en
Feedback
የአዲስ ኪዳን ካህናት

የአዲስ ኪዳን ካህናት

Open in Telegram

" እርሱም ደግሞ በመንፈስ እንጂ በፊደል ለማይሆን ለአዲስ ኪዳን አገልጋዮች እንሆን ዘንድ አበቃን፤ ፊደል ይገድላልና መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል።" (2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 3:6) ✔የዚህ ቻናል አላማ #የጸጋውን_ወንጌል ለአለሙ ሁሉ ማወጅ ነው ፡፡ ለአስተያየት: @samidaba @sofiblessed ✆✆ ☞ +251941982842

Show more
1 534
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
አርጋኖን ሲገለጥ 1

እግዚአብሔር ምህረቱን የሚሸሽግ አምላክ አይደለም ፡፡ ምህረትን የተሞላበት ሰፊው የልቡ እልፍኝ ኃጥያተኛ ሰው በፈለገው ጊዜ አግኝቶት እንዲያርፍበት በፀጋ ክምችት የተትረፈረፈና እኛን ሰዎችን ለመቀበል ዘወትር የተከፈተ ነው፡፡ስለዚህ በምህረቱ ባለጠጋ ወደ ሆነው ወደ እርሱ እንጠጋ 🥰🥰 ✍Tsion birhanu @lebegu @lebegu @lebegu

#በልዩነት_ለ12ክፍል_ተፈታኞች_አድርሱልኝ_እናም_ለሁላችን። 1ተሰ 5:17 በሁሉ አመስግኑ እንደሚል የፈተና ውጤታችሁን ለመስማት ቀን በሰላም መድረሳችሁ ጭምር የምስጋና ምክንያት ይሁንላችሁ። #በክርስቶስ ያገኛችሁት የላቀ እንደሆነ፣እግዚአብሔር ባመጣችሁት ውጤት ሳይሆን በላከላችሁ በልጁ አድርጎ እንደሚያያችሁ አስታውሱ። #እግዚአብሔርን_አወድሱት ዘዳ 33:26 እንደ እግዚአብሔር ያለ የለም ብሎ አወድሶ ሞተ።40 ዓመት ህዝቡን ወደ ከነዓን መርቶ ታያለህ እንጂ አትገባም ወደ ተራራው ሂድና ሙት ለሚለው ድምጽ ምላሹ ይህ ነው።እባካችሁ እንደ ሙሴ መልሱና ጠላትን አሳፍሩ። #የምታሰላስሉትን_ቀይሩ።ዮናስ 2:10 ነፍሴ በዛለች ጊዜ እግዚአብሔርን አሰብከኰት አለ፣ማለፋችሁ መውደቃችሁ ላይ አታተኩሩ እንድታልፉ የረዳችሁን ከወደቃችሁበት ሊያነሳችሁ የሚችለውን፣ስለ እናንተ ሁሌ መልካምና ፍጻሜው ያማረ ሐሳብ ያለውን እግዚአብሔርን አስቡ አሰላስሉ። #ነገር_ሁሉ_ለበጎ_ይለወጣል።ሁሌ በምናልፍበት መንገድ ይህን እናስተው ከእያንዳንዱ መጥፎ አጋጣሚ መልካሙን ነገር መፍጠር ጌታ ይችላል። የጨለማው ጉልበት የክዋከኴብቶችን ብርሃን ያደምቀዋል፣ውስጣችሁ ያለውን አቅም ምታውቁበት ራሳችሁን ምታገኙበት ሊሆን ይችላል። #አበቃ_አለቀ_ማለት_አይደለም።ሁላችንም ለዩኒቨርስቲ አልተፈጠርንም ሰሪያችን የሚፈልገን ቦታ በእኛ ሊደርሳቸው የሚፈልጋቸው ህዝቦች በሁሉም ቦታ አለ።ስለዚህ በእኛ ላይ ያለው የጌታ ዓላማ ይቀጥላል ገና ። በዚህ ውጤት ያለፋችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፤ያላለፋችሁ በጌታ አይክፋችሁ። #ክርስትናን_የመኖር_ዕድል ቢሆንስ ሁሌ ደስ ይለኛል በሁሉ አመሰግናለሁ ብለን የሰበክን የዘመርህ ይኸው በተግባር እናሳይ አመስግኑት በሁሉ። #በመጨረሻም ካጣችሁት ያገኛችሁት፣ከደረሰባችሁ ይልቅ የደረሰላችሁ፣ከሆነባችሁ ይልቅ የሆነላችሁ በክርስቶስ ብዙ ነው። እወዳችኋለሁ,በልቤ ትልቅ ቦታ አላችሁ።በመልዕክቴ ከተጽናናችሁ #እግዚአብሔር_ይመስገን_በሉ።ጸጋ ይብዛላችሁ። ✍✍ Bereket belay Join @Lebegu @Lebegu @Lebegu

አየር ጤና፣ ዓለም ባንክ፣ ዘነብወርቅና አካባቢው ሆናቹ እነዚህን መጻሕፍት የምትፈልጉ ከአየር ጤና ትምህርት ቤት ጀርባ ጵንኤል ሕንጻ ላይ 1 ፎቅ ጎራ ብትሉ ታገኛላቹ
+2
አየር ጤና፣ ዓለም ባንክ፣ ዘነብወርቅና አካባቢው ሆናቹ እነዚህን መጻሕፍት የምትፈልጉ ከአየር ጤና ትምህርት ቤት ጀርባ ጵንኤል ሕንጻ ላይ 1 ፎቅ ጎራ ብትሉ ታገኛላቹ

አንድ ዝሆን እና አንድ ውሻ በእኩል ቀን እርግዝና ጀመሩ።   ውሻዋ በ3 ወሯ ላይ በአንድ ጊዜ 6 ቡችሎችን ወለደች።አሁንም ደግማ 4 ቡችላ ወለደች።    እኩል ቀን አርግዘው ውሻዋ ሶስተኛ ዙር ወለደች ።ከዚያም ውሻዋ ዘወር ብላ የምር ግን አርግዘሻል እርግጠኛ ነሽ አለቻት።    እኩል ቀን አረገዝን እኔ 3 ዙር ወለድኩ አንቺ ግን አንዴም አልደወልሽም አለቻት።    በዚህ ጊዜ ዝሆኗ እንዲህ አለቻት እኔ እንደ አንቺ ቡችላ አይደለም ያረገዝኩት ዝሆን ነው ያረገዝኩት አንድ እለት የተውለደ ጊዜ ገና ማደግ እንደጀመረ የብዙዎችን ቀልብ የሚስብ የሚጎበኝ እና ድንቅ ፍጥረት ነው የሚሆነው አለቻት።      ዛሬም ቢሆን የጸሎት መልሶቻችን ስለዘገዩ እውነተኛ የማንመስላቸው ቢኖሩም የዘገየው ነገራችን መልስ ባገኘ ጊዜ የሚያስደንቅ እና ትኩረት የምንስብ መሆናችን አይቀርም።    ሁሉን ግን በትዕግስት እንጠብቀው። መልካም ምሽት ተመኘሁላችሁ። ✍ beki belay @Lebegu @Lebegu @Lebegu

#አልፈረደብኝም_ምህረቱ_አይሎበት የሆነ ጊዜ ምን ገጠመኝ መሰላችሁ - ATM ረጅም ሰልፍ ተሰልፌ ... ከሰልፉ ፊት ያሉት ሁለት ተረኛ ልጆች ገትረውን ይነጋገገራሉ። እና Offended ሆንኩኝ። ምንድነው ሚዝናኑት ሰው አስቁመው : ሲያስጠሉ ፋራዎች ሚያወሩበት አጡ ? ምናምን Stuff እያልኩ ስበሰጫጭ ልጁ ጨርሶ ወጣ። ታምኑኛላችሁ ወዳጆቼ ዓይነ ስውር ነበር ልጁ 😔 እያገዘው ነበር ከኋላው ያለው ልጅም ። ተሸማቀኩ አይገልፀውም። መፍረድም በጣም ፈራሁ ። በዚህ ምድር ባለን መንፈሳዊ ህይወትም የቱንም ያህል ጥሩና መልካም እንደሆንን ብናስብ : ጌታችን ኢየሱስ ጥቂት ያህል እንኳን ያልተወልን Ground የመፍረድ ነው። ቢፈርድ የሚያምርበት እንከን አልባው ሳይፈርድ እኛ በብዙ ድካም የተከበብን ለመፍረድ ምን ያንቀዠቅዠናል?? “እርስዋም፦ ጌታ ሆይ፥ አንድ ስንኳ አለች። ኢየሱስም፦ #እኔም_አልፈርድብሽም፤ ሂጂ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትሥሪ አላት።” — ዮሐንስ 8፥11 የኢየሱስን ርህራሄ በዘመናት ከፋፍላችሁ በህጉ ዘመን ውስጥ በህጉ Mentality የሚሰራ ብቻ አድርጋችሁ ለምትሰብኩም አንድ ነገር ልጨምር። የእርሱ ርህራሄ ከራሱ ማንነት የሚቀዳ እንጂ በምክንያት ላይ የተመሰረተ አይደለም። “እርሱ ራሱም ደግሞ #ድካምን_ስለሚለብስ፥ ላልተማሩትና ለሚስቱት ሊራራላቸው ይችላል፤” — ዕብራውያን 5፥2 ይኸውላችሁ የትኛውም ሊቀካህናት ለሀጥያተኞች የሚራራው ራሱ ድካም ስላለበት ብቻ ነው። ማለትም ሀጥያት ባይሰራ ኖሮ አንድም ሀጢያተኛ በርህራሄ አይስተናገድም : ያልቅለት ነበር። ሀጥያት የተባለ የሌለበት ፍፁም ቅዱስ ሲሆን ለሀጥያተኞች የሚራራ የአዲስኪዳን ሊቀ_ካህናት አንድ መድሃኔዓለም ብቻ ነው። ርህራሄው ከራሱና ከማንነቱ የሚፈልቅ ነው። ደግሞኮ ላልተማሩትና ለሚስቱት(በስህተት ለሚሰሩት ) ብቻ ነው ሊቀ-ካህናት ይራራ የነበረው ። የኛ ጌታ ስንት ድፍረት ትዕቢታችንን ይቅር እንዳለን የሚችል ይቁጠረው ፍቅሩ ያለአንዳች አስገኚ ምክንያት : ቸርነቱ ያለምክንያት : ርህራሄው ያለምክንያት : ላይጠላን በምክኒያት ላይለቀን ይዞናል : ምስጋና ይገባዋል Ohhh Sweet Jesus 😍 በድካም ያላችሁ : በሀጥያትም ያላችሁ እባካችሁ ሳያሸማቅቅ ወደሚያቀርባችሁ : ነገር ግን በምህረት ወደሚፈርድላችሁ ጌታ ተጠጉ ቅረቡት ። መልካም ፍሬ እውነተኛውን ግንድ ከመጣበቅ የሚመጣ ነው። ታሜ ነኝ 😍 እወዳችኋለሁ Share the post @Lebegu @Lebegu

.          የእርሱ ፍለጋ ዘማሪት ዬርዳኖስ ከበደ|New Song @Lebegu @Lebegu 👈 join 😍

. አይመጥኑህም Bemenet Mulatu - Live 😍 @Lebegu @Lebegu

#አንዳንዴም_ለፈገግታ አይ የጴንጤ ወንድ መከራ😂 የምታመናፍስ ሴት ስታጋጥመው 😂😂 (ለፈገግታ) Me - ሀይ Her - ሰላም Me - ሰላም ነሽ? Her - ሰላሜ እየሱስ ነው! Me - እውነት ነው። ጠፍተሻል ሰሞኑን ደግሞ Her - አልጠፋሁም፤ ከማይጠፋ ዘር ነኝ! Me - ልክ ነው እሱስ። እና ምን አዲስ ነገር አለ? Her - ከፀሐይ በታች አዲስ ነገር የለም! Me - ሃሃ...እኔ የምልሽ ቁርስ በልተሻል? Her - ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም! Me - ደግሞ የፖሰትሽውን ፎቶ አየሁት። በጣም ውብ ነሽ። Her - ውበት ሐሰት ነው፣ ደምግባትም ከንቱ ነው! Me - አይደል? የት ሰፈር ነሽ ግን? አድራሻሽን እኮ አልነገርሺኝም? 😂 Her - አድራሻዬ መስቀሉ ስር ነው! Me - ሃሃ...ኧረ የመኖሪያ አድራሻሽን ነው ያልኩሽ! Her - "መኖሪያዬ ጌታ ነው" የሚለውን መዝሙር ጋብዤሀለሁ Me - ስለመጋበዝ ካነሳሽ አይቀር ለምን አንድ ቀን አልጋብዝሽም ተገናኝተን? Her - ውይ በጣም አመሰግናለሁ! ጌታ ይባርክህ! ግን መጀመሪያ እኔ ነኝ የምጋብዝህ! Me - እውነትሽን ነው? በጣምም በደስታ ነዋ! Her - ከፊታችን እሮብ ከስራ መውጫ ሰአት ላይ ይመችሀል? Me - አዎን በደምብ [የትም ይመቸኛል! 😂] Her - ጥሩ! "ኤልዛቤል ትፈጥፈጥ ኢንተርናሽናል ቸርች" የነፃ መውጣት ፕሮግራም አለ እዛ ጋብዤሀለሁ! Me - ተባረኪ 😑! እና ከዛ ስንወጣ እራት አብረን እንበላለን በቃ እንደውም! Her- ውይ አልችልም! ከዛ ስወጣ የአዳር ፕሮግራም አለኝ። ባይሆን እራት በምትጋብዘኝ ብር "እጮኝነት እና ትዳር" የሚለውን መፅሐፍ ግዛልኝ። Me - በደስታ! ነገውኑ ገዝቼ አቀብልሻለሁ! Her - ውይ ነገ አልችልም! Me - እና መቼ ተገናኝተን ላቀብልሽ? Her - ኧረ አትቸገር ቸርች ዘበኛው ጋር አስቀምጥልኝ። ሲመቸኝ ሄጄ እወስደዋለሁ። Me - እሺ ካልሽ ምን ይደረጋል! Her - በቃ አሁን ከSocial media online ወጥቼ ወደመንፈሳዊው አለም online ልገባ ነው! Me - እሺ ውዴ ደህና እደሪ! ከእኔ ጋር ትንሽ ብትሆኚ ደስ ይለኝ ነበር። Here - የጌታ ፀጋ ከአንተ ጋር ይሁን። ደህና ሁን በጌታ የተወደድክ ወንድሜ! አስበው ከዚህ ሁሉ ጥረት በኋላ "ወንድሜ" ስትልህ የሚሰማህን የስሜት breakdown! ከ Fb @Lebegu @Lebegu @Lebegu

#ልፀልይላችሁ 🙏 ጌታችን "ሰላሜን እተውላችኋለሁ" እንዳለ ምንም መጣ ምን ተፅዕኖ የማይፈጠርበት የጌታ ሰላም ህይወታችሁን ይቆጣጠረው። 🙏 በተለያየ ሀዘን ውስጥ ላላችሁ : የእግዚአብሔር ጥልቅ ፍቅር ክንፍ ሆኖ ከሁኔታ በላይ ያበራችሁ ዘንድ የፍቅሩ መረዳት በሁለንተናችሁ ይትረፍረፍ። ዓለም ሁሉ በሰማያት ታላቅ አፍቃሪ አባት እንዳለው አውቆ ከሰይጣን ማባበያዎች እንዲሸሽ በመድሃኔአለም ስም ፀለይኩኝ። 🙏 አገልጋዮች በአገልግሎታችሁ የሚድኑ ሰዎች እየተጨመሩ : መንግስቱ እየሰፋ : የእግዚአብሔር ፈቃድ ሁሌ ይፈፀምባችሁ። 🙏 ብትገፉት ብትገፉት አልነቃነቅ ብሎ ያስጨነቃችሁ ሁሉ : አምላክ ትጠነክሩለት ዘንድ ያዘጋጀላችሁ መሆኑን በመረዳት በሃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ ። 🙏 የተቅበዘበዙ በወንጌል እንዲያርፉ እረኛ ወዳጡ ሁሉ የሰማዩ አባት እግዚአብሔር አብ የመከሩን ሰራተኞች አብዝቶ እንዲልክ በኢየሱስ ስም ለመንኩኝ። 🙏 መፅሀፍ ቅዱስ ማንበብ : መፀለይ : ሀጥያትን እምቢ ማለት የማያልፍበት ፋሽን የሚሆንበት የትጋት እና የቅድስና ጉልበት በምድራችን ላይ ይገለጥ። 🙏 በሚያስፈልጋችሁ ጊዜ ሁሉ ሊረዳችሁ ወደ ታመነው ጌታ ፀጋ ዙፋን አብልጣችሁ የምትቀርቡበት : ፀጋና ምህረቱን በሙላት የምትቀበሉበት ዘመን ይብዛላችሁ። 🙏 አይናችሁ በሞተላችሁ ጌታ ላይ ይፍዘዝ : ከኢየሱስ ውጪ ሱስ ሁሉ ከህይወታችሁ ይወገድ ። እርሱን መምሰልን አጥብቆ መለማመድ ይሁንላችሁ። 🙏 ቶሎ ቶሎ የሚከበን ሀጥያት : ሸክምና : ድካም በልጁ ይወገድ ዘንድ ... ቶሎ የምናስወግድበትም ትኩረት እና መታመን እንዲሁም ትጋት እለት እለት በህይወታችን ይብዛ ። 🙏 Repent and Repair ( በድካማችን በንስሃ ወደ እርሱ እየተመለስን በመንፈሱ በሀይል እየተጠገንን : ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ባለን ህብረት የማንደራደርበት ዓመት ይሁንልን። በእኔም በእናንተም ላይ እንዲፈፀም በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በእምነት ፀለይኩኝ። @Lebegu @Lebegu @Lebegu

Join for more 😍 @Lebegu                                @Lebegu

Join for more 😍 @Lebegu                                @Lebegu

Join for more 😍 @Lebegu                                @Lebegu

Join for more 😍 @Lebegu @Lebegu የቃል ጊዜ ; ርዕስ : የፀጋ ሙሉ ገፅታ 😍 በወንድም በረከት በላይ