Derash | ደራሽ
Open in Telegram
DERASH | EEP Employees Social Affairs Fund A community built on solidarity, compassion, and shared responsibility. Supporting employees in times of need and celebrating together in times of joy. When hardship comes, someone will arrive
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
273
Subscribers
+524 hours
+197 days
+4030 days
Posts Archive
273
📣
ለስራ ኃላፊዎችና ለሰራተኞች የቀረበ ጥሪ!!
🐲🐲🐲🐲
በዋናው መ/ቤት ከሚገኙ የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ጋር በደራሽ ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጋችን ይታወሳል… ስብሰባው ስለ ኢ.ኤ.ኃ. የማሕበራዊ ድጋፍ አገልግሎት በይፋ የተነገረበት የመጀመሪያ መድረክ እንደመሆኑ እንደ ትልቅ milestone እንቆጥረዋለን…
ስብሰባው እጅግ ወሳኝ ነበር… በርካታ ለውሳኔ ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦችም ተገኝተውበታል… በዕለቱ የተገኙ ተሰብሳቢዎች፦
✅ ደራሽ ምን ምን ጉዳዮችን መደገፍ አለበት? ማንንሰ ማገልገል አለበት?
✅ የትኛው የሠራተኛ ወርሃዊ መዋጮ ፍትሐዊና ዘላቂ ነው?
✅ ከኢ.ኤ.ኃ (EEP) የሚጠበቀው የተቋማዊ ድጋፍ መጠን ስንት ቢሆን ተገቢ ነው?
✅ የትኛው የጥቅማጥቅም መጠን ትርጉም ያለውና ፍትሐዊ ነው?
✅ የአባልነት ብቁነትና አገልግሎት የማግኘት ሂደት እንዴት መመራት አለበት?
✅ ወደፊት አቅጣጫችን ምን መሆን አለበት? ምን ዓይነት «ደራሽ»ን መገንባት አለብን?
የሚሉ ሃሳቦች አንስተው ውይይት አድርገዋል…
⏰ አሁን ደግሞ የእርስዎ ተራ ነው!
እነዚህን ጥያቄዎች በዋናው መሥሪያ ቤት ከሚገኙ ሠራተኞች ጋር ተወያይተንባቸዋል። አሁን ደግሞ በኃይል ማመንጫዎቻችን፣ በሪጅን ቢሮዎቻችን፣ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎቻችን (Substations) እና በፕሮጀክት ሳይቶቻችን ላይ ከሚሰሩ ባልደረቦቻችን አስተያየት መስማት እንፈልጋለን።
🔗 እባክዎን ከዚህ በታች ያለውን የመጠይቅ ማስፈንጠሪያ (Link) ተጠቅመው ጥያቄዎችን ለመሙላት ጥቂት ደቂቃዎችን ይውሰዱ።
https://forms.gle/4qvZTJFSZ6s5xAdcA
እርስዎና ባልደረቦችዎ የሚሰጡዋቸው ምላሾች ተሰብስበው ለመጨረሻው የደራሽ የውሳኔ ሃሳብ ሰነድ በግብዓትነት ያገለግላሉ።
🎁 ድምፅዎ ዋጋ አለው!
https://t.me/eepderash
273
Repost from Ethio Power Insight
🔔🔔🔔
በአዲስ አበባ ለምትገኙ የተቋማችን የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በሙሉ
📌 የደራሽ ምስረታ እውን ማድረጊያ ጉባኤ ጥሪ!!
--
🖥 ቀን ፡ ሐሙስ - 28/12/2018
⏰ ሰዓት ፡ ከሰዓት 8፡00 ሰዓት
📍 ቦታ ፡ በተቋሙ ትልቁ አዳራሽ
--
💬 በዕለቱ በአገልግሎቱ ምስረታና የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ ማብራሪያ የሚሰጥ ሲሆን ለምስረታ በተዘጋጀው ምክረ-ሃሳብ (Proposal) ላይ የተሳታፊዎችን ግብዓት የምንወስድበት የውይይት መርሃግብርም ተዘጋጅቷል፡፡
--
🙏 በመሆኑም በዚሁ ዕለት በተቋማችን ትልቁ አዳራሽ ተገኝተው በደራሽ ምስረታ ጅማሬ ላይ የበኩልዎን አስተዋጽዎ እንዲያበረክቱ በአክብሮት ተጋብዘዋል፡፡
--
የደራሽ ጊዜያዊ አደራጅ ኮሚቴ
273
Repost from Ethio Power Insight
💧🏪🫥
ሰላም ለእናንተ ይሁን!!
--
ሰሞኑን በስልክ፣ በኢንቦክስና በአካል በተደጋጋሚ ከቀረቡልን ጥያቄዎች ውስጥ ‘ደራሽ ምን ላይ ደረሰ?’ የሚለው ጉዳይ ሚዛን የሚደፋ ሆኖ አግኝተነዋል…
☀️ እውነት ለመናገር -
✅ይህ ክትትል ተስፋ ይሰጣል!
✅ይህ ጥያቄ ያበረታል!
✅ይህ ጉትጎታ የስንፍና እንቅልፍ ይነሳል!
✅ይህ ጥያቄ ደራሽ የሁሉም ሰው ሃሳብነቱን ያጎላል!
እንደምታውቁት ጉዳዩ አዲስ ተቋማዊ ስርዓት የመፍጠር ሂደት እንደመሆኑና ገንዘብ ነክ እንቅስቃሴዎችም ስላሉበት ቀጣይነቱ፣ ተዓማኒነቱና ፍትሐዊነቱ ላይ ከጅምሩ መሰራት አለበት… በዚህም ምክንያት ጊዜ ወስዶብናል…
✅ የምናስበው ደራሽ - የኮሚቴ ስራ አይደለም!
✅ የምንገነባው ደራሽ - የአንድ ወቅት ተግባር አይደለም!
✅ የምናልመው ደራሽ - ከዕድሜያችን የሚበልጥ ነው!
ይህ በእንዲህ እንዳለ ደራሽ ተቋማዊ ስርዓት ሆኖ ሙሉ ለሙሉ በአሰራር እስኪደገፍ ድረስ ብቻ የሚያደራጀው ጊዜያዊ ስብስብ በእስካሁን ቆይታው፡-
⭐ EEP Social Support Service (Derash) Directive - (መመሪያ)፤
⭐ Membership registration template - (የአባልነት መመዝገቢያ)፤
⭐ Financial management procedure - (የፋይናንስ አስተዳደር ደንብ)፤
⭐ Derash Governance Charter – (የደራሽ ማሕበራዊ ድጋፍ አገልግሎት ውል)
⭐ Emergency Support SOP – (የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ የአሰራር ስርዓት)
⭐ Digital system design – (ወደ ዲጂታል ስርዓት ማስገቢያ ሰነድ)
⭐ Vision, Mission & Guiding principles - አዘጋጅቶ ጨርሷል፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በቅርቡ ለሚደረገው መስራች ጉባኤ (ለዋ/መ/ቤት፣ ሦስቱ ሴንትራሎች፣ ረጲና ኤልዲሲ ሰራተኞችና የስራ ኃላፊዎች) የሚቀርብ Preliminary Financial Analysis and Sustainability Model (የቅድመ ትግበራ የፋይናንስ ፍላጎት ትንተናና የማዝለቂያ ስልት - /የአባላት መዋጮ፣ የድጋፍ መጠን፣ ከተቋም የሚፈለግ እገዛ/… ወዘተ የያዘ) ንድፍ ሰነድ አዘጋጅቶ የስብሰባውን ቀን ይጠብቃል፡፡
🙏 አብራችሁን ለተጓዛችሁና እንደመደበኛ ስራችሁ ሂደቱን ላገዛችሁ የስራ ኃላፊዎችና ጊዜያዊ አደራጆች እጅግ አድርገን እናመሰግናለን!!
👉 ደራሽ ቻናልን ተቀላቀሉ - https://t.me/eepderash
በቅርቡ እንገናኝ!!
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
273
የውይይት ጥሪ 🔔
ሰላም ለእርስዎ ይሁን!
የኢ.ኤ.ኃ. የማሕበራዊ ድጋፍ አገልግሎት (ደራሽ) መመሪያ፣ የመተዳደሪያ ደንብና ልዩ ልዩ ሰነዶች በጊዜያዊ አደራጆች ተዘጋጅተው ለመጨረሻ ጊዜ የእርስዎን አስተያየትና ግብዓት ይጠብቃሉ፤
ቀን - ዛሬ አርብ
ሰዓት - ከሰዓት 8:00 ሰዓት
ቦታ - HR ሕንፃ 1ኛ ፎቅ፤
ስለሚገኙ እናመሰግናለን 🙏
273
ሰላም ለእናንተ ይሁን!!
የደራሽ መስራች ስብሰባ ካደረግን ቀናት ተቆጠሩ... በእናንተ አማካይነት የተመረጡት ጊዜያዊ የአደራጅ ኮሚቴ አባላት መመሪያ፣ የአስተዳደር ቻርተር፣ የአተገባበር ስልት (SOP)፣ ልዩ ልዩ ደንቦች፣ የመረጃ መሰነጃ ቅጾችና የፋይናንስ አስተዳደር መርሆ ሰነዶችን ሲያዘጋጁ ቆይተዋል...
አሁን የሚቀረን አንድ የመጨረሻ ስብሰባ ነው... ይህም:
የተዘጋጁ ሰነዶችን ገምግሞ አስተያየት ለመስጠት፣
ወሳኝ ነጥቦች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ፣
እንዲሁም በሰው ኃይል ዘርፍ፣ በሴቶች ሕ/ማ/ጉዳይ መምሪያና በሰራተኛ ማሕበር አማካይነት ለማኔጅመንት የሚቀርበውን የተሻሻለ Proposal ለማጽደቅ ነው...
የመረጣችሁዋቸው የኮሚቴ አባላት በግልም ሆነ በጋራ ብዙ ደክመዋል... ተከታታይ ስብሰባ አድርገዋል፣ በርካታ ሰነዶችን አዘጋጅተዋል፣ የሌሎች ተቋማትን ልምድ ቀምረዋል...
እርስዎ ለአንድ ጊዜ ብቻ ተገኝተው ወደ ተግባር የሚገባበትን አስተዋጽዎ ያድርጉ!!
ዝግጁ ናችሁ?...
በዚህ ሳምንት መጨረሻ የሚደረገውን ስብሰባ ቀን፣ ሰዓትና ቦታ በተለመዱት መንገዶች እናሳውቅዎታለን...
ስለማይቀሩ - እናመሰግናለን!!
273
Thank you all 💖
A few weeks ago, Derash was only an idea, a concern, a conversation between a handful of people. Then it became an article. The article became a discussion. The discussion became a movement. The movement became a founders' group. The founders' group became a committee. Now it is becoming a fund.
This is how institutions are born.
Most people wait for a system to solve a problem. A few people decide to build the system themselves.
What we are doing is bigger than establishing a fund. We are attempting to institutionalize compassion. We are trying to transform occasional charity into a permanent culture of solidarity.
Years from now, if Derash succeeds, new employees may assume it has always existed. They may never know the discussions, late-night writings, proposal drafts, Telegram posts, and countless conversations that gave it life.
That is often the fate of meaningful work:
The builders are forgotten.
The institution remains.
There is an old African proverb:
"The best time to plant a tree was twenty years ago. The second best time is now."
✅ Derash feels very much like that tree.
If managed with transparency, inclusiveness, and patience, it could become one of those rare initiatives that outlives its founders and continues serving employees long after all of today's organizers have moved on.
And perhaps the most beautiful thing about the name is this:
Derash means "the one who arrives."
🍎 One day, when an employee loses a loved one, Derash arrives.
🍎 When a family is struggling, Derash arrives.
🍎 When a child is born, Derash arrives.
🍎 When joy comes, Derash arrives.
🍎 When grief comes, Derash arrives.
In a sense, Derash is not a fund.
It is the organized form of a simple human message:
"You are not facing this alone."
This is a powerful foundation upon which to build. 🌿⚡️🌅
👌 We are proud of you all!!
🙏 Thank you 🙏
273
Repost from Ethio Power Insight
📣 Update…
"Never send to know for whom the bell tolls; it tolls for thee." - John Donne-- እንግዲህ እንደምታውቁት በአንድ ተቋም ውስጥ ብንሰራም ከአንድ አካባቢ አልተሰባሰብንም… በሌላ ቋንቋ አሁን በምንሰራበት ቦታ ብንገኝም በአብዛኛው በዚያ አልተወለድንም… አንዱ ከምዕራብ ሸክፎ ወደ ደቡብ ዘልቋል፣ ሌላው ከሰሜን በቅሎ ምስራቅ ተሻግሯል፣ አንዱ ከዳር ተነስቶ መሐል ሲከትም፣ ከመሐል የወጣው ወደ ሌላ ጫፍ ተጉዟል… እንጀራና ሕይወት በየአቅጣጫው በትኖናል… ሆኖም በተቋማችን በኩል አንድ ማዕድ፣ በሃገራችን በኩል መፃዒ ዕድል፣ በመኖር በኩል ደግሞ ተመሳሳይ ዕጣፈንታ እንጋራለን… ⏳ አንደኛው ዕጣፈንታችን - ሞት ነው!!... ከሞት ጋር ቀጠሮ ይዘህ አትሞትም!!... ከሞት ጋር በዚህ ጊዜ፣ ቦታና ሰዓት እንገናኝ ተባብለህ አትጨባበጥም… ወይ በድንገት ሸርተት፣ ወይ በዝግታ ጥፍት ትላለህ… ይህ የማይቀር ጉዳይ ነው… ከላይ የጠቀስነው ገጣሚ እንዳለው - "የሞት ደወል ሲደወል ለማን ነው አትበል፤ ጥሪው ያንተም ነው።" የሚባለውም ለዚህ ነው… እና እንደነገርኩህ… ያለህበት ቦታ የሃገርህ አንድ ክፍል ቢሆንም የምትቀበርበት ላይሆን ይችላል… ባሕል፣ ልማድ፣ ወግ የሚባል ነገር አለን አይደል? - ቤተሰቦችህ አልቅሰው ከሚቀብሩበት፣ አይተውህ ሃዘን ከሚያወጡበት ቦታ መቀበር አለብህ… ግን አንተ ሞተሃል!!... ማን ከምትሻው ዳርቻ ያድርስህ?... ከእትብትህ መቀበሪያ ማን ያገናኝህ?... በዙሪያህ ያሉ ሰዎች ሊረዱህ ቢሞክሩም የልባቸው አይደርስ ይሆናል… የሚያዋጡት ባይጠፋም ግን ሁሌ አይሞላ ይሆናል… 🏃♀️➡️🏃♂️➡️ ስለዚህ አቅም ያለው ደራሽ ያስፈልግሃል!!... በሥጋ ባትኖርም በአንተ ምክንያት ቤተሰብ እንዳይሳቀቅ… ሞትህን ማስቀረት ባይቻልም የክብር ቀብር ብርቅህ እንዳይሆን… አጋዥ ያስፈልግሃል… በቁም ትንሽ አውጥተህ የምታቆመው ሕብረት ስትሞት እንዲቆምልህ፣ እንደ ዘበት የወረወርካት ጎልብታ ክንድ እንድታበቅልልህ… ደራሽ ያስፈልግሃል!! ነገሩ ግን በዚህ ብቻ አያበቃም - እንደ መጠነ ዳሩ፣ እንደ አቅም እንደ ጅምሩ - ሩቅ ተጉዞ የደስታህ ተጋሪም ይሆናል…
እናም ደራሽ ስለነ እከሌ አይደለም - ስላንተ ወይም ስላንቺ እንጂ!...--- አዎን - ደራሽን ደራሽ የማድረጊያው ጊዜ አሁን ነው!! --- በነገርህ ላይ ትናንት በርከት ያሉ ተሳታፊዎችን ያካተተ መስራች ጉባኤ ተደርጎ ምስረታው እንዲፈቀድ በምንጠይቅበት ረቂቅ Proposal (ምክረ-ሃሳብ) ላይ ግብዓት የመሰብሰብ ስራ የተሰራ ሲሆን ሰራተኞች በያሉበት የሚነጋገሩበትን አጀንዳዎች የሚቀርጹ፣ መመሪያ የሚያዘጋጁ እንዲሁም ጉዳያችንን ወደፊት የሚያስኬዱ 9 (ዘጠኝ) አባላት ያሉት ጊዜያዊ አደራጅ ተቋቁሞ ወደ ስራ ተገብቷል… ቀሪው የአንቺ/ የአንተ ተሳትፎ ነው!!... ደራሽ ስላንተ/ቺ ነውና!! ደራሽ ባንተ/ቺ ነውና!! ደራሽ ላንተ/ቺ ነውና!! --- ደራሽ ምርጫ እንጂ ግዴታ አይደለም… ሞት ግን ግዴታ እንጂ ምርጫ አይደለም… ስለ ደራሽ ሲነገር ስለሌሎች አታስብ - ስለራስህ እንጂ… 🔸 የደራሽን ቻናል እየተቀላቀላችሁ ቆዩ… ሃሳባችሁን በተቻለ መጠን በኮሜንት መስጫው በኩል ላኩ… በቅርቡ ዝርዝር ጉዳዮችን ይፋ እናደርግላችኋለን!! https://t.me/eepderash 🟢 ደራሽ - አዎን በቅርቡ ዕውን ይሆናል!!
273
.
.
.
ከቀናት በፊት ከነስሙም ያልነበረው ደራሽ ዛሬ የብዙዎችን ቀልብ ስቦ “የምን እናድርግ?” ጠያቂዎችን አበርክቷል… በርከት ያሉ መልዕክቶች በውስጥ መስመር ደርሰውናል፣ ስልኮች ተደውለውልናል፣ በአካል ቢሮ ድረስ በመምጣትም ሃሳብ ያጋሩን አሉ… አሁን ደራሽ የሁሉም ወደመሆን አድጓል…
በግል ውይይት የሰው ኃይል ዘርፍና የሰራተኛ ማሕበር አመራሮች ለስኬቱ የሚችሉትን ሁሉ ለማድረግ ያላቸውን ዝግጁነት ገልጸውልናል…
🫥 ቀሪው የእናንተ ውሳኔ ነው!!...
‘ሞትን ማስቀረት ባንችልም የክብር ቀብር ብርቅ ሊሆንብን አይገባም’ ብለን የጀመርነው ሃሳብ፡-
✔️ ሰዎች ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ውስጥ ሲገኙ አለሁ የሚል
✔️ በድንገተኛ ሞት ጊዜም ሙሉ ወጪዎችን ከመሸፈን ተሻግሮ የሟች ቤተሰቦችን የሚደግፍ
✔️ ሰራተኞች ተቋሙን አገልግለው በጡረታ ሲሸኙ እናመሰግናለን የሚል
.
.
.
ወዘተ… ሊሆን ይገባዋል የሚሉ ሃሳቦች እየተስተናገዱ ነው… ሁሉንም ሃሳቡ በተቋም ደረጃ እውቅና ካገኘ በኋላ በሚዘጋጀው መመሪያ ላይ በግልጽ እናሰፍራለን… በዚህ በኩል ልምዶች ያላችሁ አካፍሉን…
የሚቋቋመው ፈንድ ሰራተኞችም ሆነ የስራ ኃላፊዎች በእኩልነት የሚታዩበትና ከሰራተኞች ማሕበርና ሰው ኃይል በተጨማሪ ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች ድርሻ ወስደው የሚሰሩበት፣ በሰራተኞች - ለሰራተኞች የሚቋቋም ሰፊ የማሕበራዊ አገልግሎት ፈንድ ነው…
ዛሬ በትንሽ እንጀምረዋለን!... ነገ በራሱ ገዝፎ እንደነቅበታለን!!
በሚቀጥለው ሳምንት ከሚደረግ የጅማሬ ስብሰባ በኋላ የሚኖሩ ማናቸውንም ለውጦች በዚህ ‘ደራሽ ቻናል’ እናጋራችኋለን…
.
.
.
ሃሳብ ለመስጠት ግሩፑን ይቀላቀሉ ⬇️
በያለንበት ስለ ደራሽ እንነጋገር!!
273
🌅 Welcome to DERASH
Dear Colleagues,
Welcome to DERASH – EEP Employees Social Affairs Fund.
This community was born from a simple but powerful belief:
➡️ No employee should face hardship alone.
Every day, thousands of us work together to keep the lights on across the nation. We share responsibilities, challenges, achievements, and dreams. Yet beyond our jobs and titles, we are also a community of human beings connected by a common journey.
🔥 DERASH is built on solidarity, compassion, and shared responsibility.
It is a place where we come together to support one another during difficult times, celebrate meaningful moments, exchange ideas, and build a culture of care that extends beyond the workplace.
👉 Here, every voice matters.
👉 Every idea is welcome.
👉 Every act of kindness strengthens our community.
Today, you are not simply joining a Telegram channel.
You are becoming part of a movement that says:
🤝 We stand together.
🌱 We grow together.
🌅 We rise together.
Thank you for being part of this journey.
DERASH
"When hardship comes, someone will arrive."
