en
Feedback
Abu Menal || አቡ መናል

Abu Menal || አቡ መናል

Open in Telegram
1 309
Subscribers
-324 hours
+5487 days
+76030 days
Posts Archive
በማይመለከትህ ጉዳይ አትግባ ...ካልሆነ ግን ከባድ ዋጋ ትከፍላለህ ። በዱኒያም በአኺራም ። ሀቂቃ አላህ የሰጠን እድሜ (ጊዜ) እጅግ የተገደበ መሆኑን መርሳት የለብንም ። አይደለም በማያገባን ነገር
በማይመለከትህ ጉዳይ አትግባ ...ካልሆነ ግን ከባድ ዋጋ ትከፍላለህ ። በዱኒያም በአኺራም ። ሀቂቃ አላህ የሰጠን እድሜ (ጊዜ) እጅግ የተገደበ መሆኑን መርሳት የለብንም ። አይደለም በማያገባን ነገር ሁሉ "ዘው" እያልን ..ለሚመለከቱን ጉዳዮች የሚበቃ ጊዜ የለንም። ( አላህ ጊዜው ላይ በረካን ያደረገለት ሲቀር ) ለዚህም ነው ሰይዳችን 🤍​ " ከአንድ ግለሰብ የእስልምናው ማማር መገለጫ (መካከል)፡ የማይመለከተውን ነገር መተዉ ነው። " ያሉት ​📚 ቲርሚዚ፡ 2317 🔶 t.me/Abu_Menal

በማይመለከትህ ጉዳይ አትግባ ...ካልሆነ ግን ከባድ ዋጋ ትከፍላለህ ። በዱኒያም በአኺራም ። ሀቂቃ አላህ የሰጠን እድሜ (ጊዜ) እጅግ የተገደበ መሆኑን መርሳት የለብንም ። አይደለም በማያገባን ነገር
በማይመለከትህ ጉዳይ አትግባ ...ካልሆነ ግን ከባድ ዋጋ ትከፍላለህ ። በዱኒያም በአኺራም ። ሀቂቃ አላህ የሰጠን እድሜ (ጊዜ) እጅግ የተገደበ መሆኑን መርሳት የለብንም ። አይደለም በማያገባን ነገር ሁሉ "ዘው" እያልን ..ለሚመለከቱን ጉዳዮች የሚበቃ ጊዜ የለንም። ( አላህ ጊዜው ላይ በረካን ያደረገለት ሲቀር ) ለዚህም ነው ሰይዳችን 🤍​ " ከአንድ ግለሰብ የእስልምናው ማማር መገለጫ (መካከል)፡ የማይመለከተውን ነገር መተዉ ነው። " ያሉት ​📚 ቲርሚዚ፡ 2317 🔶 t.me/Abu_Menal

🔴አንድ የዱንያ ጉዳይ ሲገጥምህ፡ እጆችህን ወደ አላህ አንስተህ እንዲፈጽምልህ ትለምነዋለህ። .... ነገር ግን ሪዝቅህን እንዲያሰፋልህ እንደለመንከው ሁሉ፡ የልብህን ሕይወት አላህን ጠይቀሃልን? 🔴እንዲሁም ከዱንያ ጭንቀቶች እንዲገላግልህ እንደለመንከው ሁሉ፡ ከብዥታ እና ከስሜት ( ሹብሀ እና ሸህዋ ) በሽታዎች እንዲፈውስልህ ጠርተኸዋልን? ​ኢብኑል ቀይም እንዲህ ብለዋል፦ 🏷️... የሚገርመው ፡ ጉዳይ ሲገጥመው እንዲፈጽምለት ምኞቱንና ትኩረቱን ወደ አላህ ያዞራል፤ ነገር ግን ልቡ ከድንቁርናና ከመዘናጋት ሞት ሕያው እንዲሆን፣ እንዲሁም ከብዥታ እና ከስሜት ( ሹብሀ እና ሸህዋ ) በሽታዎች እንዲፈወስ ለመጠየቅ አይጋፈጥም። ነገር ግን ልብ አንዴ ከሞተ፡ ወንጀሉ (ማመፁ) አይሰማውም።.. 🏷️
📚 አል-ፈዋኢድ 111
🔶 t.me/Abu_Menal

🫥 የደርስ ማስታወቂያ ! 🔎ለሙስሊም ሴቶች ምክሮችን የያዘ አጭር ሪሳላ ነው የኪታቡ ስም 🏷️ተውጂሀት ሊል ፈታቲል ሙስሊማህ🏷️ የኪታቡ አዘጋጅ ዶ/ር ዐብዱልዐዚህ ቢን ዳውድ አልፋይዝ 🫥ደርሱ
🫥 የደርስ ማስታወቂያ ! 🔎ለሙስሊም ሴቶች ምክሮችን የያዘ አጭር ሪሳላ ነው የኪታቡ ስም 🏷️ተውጂሀት ሊል ፈታቲል ሙስሊማህ🏷️ የኪታቡ አዘጋጅ ዶ/ር ዐብዱልዐዚህ ቢን ዳውድ አልፋይዝ 🫥ደርሱ ዘወትር ጁምዐ ከምሽቱ 3:00 -3:30 ይሰጣል ። የኪታቡን 📄 ለማግኘት ይጫኑኝ! ትምህርቱ የሚሰጥበት ቻናል ⬇ ▫️ t.me/Abu_Menal

ቀጣይ ጁምአ የምትጀመረው ሪሳላ 😬

በቀጣይ ጁምአ ይጀመራል ። የኪታቡ ስም እና 📄 በቀጣይ ይለቀቃል ።

በመቀጠል አደብ እና/ወይም አዝካር ( ተዝኪያ ) ...

በመቀጠል አጭር የዐቂዳ ሪሳላ ...

በመቀጠል አጭር የሲራ ሪሳላ

🧡በመጀመሪያ የምንጀምረው ሙስሊም ሴቶችን የተመለከተ አጭር ሪሳላ ነው

🟢ዛሬ ማታ ላይ ይህ poll ይዘጋል ። እስከዚያ ድረስ ተሳተፉ

🧡እዚሁ ቻናል ላይ ዘወትር ጁምአ ከምሽቱ 3:00-3:30 ድረስ የአጫጭር ሪሳላዎች ደርስ ለመጀመር ታስቧል ። 🫥የመቅራት ፍላጎት አላችሁ ? 🤔ምን ኪታብ ቢጀመር ደስ ይላችኋል ? 🧠 በየትኛው የዒልም ዘርፍ ? ኮመንት ላይ ሀሳባችሁን አጋሩን ⬇️

"💬አንድ ባሪያ ወደ አላህ ችግረኝነቱንና ፈላጊነቱን ካሳየ፣ እሱንም ከለመነ፣ የአላህን ቃል፣ የመልእክተኛውን ቃል፣ የሶሃባዎችን፣ የታቢዒዮችን እና የእስልምና አኢማዎችን ንግግር ማስተንተንና መመልከትን ካዘወተረ፤ የቅን መንገድ (ሂዳያ) በር ይከፈትለታል።"
ኢብኑ ተይሚያህ 📚 መጅሙዑል ፈታዋ (5/118)
▫️ @Abu_Menal

"ሰዎችን ከሱና ማስወጣት ከባድ ነው" ይላሉ ኢማሙ አሕመድ። ይሄ ንግግር 1. የሱናን ጥብቅ እና ታላቅ ደረጃ ይጠቁማል። የሱናን ትልቅ ዋጋ (ቂማ) የተገነዘበ ሰው ሑክም ማስተላለፍ ላይ ይጠነቀቃል። 2. ሰውን ያላግባብ ከሱና ማስወጣት ምን ያህል ከባድ አደጋ እንደሆነ እንወስዳለን። ጉዳዩ ከግለሰብ አልፎ ደዕዋን ወይም ህዝብን የሚጎዳ አያያዝ ካለው ደግሞ መዘዙ ይበልጥ የከፋ ይሆናል። = ከኡስታዝ ሙሀመድ አህመድ ገፅ የወሰድኩት

የመዲና ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ በርቀት የሸሪአ ዲግሪ ፕሮግራም ምዝገባ ላይ ነው ፤ፍላጎቱ ያለው ይሳተፍ

تعلن #الجامعة_الإسلامية عن فتح باب التقديم والقبول على برنامج بكالوريوس الشريعة عن بُعد للعام الجامعي 1448هـ، للطلاب والطالبا
تعلن #الجامعة_الإسلامية عن فتح باب التقديم والقبول على برنامج بكالوريوس الشريعة عن بُعد للعام الجامعي 1448هـ، للطلاب والطالبات الدوليين. رابط التقديم: https://bit.ly/44ORbA0 للاطلاع على دليل القبول: https://bit.ly/4pFD5KE

​«💬በቂያማ ቀን በአላህ ፊት ቀርባችሁ ሳትመረመሩ በፊት ዛሬ በዱንያ ላይ እያላችሁ ራሳችሁን መርምሩ፤ ሥራችሁ ሚዛን ላይ ተቀምጦ ሳይመዘን በፊትም የዛሬ ውሏችሁን እና ሥራችሁን ራሳችሁ መዝኑ።» ​
ዑመር ቢን አል ኸጣብ 📚አ'ዙህድ ፤ 120
✈️ t.me/Abu_Menal

​«💬ሙእሚን ብልህ፣ አእምሮው የነቃና አስተዋይ ነው፤ ነገሮችን በጥንቃቄ ያስብባቸዋል፣ ያደራጃቸዋልም። ስለዚህ ሙስሊም ማለት ራሱን እንዲያው .. በዘፈቀደ የሚተው ሰው አይደለም። በመሆኑም—በተለይም በአሁኑ ዘመናችን—ሰው ጊዜውን ሊያደራጅ ይገባል፤ ለምሳሌ ጠዋትን ለዚህ፣ ምሽትን ደግሞ ለዚያ ያደርጋል፤ ቅዳሜን ለዚህ፣ እሁድን ደግሞ ለዚያ እንደ ሁኔታው አስፈላጊነት ይመድባል። ይህን የሚያደርገው ጊዜው በከንቱ እንዳያመልጠውና እንዳይባክንበት ነው።...»
ኢብኑ ዑሰይሚን ​📚ሸርሑ ቡሉغል-መራም 10 ፤494
▫️ t.me/Abu_Menal