en
Feedback
𝙸'ƚ𝚒dαℓ 𝙸мαи

𝙸'ƚ𝚒dαℓ 𝙸мαи

Open in Telegram

የፃፈ ሁሉ ደራሲ የተፃፈ ሁሉ ድርሰት አይባሉም !

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
2 891
Subscribers
-224 hours
-97 days
+4730 days
Posts Archive
300❤+ ይሆናል የሚል ተስፋ አለኝ እንግዲህ ሰአቱ እስከሚደርስ 😭

«ማታ ጨዋታ ነበረ እስከ ስድስት ሰአት አልተኛውም ለዛ ነው» አለኝ ደግሜ ልጠይቀው ፈልጌ ከአፌ መለስኩት «ለዛ ነዋ ፊትህ ቲማቲም የመሰለው ዛሬም የደገፍከው  ቡድን ተሸነፈ ÂŤ አዎ ባክሽ ተበላው Âť ÂŤ ምንድነው የተበላከው» ÂŤ ቤቲንግ ነዋ Âť ÂŤ ደሞ እሱ ምን ይሆን Âť ÂŤ በቃ አንቺ ነጭ ወረቀት ነሻ መች ይሆን የምትነቂው ግን  ቤቲንግ ማለት  ግምት አስቀምጠሽ ብር ትመድቢያለሽ ከዛ ግምትሽ ልክ ከሆነ ብር ትበያለሽ ማለት ነው» «እንዴ ይሄ እኮ ቁማር ነው Âť «እሱን አንቺ ነሽ ያልሽው እንግዲህ» ÂŤ ልክ ነኝ ቁማር ነው ይሄ ሲቀጥል ሙስሊም ነህ እንዴት ቁማር Âť አላስጨረሰኝም ከተቀመጠበት ተነሳ ÂŤ እርቦኛል እና ቁርስ ልብላ Âť ወደ ማእድ ቤት ሄደ ከእኔ ወሬ ሽሽት እንጂ ለይላን ጠርቶ ነው የሚቀርብለት ከእሱ ጋር ጭቅጭቅ ከምጀምር ለጊዜው ዝም ብለው ይሻላል በሰሀን ምግብ ይዞ መጣ «አንቺን ቁጭ አድርጌ አልበላው ወይ ታጥበሽ ነይ ወይ ውጪልኝ» «በልቻለሁኝ እኔ ብላ አንተ እኔ ፕሮፔሰር ጋር እሆናለሁ Âť «ሰሞኑን እናቴ ጋር ፍቅርሽ ጨምሯል በአይኔ መጣሽ Âť ÂŤ ለእኔም እናቴ ነች ካንተ እኩል ከማማ እኩል አሳድጋኛለች Âť «እንግዲህ እናትነቱን ከፈለግሽ እኔን ጠበቅ አድርጊ Âť ÂŤ ምን ማለት ነው እሱ ደሞ Âť ÂŤ ግልፅ እኮ ነው መቼስ ማማ ሴት ልጅ የላት ለወንድምሽ የምትድረው ያው ብቸኛ ልጇን እኔው ነኝ ወይ እንጋባ እንዴ ከወንድምሽ ጋር Âť «አስታግፊሩላህ አንተ እንዴት እንዴት ነው የምታስበው ግን» ÂŤ እንደሚታሰበው ነዋ ያው ብቸኛ ልጇን ትድርሻለች ደጅ አጥኚ በደንብ» ጉንጩን ከሞላው ምግብ እኩል ፈገግ ይላል «ወንድ በአለም ቢጠፋ አንተን አላገባም» «ኧረ ባክሽ እኔን አጊንተሽ ነው Âť መልሱን ሳልሰማ ጥዬው ወጣሁኝ በረንዳ ላይ አንድ ወንበር ሳብ አድርጌ ተቀመጥኩኝ «አልተነሳም አይደል እስካሁን Âť «አዎ አሁን ቁርስ እየበላ ነው Âť «እንደው ልጄ ምከሪልኝ እስኪ አይኔ እያየ እኮ አንድ  ልጄን እያጣውት ነው ተወላግዶ ያደገን ዛፍ ማቃናት ማለት መስበር ነው እሱ ችግኝ እያለ አብሬው አልነበርኩም ልኮተኩተው ሲጣመም ላቃናው አልቻልኩም አሁን ደሞ እሱ ዛፍ ሁኗል ምን እንደማደርግ አልገባኝም ለዚህ ሁሉ ተጠያቂው ደሞ አባቱ ነው  Âť «ፕሮፔሰር አትጨነቂ እኔ የተቻለኝን በሙሉ ደርጋለሁኝ» «አመሰግናለሁኝ ልጄ አንቺ የልጅ አዋቂ ብስል ብልህ ሴት ነሽ Âť «ማታ ማማ እራት እኛ ጋር ነው ብላችኾለች መቀረት አይቻልም ሁላችሁም Âť ÂŤ አንቀርም ለቃሲዮን ንገሪው እናትሽን ስለሚፈራት ያለማመንታት እሺ ይላል ሙሀመድ ሾል ሊሆን ይችላል Âť ÂŤ ለእሱ ችግር የለውም ለባባ ስለነገርኩት ይዞት ይመጣል» /////// ልብስ ቀያይሬ ቻው ብያቸው ወጣሁ እነ ኤልዮን እና ኤልሮን የተለመደው ካፌ እየጠበቁኝ ነው ከሰፈር ብዙም እሩቅ አይደለም ቶሎ ደረስኩኝ ወደ ውስጥ ስገባ ኤልሮን ጠየም ካለች ቆንጅዬ ሴት ጋር ቁጭ ብሏል በአይኔ ዙሪያዬን ሳይ ኤልዮን የለም ተመልሼ ልወጣም ፈለኩኝ እንዳልረብሸው እንዲሁ ከራሴ ጋር ስሟገት እይታው ውስጥ ገሁኝ በእጁ ምልክት ሲያሳየኝ ወደ እነሱ ሄድኩኝ እና ሰላምታ ተቀያይረን ሰው የሌለበት ወንበር ላይ ተቀመጥኩኝ ÂŤ ምነው ሰላም አትላትም እንዴ እሷን Âť እንዴት ሰላም እንዳላልኳት ለልሴ እየገረመኝ እጄን ዘረጋውላት እሷም እጇን አቀበለችኝ ጥጥ የሚያስንቅ ሀር ለምኔ የሚያስብል ልስላሴ የሰው እጅ በዚል ልክ ይለሰልሳል እንዴ ÂŤ ትቆያለህ Âť አለችኝ ደንገጥ ብዬ እጇን ለቀኳት ይበልጥ ቀርቤ ሳያት ውብ ነች ፈዘዝ ያለ እና ጠይም መልክ አይኖቿ ጎላ ጎላ ያሉ ግን የሆነ ሀይል አላቸው ወደራሳቸው ሳብ የሚያደርግ ብቻ ውብ ነች ብዬ ልለፋት የማውቃትም ሰው መሰለችኝ ምን አልባት ሞናሊዛ ጋር ተመሳስላብኝ ይሆናል አልኩኝ በውስጤ የራሴው ነገር ለልሴ አሳቀኝ «በነገራችን ላይ የክላስህ ልጅ ነች አላወካትም» አለኝ ኤልሮን በድጋሜ ትኩር ብዬ አየዋት አንድ ቀን ቢሆንም ክላስ የገባሁት ግን እንደማውቃት ነው የተሰማኝ ÂŤ ሲዮራ ወይም አቪጌያ  ከሁለቱም መርጠህ በአንዱ ጥራኝ Âť ብላ በድጋሜ ከፈገግታ ጋር እጇን ዘረጋች ውበቷ ነበር እስካሁን ያስደመኝ ድምጿ ይለያል ስታወራ እንዲህ ያማረ ብትዘፍን ሳልኳት ÂŤ ኦ ትዝ አለኝ በስርአት ስላላየሁሽ ነው የዛን ቀን »ብዬ ለስላሳ እጇ ላይ እጄን አሳረፍኩኝ የህፃን ልጅ እጅ ልሹ እንደእሷ መለስለሱን እርግጠኛ መሆን አልችልም በዚህ ሰአት እጄን በፍጥነት ከእጇ ላይ አነሳውት «በቃ እኔ ልሂድ ያልኩህን አስብበት እሺ Âť ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳች አይኔ እሷን ተከትሎ ከካፌው ወጣ ÂŤ ወጣህ እኮ አብረዃት Âť አለኝ እየሳቀ ፈገግ አልኩኝ ÂŤ ቆይ አይኔ ነው ወይስ ቆንጆ ነች Âť ÂŤ ቆንጆ ነች ከትምሯችን ሴቶች ቆንጆ ነች ብዙ ሰው አይን ውስጥ ብትገባም  ማንም ሊይዛት የቻለ የለም የማትበላ ፍሬ በላት Âť «እና እዚህ ምን ትሰራለች ኤልዮንስ Âť «ለሆነ ጉዳይ እፈልግሀለው ስትለኝ ከንፌ መጣሁ Âť «ለምን ጉዳይ Âť «እሱ ሚስጥር ነው Âť ÂŤ ኧረ እንደዛ ተጀመረ ለቸከስ ብለህ ሚስጥር ምናምን ይሁን Âť ÂŤ አንተ ደሞ አሁን እንቀሳቀስ Âť ብሎ ቀድሞኝ የተጠቀሙበትን ሂሳብ ከፍሎ ተነሳ /////// ቀኑን ሙሉ እቴቴ ጋር ለእራት ስንዘጋጅ ዋልን ማማም ከስራ መልስ እኛው ጋር ጉድ ጉድ ስትል ቆየች ከመግሪብ ቡሀላ ባባ እና የቃሲዮን አባት መጡ በነገራችን ላይ የእኔም የእሱም አባት ስም ሙሀመድ ነው በዚህ ብዙ ሰው ትክክለኛ እህት እና ወንድም እንመስላቸዋለን ቆየ ብሎ ፕሮፔሰር መጣች ÂŤ ቃሲዮን የት ቀረ ልጄ ደውይለት እስኪ Âť ወደ ክፍሌ ሄድኩኝ እና ስልኬን ፈልጌ ደወልኩለት ከረዝም ጥሪ ቡሀላ ተነሳ ስልኩን አልፎ ጆሮዬን ሊበሳ የደረሰ ጩኸት ÂŤ አንተ የት ነህ Âť ÂŤ እ Âť ነገሩን እንዴት የምለው ይሰማዋል ይበልጥ ድምፁ ሲሰማኝ ዘፈን መሰለኝ ይቀጥላል ......... @rim_han .

 .                 ╔═══ ೋ 𔘓 ೋ  ═══╗                               ኦርቶዶክሳዊቷ                          á‹°áˆŤáˆ˛  አፍናን ሩማን Âť                   ╚═══ ೋ 𔘓 ೋ ═══╝ .                       ━─━─  𓍯  ─━─━                              ραɾƚ    0:03                         ━─━─  𓍯  ━─━─ ማንንም መጠየቅ የማልችለው ፍቺ የማይገኝለት ጥያቄዬ ነው የባባ ቁጣ ድምፅ ይሰማኛል እናቴ ግን ዝም ብላለች ጆሮዬን በሩ ላይ ለጥፌ ለደቂቃ ቆምኩኝ የአባቴም ቁጣ ረገብ አለ ድምፁ ጠፋ ቀስ ብዬ ኮቴዬን ሳላሰማ እንደ አመጣጤ ክፍሌ ተመለሰኩኝ የክፍሌን መብራት አጥፍቼ አልጋዬ ላይ በጀርባዬ ተኛው  የቴሌግራም ግሩፕ  Notification ደጋግሞ ይበራል ረስቼው ነበረ   የዛሬውን ማታ ትልቅ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ ለመጠበቅ ደመቅ ያለ ውይይት ላይ ናቸው ከተኛውበት ተነስቼ ተስተካክዬ ተቀመጥኩኝ «እ ሰውዬው Âť «አለሁ አለሁ Âť የቤቲንግ መተግበሪያውን ከፈትኩት Balance ላይ የሚታየው ቁጥር 15000 ይላል ጨዋታው በ30 ደቂቃ ውስጥ ይጀምራል የመረጥኳቸውን ጨዋታዎች መደደብ ጀመርኩኝ ሪያል ማድሪድ ከ ባየር ሙኒክ ሪያል ማድሪድ ያሸንፋል (Odds: 1.85) አርሰናል ከ ፒኤስጂ ከ2 ጎል በላይ ይገባል / Over 2.5 (Odds: 1.65) ኢንተር ሚላን ከ ባርሴሎና ሁለቱም ያገባሉ / Both Teams to Score (Odds: 1.70) የእነዚህ ሶስት ጨዋታዎች ድምር ኦድ (Total Odds) 5.18 ሆነ ይህ ማለት 1,500 ብር ሙሉ በሙሉ ብመድብ ጨዋታዎቹ ከተሳኩ 7,770 ብር አገኛለሁ ማለት ነው  «ብበላስ?Âť የሚል ፍርሃት ውስጤ ገባ በማማ ጫና የሚያስፈልገኝን ነገር ከሌለ በቀር ምንም አይነት ብር እንዳላገኝ አድርጋለች ባባ ጋር በዚህ ጉዳይ ብዙ ተጨቃጭቀዋል አሁን አካውንቴ ውስጥ ያለው ብር ካለቀ ባዶ እጄን መቀረቴ ነው ይህ ብር ከተላከልኝ  ሳምንት ሳይሆነው አለቀ ብል ማማ ካለ ጥርጥር  ትገለኛለች   በቴሌግራም ግሩፑ ላይ ጓደኞቼ  ÂŤ ዛሬ አሪፍ ኦድ ነው Âť የሚሉ መልእክቶች ገቡልኝ   Place Bet የሚለውን አረንጓዴ ምልክት ተጫንኩት ስክሪኑ ላይ ትኬትዎ በተሳካ ሁኔታ ተቆርጧል የሚል ጽሁፍ ወጣ  የ15000 ብሩ ቀሪ ሂሳብ ወዲያውኑ 13500 ብር ሆነ ካሸነፍኩ እጥፉን አገኛለሁ እንግዲህ ጨዋታው ተ ተጀመረ ከምሽቱ 4:00 በስልኬ Live Score መተግበሪያ ላይ የሶስቱም ጨዋታዎች ደቂቃ መቆጠር ጀመርኩ  0'.. 5'.. 10'..በ15ኛው ደቂቃ አርሰናል የመጀመሪያውን ጎል አገባ 1-0 በ28ኛው ደቂቃ ፒኤስጂ የአቻነቱን ጎል አስቆጠረ 1-1 በግሩፑ ላይ  ጓደኞቼ  የደስታ መግለጫ ቴክስት  ላኩ አርሰናል እና ፒኤስጂ ከ2 ጎል በላይ ይገባል ያልኩት ግምቴ ሊሳካ አንድ ጎል ብቻ ቀረው በ35ኛው ደቂ ባርሴሎና ጎል አገባ  1-0  ሁለቱም ያገባሉ ላልኩት ግምት አሁን የኢንተር ሚላን ጎል ብቻ ያስፈልገዋል ነገሮች ሁሉ በእቅዴ መሰረት እየሄዱ ነው  ሁለተኛው አጋማሽ  ከምሽቱ 5:00 በ55ኛው ደቂቃ አርሰናል ሁለተኛ ጎል አገባ 2-1 የመጀመሪያው ትኬቱ ተሳካ ከ2 ጎል በላይ ይገባል ያልኩት ግምት አበቃለት በ68ኛው ደቂቃ ኢንተር ሚላን ጎል አገባ 1-1 ሁለተኛው ትኬቱም ተሳካ ሁለቱም ያገባሉ ያልኩት ግምት አበቃ አሁን የቀረው አንድ ነገር ብቻ ነው ሪያል ማድሪድ ማሸነፍ አለበት ነገር ግን በሪያል ማድሪድ እና ባየርን ሙኒክ ጨዋታ ውጤቱ አሁንም 0-0 ነው ደቂቃው እየሮጠ ነው 70'.. 75'.. 80'..  ÂŤ ማድሪድ አገባ? Âť ብዬ ቴክስት ፃፍኩኝ «እየተጫኑ ነው ግን አልገባም" Âť የሚል ቴክስት ገባልኝ ከምሽቱ 5:38 88ኛው ደቂቃ በስልኩ ስክሪን ላይ ቀይ ማሳወቂያ በራ ጎል ገባ ልቤ ለሰከንድ ቆመ ነገር ግን ያገባው ሪያል ማድሪድ አልነበረም ባየርን ሙኒክ 1 - 0 ሪያል ማድሪድ ተስፋዬ ጥፍት አለ ጭማሪ 4 ደቂቃ ተሰጠ 91'.. 92'.. 93'.. 94'..ዳኛው ጨዋታውን አጠናቀቀ የቤቲንግ መተግበሪያውን ከፈትኩት የቆረጥኩት ትኬት ላይ በትልቁ ተሸንፈዋል / Lost" የሚል ቀይ ጽሁፍ ታየኝ ስልኬን አልጋ አጠገብ ያለው መደረደሪያ ላይ ወርወር አደረኩት እና አልጋ ውስጥ ገብቼ ጥቅልል ብዬ ተኛው //////// «እናትሽ ግን ታድላ Âť የሚነሳሳውን እቃ እየሰበበስብኩ ቀና ብዬ አየዋት በመገረም ÂŤ ምነው እቴቴ Âť ሁላችንም እቴቴ ነው የምንላት ከእኔ እኩል የምትሆን ሴት ልጅ አለቻት ልጅ እያለን እቴቴ ትላት ነበረ እኛም ከእሷ ወርሰን የእቤቱ ሰው ሁሉ እቴቴ ነው የሚላት ÂŤ በልጆቿ በባሏ በህይወቷ ደስተኛ ነች ልክ እንዳንቺው ወንድምሽን እኔው እጅ ላይ ነው ያደገው ከእናትሽ ይልቅ እንደውም እኔ ነኝ እናቱ ብል ይሻላል እሷ በሰአቱ ትምህርት ትማር ስለነበረ እኔ ጋር ነው ውሎው  እያደገ ሲመጣም ሷሊህ እንደሆነ ነው እንደ ሌሎች ልጆች እንኳን አያስቸግርም ኮስተር ካሉበት ምልስ የሚል እርቦት እንኳን እኮ ስጡኝ ለማለት የሚፈራ ሰው ነበረ Âť ብላ ፈገግ አለች እኔም ፈገግታዋ ተጋባብኝ እና ፈገግ አልኩኝ ÂŤ እኔ ረባሽ ነኝ ማለት ነው እቴቴ Âť ፊቴን ጣል አድርጌ ጠየቋት «ኧረ ምን በወጣሽ የእኔ ሸጋ ወርቅ እኮ ነሽ ከእኔ እኩል ማእድ ቤት እየተንደፋደፍሽ Âť ፈገግ አልኩኝ ÂŤ እሺ እቴቴ ይኸው ጨርሻለሁኝ ሁሉንም አሁን መሄድ እችላለሁ» «የቀረውን ቀስ እያልኩ እጨርሰዋለሁ ሂጂ በቃ Âť እጄን ታጥቤ ወደ ክፍሌ ሄድኩኝ ሰፍ ያለ አቢያ እና ቡኒ ከለር ሂጃብ ለብሼ ከእቤት ወጣሁ የግቢውን በር በቀስታ አንኳኳውት ÂŤ አንቺ ነሽ እንዴ Âť ÂŤ ምነው Âť ÂŤ አይ በማለዳው ማን ነው ብዬ ነው ግቢ» ብለው በሩን ከፈት አደረጉልኝ የቤቱ ዘበኛ ቀልጠፍ ብዬ ወደ ውስጥ ገባሁ በረንዳ ላይ ቁጭ ብለዋል ÂŤ አሰላም አለይኩም ፕሮፔሰር Âť «ዋለይኩም አሰላም እንዴት አደርሽ Âť ጠጋ ብዬ ጉንጯን ሳምኳት «በጠዋቱ ምን ሾል ላይ ሁነሽ ነው» «ሰሞኑን የሆነ ሪሰርች ይዤ ነው ግቢ ለይላ ቁርስ ታቀርብልሻለች» «ኧረ በልቻለሁኝ እኔ ቃሲዮንስ» «እስካሁን ከክፍሉ አልወጣም ተኝቶ ይሆናል Âť ÂŤ ይሄ ሰነፍ Âť የፕሮፔሰርን ቃል ሳልሰማ ወደ ውስጥ ገባሁ እና ደረጃውን ወጥቼ የቃሲዮንን ክፍል አንኳኳው ለረዥም ደቂቃ ÂŤ ኧረ ዛሬ እንኳን ልተኛበት Âť ንጭንጭ እያለ በሩን ከፈተው ከታች ቁምጣ ከወገቡ በላይ ራቁቱን ነው አንገቴን ስብር አደረኩኝ «አንቺ ነሽ እንዴ ለይላ መስላኝ ነው ግቢ» ብሎኝ ወደ ውስጥ ገባ  በሩን ከፈት አደረኩት እና ÂŤ እኔ አልገባም ሳሎን ና እጠብቅሀለው» ÂŤ ብትገቢ ምን እንዳላደርግሽ ነው ወንድምሽ መሆኔን ረሳሽው እንዴ» ÂŤ ሆ ሰውዬ ሌላ ነገር አታስብ ግን ምንም ቢሆን የደም ዝምድና እስከሌለን ድረስ እኔ ላንተ ሀጂነብይ ነኝ እረሳኸው እንዴ Âť «እሺ ኡስታዝ ሌላስ የለሽም የምትይው  ለልሴ ጨጓራዬ ተቃጥሏል አንቺ ደሞ አትጨመሪ Âť ÂŤ እና እኔ ምን አገባኝ ታድያ አሁን ልብስ ለብሰህ ሳሎን ና Âť ጥዬው ወደ ሳሎን ወረድኩኝ ቤቱ በየቦታው መፀሀፍ አይታጣበትም እድሜ ለፕሮፌሰር እኔም የመፀሀፍ ፍቅር እንዲያድርብኝ አድርጋለች ÂŤ አሁን ብተኛ ምን አልኩሽ ግን Âť እያዛጋ እና እየተነጠራር ደረጃውን ወረደ ÂŤ ተኛህ እኮ እስካሁን ሰአቱን አየኸው 3:15 ይላል ለመሆኑ ሱሁቢ ተነስተኻል ግን»

ስለ ዝምተኛ ሰው ያላችው አመለካከት ምን አይነት ነው? ዝም ያለ ሰው በእናንተ አተያይ ምን አይነት ሰው ነው? ✍🏻 @rim_han .

አሰላም አለይኩም         ኦርቶዶክሳዊቷ  1 የታሪኩ ርእስ ለምን እንደዚህ እንዳልኩት ታሪኩ ሲያልቅ ትረዱታላችሁ ምን አልባት እሱ ከሆነ ግራ ያጋባችሁ 2 መርሊንን ስታነቡ በሰው ህይወት ውስጥ ገብታችሁ ነበረ ያሁኑ ታሪክ ግን ወደ ራሳችሁ ህይወት በየገፀባህሪያቱ ውስጥ እራሳችሁን እንድታዩበት ነው የምፈልገው መስከረም 1....2018 ላይ ምናባችሁን ወስዳችሁ ክፍል አንድ ጀምራችሁ አንብቡት 3 በገረፍ ገረፍ አታንብቡት እንዲገባችሁ ምን አልባት ከእናንተ ህይወት ጋር ባያያዝ እንኳን ሰፋ ያለ እውቀት  የማታውቁትን ነገር ለማወቅ ይጠቅማችዃል ይሆናል 4  ቻናሉ ኢስላማዊ የስነ ፁሁፍ ቻናል ነው የሚለቀቁትም ኢስላማዊ ፁሁፎች ነው so መድረሳ ሂዳችሁ ኡስታዝ ባዮሎጂ  እንማር እንደማለት ነው ሁሉም ነገር ቦታ እና ስርአት አለው የሆነ teacher ነበረን 2 ተማሪ ከተከታተለኝ ይበቃኛል ይል ነበረ አሁን ለምን እንደዛ እንደሚል ገብቶኛል 2k የተወሰናችሁት ከተመቸዋችሁ ይበቃኛል ማታ በሰአታችን ታሪኩን እለቀዋለሁ ለአንባቢዎቼ አፉወን ለማታነቡ ሰዎች ግን ቻናሌ ላይ ተቀምጣችሁ አጉል አጉል አስተያየት የምትሰጡ ሰዎች እንደምትወዱኝ ስለደረስኩበት ደስ ብሎኛል አልደበረኝም ያው ታሪኩን ጀምሬ እጨርሰዋለሁ ብታነቡ ጥሩ ነው ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል ሳይሆን ህይወትን ሳትኖሯት በከፊል ያስተምራል አፍናን @rim_han .

ሲስቅ ሲጫወት እንጂ ሲተክዝ አይቼው አላውቅም ሁሉም ጋር መቀለድ መግባባት የእሱ ባህሪ ነው ዛሬ ግን ከወትሮው የተለየ ነው ፊቱ የእሱ አይመስልም ትውሶት ይሆን እንዴ እንጂማ እሱ እንደዚህ አይተክዝም እንዴት አይተክዝም ሰው አይደል እንዴ ምን አይነት ሀሳብ ነው የማስበው ግን ሆ  ሰው ሁሉ ያምርብሀል የሚለው  የኦሮሚያ ክልል ፓሊስ መለዮ እና በጀርባው አዙሮ ካነገተው ክላሽ ጋር  በረንዳ ላይ ቁጭ ብሏል ምን ሆንክም ልለው ፈለኩ ግን ፈራውት ከማወራው 2% ብቻ እንደሚሰማኝ አውቃለሁ ምክንያቱም እሱ አማረኛ ሁለተኛ ቋንቋ እኔ ኦሮመኛ ከሰላምታው ውጪ የማላውቅ ፍጡር አንዳንዴ ግን ቋንቋ ማወቅ ይጠቅማል  እውነት ÂŤ እንቢ አሉ Âť እኔ አስተካክዬ አልኩት እንጂ እሱ ያለው በሚንተባተብ ቅላፄ ነው  ምኑን ልለው አልደፈርኩም አውቃለዃ ሳምንቱን ሙሉ ላገባ ነው እያለ ጆሮዬ እስኪደማ ነግሮኛል ÂŤ ለም አሉ Âť × 3 ደጋግሜ የጠየኩት ÂŤ ፓሊስ ነህ አሉኝ አንድ ቀን በወጣህበት ልትቀር ትችላለህ ብትሞትስ ከዛ ደሞ ብሄርህ ኦሮሞ ነው እሷ አማራ Âť ÂŤ ከትዳር ጋር ምን አገናኘው ታድያ Âť አልኩት ደሞም እውነቴን ነው አይደለም ፓሊስ ለምን ጠቅላይ ሚንስትር አይሆንም ቀኑ ከደረሰ ሞት ያው ሞት ነው ይወስደዋል እሺ ብሄሩስ ምን ይሉታል አሁን ብሄርህ እንደዚህ ሆነ ብሎ አንሰጥም ማለት ግን አግባብ ነው እሱ ዝም አለኝ ወይ ያልኩት አልገባውም ወይም የሚመልስልኝን ፊደላት በውስጡ እየፈለገ ነው ግን ዝምታው ረዘመ ÂŤ እሺ ምን አሰብክ Âť በእጁ ምንም ለሚለው ቃል ምትክ የሚሆን ምልክት አሳየኝ ምን ልበለው ምንስ ማለት እችላለሁ እንደሚወዳት በደንብ አውቃለሁ እሷን ለማውራት ብሎ ነው አማረኛ ቋንቋ የሚለማመደው እሷ ቴክስት በላከችለት ቁጥር ማንበብ ስለማይችል አማረኛ ከሚችለው ጓደኛው ቤት ቤቱን ጥሎ የሚያድረው ... ለእሷ ብሎ ነው ምን ምም የእቤት እቃ ልግዛ ምን ምን መሟላት አለበት እያለ የሚያዳርቀኝ .... ለእሷ ብሎ ነው ረመዳን በደረሰ ቁጥር የእኔን ሾርባ እና ብስኩት ትቶ እሷ የምታስተናግድበት ምግብ ቤት እየሄደ የሚያፈጥረው ... ለእሷ ብሎ ነው ለሴት ምን ስጦታ ይሰጣል ንገሪኝ እያለ የሚጨቀጭቀኝ እኔም የዋዛ አይደለውም በ50 birr card የሚገዛላትን የምነግረው.. ለእሷ ብሎ ነው ምሳ እቤት ቀርቦ እሷ ጋር ከፍሎ የሚበላው  መቼስ ጥለፋት ብዬ አልመክረው ነገር በዚህ ጊዜ   ቤተሰብ ያልወደደው ነገር ይሳካል የሚል ብዙም እምነት  የለኝም ዝም አልኩት እና ወደ ቤት ገባሁ ✍ አፍናን @rim_han . .

ከራሴ ፁሁፍ ደስ ያለኝን ልጋብዛችሁ መኖራችሁን👍 .

https://t.me/rim_han/709 ይሄን ፁሁፍ አስታወሰኝ ይሄ ታሪክ ልጁ ሊደነቅ የሚገባው ሰው ነው ቢያጠፋም እኔ በበኩሌ አክብሬዋለሁ ልጅ ይፈጠር ነበረ በሽታ የሚባል ነገር ሊኖር ይችል ነበረ ሲቀጥል እንደዛ ሁነሽ ጥሎሽ ቢሄድ አላቅሽም ቢልሽ ከሁሉም በላይ ስነ-ልቦናሽ ይጎዳ ነበረ ... ይሄ ልጅ ይሄን ሁሉ ጠብቆልሻል ጥፋተኛ ነሽ ወይም ጥፋተኛ ነው እያልኩ ሳይሆን እኔ ከዚህ የባሱ ብዙ ታሪኮች አውቃለሁ በጣም ብዙ ግን ብዙ ጊዜ ሰው የሚያስበው ወንዶች ጥፋተኛ እንደሆኑ ነው የእኚን ጥፋት ሚን ይይልን ከወንድ ጋር አጉል ሰፋጣ መጨረሻዋ ይሄ ነው ይሄ ሰው አሁንም ካለ መቼስ ሌላ ተልእኮ አይኖረውም ከዚህ ቡሀላ ህይወት እንመስርት እያለሽ ከሆነ ተቀበይው ይሄ የእኔ ሀሳብ ነው .

ሰላም አለይኩም እንዴት ነሽ የኔ ታሪክ ምን መሰለሽ የሆነ ሰዓት ላይ እንደ ትሬንድ ተደርጎ ወንድ ማተራመስ ጀብድ ነበር እኔም ያንን ትሬንድ በጓደኛ ምክኛት ገባሁበት በሰዓቱ ሚታየኝ ሀራም አለመሳሳም፣ዚና አለመስራት ነበር ሁሉም ማወራቸውን ወንዶች ወድጄ አላውቅም አንዳንዶቹ ይወዱኛል አንዳንዶቹ ልክ እንደኔው ሙድ እየያዙ ነው እና ግን በሆነ አጋጣሚ እንደ ነቃ ሰው ሁሉንም ማወራቸውን ወንዶች በአንድ ጀንበር ተውኳቸው።ይህ ከሆነ በኃላ አንዱ ልጅ አወራኝ እና በጣም እልህ አስያዝኩት አላወራህም ብዬ ከዛ እንደምንም አርጎ ተለማምጦ ማውራት ጀመርን (ልምምጡን ተላመድኩት) ሆን ብዬ እንዲያፈቅረኝ አደረኩና አብረን እንሁን ጥያቄ እንዲያቀርብ አደረኩት ከሌሎች ወንዶች በበለጠ የቀረብኩት እሱን ነበር ሁሌ እስምሻለው ነገ ምናምን ሲል ወንድ ነሀ እለው ነበር እሱም ወንድነቴንማ አሳይሻለው እያለ ይዝት ነበር አንድ ቀን ያለ ልማዱ ከካፌ ውጪ ጋበዘኝ (ቤቱ)አስፈቅዶኝ አይደለም የሄድነው ባለ ራይዱ በወሰደን መንገድ እንጂ ብዙ ግዜ ምንሄድበትን ቦታ መርጦ ይዞኝ ሚሄደው እሱ ነው እና ስንወርድ ያለነው መንደር ውስጥ ነው የት ነኝ? አላውቅም በጣም ረጅም መንገዶችን እንደሄድን ነው ማውቀው። የት ነው የመጣነው አልኩት የወደፊት ቤትሽ አለኝ እሱን ቤት ማየት ምፈልገው ስንጋባ ነው አልኩት ለሌላ ነገር አይደለም እዪውና ሚጎድለውን እናሙዋላ እናም ሽማግሌ ልላክ አለ በዚ ልክ የወሰነ ስላልመሰለኝ የሆነ ደስታ ውስጤ ላይ ሲፈጠር ተሰማኝ።ከዚ በላይ ከምከራከር የሚል ሀሳብ ይዞኝ ገባው በጣም የሚያምር ግቢ ነው  ሳሎኑን አየን ኪችኑን አየን ብዙ ክፍሎችን ተዟዙረን ካየን በኋላ መኝታ ክፍሉን እንይ አለኝ በጣም ብፈራም እሺ ብዬ እሱ ከፊት እኔ ከኋላ  ሁነን ገባን ሳሎን ሚያክል መኝታ ክፍል ትልቅ አልጋ አለ ከበሩ አጠገብ ደግሞ አንድ ነጭ ሶፋ  እሱ ሂዶ አልጋው ጠርዝ ጋር ተቀመጠ እና ተቀመጭ እንጂ አለኝ እኔም አይ እዚጋ እሆናለው አልኩት እሱም አልተቃወመኝም እሺ አለ ከዛ ብዙ ሰዓታትን እንደዛ ሁነን ቆየን በመሀል ስልክ ተደውሎለት ወጣ እና ምግብ እና ጁስ ይዞ ገባ ወንበር አስጠግቶ ያለሁበት ጋር መጣና በላን ጠጣን ከሆኑ ሰዓታቶች በኋላ ስነቃ እዛው ክፍል አልጋ ልይ ብቻዬን ክብሬ ተግፎ ህመም ላይ ሁኜ ነቃው በጣም አለቀስኩ ቀለደብኝ ብዬ እየጮህኩ አለቀስኩ። ከዛ የሆነ ደብዳቤ ፅፎ ነበር "የኔ ቆንጆ ይህ እንዲፈጠር አልፈለኩም ነበር ግን እልህ አጋባሺኝ ይቅርታ በጣም ከኔ ማምለጥ አትችይም የድሮዋን አንቺ ነግረሺኝ ነበር እናአንቺን የኔ ማረግበት ብቸኛው መንገድ ይሄ ነበር አሁንም ቢሆን እወድሻለው እስካሁን ምንም የዋሸሁሽ ነገር የለም በዚ ሰዓት እንጋባ ብልሽ እንደ ጠላት ነው ምታዪኝ ስለዚ ደስ ያለሽ ጊዜ ላይ እንጋባ በይ አገባሻለው ለተፈጠረው ነገር ደሞ መከላከያ ተጠቅሚያለው  መሳቢያው  ውስጥ ብር እና ስልክ ቁጥር አለ ደውለሽ መሄድ የምትፈልጊበት ቦታ ካለ ሂጂ እዚም መቆየት ትችያለሽ ቤትሽ ነው" እና ይህ ከተፈጠረ 5 ወር ሁኖታል እና ላግባው አሁንም ቢሆን ቴክስት ይልካል በየ ቀኑ እስቲ ሀሳባችሁን እህታችን ይህን ብላናለች እስቲ ሀሳባችሁን አህባብ

2016 ላይ ጊቢ ሄጄ ነበር ሬሚዲያል ለመማር። ውጤት ያየነው 2017 ህዳር ነበር። ውጤት ይመጣል የሚለው ግምቴ ከፍ ያለ ስለነበር ጓጓሁ ጀመአችንን ለማየት ከእህት ወንድሞቼ ለመገናኘት ከጊቢው ማህበረሰብ ጋር ለመገናኘት በጣም ጓጓሁ። natural ስለሆንኩ ማለፊያው 250 ነበር እኔ ግን 249.97 አመጣሁ በጣም ደነገጥኩ ጓደኞቼ ጀመአው ቤተሰብ ሁሉም ደነገጠ። ለሶስት ቀናት ታምሜ ተኛሁ ያው ማዘን ተፈቅዶልናል ድንበር ማለፍ ነው የተከለከለው                                             ምን አስተማረኝ መሰላቹ ፦ 1 የአላህን ውሳኔ ወዶ መቀበል ያለውን ሰላም(አዘንኩ እንጂ አላማረርኩም በዚህም በጣም ደስተኛ ሆኛለው)      2 በደህና ጊዜ ከመልካም ሰዎች ጋር መጎዳኘት ያለውን ጥቅም ተረዳሁ ጓደኞቼ ጊቢ ላይ የተዋወቅኳቸው የጀመዓ ልጆች አንዳቸውም ለኸይር ነው አላህ የወሰነውን አምነን መቀበል አለብን ከሚል ንግግር ውጪ የደገመልኝ የለም ያ በጣም አበርትቶኛል የመልካም ንግግር ሰደቃነት ተብራርቶልኛል                                                     3 ቤተሰብ ምን ያህል እንደሚጨነቅልኝ ገብቶኛል ባባና ማማ ሊያናግሩኝ እስኪፈሩ ነበር የተጨነቁት እህቴም እንደዛው አላህ ከይር ጀዛቸውን ጀነትን በመሸለም ይክፈልልኝ                                          4 የፈለገ ብናቅድ አላህ ከፃፋት ውጪ የሚሆን ነገር እንደሌለም ገብቶኛል አሁን ምማርበትን ኮሌጅ ስሙን ሁላ ሰምቼ አላውቅም ነበር ቀደር ነው እዛ ያስገባኝ  ብቻ ብዙ ተምሬያለው በጣም ብዙ                                                                አሁን በ IT ከተመረቅኩ ሳምንት ሊሆነኝ ነው አልሀምዱሊላህ      አንድ የስልጥኛ አባባል አለ                                 በሰበሪ አላሃን  ባልገፈሪ                                             ሰበው ታዮኒ ኢለቀሪ                                                  ትርጉሙ   ከታገስን አላህን ካልተውን ሰው ሳንሆን(ሳንለወጥ) አንቀርም    ብቻ ስለሁሉም አልሀምዱሊላህ አልሀምዱሊላህ  አልሀምዱሊላህ🥹🥰 ተማሪዎች በተለይ ቀለሜ የሆኑ ልጆች ውጤት ሳይመጣ ሲቀር ያለው ህመም አውቀዋለው ግን ሁሉም ለኸይር ነው አብሽሩ በይልኝ ብላኛለች እህታችን እንደምትማሩበት ተስፋ አደርጋለው

አሰላሙ አለይኪ  ኢለመንተሪ ውስጥ ነው ያሳለፍኩት አስደሳች እና ማይረሳ እና ትምህርት የቀሰምኩበት ህይወት እና ካፊር ጓደኞች ነበሩኝ ዘፈን አብረን እንስማለን እንጨፍራለን ምናምን ብዙ ብዙ ብቻ ( አላህ ይቅር ይበለኝ🥺🤲 ) እና በዚህ መሀል እነሱ የፍቅር ጓደኛ ይይዛሉ እኔ ደግሞ ወንዶች ላይ በፍቅር ስም መጫወትበጣም እፈልግ ስለነበር የሆነ ሰዓት ላይ የሆነ ክፍል አዲስ ወንድ ተማሪ ትምህርት ቤታችንን ተቀላቀለ ከጓደኛዬ ጋር ሆነን ለምን እሱ ላይ አንጫወትበት ም ብለን አቀድን ከዛም ተጀመረ በድንገት ኮሊደር ላይ ተገጣጠምን እና ስሙን ጠየኩት ራህመቶ አለኝ አይኑ ወላሂ ልገልፅልሽ የማልችለዉ ውበት ነው ያለው ሽፋሽፍቱ ረዥም ነበር በቃ ስታይሉ ሁሉ ነገሩ ምርጥ ነበር በርግጥ እንዳየሁት አልወደድኩትም የሆነች ሴት ትወድሀለች እና በአካል መምጣት ስለ ምትፈራ ይህን ደብዳቤ ልካል ሀለች ብዬ ሰጠሁት ተቀበለኝና ስሟን ጠየቀኝ ማን ብዬ በሰዓቱ እንደነገርኩት ወላሁ አእለም ከዛ እንዲህ እንዲህ እያለ ደብዳቤ ወደሱ እራሴው ፅፌ እራሴው ማመላለስ ጀመርኩ በዚህሁሉ ጊዜ ግን ተይ ያለኝ ጓደኛ አልነበረም ከዛ ምግብ ቤት ቁርስ ሰንበላ አንድ ቀን ኣተኵሬ አየሁት ውብ ሆኖ ታየኝ በቅፅበት ልቤ ውስጥ የሆነ ስሜት ተፈጠረ ከዛን ጊዜ ጀምሮ ፊቱ መቅረብ ፈራሁ የሆነ ቀን ለብቻችን እያወራን ያቺ ያላቹኝ ልጅ አትመጣም እንዴ? አለኝ አው ቀርታለች አልኩት ከዛ በፊት ደግሞ በደብዳቤ ውስጥ ፎቶውን አርጎ ልኮልኝ ነበር እና ያንቺን ይላል አላህ ምን አይነት ወንጀል ውስጥ ነበር ተዘፍቄ የነበረው ከዛ ሙሉ የትምህርት ክፍል ጊዜ ወን የሱን ፎቶ በማየት አሳልፍ ጀመር የሆነ ቀን የኔን ላኩለት ልክ እኔ መሆኔን  ሲያውቅ ትንሽ ሳምንት ቆይቶ ሌላ ምወደው ሰው አለኝ አለኝ ምንም አላልኩትም እሺ ብዬ ብቻ ሄድኩ ከዛ ሚወደው ማንን ቢሆን ጥሩ ነው የራሴን የልቤን የምላትን ጓደኛዬን ያኔም ምንም አላልኩም እሷም ይኸው አንቺን እንዳስከፋሽ አንለቀውም አለችኝ 3 ነበርን እኔም እሺ አልኳት ግን ወላሂ እሱ እንቅፋት እንኳን እንዲጎዳው አልፈልግም ነበር ከዛ እሳም እሺ ብላው አብረው ሆኑ ከዛ እሷና አንዷ ጓደኛችን በየቀኑ ከሱ ብር መቀበል እና መብላት ጀመሩ በጣም ቆዩ ከዛ የሆነ ቀን ሁለተኛ አጠገቤ እንዳደርሺ አላት ያኔ ደስ አለኝ በቃ እሱ አለመጎዳቱ ብቻ ነበር ሚያሳስበኝ ከዛ እስከ መጨረሻዉ ተለያየን ትምህርት ቤት ቀየረ ምናምን ከዛ በፊት ግን ፎቶዬን እንድትቀበለው ጓደኛዬን በተደጋጋሚ ልኬያት የለም ነገ ነገ እያለ ሳይስጠኝ ቀረ እኔ ደግሞ የሱን ወዲያው ቀዳድጄ ጣልኩት እኔ ይህን ሁሉ ያሳለፍኩት የ 7ኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነበርየዛሬ የ አለመንተሪ ተማሪዎች ያሉበትን ሀል ደግሞ አላህ ይወቀው ብቻ ከዚህ የተማርኩት አላህ ሁሌም ባሮቹን እንደሚጠብቅ ነው እና ጓደኛንሳይሆን አላህን ብቻ ይዞ መጓዝ እንዳለብን አሁንከሁሉም ነጻ ሆኜ ከአላህ ጋር ብቻ ነኝ (ALHAMDULILAH,🥺🥺🥺🥺😊😊🤲) ሁሌም አላህ ለኛ ያለው እኛ ለነፍሳችን ካልነው በላጭ ነው

Aselamu aleykum የኔ ገጠመኝ የ 9 ክፍል ተማሪ ነበርኩ እና ጀመአ ነበረን ከዛ ውስጣ ግን 3ታችን የ 4 አመት ጓደኛ ነን በቃ በጣም እንወደዳለን አንድ ቀን አነዷ ጓደኛዬ የሆነ ልጅ እንደሚወደኝ አጣሪልኝ አውሪው ብላ ስልክ ሰጠችኝ እና ማውራት ጀመርን ልጁ ቀስ በቀስ ወደድኩሽ ምናምን ጀመረ እኔም ማውራቴን አቆምኩ ነገር ግን ሰፈር ድረስ እየመጣ መውጣት ከበደኝ ረመዳን ሲደርስ ጭራሽ እኔን መስጊድ አስገብቶ ሰውጣ ሸኝቶኝ መሄድ ጀመረ ብነግረው እምቢ አለ ፍቅረኛ ሁሉ አለኝ ስለው እምቢ አለ ሁሉንም ነገርኳት ከዛ አንድ ቀን ደአዋ ፕሮግራም አለ ነገ እንሂድ አለችኝ ቤት ለምኜ እሺ ተባልኩ ጠዋት ሲነጋ ኡሚ አትሄጂም ውስጤ ተረብሿል  ብላ ከለከለችኝ ወላሂ በጣም ነው ያለቀስኩት በቃ ምን ልበልሽ ቀኑን ሙሉ አኩርፌ ምግብ አልበላም ብየ ዋልኩኝ ከዛ ወደ 12 አከባቢ ስልክ ተደውሎ ልጁ አስይዞብኝ እነደነበር እና እምቢ ስላሽው ጎበዝ ነሽ አህት አለኝ ለዛ ነው ጓደኛሽም አትሆንሽም አለኝ ተናድጄ ሰድቤ ዘጋሁበት አብሮን የሚማር ልጅም ፑል እየተጫወቱ እንዴት አብረሽው እንደምትሆኚ እና ጓደኛሽም እኔ አመጣታለሁ አለች ብሎ ነገረኝ ግን አላመንኩም ሌላኛዋ ጓደኛዬም እስኪ አስቢ ሁሌ አብረን ነበር የምንሄደው በ አሁን ግን ላንቺ ብቻ ነገረችሽ ለምን ብለሽ እራስሽን ጠይቂ አለች ግን በቃ እምቢ ብየ ሳለሁ ወላሂ ልጁ እራሱ ከ እኔን ፍቅር ለማስያዝ አብሮኝ አድሮ ቀርፆ ለማሳየት እንዳስያዘ ግን እንዳልተሳከለት የዛን ቀን ጓደኛዬ እንዳመቻቸችለት ግን እኔ እምቢ እንዳልኩ ነገረኝ ከዛ ተፀፅቶ ሊያገበኝ እንደሚፈልግ ነገረኝ እኔም ይቅርታውን ብቻ ተቀበልኩ ደግሞ እናቱን ጋር መቶም ይቅርታ ጠየቀኝ እኔም እሺ ግን አጠገቤ እናዳትደርስ አልኩት በ እናቱ ብዙ አስለመነኝ ግን በቃ ሰው ማመን ስለከበደኝ እምቢ አልኩ ስልክ ቁጥር ቀየርኩ እህታችን ይህን አስተላልፋልናለች እንደምትማሩበት ተስፋ አደርጋለው

Aselamualeykum werahmetulahi weberekatuh ene yemmekrew neger specially ahun gibi lemigebu lijoch new welcome freshoch eske 12 stmaru bzu negerochn asalfachu metachual gibi lay demo hlmachun ewn lemareg allah entrancen asalfuachual ene yazare amet gibi sgeba medicine miyastemru arif gibiwoch eneman nachew bye keziyan selamawi hunetaw le dines bye merche neber yegebahut enam keljnet jemro malmew medicine new so esun emaralehu bye unfortunately gibi kegebahu buhala le coc mihon GPA alhonem am so depressed mknyatun plan B or C mibal neger slelelegn mekeyer echl yimesl bzu lelitochn  anebahu familiy techenkew beyeseatu yidewlalu bcha betam fertewlgn neber enem really happen yaregew endeza new endima ayhonm el neber edlegna hugne remedan wer lay neber ena tolo wede allah temelshe yanten mrcha akebralehu alku ahun lay ye allahn wusane new mtebqew kene mitebeqbgnn adergalehu keza left to allah So ene yemlachu plane A bcha ayhin B C yasfelgal endihum andande yebetesebnm hasab makber ene gubiyen berase will new yemeretkut berase requirement meseret familiy yemeretelgn gibi bihon definetly medicine egeba neber gn lekheyr new ena mkr tekebelu seniors teyku sle mtgebubet gibi full information yinurachu elalehu Shukren እህታችን ይህን አስተላልፋልናለች እንደምትማሩበት ተስፋ አደርጋለው

ሰላም አለይኩም አህባብ እንዴት ናችሁ የሆነ ሀሳብ ብልጭ አለብኝ እና ላጋራችሁ ብዬ ነው። ሀሳቡ ምን መሰላችሁ ቻናሉ ላይ ብዙ አይነት ሰው ነው ያለው እና ሁላችንም ደሞ የተለያየ የህይወት አጋጣሚ አለን እና ሰውን ያስተምራል ብላቹ ምታስቡት እናንተንም ካለፈ በኃላ ያስተማራቹን አጋጣሚ ካለ @mamaye_31 ላኩልኝ እኔም አንዳንድ necessary information change አድርጌ እፖስታለው ።አሁን ላይ ያላችሁበትን እና የሰው ሀሳብና ምክርን መቀበል ከፈለጋችሁም ይቻላል።

. ታሪኩ አልገባንም ታሪኩ ደስ አይልም ገና ከታሪኩ እኮ መንደርደሪያውን ነው ያነበባችሁት እንዴት ነው ሊገባችሁ የሚችለው እኔ ራሱ አልገባችሁኝም ደስ ካላላችሁ እዚህ ጋር ይቁም

«ማንም የለም እቤት Âť «አይ ፕሮፌሰር አሉ ክፍላቸው ናቸው Âť ፕሮፌሰር ያለችው እናቴን ነው ከእኔ ውጪ ሁሉም ሰው ፕሮፌሰር እያለ ነው የሚጠራት ÂŤ የስ ክፍላቸው ናቸው Âť ቦርሳዋን ሶፋ ላይ ጥላ እየሮጠች ሄደች በቃ አጋና አጋግላ ልትናገር ነው አንቺው ታመጪው አንቺው ታሮጪው ሆነ ነገሩ ወደ ክፍሌ ገባሁ ልብስ ቀያይሬ ወደ ማማ ክፍል ሄድኩኝ ÂŤ እሺ ተናገርሽ Âť «አዎ ተናገርኩኝ Âť ÂŤ ማማ ስታካብድ ነው እንጂ የከፋ ነገር የለውም እኮ» ÂŤ እንዴት የለውም ልጃ የምር በጣም አፍርርብሀለው» «የምን ማፈር ነው ልትኮሪብኝ ነው እንጂ የሚገባው እራሴን አስከበርኩኝ እንጂ» «ምኑ ነው ራስን ማስከበር ተዋረድክ እንጂ ሰው እንዴት የራሱን ስም ትርጓሜ አያውቅም» ዞር ብዬ አየዋት እጇን አፏ ላይ አድርጋ  ትስቃለች ÂŤ የምን ስም ነው እናቴ Âť «አስተማሪው የስምህን ትርጉም ሲጠይቅ እንደማታውቀው  ተናገርክ ከዚህ ላይ መዋረድ አለ እንዴ Âť ሾለ ፀቡ እንዳልተናገረች ገባኝ ÂŤ እና ምድር ላይ የሌለ ስም አውጥታችሁልኝ ስሜን ስናገር ሰው ሁሉ ይገረማል» ከተቀመጠችበት ተነስታ መጣች ወደ እኔ እጄን ይዛኝ ከክፍሉ ወጣን ÂŤ የስምህን ትርጉም በደንብ እነግርሀለው አሁን ግን  እርቦኛል ለ ለይላ የምትወደውን ምግብ እንድታዘጋጅ ነግሪያት ነበረ እስካሁን ትጨርሳለች» እጄን እንደያዘችኝ መመገቢያው ቦታ  ላይ ተቀመጥን //////// ግቢ ውስጥ እንደገባው ተንደርድራ መታ ተጠመጠመችብኝ ÂŤ ኧረ አነቅሽኝ Âť በአንገቴ ዙሪያ የጠመጠመችውን እጇን ለቀቅ አደረገችው እና ጉንጬን ሳመችኝ ÂŤ በቃ እንደዚህ ነው የምናፍቅሽ» ÂŤ አዎ ከዚህም የበለጠ ነው እንጂ» እንዳቀፍኳት ወደ ቤት ገባን ÂŤ ማዚን መጣህ በአንድ እግሬ አቁማኝ ነበረ ከእንቅልፏ ስትነሳ የለህም 9:00 ሰአት አልፈ እኮ ወንድሜስ አይመጣም እንዴ ? መስጅድ ነው ብላት መስሚያዋ ጥጥ ሆነ Âť እናቴ ኪችን ቁማ አቤቱታዋን ታቀርብልኛለች ÂŤ እውነት እንደዚህ አስቸግረሻል እንዴ» በእጄ ጉንጯን ቆንጠጥ አድርጌ ሳምኳት «በትንሹ ፊትህን ምን ሁነህ ነው Âť በትንንሽ እጆቿ እየደባበሰች ÂŤ ምንም ቀላል ነገር ነው አሁን አንቺም ወደ መድረሳ በጣም ረፍዷል እንደውም  እኔም ብዙ የምሰራው ነገር አለብኝ»ብዬ ከእቅፌ አወረድኳት «ኡሚ የማግዝሽ ነገር  ከሌለ ልሄድ ነው Âť ÂŤ የለም ልጄ ወደ ጥናትህ መሄድ ትችላለህ የእሷን ልጅ ጭቅጭቅ ካስቆምክልኝም አንድ ነገር ነው »ወደ ክፍሌ ሄድኩኝ በፕሮግራሜ መሰረት online አንዳንድ ነገራቶች መመልከት ጀመርኩኝ /////// ጭንቅላቴ ውስጥ ብዙ ነገራቶች እያተመላለሱ ነው ከሰአታት በፊት በቃሲዮን ክፍል ውስጥ በ pc ላይ ያየውት የሚያስጠላ ነገር ውስጤን እየበላኝ ነው ቀለል ያለ ልብስ ለብሼ ወደ ጓሮ ዞርኩኝ እናቴ ሁሌ በዚህ ሰአት ከእኔ እኩል የምትወዳቸውን እፅዋቶቿን ውሀ ታጠጣለች ትኮተኩታለች በቃ እረፍት የላትም እቤት ከሆነች  ትንሽ የሚባሉ አይደለም ግቢዪችን ውስጥ ብዙ የአበባ አይነቶች አፕል ማንጎ ብርቱካን ብዙ ብዙ ስማቸውን የማላውቃቸው እፅዋት ግቢ ውስጥ አሉ ሁሉም በእድሜ ይበልጡኛል ለእፅዋት የተለየ ፍቅር አላት ልክ እናት ሾለ ልጆቿ ባህሪ እንደምታውቀው እንደምትጨነቀው ከልጆቿ ቀጣይ የጊቢው እፅዋቶች ትልቅ ቦታ አላቸው እሷ ጋር አትክልተኛ እራሱ አምና አታስነካቸውም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በእሷ እጅ ናቸው እኔንም አታምነኝም አይደለም ሌላ ባአድ ሰው ይቅርና ÂŤ ያ ኡሚ አሰላም አለይኩም Âť ካጎነበሰችበት ቀና አለች ÂŤ ዋለይኩም አስላም የኔ አበባ መጣሽ» ÂŤ አዎ ብዙም አልቆየውም ሳጣሽ እቤት ወደ ጓሮ ዞርኩኝ ፕሮፌሰር ጋር ነበርኩኝ» ÂŤ እንደው ከተዘያየርን ቆየን እኮ በአላህ ደህና ናቸው  ወጣቱስ እንዴት ነው Âť ÂŤ አልሀምዱሊላህ ደህና ናቸው ለምን እራት አንጋብዛቸውም ግንኙነታችሁ እየላላ ነው እኮ Âť ÂŤ ልክ ብለሻል ውዴ እኔም እያሰብኩት ነበረ ነገ በደንብ እንዘጋጅ እና እንጠራቸዋለን አሁን መግሪብም እየደረሰ ስለሆነ ወደ ቤት እንግባ Âť የለበሰችውን የእጅ ጓንት አውልቃ እዛው አቀመጠችው ጭንቅላቷ ላይ ያለውን ከሰሌን የተሰራ ባርኔጣውን ከጭንቅላቷ ላይ አንስታ በእጇ ያዘችው እና ተያይዘን ወደ እቤት ገባን /////// ወደ ታች ልወርድ ነበረ እቅዴ ከአባቴ ክፍል የሰማሁት ቃላት ግን እርምጃዬን ገታኝ ወደ ክፍሉ ጠጋ አልኩኝ «አትጨቃጨቂኝ እስኪ ገና ከመግባቴ ይሄ መርዝ ንግግርሽ አስጠልቶኝ ነበረ ውጪ የማመሸው» የአባቴ ድምፅ ነው አባቴ እና እናቴ ለውጪ ላያቸው የተሳካላቸው ምርጥ ባለ ትዳሮች ውስጥ ውስጠን ግን እኔ ነኝ የማውቀው እኔ እንደማውቅ እነሱም አያውቁም ባባ ከእኛ ጋር አንድ ላይ እራት የበላበትን ቀን በደንብ አላስታውስም ወይ አምሽቶ ይመጣል ወይ እዛው ያድራል እቤት ካደረም ሳሎን ወይ የእንግዳ ማረፊያው ውስጥ ነው አንድ ቀንም አባቴ ከእናቴ ጋር አንድ ክፍል ሲያድር አይቼው አላውቅም ቆይ ባል እና ሚስት የተለያየ ክፍል ማደር አለባቸው   ለእኔ በጣም ምርጥ አባት ነው ለእናቴ ግን ጥሩ ባል አይመስለኝም ማማም እንደዛው ለእኔ ምርጥ እናት ነች ለእሱ ጥሩ ሚስት የሆነች አይመስለኝም ለአመታት እንቆቅልሽ የሆነብኝ ነገር ይቀጥላል.    .    . @rim_han .

 .                 ╔═══ ೋ 𔘓 ೋ  ═══╗                               ኦርቶዶክሳዊቷ                          á‹°áˆŤáˆ˛  አፍናን ሩማን Âť                   ╚═══ ೋ 𔘓 ೋ ═══╝ .                       ━─━─  𓍯  ─━─━                              ραɾƚ    0:02                         ━─━─  𓍯  ━─━─ «ኧረ እሷ እህቴ ነች» አልኩኝ ቀደም ብዬ «ገባኝ አሁን እህትህን እሱ ጋር ስታያት መታኸው ድሮም ከዚህ ውጪ ምን የሚያጣላ ነገር አላችሁ የዘመኑ ልጆች ውሀ ቀጠነ ብላችሁ ከአገኛችሁት ጋር ግብ ግብ አሁን ስማቹሁን ተናገሩ» «ኧረ እንደሱ አይደለም» «ዝም በል ደሞ መልስ ይመልሳል እንዴ» ትልልቅ አይኖቹ ተጎልጉለው የሚወጡ ነው የሚመስሉት አጉረጠረጠብኝ ዝም አልኩኝ ÂŤ አንተ ማነው ስምህ» «ማዚን Âť ቀና ብሎው አየው« ማዘን ጭራሽ አንተ ነህ ትምህርት ቤቱ አለን ከምንላቸው ኮከብ ተማሪዎች ግንባር ቀደሙ ለሌሎች ተማሪዎች ሞዴል የምትሆን ልጅ አሁን በሴት ተጣልተህ ቢሮ ተቀምጠኻል» «በቅድሚያ ስሜ ማዘን ሳይሆን ማዚን ነው ሲቀጥል እኔ በሴት አልተጣላውም ልጣላም አልችልም ድንገት ከፎቅ ስወርድ ተጋጨን ይቅርታ ስለው ሰነዘረ Âť አስተያየቱ ትቢት እና ንቀት የተሞላበት ነው በጎሪጥ ወደ እኔ ይመለከታል «ያው ነው ዋናው መጣላትህ እና ቢሮ መግባትህ ነው ይሄ ደሞ ከእንደ አንተ አይነት ተማሪ የማልጠብቀው ስርአት አልበኝነት ነው  እሺ አንተኛውስ ስምህ ማነው ደሞ እንደ ጥሩ ሾል ፀጉሩን ያፍተለትላል እንዴ  ፀጉርህ ምንድነው ሹርባ ልትሰራው ሲቀጥል እንዴት ልትገባ ቻልክ እንዲ ጭንቅላትህ ላይ ከምረኸው» እጄን ከፀጉሬ ላይ አነሳው ተስተካክዬ ተቀመጥኩኝ ÂŤ ስሜ ቃሲዮን ነው ደረጃውን እየወጣሁ ሳለ ዘሎ ወጣብኝ ይሄ ደሞ አግባብ አይደለም አይን አለው አይደል እያየ መሄድ አለበት መቼሽ አይኑን ለመራመጃነት አይጠቀምበትም» «እሱን አንተ አትነግረኝም Âť «ካላወቅ ምንም ማድረግ አልችልም» «ጉድ እኮ ነው እዚህም ልትጣሉ ነው እንዴ ስነ ስርአት ይኑራችሁ እንጂ አንተኛው ስምህን ማን አልከኝ Âť ንፁህ 4A ወረቀት አንስቶ የሆነ ነገር ፃፍ ፃፍ አደረገ ÂŤ ቃሲዮን Âť ደገምኩለት የፈረደበት እጄን ፀጉሬ ላይ አድርጌ እየጠቀለልኩ «ስምህ እራሱ ግራ የገባው ነው እሺ ቃሲም እና ማዘን ባሁኑ እንዲሁ በማስፈረም አልፋችዃለሁ» «ይቅርታ ዳይሬክተር ለሁለተኛ ጊዜ ልንገርህ ስሜ ማዘን ሳይሆን ማዚን ነው Âť እኔ ሳቄ አመለጠኝ ከወረቀቱ ላይ አይኖቹን ነቅሎ አፈራርቆ ተመለከተን «ምን ያስቅሀል አንተ ከሰው ስህተት ከብረት ዝገት አይጠፋም ፀጉርህን መተብተብህን ትተህ ፈርም» ብሎ ወረቀቱን ወደ እኔ አስጠጋው በስሜ ልክ ፈረምኩኝ ስሜ አልኩት እንጂ  ቃሲም ነው የሚለው ወረቀቱ ላይ ይሄ ሰውዬ አሁን በየትኛው እውቀት ነው እዚህ ቦታ የተቀመጠው ስም እንኳን በስነ ስርአት መስማት የማይችል ሰው ወረቀቱን ወደ ማዚን አስጠጋውት እሱም በተመሳሳይ ፈረመ እና አቀበለው «ከዚህ ቡሀላ በእንደዚህ አይነት ጉዳይ እዚህ ቢሮ እግራቹህ ቢረግጥ እኔን አያድርገኝ እናንተ አሁን ቤተሰብ አታስተዳድሩም እንዴ ከተማ ሁናችሁ ነው እንጂ ገጠር ብትሆኑ የአንድ ልጅ አባት ነበራችሁ ለማንኛው ዳይ ወደ ክላስ» ምንም ምላሽ ሳንሰጥ ተከታትለን ከቢሮ ወጣን በራሱ አለም የሚኖር ሰውዬ እራሱ ይጠይቃል እራሱ ይመልሳል  በር ላይ ቁማለች ÂŤ አትኮሳተሪ በጣም እንጂ ማማ እራሱ ብትሰማ እንዳንቺ አትሆንም እኮ» ÂŤ ደሞ አፍ አለኝ ብለህ ታወራለህ እኔ ክፍል ውስጥ ቁጭ ብዬ ፀብ ፀብ እያሉ ሲሮጡ እንዴት በርሬ እንደማጣሁ ይኸው እንደፈራሁት የእኔው ጉድ ነህ» «እና ሲገፈትረኝ ምን ላድርገው ችላ ብዬ ማለፍ ነበረብኝ እንዴ ወንድ ነኝ ያው የሚገባውን ሰጠውት» ÂŤ ተው ባክህ ወንድ ሁነህ ሙተኻል ወንድ መሆን መደባደብ መሰለህ እንዴ» «ውይ አንቺ ጭቅጭቅ ትወጂያለሽ» ቀደም ብያት ተራመድኩኝ እና ወደ ክፍል ገባሁ ከዃላ ወንበር ተቀመጥኩኝ ከደቂቃዎች ቡሀላ እሷም ወደ ክፍሏ ገባች እና እየተገላመጠች ልበለው እንጂ ግልምጫስ አይመስልም ቦታዋ ላይ ተቀመጠች የማወራው የማውቀው ጓደኛ ስለሌለኝ ዝም ብዬ ክፍሉ ውስጥ አይኖቼን አንከራትታለሁ የክፍሉ በር ተከፈተ እና ወደ ውስጥ ገባ እንዴ እዚሁ ነህ እንዴ አልኩኝ በውስጤ ከቅድሙ ባልተናነሰ አስተያየት አይቶኝ ከእኔ ተቃራኒ አቅጣጫ ላይ ተቀመጠ ፈገግ አልኩኝ  ጥጌን ይዜ ተቀመጥኩኝ እንዲሁ እያዛገ ሰአቱ እንደ ምንም ሄደ እነ ኤልዮን ወደ  እኔ ወዳለኹበት ክፍል ካልመጡ ወይ እኔ ካልሄድኩ ክፍሉ ጭራሽ አይገፋም እንዲሁም ደቂቃ ስቆጥር ዋልኩ እንደምንም ወደ ብት መሄጃ ሰአት ደረሰ «እሺ ተነስ እንሂድ» አሁንም ቁጣዋ አለቀቃትም ሰው ተናዶ እንደ እሷ ያስቃል መናደድ መገላመጥ የሚባሉ ነገራትን አትችልበትም «እሺ አትቆጪ ትንሽ ደቂቃ እነ ኤልዮን ይመጣሉ» «አይመለከተኝም ሾለ እነሱ የምትሄድ ከሆነ እንሂድ» መልሴን ሳትሰማ ከክፍሉ ወጣች ብሽቅ እያሉ እኔም ተከተልኳት ደስ የሚለው እነ ኤልዮንም በር ላይ አገኘዃቸው እስከ ትምህርት ቤቱ መውጫ እያዛግን ደረስን ከዛ ቡሀላ ተሰነባብተን እነሱ በሌላ አቅጣጫ እኔም በመንገዴ እሷ ላይ ለመድረስ በሶም ሶማ እሮጥኩኝ ÂŤ ልትበሪ ነው እንዴ ወይስ ተደባደበ ብለሽ ለማቃጠር ነው ይሄ ሁሉ ፍጥነት» «የት ነው ሳቃጥር ያየኸኝ ደሞ እኔ ሳላወራ በፊት ይሄ ፊትህ ይናገራል መቼም እንደዚህ በልዘህ  ቡጡ እንደቀመስክ ማወቅ ይቻላል» «ወላሂ በይ ይሄን ያህል ፊቴ ያስታውቃል እንዴ» በእጄ ደበስኩት ህመም አለው እስካሁን አልታወቀኝም ነበረ «ቀላል እንደውም አሁን ፀሀይ ላይ ስለሆንን ነው መሰለኝ በደንብ ታየኸኝ እንደዚህ በጣም መቶኻል እንዴ Âť «ማካበድ ትወጃለሽ የእሱን ፊት አላየሽውም እንዴ እንዴት እንደሆነ» «ሲጀመር ዛሬ እንዴት ክላስ ገባህ ሰው የመጀመሪያ ቀን እንጂ የመጨረሻ ቀን ክላስ ሲገባ አላውቅም» «እነ ኤልዮን ጨቅጭቀውኝ ነው ዛሬ የገባውት እንጂ ምንም ሙዴ አይደለም  በዛላይ በጠዋቱ ሼባው ለከፈኝ ከዛ ልጁ ብቻ ይደብራል Âť «ለምን ከእነዚህ ልጆች አትርቅም እኔ ምንም ደስ አይሉኝ ሼባው ያልከው ፕሮፔሰሩን ብቻ እንዳይሆን አንተ የተከበረ ሰው ነው ሲቀጥል የስምህን ትርጉም ነው የጠየቀህ ያው አታውቀውም እንጂ» «ቀርበሽ ብታያቸው የሚገርሙ ልጆች ናቸው  ምን ይመለከተኛል እና  እኔ ፕሮፌሰር ይሁን ዶክተር ደሞ ሼባ ነው ሲቀጥል የእኔ ስም ትርጉም ምን ያደርግለታል» «ወሬ አለብህ አንተ አሁን አሱር እንዳያልፈን ቶሎ ቶሎ ተራመድ» «አዎ አንቺ ማታ ያላየውት ጨዋታ ነበረ አሁን አየዋለ» ብዙም የሚባል እርቀት የለውም እንዲሁ እያወራን እቤት ደረስን ከእኛ ቤት 3 ወይም አራት ቤቶች ቀጥሎ የእሷ ቤት ይገኛል ÂŤ ነይ ግቢ ማማንም ታገኛታለሽ በዛው ምነው ጠፋች እያለች ነበረ» «ልብስ ቀይሬ ሰግጄ መቅሰስ በልቼ እመጣለሁ» «ማማ ብትሰማሽ ትታዘብሻለች  አሁን ነይ ግቢ ቶሎ በይ »እቤት መግባቷ ያን ያህል አሳስቦኝ ሳይሆን ማማ ፊቴን አይታ እንዳትናደድ እንዳትቆጣ አስቤ ነው ደስ ከሚለኝ ባህሪዋ ሰው ፊት የፈለገ ላጥፋ ኮስተር እራሱ አትልም« እሺ እሺ በቃ Âť ከዃላ ተከተለችኝ እና ወደ ውስጥ ገባን ሳሎን ውስጥ ማንም የለም ÂŤ ለይላ Âť ከመጣራቴ ቀልጠፍ ብላ ወጣች የቤታችን ሰራተኛ ነች እኔ ነፍስ ሳውቅም እዚህ ቤት ነበረች አሁንም አለች  ስገምት ሳልወለድም በፊት እዚህ ቤት ነበረች መሰለኝ

. ክፍል -2 18 min left...... አላችሁ ? .

«እንዴ ሶስተኛ ስም»የቃላት አጠቃቀም ቅላፄዋ ክፍሉ ውስጥ የነበሩትን ተማሪዎች አሳቃቸው «ምን ችግር አለው እኔስ ብሆን የቀለም አባትሽ አይደለሁ እንዴ »ፈገግ አለች አሁንም አይኖቹን ወደ ሌላ ተማሪ አነጣጠረ ÂŤ እሺ ጎረምሳው አንተንስ ማን ልበል» ተኮሳትሮ እና ጅንን ብሎ የተቀመጠው ልጅ ቀና ብሎ ፊት ለፊቱ በቅርብ ርቀት የቆመውን አስተማሪውን ተመለከተው «እኔ ማዚን ጀውደት እባላለሁ Âť አለ እና እንደ ቀድሞ አንገቱን ደፍ  «እስካሁን የሰማዃቸው ስሞች ለየት ያለ ቅላፄ ትርጉሙስ Âť «ማዚን ማለት የበረካ እና የህይወት ምልክት ነው ጀውደት የአባቴ ስም ነው  ደግነት ፋፁምነት እንደማለት Âť «ደስ የሚል ስም እና ትርጉም አንድ ተጨማሪ ሰው ልተዋወቅ እና የዛሬው ፕሮግራማችን በዚሁ ይጠናቀቃል  እዛ ጋር  ነጭ ሂጃብ ያደረግሽው ብርቱካን የምትመስይው ልጅ ልተዋወቅሽ Âť ተማሪዎቹ በድጋሜ ክፍሉን በሳቅ አወኩት ፊታቸውን ወደተባለችው ልጅ አዞሩ አይኖቿ ጥቁር ከናፍርቷ ልክ ብሉኝ ብሉኝ እያለ እንደሚጣራ ዛፍ ላይ እንደተንጠለጠለ ኢንጆሪ የሚያስጎመዥ የፊቷ ቅላት ማንም አይቶ ኢትዮጵያዊ ነሽ ብሎ ሊያስጠይቅ የሚችል መልክ አይኖቿን ካዘቀዘቀችበት ቀና አድርጋ ÂŤ እኔ ሮዛሊን እባላለሁ Âť አለች ከቀይነት አልፈው ቢጫ የሚመስሉ አለንጋ ጣቶቿን በፍርሀት እያፍተለተለች ÂŤ መልክሽም ልክ እንደስምሽ ነው ተሳሳትኩ» አላት ፈገግ ብሎ ተደናገጠች ቀይ ፊቷ በአንዴ ቲማቲም መሰለ ÂŤ ሮዛሊን ብዙውን ጊዜ የሻም ህዝቦች የሚጠቀሙት ስም ነው እያበበች ያለች ውብ ፅጌሬዳ ማለት ነው ከተሳሳትኩ አርሚኝ ቤተሰቦችሽ ኢትዮጵያዊ አይደሉም እንዴ ?Âť የስሟን ትርጓሜ ከአስተማሪዋ በመስማቷ ተደንቃለች «አልተሳሳትክም ትርጉሙ እንደዛ ነው እናቴ ኢትዮጵያዊት አይደለችም» «አንቺም ወደ እናትሽ አዘንብለሻል ምንም ኢትዮጵያዊ አትመስይም ለማንኛውም ሁላችሁንም አመሰግናለሁ ሌሎቻችሁን ደሞ በቀሩን ቀናት በደንብ እንተዋወቃለን» አለ እና ይዞት የመጣውን ንብረቶች ካስቀመጠበት ብድግ አደረገ ÂŤ ቲቸር Âť ከጥግ ላይ ጥሪ ሰማ እና ቀና ብሎ የተጣራው ሰው ላይ  አይኖቹ ከመነፀሩ አልፈው አንዣበቡ ÂŤ10 ደቂቃ ይቀረናል እና እኛስ የአንተን ስም ማወቅ አንችልም Âť ፈገግ አለ እና የያዘውን መፀሀፍ ጠረንጴዛው ላይ አስቀመጠው ከኪሱ ሰማያዊ ፓርከር አውጥቶ ንፁህ  ቦርድ ላይ ÂŤ ፕሮፌሰር ያዶት አውሳፍ Âť ብሎ ፃፈ ÂŤ ትርጉሙም Âť አለችው የስሙ ጠያቂ« ብድር መሆኑ ነው ያዶት በደቡብ ኦሮሚያ ባሌ ዞን የምትገኝ ደሎ ከተማ ውስጥ የሚገኝ እና ከተማዋን ለሁለት የሚከፍላት  ግዙፍ ወንዝ ነው ። ለዶሎ ነዋሪዎች ያዶት ትልቅ ጥቅም እና ትርጉም ያለው ወንዝ ነው እኔም እዛው አከባቢ ተወልጄ ስላደኩኝ ነው ይሄ ስም የወጣልኝ አውሳፍ የአባቴ ስም ነው መልካም ባህሪያት  ማለት ነው ወደ ፊት እኔም ከእናንተ እናንተ ከእኔ ትምህርት ብቻ ሳይሆን የህይወት ልምድም ትቀስማላችሁ የእናንተን እድሜ 3 እጥፍ ምድር ላይ ኑሪያለሁ ከትምህርቱ እኩልህ የህይወት ልምዴንም ሟር አደርጋችዃለሁ  መልካም ውሎ ይሁንላችሁ »ፈገግ አለ ያስቀመጠውን መፀሀፍ አንስቶ ክፍሉን ለቆ ወጣ ሁሉም ተማሪዎች በአዲሱ አስተማሪያቸው ተገርመዋል አንዳንዶቹ ወደውታል ገና በመጀመሪያ ቀን //////// ሙዴ አልነበረም ክላስ መግባት በኤልዮን ጭቅጭቅ ነው ዛሬም የገባሁት በግራ እጄ ፀጉሬን እየጠቀለልኩኝ ክፍሉን ዙሪያውን ቃኘውት ተማሪዎች አልመጡ ይሆን ወይ እንደዚሁ ይሆን ክፍሉ ውስጥ ከወንድ ሴት ይበዛል ከጥግ እስከ ጥግ በአይኔ ቃኘው የሚደብር መልክ ያለው የለም ሁሉም ቆነጃጂት ናቸው በዛ ላይ አንዳንድ ሴቶች አይኖቻቸውን ያቅበዘብዣሉ  ኮስተር እንዳልኩኝ በዝምታ ተቀመጥኩኝ የክፍላችን በር በቀስታ ተከፈተ አይኖቼን ወደ በሩ ላኩት የእኔው ሰው ነው ከተቀመጥኩበት ቦታ ብድግ ብዬ ወደ በሩ ሄድኩኝ «እዚሁ ትሆናለህ ወይስ እንውረድ» «ኧረ ይደብራል እዚህ እንውረድ»ተከታትለን ወደ ታች ወረድን ግቢው ጭር ያለ ነው በጀርባ በኩል ዞርን ሁለት ተጨማሪ ሰዎች ቁመዋል አንዱ የኤልዮን መንታ ወንድም ነው አንዱን ግን አላውቀውም ሰላም ተባባልን ÂŤ ቃሲዮን እንደምታየው ትምሯችን ይሄን ይመስላል አንድ ሁለት ቀን ነው ትላመጅዋለሽ እኛም አለን አብሽር እሺ Âť ፈገግ አልኩለት 7 ክፍል ጀምሮ አብረን ነው የተማር ነው በቃ ተለያይተን አናውቅም ምርጥ ጓደኛሞች ነን ከአመት በፊት ሰፈር ቀየሩ በዛውም ትምሮ ቀየሩ አሁን ያለንበት ትምህርት ቤት ተነስተን እነሱ ቤት ለመድረስ 15 ደቂቃ ያላነሰ ይፈጃል ቅርብ እዚህ እያለ የድሮ ትምህርት ቤት አይሆንም ተብለው ለአንድ አመት ተለያየ ለእኔ የድሮም የአሁንም ትምህርት ቤት ለእኔ እኩል እርቀት ነው ያላቸው ያለን አማራጭ እኔ እዚህ መግባት ነው አደረኩት  ያው የተለያየ ክፍል ቢደርሰንም ÂŤ ኤልዮን  በቃ እኔ ወደ ክላስ ልመለስ Âť «ምነው ደበረሽ እንዴ Âť «ሳይሆን ሙዴ ጥሩ አይደለም» «ሂድ በቃ እሺ አየሩም ደስ አይልም» ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ወደ ህንፃው ሄድኩኝ በግራ ብሎክ ደረጃውን ስወጣ አንድ ደንባራ እየተክለፈለፈ መቶ ተጋጨኝ «ያምሀል እያየህ አትሄድም» ÂŤ ይቅርታ ስላላየውህ ነው አታካብደው»ከይቅርታው በላይ ፊቱ ላይ የሚነበው ንቀት ይበልጥ አናደደኝ ቀኝ እጄን ሰነዘርኩበት ሌባ ጣቴ ላይ የነበረው ቀለበት ቀጥታ አፍንጫው አገኘው ተንገዳግዶ ቆመ ከመቅፅበት ባላሰብኩት ሁኔታ ጉንጬ ላይ አንድ ቡጢ አረፈ ÂŤ እናንተ አቁሙ እናንተ Âť እየጮኸ እና እየሮጠ ወደ እኛ መጣ እና ገላገለን በፈርጣማ እጁ ሁለታችንንም ይዞን ሄደ ይመስለኛል ወደ ቢሮ ነው  አንድ በር ከፍቶ ወደ ውስጥ አስገባን ግዙፍ ክፍል ነው በግራ መደርደሪያው ላይ  ብዙ ፋይሎች አሉ ፎቶዎች አሉ እንዲሁም ሽልማቶች  ትልቅ ጠረንጴዛ እና መቀመጫዎች ከጠረንጴዛፍ አሻጋሪ ተሽኸርካሪ ወንበር ላይ አንድ ድቡልቡል ሰው ተቀምጧል ፊቱ ክብ ነው አንገቱ ቦርጭ የመሰለ ስጋው ተደራርቦ መሾመር ሰርቶ ደረጃ ይመስላል ከግንባሩ እስከ ግማሽ የአናቱ ክፍል ፀጉሩ የለም ከዃላ አለ በከፊል ልሰ በረሀ ነው የሚባለው« ምን አጥፍተው ነው Âť ድምፁን ስሰማ ሳቄ ሊያመልጠኝ ነበረ የጎረነነ የሚያስፈራ ድምፅ ስጠብቅ ከአይጥ ድምፅ ያልተናነሰ ቀጭን ድምፅ ሰማው«ኮሊደሩ ላይ ሲደባደቡ አጊንቻቸው ነው» «ገና መጀመሪያ ቀን ለዛው 4:00 ሰአታት ትምህትር ላይ ሳታሳልፉ ምን ለፀብ የሚጋብዝ ነገር ገጠማችሁ ቁጭ በሉ Âť ድምፁ በደቂቃ ወደ አስገምጊሚ የአንበሳ ድምፅ ተቀየረ ብል ማጋነን አይሆንም ሁለታችንም ተቀመጥን ÂŤ ምንድነው ያጣላችሁ ሴት ?Âť ሁለታችንም ዝም አልን ÂŤ እሷ ነች ያጣላቻችሁ Âť አለን ወደ በሩ እየጠቆመ ሁለታችንም ወደ በሩ ዞርን አንብባችሁ ስትጨርሱ ላይክ ማድረግ አትርሱ ! ይቀጥላል .   .   . @rim_han .

 .               ╔═══ ೋ 𔘓 ೋ  ═══╗                               ኦርቶዶክሳዊቷ                          á‹°áˆŤáˆ˛  አፍናን ሩማን Âť                   ╚═══ ೋ 𔘓 ೋ ═══╝ .                       ━─━─  𓍯  ─━─━                              ραɾƚ    0:01                         ━─━─  𓍯  ━─━─ የራሴ የጋለ ትንፋሽ የተሰነጣጠቁትን ከንፈሮቼን አልፎ ሲወጣ ይሰማኛል አይኖቼ ድክምክም ብለው በብዥታ በከፊል የተገፈፈው ጨለማ ይታየኛል እግሬ ግን ከመራመድ አልባዘነም በጣም ደክሞኛል በጣም ፈጣሪ ግን ያዳላል በህይወት መኖር የፈለገውን ወስዶ መሞት የፈለገውን እንደ እኔ ሲባዝን እንዲኖር ይፈቅድለታል ከዛም በላይ እንዲሞት አይፈቅድም መኖሬ ካልጠቀመ ለምን እንድሞት አትፈቅድልኝም ፈጣሪዬ ነገሩ ፈጣሪ ከተጠየፈኝ ቆይቷል እረስቶኛል ብቻዬን ፈገግ አልኩኝ ግን ቁስል አለው ከፈገግታዬ እኩል እንባዬ ከአይኔ አልፎ የጎፈረው ፂሜ ውስጥ ሰተት ብሎ ሲገባ ይሰማኛል  እግሬ ከጭንቅላቴ ሳይማከር  የሁልጊዜ መዳረሻዬ ጋር ደርሷል አይኖቼን ቀና አደረኩት  መንበረ ጽብኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን አባታችን ሆይ! በሰማያት የምትኖር፤ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤ የዕለት እንጀራችንን ስጠን ለዛሬ... አበሳችንንም ይቅር በለን፤ እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል... ከክፉ ሁሉ አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታስገባን፤ መንግሥት ያንተ ናትና፣ ኃይል፣ ምስጋና ለዘላለሙ፤ አሜን! ከሩቅ ተቀምጩ እስኪጨርሱ ጠበኩኝ ነጭ ነጠላ እና ጋቢ የለበሱ ሰዎች በቤተክርስቲያኑ በር አከባቢ ቆመዋል የደቀቀው እና የተልፈሰፈሰውን ሰውነቴን እየጎተትኩ ከተቀመጥኩበት ተነሳው የቤተክርስቲያኑን መግቢያ አልፌ ወደ ውስጥ ገባሁ ነጭ የለበሱ አማኞች ወደ ቤተክርስቲያኑ ሲያመሩ እኔ ግን ወደ መቃብር ስፍራው አመራው የሁልጊዜ ቦታዬ ላይ ተቀመጥኩኝ 00:00.. 00:01...00:02...00:03...00:04...00:05 ፀሀይ ብርሀኗን እያሰፋች ነው ትከሻዬ ላይ እንድ ነገር ሲያርፍ ቀና ብዬ አየው አንድ ፊታቸው የተሸበሸበ ጭንቅላታቸው ላይ  ቢጫ ነገር አድገዋል«ልጄ ደህና አደርክ Âť መልስ አልሰጠዋቸውም ሁሌም ይመጣሉ እንዲሁ ብቻቸውን አውርተው ከእኔ መልስ ሳያገኙ ይሄዳሉ  ምርኩዛቸውን ቀደም አድርገው ልክ እኔ እንደተቀመጥኩት ተቀመጡ ÂŤ ዛሬም አታነጋግረኝም» አሉ ድምፃቸው ይቆራረጣል እርጅና ጋር ነው መሰለኝ እኔ ግን አለመናገርን መርጫለሁ ዝም ዝምታ ÂŤ አንተ አታወራም እኔ ላውራ እንጂ ለምን ታድያ እዚህ ድረስ መተህ ለምን ገብተህ አትሳለምም ወይስ ከእግዜር ተጣልተህ ነው Âť ÂŤ እሷን አዪት እኔ ነኝ የገደልኳት Âť ከአንደበቴ የወጣው የመጀመሪያ ድምፅ የተሰባበሩ እና ድክም ያሉ ቅላፄዎች አይኔ ፊት ለፊቴ ያለው ከእምነ በረድ የተሰራ መቃብር ላይ ተተክሏል አጠገቤ ያሉት ሰው ዝምታቸው ረዘመብኝ ቀና ብዬ አየዋቸው መደነቅ ይሁን መጠየፍ ግራ የገባው አስተያየት ያዩኛል አልደነቀኝም ከተቀመጥኩበት ቦታ ብድግ አልኩኝ «አባ ገብረ ስላሴ እባላለሁ ያንተስ ስም Âť ብቆጥር ለ 100 ጊዜ ይሆናል ስማቸውን ነግረውኝ ስሜን ለማወቅ የጠየቁኝ   «ደህና ይዋሉ Âť አለፍ ብያቸው ሄድኩኝ «ነገም ትመጣለህ Âť እርምጃዬን ገትቼ ዞር ብዬ አየዋቸው ረጋ ባለ እና እዝነት በተሞላበት ድባብ እሳቸውም አዩኝ ጀርባዬን ሰጥቼያቸው ሄድኩኝ                        ━─ ━─ đœ—đœš  ─ ━─━                                  ƚፈፀመ                        ━─ ━─ đœ—đœš ━ ─━─ የክረምቱ ወራት አልፈው መስከረም ቀናትን አስቆጥሯል ለጥቅምት ጊዜውን ሊያስረክብ ቀናት ብቻ ቀርቷል ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው የሚመለሱበት ወር ከኖርዌ ከተመለሰ ቀናት አልፈውታል ግን እስካሁን ወደ ሾል ገበታው አልገባም ዛሬ ግን የመጀመሪያ የማስተማር ቀኑን ሊጀምር ነው የሚያስፈልጉትን ነገራት ይዞ ወደ ተመደበበት ክፍል አመራ 12⁰⁸  በሩን በቀስታ ከፈት አድርጎ ወደ ውስጥ ገባ በስርአት ያልተቀመጡ በስርአት ተቀመጡ የሚያወሩትም ዝም አሉ  ወደ ውስጥ ገብቶ በጥሞና ሁሉን ተመለከታቸው «እስከዛሬ ድረስ ባለመገኘቴ ከልብ ይቅርታ እጠይቃለሁ ሀገር ውስጥ ስላልነበርኩኝ ነው ከዚህ ቡሀላ ግን አንድም ክፍለ ጊዜ ዝንፍ ሳይል ትማራላችሁ Âť አለ መነፀሩን ዝቅ አድርጎ ከጥግ እስከ ጥግ በመርማሪ አይኖቹን እያንዳንዱን ተማሪ እየተመለከተ ማንም ምላሽ አልሰጠውም ተማሪዎቹ  በመገረም አስተያየት አስተማሪ ነኝ ብሎ የመጣውን እንግዳ ሰው በዝምታ እያዩት ነው እሱም የእነሱን ትኩረት በማግኘቱ ውስጡ ረክቷል ÂŤ ወጣቱ እስኪ ስምህን ንገረኝ Âť አለ ጥግ ላይ ወደ ተቀመጠው ፀጉሩን ወደሚያፍተለትለው ልጅ እያየ የአስተማሪያቸውን ጥያቄ ተከትሎ ሁሉም ተማሪዎች ወደ ዃላ ወንበር ዞሩ ልጁ የሁሉም አይን እሱ ላይ ሲሆን ሽምቅቅ ብሎ እጁን ከፀጉሩ ላይ አነሳ «ቃሲዮን እባላለሁ Âť አለ ሁሉንም ተማሪ ስሙ አስገርሟል እሱም ስሙን ሲናገር ሁሉም ሰው እንደሚገረም ያውቃል በዚህም ስሙን አምርሮ ይጠላዋል ÂŤ ቃሲዮን የስምህን ትርጉም ታውቀዋለህ» አስተማሪው ትኩረቱን ወደ እሱ አድርጎ ጠየቀው ÂŤ አይ Âť «ለየት ያለ ስም ነው ያለህ ማን ነው ያወጣልህ Âť የመምህሩ የተከታተሉ ጥያቄዎች ምንም ምቾት አልሰጠውም ሁኔታው ይናገራል ÂŤ እናቴ ነች ያወጣችልኝ Âť የሚል አጭር መልስ ሰጠው  «ቃሲዮን በሶሪያ ዋና ከተማ ደማስቆ አጠገብ የሚገኝ ታዋቂ ተራራ ነው ተራራው ደማስቆን ቁልቁል አቅፎ የሚጠብቅ በመሆኑም በታሪክ የደማስቆ ዘበኛ ይባላል  ይህን ያህል ፍንጭ ከሰጠውህ ይበቃል ሌላውን ደሞ ላንተ የቤት ሾል ሰጥቼሀለው ይህ ተራራ ብዙ ታሪክ አለው ነገ ስንገናኝ የመጀመሪያው ስራዬ ያንተን የቤት ሾል ማዳመጥ ይሆናል Âť አለ እና አይኖቹን ወደ ሌላኛው ጥግ ÂŤ ያንቺስ ስም ማን ይባላል Âť አላት የደከሙ እና የተሸበሸቡ የሚመስሉት አይኑን ከመነፀሩ ሌንስ አልፎ እይታው እሷ ላይ እያረፈ ከእሷ ውጪ ማንም ስለሌለ እሷን እንደሆነ እሷም ገብቷታል «እኔ አቪጌያ ወይም ሲዮራ እባላለሁ» አለች ለዘብ ያለ ፈገግታ አሳያት «ሁለት ስም ያላት ብቻ ሰው ነሽ ምክንያት አለው እንዲሁም የሁለቱም ስሞች ትርጉምስ?Âť ÂŤ አቪጌያ እናቴ ያወጣችልኝ ስም ነው የአባቴ ደስታ ወይም አባቷን ደስ የሚያሰኝ እንደማለት ነው ትርጉሙ እኔ በመወለዴ የእኔ አባትም እንዲህም የእናቴ አባትም በጣም ደስተኛ ስለሆኑ ነው ይህን ስም ያወጣችልኝ እንዲሁም በመፀሀፍ ቅዱስ  ሳሙኤል 25 ላይ በብልሃቷ እና በበጎነቷ እንዲሁም በውበቷ የምትታወቀው በዃላም የንጉስ ዳዊት ባለቤት የሆነች ታላቅ ሴት ስም ነው» «አንቺም እንደዚህች ሴት ነሽ ታድያ ስምን መላእክ ያወጣዋል አይደል ቢሂሉም Âť «አዎ እሆናለሁ ነኝም» ብላ ፈገግ አለች ፈገግታዋ ተጋባበት መሰል እሱም ብልጭ አደረገ የተደረደሩ ነጭ ጥርሶቹን ÂŤ እሺ ሁለተኛው ስምሽስ ስዮራ ነው አይደል ያልሽኝ Âť «አዎ እሱን ደሞ አባቴ ነው ያወጣልኝ   ትርጉሙም ንፁህ እና ነፃ ማለት ነው  እንዲሁም የነቢዩ ሙሴ የሴፎራ ስም ሌላኛው ቅላፄ ነው Âť ÂŤ አልተሳሳትሽም አንድ ሌላ ነገር ደሞ እኔ ልጨምርልሽ ሲጳራ ከሚለው የእብራኤስጥ ቃል የተወሰደ ነው ስለዚህ እኔ ሲጳራ ብዬ እጠራሻለሁ»