲሆን ትልቋ ሴት ልጃቸው ናት
♦ አቡል አል-ዓስን አግብታ ዐሊይ እና ዑማማህ የተባሉ ሁለት ልጆች ወልዳለች። ዐሊይ በልጅነቱ ሞቷል።
አቡል አል-ዓስ የእናቷ እህት ወይም የአክስቷ ልጅ ነው። በኋላም ነቢይነት ሲመጣ ተፋቱ። ሆኖም አቡል አል-ዓስ ዘይነብን በጣም ይወዳት ነበርና ሌላ ሴት ማግባት አልፈለገም። በበድር ጦርነት ተማረከና ዘይነብ ካሳ ከፍላ አስለቀቀችው። ከመካህ መከፈት ቀደም ብሎ አቡል አል-ዓስ ኢስላምን ተቀበለና እንደገና ከዘይነብ ጋር መኖር ጀመሩ።
♦ ዘይነብ የሞተችው በ8 ሒጅራ ሲሆን ከአቡል አል-ዓስ ጋር መኖር ከጀመረች ብዙም አልቆየችም።
♦ ዕድሜ 30
♦ የተቀበረችው መዲና
♦️ አቡል አል-ዓስ ከዚያ በኋላም ሳያገባ ለ4 ዓመታት በብቸኝነት ኖሮ በ12 ሒጅራ ሞተ።
♦️ ዐሊይ ኢብን አቡጧሊብ ፋጢማ ከሞተች በኋላ የዘይነብን ልጅ ዑማማህን አገባና ሙሐመድ አል-አውሰጥ የተባለ ልጅ ወለደች። ሙሐመድ አል-አውሰጥ ዘሩ ይቀጥል አይቀጥል የተለያየ ትረካ አለ።
(ጠበቃት ኢብን ሰዓድ 8/36)
🟣 ሩቂያህ
♦ ከኸዲጃ የተወለደች
♦️ የተወለደችው በመካህ ከነቢይነት በፊት ነው
♦️ ከነቢይነት በፊት ከአባቷ አጎት ልጅ ከዑትባህ ኢብን አቡ-ለሐብ ጋር ተጋቡ። ነገርግን አብረው አልኖሩም።
♦ ከነቢይነት በኋላ ከዑትባህ ጋር ተፋቱና ዑስማን ኢብን ዐፋን አገባት። በመካም ከዑስማንና ከሩቂያህ የበለጠ የተዋበ ተጣማሪ አልታየም ይባላል።
ከዑስማንም ጋር ወደ ሐበሻ ተሰደዱ። ከስደት እንደተመለሱም ዐብዱላህ የተባለ ልጅ ወለዱ። ዐብዱላህ የ6 ዓመት ልጅ እያለ በመዲና ህይወቱ አለፈ። ሩቂያም ሌላ ልጅ አልወለደችም።
♦ ሩቂያ የሞተችው በበድር ዘመቻ ቀን በ2ኛው ሒጅራ ነው።
♦ ዕድሜዋ 23 ሲሆን የተቀበረችው በመዲና ነው።
(አሊስቲዓብ 4/1839)
🟣 ዑሙ-ኩልሱም
♦ ከኸድጃ የተወለደች
♦️ ውልደቷ በመካህ ሲሆን ከአባቷ አጎት ልጅ ከዑተይባህ ኢብን አቡ-ለሐብ ጋር ተጋቡ።
♦ ነቢይነት ሲመጣ ከዑተይባህ ጋር ተፋቱ።
♦️ ከሒጅራ በኋላ ሩቂያህ ስትሞት ዑስማን በጣም ሃዘን ሲወድቅበት ነቢዩ ﷺ ዑሙ-ኩልሱምን ዳሩት።
♦ ዑስማንና ዑሙ-ኩልሱም ለ7 ዓመታት አብረው ቢኖሩም ልጅ አልወለዱም።
♦ ዑሙ-ኩልሱም ምንም ልጅ ሳትወልድ በ9 ሒጅራ በ27 ዓመቷ ህይወቷ አለፈ።
(ሲየር 2/252)
🟣 ፋጢማ
♦ ከኸድጃ የተወለደች
♦️ የተወለደችው የነቢይነት 5 ዓመት ቀደም ብሎ በመካህ ነው።
♦ ከሒጅራ በኋላ በመዲና ከዐሊ ኢብን አቡጧሊብ ጋር ተጋቡ። ከዚያም 5 ልጆችን ማለትም ሐሰንን፣ ሑሰይንን፣ ዘይነብን፣ ዑሙ-ኩልሱምን እና ሙህሲንን ወልዳለች። ሴት ልጆቿን የሰየመቻቸው እህቶቿን በጣም ስለምትወድ ለማስታወሻ ነው።
♦️ ሙህሲን ብቻ በተወለደበት ዓመት ሲሞት ሌሎቹ ልጆቿ አግብተው ወልደዋል።
♦️ ፋጢማ ነቢዩ ﷺ በህይወት እያሉ የቆየች ብቸኛ ልጃቸው ስትሆን ለእሷ ካላቸው ውዴታ የተነሳ ከጉዞ ሲመለሱ ከፋጢማ ቤት ጎራ ሳይሉ ቤታቸው አይገቡም ነበር።
♦️ ፋጢማ ህይወቷ ያለፈው በ11ኛ ሒጅራ በአቡበክር ዘመን ሲሆን ዕድሜዋ 26 ነው። የተቀበረችው በመዲና ነው።
♦ ፋጢማ ስትሞት አራቱም ልጆች ገና ልጅ ስለነበሩ አላገቡም። በኋላ ሐሰንና ሑሰይን በርካታ ሚስቶችን አግብተው ሐሰን 16 ሑሰይን 6 ልጆች ወለዱ።
♦ ሴት ልጆቿ የመጀመሪያዋ ዘይነብ የአጎቷን ልጅ ዐብዱላህ ኢብን ጃዕፈርን አግብታ 5 ልጆችን ወለደች። ከእነሱም ሁለቱ ሙሐመድና አውን ከአጎታቸው ሑሰይን ጋር በከርበላዕ ተገደሉ። ዘሯ በቀሩት ልጆቿ ይቀጥል አይቀጥል የተጣራ ማስረጃ የለም።
♦️ ሁለተኛዋ የፋጢማ ልጅ ዑሙ-ኩልሱም ከዑመር ኢብን አል-ኸጧብ ጋር ተጋብታ ዘይድ የተባለ ልጅ ወለደች። ዘይድም በወጣትነቱ በቤተሰቡ መካከል ፀብ ተፈጥሮ ሊያገላግል ሲገባ ተገደለ። ዑሙ-ኩልሱምም በልጇ ሞት ደንግጣ ህይወቷ አለፈ።
(አል-ቢዳያህ 2/60)
ተፃፈ በወንድም ሰል ማን
ዘግይቶም ቢሆን ከአላህ የሚመጣ ችሮታ ያለፈን ሀዘንና ችግር የሚያስረሳ ፤ በረከተ ሰፊ እና እጅግ አስደሳች የሚሆን ነውና ፤ አብሽሩ ችሮታውን በትዕግስት ተጠባበቁ!
ጀግናዋ እናት
ከስር የምትመለከቷት እህታችን ዛሬ ከተመረቁት ሁፋዞች መካከል አንዷ ናት። የሦስት ልጆች እናትም ነች።
የቤት ሥራ፣ የልጆች እንክብካቤና የዕለት ተዕለት ሀላፊነቶቿ ብዙ ቢሆኑም፣ እነዚህ ሁሉ የአላህን ቃል ከልቧ እንድትይዝ አልከለከሏትም።
ባላት ጥቂት ጊዜ እንኳን አጋጣሚ ፈጥራ፣ በትጋት ቁርአንን ሸምድዳ ዛሬ ሀፊዛ ሆናለች። አላሁ አክበር!
ይህች እህታችን ለእኛ አንድ ትልቅ ትምህርት አላት፦ ጊዜ አጥሮን ሊሆን ይችላል፤ ሀላፊነትም ሊበዛብን ይችላል፤ ነገር ግን ፍላጎትና ትጋት ካለ ቁርአንን ለመሸምደድ መንገድ እናገኛለን።
ዛሬ ብዙ ነገሮች በተመቻቹበት ዘመን ሰበብ ማብዛት ቀላል ሆኗል። እሷ ግን በሀላፊነት መካከል ሆና ቁርአንን መርጣለች። ለዚህም ነው ዛሬ አርአያ የሆነችው።
አላህ የሸምደደችውን ቁርአን የሚጠቅማት ያድርግላት፣ በቁርአንም ላይ ያጽናት። 🤲
ለሌሎች እህቶቻችንም፦ ሰበብ ከመፈለግ በፊት ትንሽ ጊዜ መድቡ፤ ትንሽ ትንሽ በመጀመር ታላቅ ግብ ላይ መድረስ ይቻላል። 🤲📖
አላህ ለሁላችንንም የቁርአን ሰዎች ይድርገን። አሚን!
ታላቅ የቁርአን ሂፍዝ ምርቃት በከሚሴ!
ከሚሴ ከተማ በመጪው እሁድ በታላላቅ ዑስታዞች እና በቁርአን ሀፊዞች ትደምቃለች፣ ኢንሻአላህ! 🤲✨
📢 ታላቅ የቁርአን ምርቃት ፕሮግራም! 📖❤️
በመጪው እሁድ በሚካሄደው የቁርአን ሂፍዝ ምርቃት ላይ የሚታደሙ የተከበሩ እንግዶቻችንን በክብርና በፍቅር ለመቀበል፣
🚗 መኪና
🛺 ባጃጅ
🏍️ ሞተር ሳይክል
ያላችሁ ወንድሞች በሙሉ፣ ነገ ቅዳሜ ከዓሱር ሰላት በኋላ በደዌ በር መስጂድ በመገኘት የእንግዶቻችንን ደማቅ አቀባበል እንድናደርግ ጥሪ ቀርቦላችኋል። 📢❤️
🤝 እንግዳ መቀበል ክብር ነው፤ የቁርአን ሰዎችን ማክበርም ታላቅ ክብር ነው! 📖❤️
እንደ አንድ ሙስሊም ማህበረሰብ በአንድነት ተሰባስበን፣ የከሚሴን የቁርአን ፍቅር እናሳይ!
📢 ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!
ቅዳሜ ከዓሱር በኋላ በደዌ በር መስጂድ!
بارك الله فيكم وجزاكم الله خيرًا 🤲
ሕይወት ብዙ አስተማረችኝ... ዛሬም ማስተማሯን አላቆመችም።
አንዳንድ ትምህርቶች መጻሕፍት ላይ እንደማይጻፉ፣ ይልቁንም በልባችን ሰሌዳ ላይ በቀናት ሂደት ተቀርጸው እንደሚቀሩ ሕይወት አስተማረችኝ።
የምንወዳቸው ሰዎች ሁሉ ሁልጊዜም እንደ ቀድሞው ሆነው እንደማይቀጥሉ፤ እንዲሁም አንዳንድ ርቀቶች በጥቃቅን አለመግባባቶች ተጀምረው በዝምታ ውስጥ እያደጉና እየሰፉ እንደሚሄዱ አስተማረችኝ።
ይቅርታ መጠየቅ ክብራችንን እንደማያሳንስ፣ ይቅር ባይነትም ለሌሎች የሚሰጥ ስጦታ ከመሆኑ በፊት ለገዛ ነፍሳችን የሚሰጥ ትልቅ እፎይታ እንደሆነ አስተማረችኝ።
ከሰዎች ጋር ከልክ በላይ መጣበቅ ህመም እንደሚያስከትል፣ ከሁሉም በላይ ውብና ጥብቅ የሆኑ ግንኙነቶች በእውነተኝነትና በጋራ እንክብካቤ ላይ የተመሰረቱት ብቻ እንደሆኑ አስተማረችኝ።
በመጨረሻም ደግሞ እንዲህ ስትል መከረችኝ፦ ለአንተ የተጻፈው (የተወሰነው) ነገር መቼም ቢሆን ያንተ ሆኖ ይቀራል፤ ለአንተ ያልተጻፈው ነገር ግን የዚህች ምድር ጥረቶችና የዓለም ሙከራዎች ሁሉ በአንድነት ቢደመሩ እንኳ ፈጽሞ ሊያገናኙህ አይችሉም።
© Murad Tadesse
"የአባት ላብ የልጆቹ ፈገግታ ነው፤ የአባት ድካም የቤተሰቡ እረፍት ነው።"
አላህ ሆይ!በሕይወት ያሉ ወላጆቻችንን ይጠብቅልን፣ ያለፉትንም በረህመትህ ማርልን 🤲
اللَّهُمَّ أَحْيِنَا مُسْلِمِينَ ، وَتَوَفَّنَا مُسْلِمِينَ ، وَأَلْحِقْنَا بِالصَّالِحِينَ.
አያልፉም ያልናቸው እጅግ በጣም ብዙ ፈታኝ ጊዜያት አልፈዋል ። ዛሬ ላይ ስናስባቸው ይቀሉን ይሆናል እንጂ በወቅቱ ቀናችንን በልተው ሌሊት እንቅልፍ ነስተውናል ፣ እንይዘው እንጨብጠው አጥተናል ። ያም ሆነ ይህ ግን ፈተናው ታልፏል ፣ ጭንቀቱ ተረስቷል ። ይህ ሊሆን ግን ስንቱን አሰብን ?!
ዛሬም እየተፈተንን እየተጨነቅን አለን ። እነዚህ ጊዜያትም ግን እንዳለፉት ጊዜያት ሁሉ ያልፋሉ ። ወቅትና ጊዜውን ጠብቆ መሳካቱ ላይቀር ዛሬያችንን አናበላሽ እንዲሉ አበው ከትናንት እንማር ፣ ዛሬን እንኑር ፣ ለነገ እናስምር 😉
አላህ ልባችን የሚያረጋጋበትን እርካታ ይወፍቀን ዘንዳ ሰለዋት ላይ ሙጥኝ 🤎
ሰለዋቱ ረቢ ወሰላሙሁ ዓለይክ 💚
ኸሚስ ሙባረክ 🙏
