en
Feedback
𝙸'ƚ𝚒dαℓ 𝙸мαи

𝙸'ƚ𝚒dαℓ 𝙸мαи

Open in Telegram

የፃፈ ሁሉ ደራሲ የተፃፈ ሁሉ ድርሰት አይባሉም !

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
2 899
Subscribers
-224 hours
-97 days
+4730 days
Posts Archive
በጊዜ ልናገር ብዬ ነው ለዛሬ ታሪክ ይለፋችሁ 😭

ÂŤ ችግር አለው እንዴ Âť ÂŤ መሽቷል ሰአቱ Âť ÂŤ 12:00 መች ሆነ ገና 10 ደቂቃ ብቺ ነው እሺ በለኝ እ» ውስጥር ለሕን እንደሚሟገት አላውቅም ግማሽ ጎኔ ተገናኙ ግማሽ ጎኔ አይሆንም ከዚህች ልጅ ራቅ እንዴት እንደማስማማቸው አላውቅም ÂŤ ዝምታህ መስማማትህን ነው የሚገልፀው ባለው ከእነ ኤልዮን ጋር ያሳለፍንበት ቦታ እንገናኝ 15 ደቂቃ ውስጥ እደርሳለሁ Âť ዝላ ስልኩን ዘጋችው እራሷ አውርታ እራሷው ሀሳብ አምጥታ እራሷ የምትወስን አይነት ሰው ነች ፋላጎቴን ሀሳቤንም አትሰማኝም ስልኬን አስቀምጩ ተቀመጥኩኝ ተመልሼ ተነሳው እና ልብስ ቀይሬ ወጣሁ ለሰፈር ቅርብ ስለነበረ ያለችኝ ቦታ  ደረስኩኝ የሁለት ደቂቃ ልዩነት እሷም መጣች ÂŤ ቀደምከኝ ማለት ነው Âť ጎንበስ ብላ ልትሰመኝ ስትል እጄን ዘረጋውላት ፈገግ አለች እና እጄን ጨብጣ ተቀመጥች ፀጉሯ ተለቋል ጠቆር ያለ ሹሪ እና ነጭ ሸሚዝ ለብሳለች ቀለል ያለ ልብስ ቢሆንም አምሮባታል «የሆነ ነገር እንዘዝ Âť አስተናጋጁን ጠርታ ለእሷም ለእኔም አዘዘች ምን ያስፈልግሀልም አላለችም «ደሞ አትኮሳተር እንደዚህ ፈገግ በል» ÂŤ ፈገግ Âť ÂŤ No, እኔ አትኮሳተር እንጂ ቃል በቃል በልልኝ አላልኩህም Âť «እስኪ ስለራስህ ንገረኝ በደንብ እንድንተዋወቅ» «ምን ልንገርሽ» ÂŤ እሺ እኔ ልንገርህ እና እሱን ምሳሌ አድርገህ ትነግረኛለህ ሲዮራ ማለት ለእናት እና አባቷ ብቸኛ ልጅ የሆነች በሰዎች ዘንድ ተወዳጅ ቅልል ያለች ሰው ብቻ ከሁሉም ጋር ተግባቢ እና እንደምታየኝ ቆንጆ ነኝ Âť «ጥሩ ጥሩ ነገርሽን ብቻ አወራሽ Âť «እንዴ ሰው ሾለልሹ ሲናገር መጥፎ ነገር እንዴ ያወራል Âť «ሁለቱም የራስሽ ማንነት አይደሉ እንዴ ምን ችግር ስለሁለቱ ጎኖችሽ ብትናገሪ» አስተናጋጁ ጠረንጴዛው ላይ አስቀምጦልን ሄደ ÂŤ እሺ እኔ መጥፎ ባህሪዬን አላውቅም ግን በጣም የዋህ ነኝ አሁን ደሞ ስለራስህ ንገረኝ Âť «እሺ ስሜ ቃሲዮን ነው አለቀ ከዚህ በተጨማሪ ምንም የምነግርሽ ነገር የለኝም Âť ፈገግ አለች እጇን ወደ እኔ ሰነዘረች ÂŤ ጉርሻ አልወድም Âť ፊቷ ቅዝቅዝ አለ «ሳታጎርሺኝ በፊት መጠየቅ ነበረብሽ Âť «ይቅርታ ስላላወኩኝ ነው Âť «እሺ አትከፊ አጉርሺኝ Âť ፊቷ ፍክት እያለ አጎረሰችኝ ለደቂቃዎች በዝምታ ተመገብን «እየመሸ ነው እንውጣ»ሂሳብ ከፍዬ ወጣን አንድ እጇን እጄ ላይ ጠመጠመች ÂŤ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ Âť «ደስ ይለኛል Âť «ጓደኛ ምናምን የለሽም እንዴ» «ባለፈው ያየኻቸው እነ ኤልሮን ሁሉም ጓደኞቼ ናቸው Âť «አይ ማለቴ የፍቅር ጓደኛ ምናምን Âť ÂŤ እሱማ የለኝም Âť ምንም አላልኩም በዝምታ መራመድ ጀመርን እሷም ምንም አላለችም ወደ ሰፈሯ ተጠጋን «ባለፈው ያልኩትን ነገራቶች ተስማማህበት እንዴ Âť «የምን ሀሳብ Âť «ፍቅረኛሞች እንሁን ያልኩህን» «እኔ እና አንቺ ብዙ ልዩነት ያለን ሰዎች ነን Âť ÂŤ ሀይማኖት ከሆነ ፍቅር ሀይማኖት እና ብሄር የለውም ሲባል አልሰማህም» ÂŤ ጥሩ ፈላስፋ ነሽ Âť ÂŤ እና ምን አልከኝ Âť ስልኬ ከኪሴ ውስጥ አቃጨለ አውጥቼ አየውት ሮዝ ይላል ይቀጥላል .  .    . @rim_han .

 .                 ╔═══ ೋ 𔘓 ೋ  ═══╗                               ኦርቶዶክሳዊቷ                          á‹°áˆŤáˆ˛  አፍናን ሩማን Âť                   ╚═══ ೋ 𔘓 ೋ ═══╝ .                       ━─━─  𓍯  ─━─━                              ραɾƚ    0:08                         ━─━─  𓍯  ━─━─  ÂŤáŒ“á‹°áŠáŠá‰ľ ብቻ እነ ኤልዮን ጋር ይተዋወቃሉ በእነሱ ነው ያወኳት Âť «እኔ ግን ምንም ደስ አላለኝም የእነሱ ሳይበቃ ጭራሽ ሴት ብቻ አስብበት Âť «ምኑን ላስብበት በሀይማኖት የተለያየን ሰዎች ጋር ጓደኝነት መፍጠር የለብንም ማለት ነው የሌሎችን እምነት ተከታዮችን ሰዎች መጥላት አለብን Âť «ቃሲዮን ወሬ አታጣም እኔ ጥላቸው ወይም ሌላ ነገር አላልኩም ግን ለቅርበትህ ገደብ ሊኖር ይገባል ካልሆነ ግን ወደተሳሳተ መንገድ ፈቅደህ እና ፈልገህ እራስህን ትምረዋለህ እነሱ ተፅኖ ሾር ትወድቃለህ እነሱን ለማስደሰት ብለህ ፈጣሪህን ታሳዝናለህ እኔ የምፈራው ይሄንን ነው «የእኔ አሳቢ ገብቶኛል አታስቢ ግን ይሄ አይፈጠርም ይሄን ጥላቻሽን ተተሽ ብትቀርቢያቸው እኮ አንቺም ትወጂያቸዋለሽ» «እኔ ጥላቻ የለብኝም አይደለም እነሱን ምንም ያላደረጉኝን የተጣላውትንም ሰው አልጠላም ጥላቻ ነው ብለህ አታስብ ግን በጣም የበዛ ግንኙነት ውሎህ ወሬህ ወንዶቹ ይሁን እሺ ግን ሴቷ ለአንተ ሀጂነብይ ናት ካልነገርካት እሷ ይሄንን ልትጠብቅ አትችልም ብቻ አስብበት Âť «እሺ በቃ Âť ከዚህ በላይ መልስ ከሰጠዋት ነገሩ እየከረረ ይሄዳል ዝምታ ይሻላል እሷም ዝም አለች «አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ Âť አዲስ ወሬ ለመፍጠር ሌላ ርእሰ ጉዳይ አነሳውባት ÂŤ ጠይቀኝ Âť «እንደ ነፍስሽ የምትወጂያትን ጓደኛሽን እንደዛ ስፍስፍ የሚሉልሽን አስተማሪዎች በቃ ትምህት ቤቱን ለምን ቀየርሽ እና ወደ እዚህኛውን ትምህርት ቤት ለምን መጣሽ መጀመሪያ እንቀይር ስልሽ ያልፈለግሽ ምን ተገኘ Âť ለቀናት ሲበላኝ የነበረ ጉዳይ ነበረ «አንተ ስለለቀክ ነዋ Âť ፈገግ አልኩኝ ከእኔ አለመራቋ ወይስ ለእኔ ብላ የምትወዳቸውን መተዋ የቱ ነው ደስ ያሰኘኝ ብቻ መልሷ አስደስቶኛል ÂŤ የሚያስቅ ነገር ተናገርኩ እንዴ ፈገግ አልክ እኮ Âť ÂŤ አይ ለእኔ ብለሽ ታደርጊዋለሽ ብዬ አልጠበኩትም ነበረ Âť «ኧረ ላንተ ብዬ አይደለም Âť ደስታዬን ክስም ስታደርገው «እና ለምን ቀየርሽ Âť «ማማ አንተ ትምህርት ቤት ልትቀይር እንደሆነ ስነግራት ከእሱ ጋር መራራቅ የለባችሁ ብላ እኔም እንድቀይር ሀሳብ ሰጠችኝ Âť ÂŤ ማማ ምን አስባ እንደዛ አለች እንድንራራቅ ለምን አልፈለገችም» ÂŤ ያው አሉን ወንድሜ ስለሌለ አንተ ነህ ያለኸኝ መከታዬ ደብሮኝ ነበረ ፕሮፌሰሩን ሳይ ግን እንኳንም ቀየርኩ ነው ያልኩት »የዚህ ሰውዬ ነገር አሁንስ መረረኝ «የዚህን ሼባ ስም እንዳታነሺ ከዚህ ቡሀላ Âť «እሺ Âť ከዛ በላይ ቃላት አልተለዋወጥንም እሷም ተኛች እኔም እንዲሁ እሷ አጠገብ ተቀምጬ ሰአቱ ሄደ «ሮዝ በቃ ልሂድ ማማ እንዳትጨነቅ ደውልልሻለሁ ነገ ክላስ አትገቢም አይደል Âť «ኧረ እገባለሁ አሁን እኮ ተሽሎኛል» ÂŤ እሺ ጠዋት በዚሁ መጥቼ እወስድሻለሁ Âť «ኧረ ራሴው እመጣለሁ አላውቅህም እንዴ አንተ ነህ በጠዋት የምትነሳው» «እሰይ ሁል ጊዜ እኔ ላንቺ ሰነፍ ነኝ ማለት ነው Âť «ሰነፍ አይደለህም እንቅልፋም ነህ እንጂ ለማንኛውም እመጣለሁ በጠዋት ተነስ ሱሁቢን ሰግደህ ለምን ትተኛለህ መስገድህንም እንጃ Âť ለልሡ በሚሰማ ድምፅ ተናገረች ግን ሰምቻታለሁ ÂŤ አሞሻል ብዬ እንጂ Âť «ምን ልትመታኝ ነው Âť ÂŤ አይ ልስምሽ ወይስ አሁን እንደ ድሮ እያለቀሽ ሳመኝ ብለሽ ልትናገሪ ነው Âť ይሄን ጉዳይ ሳነሳባት ሽምቅቅ ትላለች አውቄ ነው ያነሳውባት እኔም ለመገላመጥ ሞክራ ተሸፍና ተኛች ÂŤ መገላመጡ ተይ የምር ያለሙያሽ እየገባሽ ነው ፊትሽን ብታይው በራስሽ ታፍሪ ነበረ ቻው ለማንኛው እወድሻለሁ Âť ከቤት ወጣሁ ግቢው  ጨለምለለም ብሏል ቀጥታ ወደ ቤት ሄድኩኝ ግቢ ውስጥ ማንም የለም ዘበኛው ብቻ ነው ወደ ውስጥ ስገባ ባባ ሳሎን ተቀምጧል ÂŤ እንዴ አባ እንዴት ተገኘህ ዛሬ Âť ሰው ቢሰማው ይሄን ቃሌን ሊገረም ይችላል አንድ አባውራ እቤት ውስጥ ቢገኝ እንዴት ሊያስገርም ይችላል ከዛም አልፎ እንዴት ተገኘህ የሚል ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል ? እኛ ቤት ግን ያስነሳል አባቴ የሩቅ ዘመድ ይመስል በሆነ ጊዜ አንዴ ይመጣል ወይም እኔ ሳላየው ወቶ ይገባል ለቤቱ እና ለልጁ ጊዜ የለውም «ምነው ልጄ የገረመህ ይመስላል ምነው ስትጠፋብኝ እኮ ነው የመጣሁት ድሮ ትመጣለህ የት ነህ ብር ያስፈልገኛል በሚሉ ሰበቦች ትደውልልኝ ነበረ አሁን እርግፍ አድርገህ ተውከኝ «አልተውኩህም ማማን እጠይቃታለው ሁሌ ና ብልህም ስለማትመጣ ነው ጭቅጭቅ እንዳይሆንብኝ ነው የተውኩት» ÂŤ አይ የኔ ልጅ ሾል ስለሚበዛብኝ ነው ከዚህ ቡሀላ አልጠፋም Âť «እሺ ማማ የለችም እቤት እንዴ Âť «እኔንጃ አላያዋትም Âť ፊቱ ላይ ያነበብኩት ስሜት እሷን ስለእሱ ስጠይቃት የምታሳየኝን ሁኔታ ነው ቆይ እነዚህ ሰዎች ይጠላላሉ እንዴ ቢጠላሉ ደሞ ለምን እስካሁን በትዳር ቆዩ ችግራቸውስ ምንድነው ከበባ አጠገብ ተቀመጥኩኝ እራሴን እንደምንም አደፋፍሬ ÂŤ ባባ እናቴን ትጠላታለህ እንዴ» ፊቱ ብርዝ ቁጥት ሲል አየውት ምኑ ጋር ይሆን የተሳሳትኩት አጠያየቄ ወይስ ጥያቄዬ ÂŤ ለምን እንደዚህ አልክ እንዴትስ ልታስበው ቻልክ» ቃላቶቹ ድምፁ የቁጣ ቃና አላቸው «አይ እንዲሁ ከእኛም ከቤትህ የራክበት ጉዳይ ምን ይሆን ብዬ ነው ማማ ጋር ያላችሁም ግንኙነት ጥሩ አይመስለኝም» «ባለትዳሮች መሀል ጥል ሊኖር ይችላል መጠላላት ግን አይኖርም እንደዚህ አይነት ሀሳብ እንዳይኖርህ ለእኔ ሚስት ለብቸኛው ልጄ ደሞ እናት ነች እንዴት ነው ልጠላት የምችለው Âť. «ይቅርታ ባባ ግራ ስለገባኝ ነው እንደዚህ ያልኩት እንጂ ክፉ ነገር አስቤ አይደለም አንድ ሌላ ውስጤን የሚበላንኝ ነገር አለ ልጠይቅህ Âť በእንቅስቃሴው ፍቃደኛ መሆኑን ገለፀልኝ «ድሮ ትዝ ይለኛል መልኳ ድብዝዝ ብሎ አክስቴ የት ሄደች እቤት እንደምትመጣ ትዝ ይለኛል ድሮ ድሮ» «እሷ የለችም በቃ ልትመጣም አትችልም ስለእሷ በድጋሜ እንዳትጠይቀኝ» ምንም ማለት አልቻልከም ዝም አልኩኝ «ቃሲዮን አንተ ብዙ የማታውቀው ነገር አለ አሁን ላይ ብዙ የማይገቡህ ነገራቶች አሉ የገቡህ ቀን ውስጥህ ላሉት ነገራት መልስ ታገኛለህ »ፈገግ አልኩለት ÂŤ እሺ በቃ ልብስ ልቀይር እና ወጣ ልበል Âť አልኩት እና ከተቀመጥኩበት ተነሳው ÂŤ ብር አለህ እንዴ ልላክልህ Âť «ኧረ ማማ ከሰማች ትናደዳለች» «ለካ ህግ ወቶብሀል እንግዲህ በእሷ ትእዛዝ መሰረት እንቀሳቀሳለን Âť ደረጃውን ወጥቼ ወደ ክፍሌ ገባሁ የለበስኩትን አውልቄ ቀለል ያለ ልብስ ለበስኩ ከእኔ ርቆ የዋለውን ስልኬ ሳያየው ብዙ call አሉት ሁሉንም ሳያሳቸው ኤልዮን 3 ጊዜ እንድ ያማላውቀው ስልክ ከ 5 ጊዜ በላይ ተደውሏል ቅድሚያ ለኤልዮን ልደውልለት ቁጥሩን ከመጫኔ ስልኬ ጠራ የማላውቀው ቁጥር ነው አነሳውት «ሄሎ» «ተመስገን ጌታዬ Âť «ማን ልበል Âť ÂŤ ሲዮራ ነኝ ክላስ ሳጣህ አሞት ወደ ቤት ሂዷል ሲሉኝ እኮ በጣም ተጨንቄ ነበረ ጌታን እንኳን ድምፀን ሰማሁት Âť «ይሄን ያህል የሚያስጨንቅሽ ቅርበት ያለን አይመስለኝም Âť «ዋናው ደህና መሆንህ ነው አሁን ብንገናኝ ደስ ይለኛል Âť «ለምን እንገናኛለን Âť

ቅዝቅዝ አላችሁ በጣም ምን ቅር ብሏችሁ ነው ግን ? .

ደግነት መጠኑ ካለፈ መብት ሳይሆን ግዴታ ይመስላል 🗣 Dr.no @rim_han

«እሺ እቴቴ አሁን ውሀ ሲፈላ ነው አንጀራውን የምጨምረው Âť ÂŤ አዎ ነው ዛሬማ ሙያ ተማርክ Âť ÂŤ እንዴ አዋ ነገ ደሞ ለማማ ብሰራላት በቃ ምርጥ ነው የምሆነው» «ዛሬማ በሳቅ ልትገለኝ ነው በል አሁን እንጀራውን ጨምር Âť እንዳለችኝ አደረኩኝ እሷ ሰሀን አዘጋጅታ አስተካክላ አደረገችልኝ ሳሃኑን ይዜ ወደ ሳለን ሄድኩ ÂŤ ትእዛዞት ደርሷል Âť አጠገቧ አስቀመጥኩላት ቀስ ብላ ተነሳች «አንተ አምርረህ ስራኸው እንዴ ቆይ ምን ፈልገህ ነው ግን እኔ እኮ የሆነ ነገር አድርግልኝ ብልህ በፕሮፌሰር ወይ በማማ መልእክት ካላስተላለፍኩልህ የማታደርግ ሰው  ዛሬ ከመሬት ተነስተህ ዱብ እንቅ አልክ» «ዛሬ ግን ቀኑ ምንድነው የማላውቃቸው ቃላት እየሰማሁ ነው አሁን ምርመራሽን ትተሽ የተዘጋጀልሽን በልተሽ ዳኚ Âť ÂŤ ግን ፈሳሽ ነገስ ተጠቀሚ ነው የተባልኩት Âť ብላ ሳቀች «እንጀራ ሳልጨምርበት በፊት ፈሳሽ ነበረ እንጀራው ነው ጠጣር ያደረገው አርፈሽ ብይ ወይስ ላጉርሽ Âť ÂŤ ሰው ማጉረስ እንደማትወድ ላስታፍስህ Âť ÂŤ ሰው ነዋ ታድያ አንቺን መች እጠላለሁ አልኩ» ÂŤ ምን Âť ÂŤ አትናደጂ አንቺን ግን አጉርሼሽ አውቃለሁ አይደል» «እሱ ከዛሬ ከመታት በፊት ነው ልጅ እያለን» «እና አሁን አድግያለሁ መሆኑ ነው በይ በይ ለእኔ አሁንም ህፃን ነሽ» አጠገቧ ተቀመጥኩኝ አነስ አነስ አድርጌ ጠቅልዬ አጎረስኳት እቴቴ የብርቱካን ጭማቂ አዘጋጅታ ይዛልን መጣች «ይኸው ፈሳሽሽ ጠጪው Âť ብዬ ሳኩኝ «አንተ ልትገለኝ ነው እንዴ ቀስ እያልክ ደሞ አሳንሰው ትንሽ እንዳንተ መሰልኩህ እንዴ ሲቀጥል ለራስህ ጉሩስ» ÂŤ ኧረ አትነጫነጪ ከዚህ ያነሰ እንዴት የማጎርስሽ» አንድ ለእኔ አንድ ለእሷ እያልኩ ጨረስን «ይሄን ጨርሸሽ ጠጪ በቃ ተፈወስሽ ማለት ነው Âť የበላንበትን ወደ ኪችን አድርሼ  እጄን ታጥቤ ተመለስኩኝ «እስከ ስንት ነው እዚህ የምትቆየው» ÂŤ ምነው እንድሄድ ፈልገሽ ነው Âť ÂŤ አይ አይደለም  ዩኒፎርም እንደለበስክ ነክ ብዬ ነው Âť ÂŤ ይሁና እቤት ውስጥ ነኝ እኮ እናትሽ ስትመጣ ነው የምሄደው Âť ከስንት ዘመን በፊት የተውኩትን tv ከፍቼ እንደ ቅድሙ  ተቀመጥኩኝ  ÂŤ ቃሲዮን Âť ÂŤ ወዬ Âť በከፊልም ፊቴን እያዞርኩ ወደ እሷ «የትላንትናዋ ልጅ ግን ማነች ምንህስ ነች Âť ÂŤ ሲዮራ ነች እኛ ክፍል ያለችው ልጅ አታቂያትም እንዴ Âť ÂŤ እሺ ላንተስ ምንህ ነች ማለቴ ግንኙነታችሁ Âť ለዚህ ጥያቄ ምን ብዬ ነው የምመልሰው ምኔም አይደለችም ወይስ ምን ከመልስ ይልቅ አተኩሬ አየዋት ይቀጥላል .     .  . @rim_han .

 .                 ╔═══ ೋ 𔘓 ೋ  ═══╗                               ኦርቶዶክሳዊቷ                          á‹°áˆŤáˆ˛  አፍናን ሩማን Âť                   ╚═══ ೋ 𔘓 ೋ ═══╝ .                       ━─━─  𓍯  ─━─━                              ραɾƚ    0:07                          ━─━─  𓍯  ─━─━ ÂŤ አሁን ልፍቀድልህ ብል እራሱ ምንም ያመመው ሰው ምልክት አላይብህም ስለዚህ ቁመህ አትየኝ ውጣ ከቢሮዬ Âť «ውስጤን ስላመመኝ እኮ ነው Âť «ውስጥህን ስላመመህ ነው ውጪህ ደህና የሆነው አሁን ለምን አትሄድም» «ለዛሬ ብቻ እኮ ነው እቤት መሄድ አለኝ ካልሆነ ከዚህ አልሄድም» ትኩር ብሎ አየኝ አነስ ያለች ወረቀት አነሳ እና «ስምህን ማነው ያልከኝ Âť «ቃሲዮን መሀመድ Âť ወረቀቱ ላይ ፃፋ ፃፍ አድርጎ ሰጠኝ ÂŤ ከዚህ ቡሀላ ግን አሞህ ልትሞት ቢሆን እራሱ አልፅፍም ገባክ »ወረቀቱን ተቀብዬ አነበብኩት ቃሲም መሀሙድ ይላል ይሁን ዋናው የእሱን ፋቃድ አጊንቼ ከዘህ ጊቢ መውጣቴ ነው «አመሰግናለሁ »ፈጠን ብዬ ወጣሁ ከቢሮ በር ላይ ያሉት ዘበኞች ብዙም አላንገራገሩም የፍቃድ ወረቀቱን ሳሳያቸው አስወጡኝ ከእሷ ጋር ስሆን በእግራችን ቀስ እያልን የምንሄደውን ጎዳና ለብቻዬ ከበደኝ ወደ ሰፈር ሚወስደኝ ታክሲ ውስጥ ገባሁ የሆነ ነገር ሳትሆንማ አትቀር ምን ሁና ይሆን ይሄን ያህል እሷን የሚያበሳጭ ነገርስ ምን አደረኩኝ ጭንቅላቴ ይጠይቃል ሚን ይመልስ ማንም እንዲሁ ይሄንኑ ጥያቄ ሳወጣ ሳወርድ ÂŤ እ አባቴ አትወርድ Âť ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ወረድኩ ከኪሴ ብር አውጥቼ ከፈልኩኝ ሰፈር መግቢያ ላይ ስለወረድኩ ብዙም አልቆየሁም በሩን በቀስታ አንኳኳው «እንዴ ትምህርት የለም እንዴ ምን ሁነህ ነው Âť በሩን ከፍቶ ከላይ እስከ ታች እየተመለከተኝ «አይ ሮዛሊን አለች Âť ÂŤ አዎ ትንሽ አሟት አሁን ነው ከሆስፒታል የተመለሰችው Âť አለኝ እንድገባ ከበሩ ላይ ገለል እያለልኝ ፈጠን ብዬ ገባሁ ሳሎን መጅሊስ ላይ ጋቢ ለብሳ ተኝታለች እናቷ እግሯ ሽር ተቀምጣለች ÂŤ እንዴ ይሄን ያህል ምን ሁና ነው Âť «ተረጋጋ ደህና ነች» «እሷን እኮ በሽታ አያስተኛትም ማማ እያወቅሽ የከፋ ነገር ካልሆነ በተአምር የማትተኛ ልጅ እንዴ አሁን Âť ቁልቁል የደፈረሱ አይኖቿን እዪየሁኝ «አልሀምዱሊላህ ደህና ነች በስንተ መከራ ነው ሆስፒታል የሄድነው እሺ ብላኝ ፈሳሽ ነገር ትጠቀም ብለዋል Âť «እና ትጠቀማ ምን ልግዛላት Âť ፈገግ አለች ÂŤ አይ ልጄ ወንድሟ ቢሄድ ወንድሟን ተካህላት ሁሉም አለ አትጨነቅ አሁን አንተ ከመጣህ እኔ ልሂድ Âť ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳች «እንዴ ግን ትምህርት የለም እንዴ እንዴት በዚህ ሰአት መጣህ Âť «ኧረ አለ ጠዋት ሳትመጣ ቀረች እዛው አገኛታለሁ ብዬ ስሄድ እዛም የለችም የሆነ ነገር ካልተፈጠረ ልትቀር አትችልም እስካያት ልቤ ልትወጣ ነበረ አስፈቅጄ ነው የመጣሁት Âť ÂŤ እንዴት ልጄ class ትተህ ትመጣለህ» «እዛም ብሆን በድኔ እንጂ ቀልቤን ሰብስቤ መማር አልችልም ነበረ እዚህ ብሆን አይሻልም ታድያ» «ወይ እናንተ በሉ እሺ እኔ ልሂድ Âť እሷ ከተነሳችበት ቦታ እኔ ተስተካክዬ ተቀመጥኩኝ «ደህና ነሽ Âť «አልሀምዱሊላህ Âť «ምን ላምጣልሽ የምትፈልጊውን ንገሪኝ»ቃላቶቿ ልሹ የቁጣ ቃና  አላቸው «ምንም አልፈልግም ግን በጣም ነው የከፋኝ Âť ÂŤ ምነው ለምን ከፋሽ Âť የትናንትናውን ነገር ልታነሳብኝ ይሆን ውስጤ ሰጋ «ዛሬ ፕሮፌሰሩን ሳላገኘው ልውል እኮ ነው» ÂŤ ምን አይቷ ነሽ በአላህ ታመሽ ተኝተሽ ለ ሼባ ታስቢያለሽ በጥፊ ማለት ነበረ Âť «ሼባ አይደለም ሼባ አትበለው ፕሮፌሰር ነው ሲቀጥል 54 አመት ቢሆነው የእሱ ቃላት እኮ ህይወት ናቸው ቆይ የሚናገራቸው ነገራት ነገራቶችን የሚረዳበት ብቻ ሁሉ ነገር ይለያል Âť ምን እንዳናደደኝ አላውቅም ሰውየውን አልወደድኩትም አሁን ይባስ ጠላውት «ኧረ ተይ ይለያል በጣም ነው እንዴ የተለየብሽ ደሞ እድሜውን ምን ስትይ አሰብሽው  ከእኔ ትደብቂያለሽ ንገሪኝ እስኪ ሼባውን ወደድሽው እንዴ Âť «አንተ አልወደድከው እንዴ Âť «አንቺ ልጅ ግን ጤነኛ ነሻ  እኔ እንዴት ነው የምወደው አንቺ ግን መልሺ ወደድሽው Âť «አዎ ወድጄዋለሁ ልክ እንደሱ ቢሆን ሁሉም መምህር በተማሪዎቹ  ሊይ ሀላፊነት ቢሰማው ኑሮ አሁን የምናየውን የተማሪን ውድቀት ባላየን ነበረ Âť «ሆይሆይ በቃኝ በቃ ከዚህ ቡሀላ ስለእዚህ ሼባ አናወራም ጭራሽ ልዩ ሰው ነው ትያለሽ» «እሺ ሼባ አትበለው» «እሺ ወጣቱ  ልበልልሽ Âť «አይ ፕሮፌሰር በለው Âť «እሺ ሼባው ፕሮፌሰር Âť በለበሰችው ጥቅልል  አለች እሰይ እኔ እንዳናደደችኝ አናደድኳት አንጀቴ ቅቤ ጠጣ ትላለች እናቴ የሆነ ነገር ሲያስደስታት «እሺ የምትወጂውን ምግብ ልስራልሽ ?Âť ከአንገቷ በላይ ተገለጠች «የምርህን ነው የፈለኩትን ትሰራልኛለህ  ቆይ ቆይ ግን በእኔ አሳበህ ዛሬም ክላስ ቀረህ Âť «አሁን ወሬውን ትተሽ የምትፈልጊውን ንገሪኝ» «ፍርፍር Âť «ጠብቂኝ» ከእግሯ ሾር ተነሳሁኝ እና ወደ ኪችን ገባሁኝ እቴቴ እዪፀዳች ነበረ ኪችን ውስጥ የምገባው ወይ የሆነ ነገር ፈልጌ ወይ የሆነ ነገር ላስቀምጥ ካልሆነ በቀር  ላበስል አስቤውም አላውቅ ÂŤ ምነው ልጄ ምን ፈልገህ ነው Âť በአይኖቼ ሁሉንም ሳማትር ግራ ገብቷት ነው መሰለኝ  ÂŤ እቴቴ ምን መሰለሽ ምግብ ፈልጋ ነው ማለቴ ፍርፍር Âť «ውይ ልጄን ጠዋት አንድ ጉርሻ በግድ እንደቀመሰች ነው እሺ ትንሽ ጠብቁኝ አዘጋጃለሁ Âť ÂŤ አይ እንደሱ አይደለም እቴቴ እኔ ነኝ ላዘጋጅላት የፈለኩት Âť «እሺ ካልክ Âť አስተያየቷ ገብቶኛል አይደለም ልስራ የበላሁበትን እንደማላነሳ ታውቃለች ባትታዘበኝ ይገርመኝ ነበረ «ግን እቴቴ እንዴት እንደምሰራ  አላውቅም እኮ  አታሳይኝም» ፈገግ አለች «እሺ አሳይሀለው »የሚያስፈልጉትን ነገራቶች አዘገጃጀች ÂŤ ሽንኩርቱን እኔ ልላጥልህ አይንህን ይቆጠቁጥሀል» ÂŤ እንዴ እቴቴ ይቆጠቁጥሀል ደሞ ምን ማለት ነው Âť «አይንህን ያቃጥልሀል ማለቴ ነው Âť ብላ ሳቀችብኝ ÂŤ አይ ችግር የለውም አያቃጥለኝም እኔው ልሴ ነኝ ሁሉንም ነገር ማድረግ የምፈልገው አንቺ ቁጭ ብለሽ ብቻ እይኝ ስሳሳት ታርሚኛለሽ» ከሳሎን ወንበር አምጥቼ አሰቀመጥኳት በቢላ ሽንኩርቱን መላጥ ጀመርኩኝ ግን ምንም ሊሆንልኝ አልቻለም በእጄ ጀመርኩት ÂŤ እቴቴ ግን እውነትሽን ነው ይሄ ነገር ያቃጥላል አይን አስለቀሰኝ እኮ Âť «ብዬህ ነበረ እኮ እኔ ልስራልህ የማታቅበትን አትባክን ልጄ» «ችግር የለም እናንተ ሁሌ አይደል የምትሰሩት እኔ አንድ ቀን ብሰራ ምን እንዳልሆን ነው ግን እቴቴ ጠንካራናችሁ እናቶች Âť ÂŤ አይ አንተ አሁን ሽንኩርት አይኔን አቃጠለኝ ብለህ ነው እንደዚህ ያልከው» «እንዴ አዋ የሁልጊዜ ስራትችሁ እኮ ነው» ÂŤ አይ አንተ ይሄ ቀላል ነው የሴት ልጅ ፈተና ብዙ ነው» እቴቴ በምትመራኝ መመሪያ የላጥኩትን ሽንኩርት አጠበኩት ለመክተፍ ግን አልሆነልኝ 4ፍሬ ሽንኩርት መፍጫ የተጠቀመ የመጀመሪያ ሰው እሆን ይሆናል እኮ የተፈጨውን ከምል የጠፋውን ብል ይቀለኛል ብቻ የምሰራበት ድስት ላይ አደረኩት እና ተጣደ እሷ እየለካችልኝ እኔ የሚጨማመረውን ነገር ጨማመርኩኝ

አበባዬ ፍሬዬ     ልጠይቅሽ ? መልሽልኝ ናፍቆሻል አይደል ፊትሽ ያስታውቃል ፈገግ አልኩላት አይኔ እያነባ ምን ብዬስ ልንገራት አይደለም ፊትሽን ውስጥሽን አውቃለሁ እውነቱን ንገሪኝ ናፍቆሻል? አዎ ናፍቆኛል! ፊቴ ያስታውቃል? አይኔ ይናገራል? አዎ ናፍቆኛል። ለምን አታገኚውም ? እሱ ይወድሻል አንቺ አትወጂውም ? ማፍቀሬን አልክድም መውደዴን አምናለሁ    ግን አላገኘውም ከወደድሽው ለምን አታገኚው ከናፈቀሽ ለምን ምን አስፈራሽ ፍቅር ሀይል አለው መውደድ ህመም አለው እሱ አበባዬ ነው ሳየው ይጨንቀኛል ላገኘው አፈራለው አበባዬ ነው ምን ለማለት ነው ወሬሽም ቅኔ ነው አዎ አበባዬ ነው ፍሬ የሚያፈራ ወይም የማያፈራ መቼስ ነው የሚያፈራው ? እንዴት ነው የማያፈራው ? ፍቅረኛዬ ሲሆን ሁለቱም ያስኬዳል አበባዬ አብቦ ለፍሬ ይበቃል ወይንም ደርቆ ክስም ብሎ ይቀራል ጭንቀቱ ፍርሀቱ ፍሬዬን ለማየት ሰቀቀን ስጋቱ ለማያስተማምን እውንም ያልሆነ ያልተረጋገጠ ፍቅር ብቻ ተብሎ ፍቅረኛዬ ሆነ ከዛስ? ፋሬ እንደሚሰጥ አንደ አበበ አበባ ጭንቀት ይጠይቃል እስኪሆን አበባ ለማይታወቅ ነገር ጥርጣሬ ላለው አፈሬንም ስቸር ውሀዬንም ስሰጥ ጊዜን ገድዬ ፈጣሪዬን እያመፅኩ እስካሁንም አለው አሱን ከማገኘው ሞቴን አመርጣለው እየናፈቀኝም ናፍቆት ቢገለኝም አብቦ ጨርሶ ፍሬ እስከሚሰጥ እጠብቀዋለው እስከ መቼ ? ፋሬ እስከሚሆን ፍቀረኛዬ ሳይሆን ባሌ እስከሚሆን ትዳር ማለት እኮ ስጋት የሌለበት ጭንቀት የሌለበት የደረስን ፍሬ አወርዶ እንደመብላት ጌታዬን ከማምፅ በዱዐ ብማፀን ዲኔንም ገምገፍ በናፍቆቱ ልክነፋ አፍኑዬ ወዬ ነይልኝ እስኪ ጠጋ በይ ወደ እኔ ምነው አሳዘንኩሽ ነይልኝ ልቀፍሽ ቅረቢኝ ወደ እኔ ✍  አፍናን  @rim_han .

ከአንድ አንባቢዬ ሀሳብ ተሰቶኝ ነው የተሰጠኝን ሀሳብ በደንብ ልግለፀው አልግለፀው አላውቅም የቻልኩትን ሞክሪያለሁ ወግ ብፅፍ አይመጣውም ግጥም ቢሆን ይሻል ብዬ ፃፍኩት ርእሱ አበባዬ ( ፍቅረኛዬ) ፋሬዬ ( ባሌ ) ስሜት ካልመጣም ገጣጥማችሁ አንብባችሁ መልእክቱን ለመረዳት ሞክሩልኝ ብቻ 😁 የተፃፈው እኔን አይወክልም ግን እኔም ሰው እስከሆንኩ ድረስ ያካትተኛል ! .

https://t.me/+tNSeqoPNvIdjZTE0 ማንኛውም አይነት ከሸሪዓ ጋር የማይጋጩ የስራ ማስታወቂያዎችን በአንድ ፕላትፎርም ላይ ማግኘት ከፈለጉ Halal Jobsን ይቀላቀሉ ! ውድድር ላይ ነች join በሉት

ቸልተኝነት የተሞላበት መልስ ÂŤ ይሄማ ነገር አለ ከአንቺ ጋር ነው እንዴ የተጣላችሁት ልጄ ምን አድርጎሽ ነው» ÂŤ አይ አይደለም ፕሮፌሰር እንዲሁ ትንሽ እራሴን አሞኝ ነው Âť ÂŤ አላህ ያሽርሽ በቃ እኔም አላድክምሽ ደህና እደሪ Âť ስልኩን ዘጋችው ÂŤ አንተ የማትረባ ልጅቷን ምን አድርጋሀት ነው እ Âť በአጆቿ ጀርባዬን ትደበድባለች ÂŤ ኧረ ማማ ያማል ልቤን በአፌ ልታወጪያት ነው እንዴ Âť በእጄ እጆቿን ይዤ ሲምኳት ÂŤ የማትረባ አስታግፊሩላህ ደሞ አስዋሸኸኝ አሁን ተናገር ምን አድርገኻት ነው Âť ÂŤ ትንሽ ተናዳብኝ ነው ነገ እግሯ ሾር ድፍት ብዬ ነው ይቅርታ የምጠይቃት አታስቢ Âť «ይሻልሀል እሷን የመሰለች ልጅማ አታስከፋብኝ በደንብ ጠበቅ አድርጋት» ÂŤ ለምን ልጆት ለልጄ አትዪም ማማ Âť ብዬ ሳኩኝ እሷም በከፊል ፈገግ አለች ÂŤ ችግር የለውም እላለሁ ጊዜው ይድረስ እና እራት በልተሀል Âť ÂŤ አልፈልግም ዝግት ነው ያደረገኝ ባባ አይመጣም እንዴ ዛሬም Âť ፊቷ በሰከንድ ቅይርይር አለ «እኔ አላውቅም ደውለህ ጠይቀው Âť ንዴት ባለው ቃና መለሰችልኝ «እሺ ማማ ደህና እደሪልኝ ልተኛ» ግንባሯን ስሜ ክፍሏን ለቅቄ ወጣሁኝ //////// ሱሁቢን ሰግጄ መልሼ  ጋደም አልኩኝ በዛው እንቅልፍ ይዞኝ ሂዷል ሰውነቴ ቅዝቅዝ ሲለኝ ከእንቅልፌ ብድግ አልኩኝ ÂŤ ተረጋጊ ሰውነትሽ ትኩሳት ጨምሯል Âť አለችኝ በእርጥብ ፎጣ ሰውነቴ ሊይ እያደረገችልኝ «አሞሻል ልጄ ሀኪም ቤት እንሂድ እሺ በይኝ እና Âť «አይ ደህና ነኝ ትንሽ ሳርፍበት ይሻለኛል» «ልጄ እንዲህ እያልሽ ነው አባትሽ እራሱ እየተጨነቀ ነው ወደ ሾል የሄደው እኔንም አታስጨንቂኝ እንሂድ እሺ በይኝ እና Âť ÂŤ እውነት ደህና ነኝ አሁን ትንሽ ልረፍ» «እሺ ቢያንስ ምግብ ብይ እቴቴ ደሞ ነግራኛለች ከትምህርት ቤት ስትመለሺ ጀምሮ ክፍልሽን ዘግተሽ ስታለቅሺ እንደነበረ Âť ÂŤ አይ ምግብ አልፈልግም ትንሽ ተናድጄ ስለነበረ ነው Âť የለበስኩት አስተካክላ አለበሰችኝ ////// ይበልጥ እንደተናደደችብኝ የገባኝ ጠዋት ትምህርት ቤት ጥላኝ ስትሄድ ነው ግን እዚህ ስመጣም የለችም የመጀመሪያው ክፍል ጊዜ አለፈ የለችም ሁለተኛውንም ጠበኳት የለችም ሶስተኛው ሊይ ተስፋ ቆረጥኩኝ እሷ አሟት እንኳን ከትምህርት ቤት ቅሪ ብትባል እሺ አትልም ዛሬ ታድያ ምን ተፈጠረ ሶስተኛው ክፍለ ጊዜ ሲያልቅ አስፈቅጄ ወደ ቤት ለመሄድ አሰብኩኝ 10 ደቂቃ ሲቀር አስተማሪው ወጣ እኔም ከተቀመጥከቡት ተነሳው ÂŤ ቃሲዮን Âť ወደ ዃላ ዞርኩኝ ፈገግ ብላ ወደ እኔ መጣች «እንዴ አደርክ Âť ብላ ጥምጥም አለችብኝ በአጆቼ ጎትቼ ከእራሴ አላቀኳት ÂŤ ይቅርታ አሁን መሄድ አለብኝ Âť እልፍ ብያት ቀጥታ ወደ ቢሮ ሄድኩኝ በሩ ክፍት ነው አንዴ አንካኩቼ ወደ ውስጥ ገባሁኝ «መውጫ ይፃፍልኝ አሞኛል ወደ ቤት መሄድ እፈልጋለሁኝ Âť «ያመመው ፊት አይታየኝም እኔ Âť ቀና ብሎ እያየኝ «ወደ ቤት መሄድ እፈልጋለሁኝ Âť «ስትፈልግ የምትወጣበት ስትፈልግ የምትገባበት የእናትህ ቤት መስለህ እንዴ ስምህ ማነው Âť ÂŤ ቃሲዮን Âť «እሺ ቃሲም አሁን ብዙ ሾል አለብኝ ትሄድ Âť ይቀጥላል.   .    . . @rim_han

 .                 ╔═══ ೋ 𔘓 ೋ  ═══╗                               ኦርቶዶክሳዊቷ                          á‹°áˆŤáˆ˛  አፍናን ሩማን Âť                   ╚═══ ೋ 𔘓 ೋ ═══╝ .                       ━─━─  𓍯  ─━─━                              ραɾƚ    0:06                         ━─━─  𓍯  ━─━─ ከእኛ ቅርብ ርቀት ነበረች ፈገግ ብላ መጣች አጇን በእጄ አጠላለፈች «ጠብቀኝ ብዬህ አልነበረ ለምን ጥለኸኝ ሄድክ» ፊቷን አንደማኩረፍ ጣል አደረገችው ደረቴ ላይ ልጥፍ አለች ምኑን ከምኑ እንደማደርገው ግራ ገባኝ ሮዛሊን እስከዛሬ አይታኝ በማታውቀው አስተያየት ትኩር ብላ አየችኝ አይኖቼ ውስጥ የሆነ ነገር ትፈልግ ይመስል ፊቷ ቅልት ሲል አይኖቿ እንባ ሲያዝሉ አየዋት በእጄ «ኦ ይቅርታ አላየሁሽም ነበረ እህትህ ነች አይደል »እጇን ዘረጋችላት አንዴ እኔን አንዴ የዘረጋችላትን እጅ አፈራርቃ ተመለከተችው እኔ የልቤ ምት ጨምሮ በአፌ ልትወጣ ነው «አዎ Âť ድምጿን ሳግ ደርሶ እንቅ አደረገው እጇን ጨበጥችው እና እየሮጠች ከእኛ እርቃ ሄደች ልቤ አብሯት ሄደ «ምን ሁና ነው መጥፎ ነገር ተናገርኩኝ እንዴ ?Âť መልስ አልሰጠዋትም አይኖቼ እሮዛሊን ጋር ናቸው በቆምኩበት ድርቅ ብዬ መታጠፊያው ጋር እስክትደርስ ተከተልኳት ÂŤ ሄይ ቃሲዮን ምን ሁነህ ነው Âť እጇን ፊቴ ላይ እያውለበለበች ብንን እንደማለት አልኩ ለምን ከአጠገቧ እንዳልሄድኩ ለምን አሁንም እሷ ጋር እንዳለሁ እኔም አላውቅም እራሴን ብጠይቅም መልስ አላገኝም «አይ ምንም የለም Âť አልኳት «እሺ እንሂዳ እዚሁ ቁመን ቀረን እኮ» እጄን አቆላልፋ ያዘችው በደመነፍስ ነው የምራመደው በድኔ እንጂ መንፈሴ አብሯት ሂዷል እንደምታወራ ይሰማኛል ግን መስማት ብቻ ሆነብኝ የምታወራው አልገባኝም አእምሮዬም ማመዛዘን አልቻለም እንዴት መልስ ልስጣት እሷ ይሄንን ያስተዋለች አይመስለኝም ማውራቷን ቀጥላለች «እንዴ በቃ ደረስን Âť አለችኝ የሚራመደውን እግሬን ለመግታት የያዘችውን እጄን ወደ ልሡ እየጎተተች ከሰመጥኩበት የሀሳብ መአበል መለሾ አልኩኝ እና ያለንበትን ቦታ ቃኘውት ባለፈው ምሽት የቆምበት ቦታ እንደሆነ በከፊል ያስታውቃል በቅርብ ርቀት ያለውን ቤት አየውት ÂŤ ቻው Âť ተንጠራርታ ከንፈሯን ከንፈሬ ላይ አሳረፈች ሙሉ ሰውነቴን ነዘረኝ እግሮቼ ድንዝዝ ሙሙት ሲሉ ተሰማኝ ከንፈሯን ከእኔ አላቃ ምንም ሳትል እየሮጠች ከእኔ እርቃ ወደ ቤቷ ገባች እኔ እንደተተከለ ፖል ቁሚያለው እግሬ መንቀሳቀስ አቅቶ ከእሷ ውጪ ማንንም ስሜ አላውቅም ውስጤ ቅዝቅዝ አለብኝ  ከዛሬ 9 አመት በፊት መጫወት ከፈለኩ ወይ እነሱ ግቢ ካልሆነም እሷ እኛ ግቢ ትመጣለች ምንም ብላት ምንም ታደርግልኛለች መጋባት ምን እንደሆነ መውደድ ምን እንደሆነ በማላውቅበት እድሜ ሳድግ እሷን ነው የማገባው እያልኩ አወራ ነበረ እናቷ ሁሌም ÂŤ የልጄ የወደፊት ባል Âť ሲሉኝ ውስጤን ደስ ይለኝ ነበር «ማማ እኔ መቼ ነው የማድገው እኔ ትልቅ ስሆን ሮዛሊንም ትልቅ ስትሆን እንጋባለን አይደል Âť የዘውትር ጥያቄዬ ነው ለእነሱ ልጅነት የመሰላቸው ለእኔ ግን እውነት የነበረ እነሱ ፈገግ ብለው የሚያልፉት ለእኔ ግን ትልቅ ህልም አንድ ሰው አድጌ ተምሬ ዶክተር እሆናለሁ እንደሚለው ትልቅ ህልም አድጌ ሮዛሊንን ማግባት ነበረ ። እኔ እንዲከፋኝ አትፈልግም ምን ሁኚ ምንም አድርጊ ብላት ፋቃደኛነች  ፊልም ላይ  ምንነታቸውን በግልፅ የማላውቃቸው ሰዎች ምን ምን እንዳደረጉ በውል ያልገቡኝ ነገራቶች አየው ሲሳሳሙ አየው ባል እና ሚስት እንደሆነ አውቃለሁ አላስፈቀድኳትም ሳምኳት አይኖቿ እስኪያብጡ አለቀሰች ለእናቷ ተናገረች ማማ ስትሰማ ሰውነቴ ሰንበር እስኪሆን ቆዳዬ እስኪላጥ ድረስ በደንብ ገረፈችኝ መቼም የማረሳው ቅጣት ነፍስ ካወኩ በእናቴ የተመታሁት ምት ከእሷ እና ከእናቴ ውጪ ማንንም ያልዳበሰው ከንፈሬ ዛሬ ግን አሁን በመጣች ሴት ተነካ በእጄ ከንፈሬን በተደጋጋሚ ጠረኩት ቀጥታ ወደ ሰፈር እየሮጥኩኝ ሄድኩኝ ወደ ቤት ሳይሆን ወደ እነ ሮዛሊን ቤት ምን ያህል ሀይል እንደተጠቀምኩ አላውቅም በሩን ደበደብኩት ዘበኛው በሩን ከመክፈቱ ግፍት አድርጌ ገባሁ ሳሎን የለችም መኝታ ቤቷ ደረጃውን በፍጥነት ወጥቼ የእሷ መኝታ ቤት ጋር ደረስኩኝ እቴቴ መኝታ ቤቷ ጋ ቁሟ ታንኳኳለች «ልጄ  ምን ሁና ነው እ ከሰው ተጣልታ ነው ምን ሁና ነው ንገረኝ እንጂ Âť እቴቴ የእኔን መምጣት ስታይ ጥያቄዎቿን አዥጎደጎደችብኝ የእሷን ጥያቄ ችላ ብዬ የመኝታ ቤቱ በር ላይ ተለጠፍኩ እያለቀሰች ነው ድምፃ ይሰማኛል ምን ብዬ እንደምጀምር ቃላት አጠሩኝ ÂŤ ሮዝ በሩን ክፈቺልኝ ቃሲዮን ነኝ Âť መልስ የለም በተደጋጋሚ በተለያዩ ቃላት ለመንኳት ምላሽ ላገኝ አልቻልኩም «ልጄ በቃ ተወት እናድርጋት እሷን ታውቃታለህ ግትር ነች በረድ ሲልላት እራሳው ትመጣለች Âť ÂŤ እሺ በቃ እቴቴ ደህና አምሹ እኔ ልሂድ Âť አልኩኝ እና ቤቱን ለቅቄ ወደ ቤት ሄድኩኝ ÂŤ ቃሲዮን ምን ሁነህ ነው Âť ማማ ነች ገና ከመግባቴ በጥያቄ ያጣደፈችኝ ÂŤ ምንም አልሆንኩም ማማ» «ሁነሀል እንጂ ልጄ  ፊትህ ልክ አይደለም ከሰው ጋር ተጣልተሀል እንዴ» «አይ ማማ ደህና ነኝ  እውነት ትንሽ ደክሞኝ ነው አሁን አረፍ ልበል» ሌሎች ጥያቄዎች ከመጠየቋ በፊት ከእሷ ለመሸሽ ነው /////// ሻወር ወስጄ መግሪብን ሰገድኩ እና ወደ ሳሎን ወረድኩኝ ማማ መጅሊስ ላይ ቁጭ ብላለች አጠገቧ ተቀመጥኩኝ «አበባዬ ደህና አይደለሽም እንዴ Âť «ደህና ነኝ Âť እንዲሁ እንድታቅፊኝ ስለፈለኩኝ ብቻ ነው እስሯ ሽጉጥ አልኩኝ ጥብቅ አድርጋ አቀፈችኝ ///// ለመተኛት ሞከርኩኝ አልጋዬ ላይ ብገላበጥም እንቅልፍ ሊወስደኝ አልቻለም 💬 እንዴ ነህ Âť ስልኬን እያየሁ ሳለ መልክት ገባልኝ እሷ ነች ውስጤ ሁለት ሙግት አለ ልመልስላት አልመልስላት ጣቶቼ ኪቦርዱ ላይ ያሉትን ፊደላት ነኩት በራሴ ሰውነት እጄን ማዘዝ አቃተኝ 💬 ደህና 💬 በቃ እኔ ካላወራውህ አንተ አታወራም» ፅፏ ያዘጋጀችው ይመስል በፍጥነት ገባልኝ ከሰአታት በፊት ያደረገችውን ነገር  ተራ ነገር ይመስል ምንም እንዳልተፈጠረ ሌላ ነገር ታወራለች 💬 ደህና እደሪ Âť ከእዚህች ልጅ ካልራኩኝ ጥሩ አይሆንም እሷ ለምንም ነገር መጨነቅ ማፈር ያልፈጠረባት ሰው ነች የሮዛሊን account አየውት online የለችም ከአልጋዬ ላይ ተነሳው እና ወደ ማማ ክፍል ሄድኩኝ «ማማ አንድ ነገር  አድርጊልኝ እንቢ እንዳትይኝ ሮዛሊንን ዛሬ አናድጃታለው እና አኩርፋለች አሁን አንቺ ደውለሽ ቃሲዮን ጋር ምን ሁናችሁ ነው እሱ ደብሮታል ምናምን ትያታለሽ ብቻ ድምጿን ነው መስማት የምፈልገው  እ ማሚ እሺ በይኝ በአላህ Âť ስልኳን ከጠረንጴዛው ላይ አንስቼ እጇ ላይ አስቀመጥኩት የንባብ መነፀሯን አወለቀችው ÂŤ አሀ ከእሷ ጋር ተጣልተህ ነው ፊትህን የጣልከው ደሞ እሷ አትጨክንም ታውቃታለህ ነገ መታ ባንተው ጥፋት ይቅርታ ስትልህ አገኛት የለ በምንስ ነው የተጣላችሁት Âť ÂŤ ማማ ጥያቄውን ትተሽ የምልሽን አድርጊልኝ እስኪ እናቴ ደውዪ Âť እየሳቀች ስልኳን ከፍታ ደወለች ከሁለት ጥሪ ቡሀላ ስልኩ ተነሳ «አሰላም አለይኩም ልጄ እንዴት አመሸሽ Âť «ዋለይኩም አሰላም ፕሮፔሰር  አልሀምዱሊላህ እንዴ ነሽ አንቺ» ÂŤ አልሀምዱሊላህ ልጄ ቃሲዮን ዛሬ ምንም ደህና አይደለም ምን ሁኖ ነው ምን ተፈጥሮ ነው ከሰው ጋር ተጣልቶ ነበረ እንዴ Âť ÂŤ እኔንጃ ፕሮፌሰር Âť

አንቺ! አትዋሺኝ አትደብቂኝ ደህና ነሽ ? ያዩኛል አይኖችሽ እንባ ሞልቶባቸው ይስቃሉ ጥርሶችሽ ህመምን ደብቀው ንገሪኝ! አትዋሺኝ! እያመመሽ አትሳቂ አይንሽ ይናገራል አንቺ ብትደብቂ የልብሽን ቁስል የውስጥሽን ህመም አጋሪኝ ውስጥሽን ልሰልል አንቺ ! አትደብቂኝ መኖር ግራ ገብቶሽ መንገዱ ጠፍቶብሽ ተስፋ እየቆረጥሽ እኔ ፊት ስትሆኚ አትሳቂ በጥርሶችሽ ጫፍ ህመም አትደብቂ ንገሪኝ ላዳምጥሽ ህመምሽን ልስማሽ ጆሮዬንም ልስጥሽ አትሳቂ እያመመሽ እኔን ተደገፊ አልቅሰሽ ይውጣልሽ ✍ አፍናን @rim_han

. ሀሳብ መጣልኝ ፃፍኩት ቤት ይምታ ይድፋ ፈጣሪ ይወቀው ስሜቱ ከናንተ ቃላቱ ከእኔ ሁኖ ግጥም ላስነብባችሁ ?😂 .

ÂŤ በስንት ፋለጋ እንዳገኘውህ አታውቅም Âť ተንጠራርታ ጉንጬን ሳመችኝ «ለምን ነበር የፈለግሽኝ Âť «እንዴ የዛን ቀን ያን ሁሉ ነገር ተነጋግረን እረሳውት ለማለት ነው Âť «ምኑን ነው የቱነጋገርነው ምኑን ነው የጋራ የረሳውትስ» «ውይ ወሬ መደጋገም በጣም ነው የምጠላው ለማንኛውም ክላስ እንግባ አሁን» «አልገባም እኔ አንቺ መግባት ትችያለሽ» «ምን ትሰራለህ እዚህ ብቻህን ከተያዝክ ደሞ ሰውዬው አይፋታህም ባለፈውም በፀቡ case file ይዞብሀል አሁን ደሞ ሌላ አጀንዳ አትፍጠርለት» «ችግር የለውም ግቢ አንቺ እኔ አልገባም እነ ኤልዮንም ይመጣሉ» «እነሱ ካሉ እሺ በቃ ስንወጣ በሩ ጋር ጠብቀኝ እሰከ ቤት ተሸኘኛለህ Âť ፈገግ ብላ መልሴን ሳትሰማው ሄደች ማማ ወዳ አይደለም አይን ያወጣ ዘመን እና ትውልድ እያለች የምትማረረው ትንሽ ቆይታ የፍቅር ጥያቄ ማቅረቧ አይቀርም በዚህ አያያዧ ነገሩ በከፊል አድርጋዋለች ፈገግ አልኩኝ ሁኔታዋ ምናቤ ላይ ውልብ ሲል «ብቻህን መሳቅ ጀመርክ» ዞር አልኩኝ ልክ እኔ በተቀመጥኩበት ፊት ለፊት ተቀመጠ ÂŤ አይ እንዲሁ የሆነ ነገር ትዝ ብሎኝ ነው Âť ÂŤ ኧረ ተው አሁን ሲዮራን ደረጃው ላይ አጊንቻት ነበረ እሷም ፍንድቅድቅ እያለች ነበረ አሁን ደሞ አንተ ሳምካት እንዴ?Âť «ኧረ ይቅር ይበልህ እንዴት እንደዚህ አይነት ነገር ታስባለህ ግን ልጅቷ ጤነኛ ነቻ Âť ÂŤ ምነው አትመስልም ?Âť ÂŤ እኔ ጤነኛ እንዳልሆነች ነው የታየኝ እኔ እስከማውቀው ሴት ልጅ ተሽኮርማሚ እንጂ አሽኮርማሚ ስትሆን አላውቅም ይቺ መለስተኛ ደንበኛ ጀንጃኝ እኔ ማለት ያለብኝ ቃላት ከእሷ እሰማዋለሁ Âť «እንግዲህ አንተ እንደ ኤሊ ስትንቀረፈፍ እሷ ፈጠነችብህ» ÂŤ ቀልድ አንተ ምን አለብህ አሁን ምን ያህል ደቂቃ ይቀራል Âť ÂŤ የምሬን ነው ቀልጠፍጠፍ ብለህ ከእጅህ አትጥላትም እና ተንቀርፈፍ እኔ ምነው አንተን ባደረገኝ እንጃ ትንሽ ደቂቃዎች ነው የሚቀሩን Âť ÂŤ እኔን ብትሆን ምን ልታደርግ ነበረ Âť በመገረም እይታ እያየሁት ጠየኩት ÂŤ ተው እንጂ ቃሲዮን ምን ላደርግ እችላለሁ ስታስበው Âť ÂŤ አንተ ጉደኛ ነህ የምር ኤልሮን ግን ሰሞኑን ምነው ራቅ ራቅ አለ ከእኛ Âť «ከሚስቱ ጋር ነው ቅድሚያ ለሚስት አይደል ነገሩስ Âť ÂŤ አንተ ታድያ እዚህ ምን ትሰራለህ Âť ÂŤ ብቻህን እንዳትሆን አስቤ ነዋ» «ኧረ ባክህ ለእኔ አስበህ ነው አላቅህም እንዴ Âť «እሺ በቃ እማራለሁ ምናምን ብላ ጓ ስትል ጥያት መጣሁ ካልተማርኩ እሞታለሁ ትላለች እንዴ የተማረም ያልተማረም ይኸው ተመሳሳይ ውጤት ነው የሚያመጣው ማሽቃበጥ ካልሆነ በስተቀር Âť የደውል ድምፅ ሰማን ÂŤ በል ተነስ እንሂድ ሮዛሊን ካጣችኝ ትበሳጭብኛለች Âť ተያይዘን ወደ መውጫው በር ሄድን ተማሪዎቹ ገና እየወረዱ ነበረ  ከሩቅ አየዋት ቀይ ፊቷ ለማኩረፍ ፈልጎ አላኮረፈም በዛን ቀን ነገር እስካሁን ተናዳብኛለች ለመገላመጥ እየሞከረች ሁለታችንንም አልፋን ሄደች ÂŤ ቃሲዮን ግን ቆይ ይቺ ልጅ ምን አድርጊያት ነው ሁሌ በዚህ አይነት አይን የምታየኝ በስህተት እንኳን አናግሪያት አላውቅ ሳንተዋወቅ ጥላቻ ወይስ ከወንድሜ ጋር ተቀያይማለች Âť ÂŤ በእኔ ስለተናደደችብኝ ነው እንጂ እሷን አስደብርሀት እራሱ አትጠላህም ለማንኛውም ልሂድ እንዲሁም ላባብላት ነው ገና ቻው Âť ÂŤ ኧረ ባክህ የራስህ ሰው ሲመጣ ጥለኸኝ ሄድክ ችግር የለውም Âť ባልሰማ ጥዬው ከጊቢው ወጣሁ በጀርባዋ የራሷን ቦርሳ በፊቷ የእኔን ደብተሮች ደረቷ ላይ ለጥፍ ይዛቸዋለች ÂŤ መሄድ እንችላለን Âť መልስ አልሰጠችኝም ዝም ብላ ከጎኔ ትራመዳለች ÂŤ ዛሬ እኛ ቤት አናመሽም አብረን Âť አሁንም መልስ አልመለሰችልኝም እጆቿ ላይ ያለውን ደብተር ምንጥቅ አደረኳት  ÂŤ እንደውም ብቻዬን ነው የምሄደው እሺ Âť አልኳት ኩስትርትር ብዬ ከፊት ለፊቷ ቀደም ቀደም እያልኩኝ «እንዴ ካንተም ብሶ ልታኮርፍ ነው እንዴ ደሞ Âť ከእኔ እርምጃ እኩል መራመድ አቅቷት አየሮጠች ነው ከዃላዬ የምትጮኸው ሰዎች ትኩረቲቸው ወደ እኛ ሆነ በዚህ መንገድ ካልሆነ ልትታረቀኝ አትችልም ÂŤ እሺ ይቅርታ በቃ Âť እርምጃዬን ገታ አድርጌ ቆምኩኝ ሀሳቤ ተሳክቷል ወደ እሷ ዞር ብዬ ደብተሬን እንድትይዘው ደግሜ ሰጠዋት« እንደ ህፃን አታኩርፊ ይቅርታ ስጠይቅሽ እሺ ማለት አለብሽ Âť ፈገግ ብላ መስማማቷን ገለፀችልኝ ÂŤ ዛሬ ለምን ክላስ አልገባህም Âť ÂŤ ደብሮኝ Âť ÂŤ መች ነው ግን ደስ የሚልህ Âť ÂŤ ትምህርት ሳቆም Âť ÂŤ ገና እየጀመርክ ምኑን ነው የምታቆመው» ÂŤ ትምህርቱን Âť «ኧረ በስርአት መልስልኝ Âť ÂŤ ምን ተማራችሁ Âť ÂŤ ትምህርት Âť ÂŤ ኧረ ብድር መሆኑ ነው እንደውም አላወራም አታውሪ አርፈሽ ሂጂ Âť በእጄ ወደ ፊት ገፈተርኳት ÂŤ አንተ ግን ፕሮፌሰር ደስ አይሉም በተለይ ዛሬ ያነሱት ሀሳብ Âť ÂŤ አንቺ ልጅ ይሄን ሼባ ወደድሽው እንዴ Âť ÂŤ ሼባ አትበል ፕሮፔሰር ነው ሲቀጥል አንተ አልወደድከውም እንዴ Âť ÂŤ ያው ነው ሼባ ነው ወንድ እኮ ነኝ እንዴት ወንድን እወዳለሁ Âť ÂŤ ቃሲዮን Âť የስሜ ጥሪ ሁለታችንንም  ወደ ዃላ አዞረን ይቀጥላል .     .    . @rim_han

 .                 ╔═══ ೋ 𔘓 ೋ  ═══╗                               ኦርቶዶክሳዊቷ                          ደራሲ  አፍናን ሩማን »                   ╚═══ ೋ 𔘓 ೋ ═══╝ .                       ━─━─  𓍯  ─━─━                              ραɾƚ    0:05                         ━─━─  𓍯  ━─━─ «በቅድሚያ እናንተ የተማራችሁ ሰዎች አይደላችሁ እንዴ ማንሾካሾክ ምንድነው በስርአት እጃችሁን አውጥታችሁ ሀሳባችሁን መግለፀ ትችላላችሁ ከሴቶቹ ልጀምር » ከሁሉም ተማሪ በፊት እጇን አወጣች «እሺ ሲጳራ ሀሳብሽን ተናገሪ» አላት «እሺ ፕሮፌሰር በምንም አይነት ሁኔታ ተጎጂዋ ልትቀጣ አትችልም  በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ አንፃር የወንጀል ተጠያቂነት የሚኖረው ወንጀሉን በፈፀመው አካል ላይ ብቻ ነው ተጎጂዋን በትንሹ እንኳን መቅጣት የሚለው ሀሳብ በህግ ፊት ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የሌለው እና የተጎጂዋን መብት የሚጥስ ነው በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ አስገድዶ መድፈር ከባድ ወንጀል ነው ስለዚህ ደፋሪው ነው መቀጣት ያለበት ነው የምለው » ብላ ወንበሯ ላይ ተቀመጠች « እሺ ሌላ በዚህ ጉዳይ ሀሳብ የሚያቀርብ ሰው አለ ከወንዶች እስኪ ማዚን የሆነ ነገር በለን » ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ አይኖቹን ወደ መምህሩ ጣል አደረገ «የኔ ሀሳብ ደፋሪው አጥፊ ነው ነገር ግን ሴቶችም እራሳቸውን መጠበቅ እና ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው ባይ ነኝ » አለ እና ተቀመጠ « መምህር እኔ እሱ ሀሳብ ላይ ቅሬታ አለኝ » አለች እጇን አውጥታ «ለአንቺ ሁለተኛ እድል አልሰጥም ሌሎች ተማሪዎችን ምን ትላላችሁ በዚሁ ዙሪያ »ሁሉም ተማሪዎች ዝምታን መረጡ « እሺ ሲጳራ ድጋሜ እድል ልስጥሽ » ከተቀመጠችበት ተነሳች « ጥያቄው በራሱ አከራካሪ ሊሆን አይችልም አንዲት ሴት ስለተደፈረች እንዴት ልትቀጣ ትችላለች? ቆንጆ ስለሆነች ወይም  አለባበሷ ወይም አካሄዷ ምክንያት ሆኗል ብሎ ማሰብ ተጎጂዋን እንደገና መበደል ነው ቅጣቱ 100% በደፋሪው ላይ ብቻ ማረፍ አለበት ለሴቷ ደግሞ የህክምና የስነ-ልቦና እና የህግ ድጋፍ ሊደረግላት ይገባል ምንም አይነት ምክንያት ለደፋሪው መከላከያ ሊሆን አይችልም ወንጀል ወንጀል ነው የተደፈረችዋ ሴት ምንም አይነት ጥፋት የለባትም » በንግግሮቿ መሀል በጣም ስሜታዊ እየሆነች ነው «እሺ ለሁለታችሁ አመሰግናለሁ ሌሎቻችሁም አልተናገራችሁትም እንጂ በውስጣችሁ ሀሳቦች አሉ እኔ አንድ ነገር ልናገር ይህን ጥያቄ ያቀረብኩላችሁ በቀላሉ ወንጀለኛው ይቀጣ የሚል የተለመደ ምላሽ እንድትሰጡኝ አይደለም የጉዳዩን ስነ-ልቦናዊ ማህበራዊ እና ተፈጥሯዊ እውነታዎች በጥልቀት እንድንመረምር  ስለፈለኩ በመጀመሪያ ደረጃ በህግ መብቶች እና ተፈጥሮአዊ ስነ-ልቦና መካከል ያለውን ልዩነት መረዳት አለባችሁ በህግ ፊት ወንጀል ፈጻሚው ሙሉ በሙሉ ተጠያቂ ነው በዚህ ላይ ምንም ጥርጥር የለውም  ግን በህብረተሰብ ጥናት እና በወንጀል መከላከያ  እይታ የአንድ ወንጀል መከሰት ከአካባቢ ሁኔታዎች እና ከቀስቃሽ ምክንያቶች ተለይቶ አይታይም ዛሬ በከተማችን የምናየው ሁኔታ ምን ይመስላል? ዘመናዊነት በሚል ስም የሚታዩ የሰውን ትኩረት እና ስሜት በከፍተኛ ደረጃ የሚስቡ የአለባበስ ዘይቤዎች እየተስፋፉ መሆናቸውን ለእናንተ እኔ አልነግራችሁም ሴቶቻችን እርቃን ሊባል በሚችል ደረጃ ነው የሚለብሱት ለበሰች ሳይሆን አለበሰችም የሚያስብል አለባበስ ነው የሚለብሱት  ወንዶች ደግሞ በተፈጥሮአቸው ለይታ በማነቃቃት (visual stimulation) የሚነሱ የስሜት እና የሆርሞን ግፊት የሚበልጥባቸው ፍጡራን ናቸው እኔም ወንድ ነኝ ነን በተለይም በታዳጊነት እና በወጣትነት እድሜ ላይ ያሉ ወንዶች ስሜታቸውን የመግታት እና የማመዛዘን አቅማቸው ገና ሙሉ በሙሉ ያላደገ ሊሆን ይችላል አንድ ሰው እሳት አጠገብ የሚቃጠል ነገር አስቀምጦ እሳቱ ለምን አቃጠለው? ብሎ ቢጠይቅ እሳቱ ማቃጠሉ ተፈጥሮው ነው እሳቱን አጥፊ ልንለው እንችላለን ነገር ግን የሚቃጠለውን ነገር እሳቱ አጠገብ ያቀረበው አካልም ጥንቃቄ አላደረገም ማለት አይቻልም? ስለዚህ  የአንድ ማህበረሰብ ሰላም እና ደህንነት የሚጠበቀው ሁለቱም ወገኖች ኃላፊነታቸውን ሲወጡ ነው ወንዶች ስሜታቸውን መግታት እና የሰውን መብት ማክበር እንዳለባቸው ሁሉ ሴቶችም የማህበረሰቡን ስነ-ልቦና እና የተፈጥሮ ህግጋትን ያገናዘበ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው ባይነኝ  ተጎጂዋን መቅጣት ማለት ወንጀለኛ ማድረግ ማለት ሳይሆን ለአደጋ መጋለጥን የሚፈጥሩ ሁኔታዎችን ማስወገድ መቻል ማዚን በጨረፍታ ገልፆታል ሲጳራ ተረዳሽኝ » አላት ወደ እሷ አይኖቹን ልኮ « አይ  ምንም አላሳመነኝም ሴት ልጅ በአለባበሷም ሆነ በምታደርገው ነገር ተጎጂ ትሁን እያልክ ነው » «እኔ እንደዛ አላልኩም ይህንን ወንጀል በከፊል  ለማስቅረት መደረግ ያለባቸውን ነጥቦች እያነሳውላችሁ ነው  የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነሽ አይደል  መጽሐፍ ቅዱስ በ1ኛ ጢሞቴዎስ 2፡9 ላይ ሴቶች 'በማፈርና በመጠንፈን' የተገባ ልብስ እንዲለብሱ ያዝዛል ይህን ታውቂያለሽ ይህንን ትታ ግን ገላዋን በመግለጥ ለሌሎች ወንዶች የስሜት መነሳት ምክንያት የምትሆን ሴት ደግሞ በማቴዎስ 18፡7 'ማሰናከያ ከሚመጣበት ለዚያ ሰው ወዮለት' በሚለው መለኮታዊ ማስጠንቀቂያ ስር ትወድቃለች ይላል  ምክንያቱም በራሷ አለባበስ ምክንያት ሌላው ሰው ወደ ኃጢአት እንዲያይ እና እንዲሳሳት ማሰናከያ ሆናለችና አሁን የእኔ ሀሳብ ግልፅ አልሆነልሽም » አንገቷን በማንቀሳቀስ መስማማቷን ገለፀችለት « ቀለል ያለ ምሳሌ ልስጣችሁ አሁን የምናገርውን ነገር ከሀይማኖት አንፃር አታነፃፅሩት እውነታውን ከሚከወነው አንፃር ገምግሙት በእስልምና እምነት አስተምህሮት وَقُل لِّلْمُؤْمِنَاتِ وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ ۖ وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا لِبُعُولَتِهِنَّ أَوْ آبَائِهِنَّ ሱረቱ አን-ኑር (24:31) ለምእመናትም ንገራቸው፡  መሸፈኛዎቻቸውን በደረት አንገቶቻቸው ላይ ይጣሉ ገላቸውንም ለባሎቻቸው ወይም ለአባቶቻቸው... ቢሆን እንጂ አይግለጡ ይህን ህግ ሴት የሙስሊም እምነት ተከታች እህቶቻችን  በትክክል ተግባራዊ ያደርጋሉ አሁን ዘመናዊነት ካጠቃቸው በየሚዲያው ከሚገላለጡት ሴቶች ውጪ እና እኝህ ሙስሊም ሴቶች አይደለም ለሌላ አላማ ይቅር እና በመንገድ ላይ እራሱ ወንዶች ደፍረው ለለከፋ ቃላት ሲሰነዝሩ  አስተውላችሁ ታውቃላችሁ ? እምነት እያመዛዘንኩ ወይም ስብከት አይምሰላችሁ  የእኔ ተማሪ እስከሆናችሁ ድረስ ሚዛናዊ እና ሰፋ ያለ ግንዛቤ አረዳድ እንዲኖራችሁ ነው የምፈልገው ብሄር ሀይማኖት ከእኔ አይበልጥም ያንተ ያንተ ልክ አይደለም የሚል ነገር የለም ሁላችሁም ኢትዮጵያዊ ናችሁ እምነታችሁን በልባችሁ ማንም የማንንም በክፉ ማንሳትም ሆነ ማንቋሸሽ አይቻልም ዘመናዊ ነን ካላችሁ መከባበር መቻል አለባችሁ ማወቅ አይጎዳም የአንዱን ባህል ሀይማኖት  ብዙ አወራውባችሁ መሰለኝ ይቅርታ እንግዲህ ነገ እንገናኛለን  የሰጠዋችሁን ተዘጋጅታችሁ ኑ መልካም እረፍት » ከተቀመጠበት ተነሳ እና ይዞት የመጣውን ንብረት ይዞ ከክፍሉ ወጣ ////////

. ክፍል አምስት ከተለቀቅ ቡሀላ በደንብ አንብባችሁት እናንተም የራሳችሁን ሀሳብ ታስቀምጡልኛላችሁ ‼️ .

💬 ቤቷ ድረስ ሸኝተኻት ግን ሳትሰናበታት የሄድካት ልጅ Âť ቅኔዋ ገብቶኛል 💬 እንዴት accounten አገኘሽው 💬 ከኤልዮን ተቀብዬ ነው 💬 ለማንኛው በሰላም ገብቻለሁኝ ደህና እደሪ Âť የሚል ቴክስት ልኬ ስልኬን አጥፍቼ ተኛውኝ /////// እሁድ እሁድ ሁሌም አባቴ እና እናቴ የራሳቸውን ጊዜ የሚያሳልፉበት ቀን ነው ምን አልባት በታላቅ ወንድሜ እድሜ ቢታሰብ ልሹ 23 አመት የትዳር ቆይታ አላቸው ግን አሁንም ድረስ እንደ አዲስ ፍቅረኛሞች ነው ነገር ስራቸው የእነሱን የፍቅር የትዳር ህይወት ልፃፍ ብል አንድ አራት ምርጥ መፀሀፍ ይወጣዋል እሁድ የእረፍት ጊዜያቸው ነው ሁለቱም ቤት ውስጥ አብረው ያሳልፋሉ ወይ ባባ ይዟት ይወጣል ድሮ ድሮ እቀና ነበረ በእናቴ አሁን ሳስበው ግን ሰው ቢሰማ የሚስቅብኝ ይመስለኛል ሴት ልጅ አባቷን ትወዳለች የሚባለው ነገር  እውነት ይመስለኛል በተለይ በእኔ በእናቴ እስከመቅናት ድረስ high school ስገባ ነው ከእናት እና አባቴ መኝታ ቤት የወጣሁት እስከ እዛ እድሜ ድረስ ግን ከእባቴ ጋር ነው የምተኛው ብዬ ለያዥ ለገናዥ አስቸግሬ ነበረ በእናቴም የምቀናው አባቴ ጋር ስለምትተኛ ነው ብቻ ምን አለፋችሁ የአባቴ ነገር ሞቴ ነው እናቴንም በጣም ነው የምወዳት ግን .. በቃ ቃል የለኝም እቴቴ እንደሁሌው ሁሉን ነገር አሰነዳድታ የእረፍት ቀኗ ስለሆነ ሂዳለች እኔም እቤት አልውልም ወይ እነ ፕሮፔሰር ጋር ወይ ደሞ አንዲት የልብ ጓደኛ አለችኝ እነሱ ጋር ነው የማሳልፈው ዛሬ ግን እንዲሁ ደብሮኛል ከክፍሌ አልወጣሁም ለወደፊት ትምህርቱን ቀለል ያደርጥልኛል ብዬ ያሰብኩትን ነገራቶች በገረፍታ እያየዋቸው ነው አጠር አጠር ያሉ ኖትም እያወጣሁ ነው በነገራችን ላይ አዲሱን አስተማሪያችን ፕሮፌሰር ያዶትን በድጋሜ እስከማገኛቸው ድረስ ቸኩያለሁኝ ቀኑ አልመሽ ነው ያለኝ ከእቤት ስላልወጣው ይሁን እንጃ ብቻ ከአሱር ቡሀላ ደርስ አለብኝ  ለእሱ እየተዘጋጀው ነው ድሮ ድሮ ከወንድሜ እና ከቃሲዮን ጋር ነበረ የምሄደው  አሁንም ግን ሁለቱም ሄዱ   ብቻዬን ነው የምሄደው /////// ÂŤ ይቅርታ አታደርግሊኝም Âť አልጋዋ ጫፍ ላይ ተቀምጩ ለጥፋቴ ይቅርታ እየጠየኩኝ ነው ግን ከዝምታ ውጪ ምንም መልስ አሰጠኝም እንዲህ የምትሆነው ደሞ በጣም ስትናደድ ነው ከዚህ በላይ ልጫናት አልፈለኩም ከክፍሏ ወጣው ዛሬ ሙሉ ቀን ከእቤት አልወጣሁም ይባስ እሷን ላለማናደድ ሰአቱ መሽቷል እንደ ዛሬ እቤት የዋልኩበትን ቀን አላስታውስም  ግቢውን የቤቱ ክፍሎችን ሳይቀር ነው እየተዘዋወርኩ ያየውት እንደ ምንም ግን መሸ ÂŤ ማማ አሁንም አታዋሪኝም Âť ክፍሏ በር ላይ ቁሜ እየተለሳለስኩ ነው «ና እስኪ ወደ እኔ Âť ደስ እያለኝ ወደ ውስጥ ገባሁኝ የምታነበውን መፀሀፍ ዘግታ አስቀመጠችው የንባብ መነፀሯንም እንደዛው ÂŤ ትንሽ አበሳጭተኸኝ ነው እንጂ እንዴት አንድ ብቸኛ ልጄ ላይ እጨክናለሁ ብለህ ታስባለህ ግን ልጄ መሾመር እየሳትክ ነው አሁን አንተ 18 አመት ሊሞላህ ነው እኮ እንደ ልጅነትህ ገርፌ ወይ ተቆጥቼ ከመጥፎ ነገር ልመልስህ አልችልም አሁን አፍላ እድሜ ላይ ነህ ይህ እድሜ ደሞ ወይ ያጠፋሀል ወይ ያለመልምሀል እንደ አጠቃቀምህ ነው ብዙ ጫናዎችን ተቋቁመህ ካላለፍከው እንዳትነሳ ሁነህ ስብርብር ብለህ ትቀራለህ እኔ የምፈራው ይሄን ነው ልጄ አደራህን እንደው ራስህን ጠብቅ ÂŤ እሺ እናቴ እጠነቀቃለሁኝ አትጭነቂ አንቺ Âť እጇን ሳብ አድርጌ ሳምኩት እሷም ግንባሬን ሳመችኝ ÂŤ ባባ አይመጣም እንዴ ዛሬ» «እኔ ምንአውቄለት ብለህ ነው» ሾለ እሱ ብዙም ማውራት ደስ አይላትም ልጠይቃት ብዙ ጊዜ አስቤ ከአፌ የመለስኩበት ቀናት አያሌ ናቸው ÂŤ እሺ በቃ ደህና እደሪልኝ  Âť ክፍሏን ለቅቄ ወጣሁኝ ቀጥታ ወደ ክፍሌ ስልኬን አንስቼ አየውት  ምንም መልእክት የለም ሳትናደድብኝ አልቀረችም ብትናደድስ አንድ ቀን ላወኳት ሴት ምን አስጨነቀኝ ////// አንድ ቀን በነበረው ውሎ የተማሪዎቹን ስነ ልቦና በደንብ ተረድቷል ቀላል ቢመስሉም ጥልቅ ግንዛቤ ያላቸው እንደሆኑ አጠር ያለው ጋውኑን ለበሰ እና የሚያስፈለግውን ነገር ይዞ ብቸኛ የሆነ ው የሚያስተምርበት ክፍል ሄደ ÂŤ እንደምን አደራችሁ Âť አለ ሁሉንም በአይኑ እየቃኘ በአንድነት ሁሉም ምላሽ ሰጡት ÂŤ ቅዳሜ እና እሁድ እንዴት አለፈ በምን አለፈ ሲጳራ ቀጥይ ቅዳሜሽን በምን አሳለፍሽ Âť ግራ እየተጋባች ተመለከተችው ÂŤ ቅድሚያ ከተቀመጥሽበት ተነሺ ከዛ ጊዜሽን በምን እንዳሳለፍሽ ተናገሪ Âť ከተቀመጠችበት ተነሳች ÂŤ እሺ መምህር ቅዳሜ ያው ጠዋት ተነሳው ከዛ ቁርስ በላው ጠዋት ላይ ቤተ ክርስቲያን ከእነ ማም ጋር ሄድኩኝ ከዛ በቃ ጓደኞቼ ጋር ነው ያሳለፍኩት እሁድም በተመሳሳይ Âť ÂŤ አመሰግናለሁ ሲጳራ ሌላ  ለየት ባለ ነገር ቅዳሜ እና እሁዱን ያሳለፈ ሰው አለ ካለ መናገር ይቻላል Âť ሁሉም ተማሪውች ዝም አሉ ÂŤ እሺ አላስጨንቃችሁም ምን አልባት ከምንማረው ትምህርት ጋር ምን ያገናኘዋል እያላችሁ ነው ልክ ናችሁ አያገናኘውም ግን ጊዜ ውድ ነገር ነው ጊዜያችሁ በምን አይነት ነገር እያሳለፋችሁት እንዳላችሁ ቆም ብላችሁ እንድታስብት ስለፈለኩ ነው ለጥሩ ነገር ጥቅም ላለው ነገር አውዬዋለሁ ወይስ ባክኗል የሚለውን እንድታገናዝቡት ነው ሁሌ ሰኞ ስንገናኝ ይህ ነው ጥያቄዬ ሁላችሁም ይደርሳችዃል ጥያቄው Âť ወደ ቦርዱ ሂዶ History ብሎ እንዲሁም ርእሱን ፃፈ ÂŤ እንግዲህ ይህን አመት ከእኔ ጋር ነው የምትዘልቁት ብሄራዊ ፈተና ወሳጅ እንደመሆናችሁ መጠን የተቻለኝን አደርጋለሁኝ የመማር ማስተማር ሂደቴ  የሚሆነው እኔ መንገድ ብቻ ነው የማሳያችሁ እንጂ ሁላችሁ ለራሳችሁ መምህር ናችሁ እራስን በራስ ማስተማር ማለት ነው በእያንዳንዱ በምንማረው ርእስ ላይ ሁላችሁ እጥር ምጥን አድርጋችሁ ትዘጋጃላችሁ ሽምደዳ አልፈልግም  መረዳት ጥያቄዎች ከተለያዩ አንግል ብትጠየቁ መመለሾ የምትችሉበት መረዳት ነው የምፈልገው እንዲሁም ካለን 45 ደቂቃ 10 ደቂቃውን ከትምህርት ውጪ ባሉ መወያያ ጥያቄዎች ላይ ነው የምንወያየው የእኔ ልጆች ስኮፓችሁ ጠባብ እንዲሁም  አልፈልግም እንደ መንደር ወይ እንደ ሰፈር አሊያም እንደ ሀገር እንዲሆን አይደለም አስተሳሰባችሁ የምፈልገው ከአራቱም አቅጣጫ እንደ አለም እንድታመዛዝኑ ነው የምፈልገው የተረዳችሁኝ ይመስለኛል የመጀመሪያው lesson የሚሆነው capitalism  ይህን ርእስ ለእናንተ አዲስ አይመስለኝም በአዲሱ መፀሀፍ ከተማራችሁ 10ኛ ክፍል በደንብ ተወያይታችዃል  አሁን ምን ታደርጉልኛላችሁ  ይህን ርእስ በደንብ ታስሱ እና ወደ ራሳችሁ ታስገቡታላችሁ በቃ በደንብ መረዳት ከዛ ነገ ስንገናኝ ማንን እንደሆነ አላውቅም አስነስቼ ማብራሪያ እጠይቃለሁኝ በደንብ ግልፅ አድርጎ ያብራራልኛል ከዛ እኔ short note ሰጥቼ ተጨማሪ ግልፅ ማብራሪያ አደርግላችዃለሁ ማለት ነው እና ሰነፍ ተማሪ አልወድም እንደ ኢትዮጵያ ያለ ታዳጊ ሀገር ላይ ተቀምጣችሁ ሰነፍ መሆን በጣም ከባድ ነው ሞክሩ የተቻላችሁን አድርጉ የግማሽ አመቱን ትምህርት ነገ እንጀምራለን ማለት ነው Âť ፊት ለፊት ያለውን ወንበር ሳብ አድርጎ ለሁሉም እይታ ግልፅ በሆነው በኩል ተቀመጠ ÂŤ አንድ ሀሳብ ላንሳላችሁ ዛሬ ምን መሰላችሁ አንዲት ቆንጆ ወጣት ልጅ ተደፈረች የሚል ዜና ተነገራችሁ የእናንተ ፍርድ ምንድነው ደፋሪው ብቻ ነው መቀጣት ያለበት ወይስ ተደፋሪዋም ከእሱ አነስ ያለ ቅጣት ይገባታል ምን ትላላችሁ ?»ሁሉም ተማሪ አንሾካሾከ ይቀጥላል .    .   . @rim_han .

 .                 ╔═══ ೋ 𔘓 ೋ  ═══╗                               ኦርቶዶክሳዊቷ                          ደራሲ  አፍናን ሩማን »                   ╚═══ ೋ 𔘓 ೋ ═══╝ .                       ━─━─  𓍯  ─━─━                              ραɾƚ    0:04                         ━─━─  𓍯  ━─━─ ስልኩ ተቋረጠ ደግሜ ብደውልም ጭራሽ ማግኘት አይችሉም አለኝ ስልኬን ይዤ ወደ ሳሎን ወረድኩኝ « ምን አለሽ ልጄ » ፕሮፌሰር ነች ጠያቂዋ ምን መመለስ አለብኝ የትስ ነው ብዬ ልናገር ዝምታዬ ሲረዝምባቸው ሁሉም ወደ እኔ አዩ« ስልኩ ተነስቶ ነበረ ግን ድምፅ ስለነበረ አልተሳማማንም ከዛ ስልኩ ተዘጋ ቻርጅ ጨርሶ ይሆናል መሰለኝ » ምኑን ከምኑ እንዳወራሁት አላውቅም ግን ያልኩት ባይዋጥላቸውም አምነውኛል ወደ ማእዱ ተመለሱ እኔም ተቀላቀልኳቸው /////// ኤልሮን እና ኤልዮን ከሴቶቻቸው ጋር በተቃራኒ አቅጣጫ ተቀምጠዋል «ወንድ ልጅ ቆንጆ ነው አይባልም ብዬም አላቅም እላለሁም ብዬ አስቤ አላውቅም ያንተ ግን አይን ያወጣ ቁንጅና ነው ያለህ ከሴት ውንድንም አይን ጣልየሚያደርግብህ መሆኑን ምስክር ነኝ  አለማድነቅ አልቻልኩም »ከፈገግታዋ እኩል ቃላቶቿን ሰነዘረች ከፊት ለፊቴ እግሮቿን አነባብራ ስፕራይት እየተጎነጨች ነው « አመሰግናለሁ » ብቻ የሚል ምላሽ ሰጠዋት «ኤልሮን እና ኤልዮን  ጋር በጓደኝነት ብዙ ጊዜ ሆናችሁ እንዴ » «አዎ 6 አመታት ያላነሰ » «መልሶችህ ሁሉ ቁጥብ ናቸው እንደ እዚህ አይነት ወንድም ደሞ type ነው ፍቅረኛ አለህ?» ከቅልጥፍናዋ ፍጥነቷ ሴትነቷ ሳይገድባት በፈጣጣው መንጎፋጠጥ በጣም አስገረመኝ « የፈጠንሽ አልመሰለሽም ? » ወንድነቴን የተጋፋችን ስለመሰለኝ ነው ድምፅ የሌለው ከንፈር ገለጥ አድርጎ ጥርሶቿን የማሳየት ያህል ሳቀች «መግደርደር መቅለስለስ ባህል ወግ ልማድ የሚሉት የሀገራችን ባህል በከፊል እኔ ጋር ተፈፃሚነት የለባቸውም ላመንኩበት ነገር ማግኘት ለፈለኩት ነገር መቅለስለስ አይመቸኝም በግልፅ መጠየቅ » «የምትገርሚ ሰው ነሽ » « ምን አልባት ... ግን ጥያቄዬን አልመለስክልኝ » « የለኝም » ፈገግ አለች ። « ጓደኛሞች መሆን እንችላለን ማለት ነው » ከአይኖቿ የሚመነጨው ብርሀን በደበዘዘ ብርሀን ውስጥ ሁነን እራሱ ውስጥ ድረስ ሰርስረው የመግባት አቅም አላቸው « ምን አይነት ጓደኝነት ብዙ አይነት ጓደኝነት አለ እኮ » ጠረንጴዛው ላይ ያለውን ብርጭቆ አንስቼ ተጎነጨው «የፈለከው ሁሉም ለእኔ ይመቸኛል more ደሞ ፍቅረኛሞች ብንሆን አየህ ያንተም የእኔ ጓደኞች በዙሪያችን ያሉ ሰዎች  ጥንድ ናቸው so አብረን ብንሆን » በዚህ ልክ ፈጣጣ ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም high school በገባሁበት አመት ሁሉንም አይቸዋለሁ ፍቅረኛም ነበረኝ ግን ሙስሊም ሴቶች ጋር ነበር relation ውስጥ የምገባው « ብዙ የማያመሳስሉን ነገራቶች እንዳሉ አልታየሽም ? » ጉሮሯዋን ጠራረገች  ልዝብ ልስልስ ባለ ተሰረቅራቂ ድምጿ ከምሽቱ ፀዳል ጋር ፍዝዝ የሚያደርግ ቅላፄ « ቴዲ ምን ሲል አቀነቀነ መሰለህ » ተዋዶ ያለበት  እስላም ክርስቲያኑ ተዘነጋሽ እንዴ  ኢትዮጵያ መሆኑ አንቺም በሀይማኖትሽ  እኔም በሀይማኖቴ መኖር እንችላለን  አይጠበንም ቤቴ « ልክ አይመስልህም ታድያ » አለች ፈገግ አልኩ ለጥያቄዋ መልስ ከመስጠት ይልቅ ወደ ሌላ ርእስ ገባሁ « ሰአቱ እየሄደ ነው እቤት ምንም አትባሉም እንዴ » « አዎ ልክ ብለኻል ሰአቱ ሂዷ እንጥራቸው እና እንውጣ » አለችኝ ከተቀመጠችበት ተነሳች ለጓደኞቿ ምን እንዳለቻቸው አላውቅም እነሱ ጋር ደርሳ ወደ እኔ ተመለሰች « እንውጣ በቃ » አይኖቼ ወደ እነ ኤልዮን አዞርኩት «እነሱ እንቆያለን ብለዋል አንተ ወደ እቤት ሸኘኝ እና ከፈለከ ትመለሳለህ » ቀደም ብላኝ ወጣች ሳላንገራግር ተከተልኳት የመንገድ ዳር መብራቶች ጨለማውን ገፈው ብርሀን ሰተውታል ቀዝቀዝ ያለ ንፋስ መንገዱ ላይ ሽው ይላል እጄን የለበስኩት ኪስ ውስጥ ከትቼ ጎን ለጎን ዝግ ባለ መልኩ እየተራመድን ነው ቀኝ እጇን በእጄ መሀል አሳልፋ ያዘችኝ ዞር ብዬ አየዋት ምንም አልመሰላትም « ስለ ፍቅር ግን ምን ታስባለህ ማለቴ ከዚህ በፊት ምንም ፍቅረኛ ሳይኖርህ ይቀራል ብዬ አላስብም » « ፍቅር ያው ፍቅር ነው የሁለት ፆታዎች ጥምረት ፍቅረኛ ላልሽው ደሞ ነበረችኝ ግን ተለያይተናል » « ኦ ይቅርታ በጣም ግን ለምን ተለያያችሁ ማለቴ ችግራችሁን ተነጋግራችሁ መፍታት አትችሉም ነበረ» « ተለያየን እንጂ ተጣላን መች አልኩሽ መሰነባበት መጣላት የሌለው መለያየት በቃ እንደተዋደድሽ መለያየት እንገናኛለን ብለሽ ተለያይተሽ ዛሬ ነገን ግን ሳትገናኚ መቅረት ልክ እንደዚህ አይነት መለያየት » « አልገባኝም » « እኔም አልገባኝም ግን አንድ ነገር ተረድቻለሁ ሰዎች ህይወትን በፈለጉት መንገድ ሳይሆን የሚመሯት ህይወት ነች ሰዎችን በፈለገችው መንገድ የምትመራው እኛንም እኛ ባሰብነው ሳይሆን ህይወት ባዘጋጀችልን መንገድ ተጓዝን ለጊዜው አሁን ያለንበት መንገድ ላይ እንገኛለን » «በእጣፋንታ ታምናለህ ማለት ነው » «ብዙም ባይሆን አንዳንድ ነገራት እድል ናቸው ብዬ አስባለሁ » እሷም ዝም አለች እኔም ዝም አልኩኝ ንፋሱ ትንሽ ከበድ እያለ እሷም ሰውነቷ ሲንቀጠቀጥ ወደ እኔ ልጥፍ ስትል ይታወቀኛል  ፊልም ላይ እንዳለ ገፀባህሪ ጃኬቴን አውልቄ ለእሷ ማልበስ እንደዚህ አይነት romance የሆኑ ነገራት አይመቹኝም  «ደረስን በቃ እዛ ጋር ያለው ነው ቤቴ አመሰግናለሁ » አለችኝ እጄን ለቃ ፊት ለፊቴ እየቆመች « ችግር የለውም ደህና ደሪ » በቆመችበት ጀርባዬን ሰጥቻት ጥያት ሄድኩኝ ዞር ብዬ ላያት ከአንዴም ሶስት ጊዜ እርምጃዬን ለዘብ አድርጌ ነበረ ግን መዞር አልቻልኩም የእግሬን አቅጣጫ ወደ ቤት ነው ያደረኩት ሰአቱም መሽቷል ማማ ጋር የምጨቃጨቅበት አጀንዳ  መክፈት አልፈልግም እሷ ትንሽ ነገር ነው የሚበቃት በዚህ በዚህ ጉዲይ አባቴ ይመቸኛል ለሁሉም ነገር ቅልል ያለ ሰው ነው አሰፓልቱን ጨርሼ ወደ ሰፈር ገባሁ የእያንዲንዱ ቤት የውጪ መብራት ስላለ ብዙም የሚያሰጋ አይደለም  ወደ ግቢያችን ተጠግቼ በቀስታ አንኳኳው በቀስታ ትንሹ በር ከፈተልኝ « እንዴ እንዴት መጣህ » አለኝ በር ላይ ያለው ዘበኛ «ማለት እነ ማማ የሉም እንዴ ምነው ጭር አለ » አልኩት ወደ ውስጥ ገብቼ « አዎ እራት ግብዣ አለን ቃሲዮንም ከመጣ እኛው ጋር እንዲመጣ ንገሩት ብላለች ፕሮፌሰር» ሮዛሊን ቀን ደውላ እቤት እራት ግብዣ አለ አደራ እንዳትቀር ብላ ያስጠነቀቀችኝ ትዝ አለኝ ቅድምም ይሄንኑ ለማስታወስ ነው የደወለችው « አሁን ስንት ሰአት ነው » አልኩት ስልኩን አውጥቶ አሳየኝ 3:20 በዚህ ሰአት እንግዲህ ሰው ቤት አልሄድም እነ ማማም ሊመጡ እየተዘጋጁ ይሆናል ቀጥታ ወደ ቤት ገባሁ የማማን ቁጣ የሮዛሊንን ኩርፊያ የምችልበት አቅም ለማግኘት በግዜ መተኛት አለብኝ እራት አላስፈለገኝም ክፍሌ ገብቼ ልብስ ቀያየርኩኝ የስልኬ notification ስሰማ አየውት instagram ላይ new message ይላል የማላውቀው አዲስ account  💬  በሰላም ገባህ ? አካውንቱን ሳየው የሴት ነው ጓደኞቼ ሊሆኑ አይችሉም ይቺ ጉደኛ ልጅ ከየት ልታመጣ ትችላለች አካውንቴን 💬 ማን ልበል» የሚል ቴክስት ላኩኝ እርግጠኛ ለመሆን

300❤+  ይሆናል የሚል ተስፋ አለኝ  እንግዲህ ሰአቱ እስከሚደርስ 😭