en
Feedback
ㅤ♰ ማሕተቤ ✟

ㅤ♰ ማሕተቤ ✟

Open in Telegram

“ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።” — መዝሙር 122፥1 💬 ለማንኛውም ጥያቄና አስተያየት @Ortho_29 🙏 ♡ እንኳን ደኅና መጡ። ♡

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
294
Subscribers
No data24 hours
-17 days
+730 days
Posts Archive
😇 " ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።"🧡
😇(2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:9)

ንስሐ🙌 🛜 ንሰሐ ሰው ሕይወቱን ወደተሻለ ደረጃ ለመለወጥ የሚያስችለው መንፈሳዊ ጥንካሬ ወይም ኃይል ነው:: 💙ንስሐ በልቡናችን ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ፍቅረ እግዚአብሔር እንዲወለድ ያደርጋል:: 🔻ምክንያቱም በንስሐ ሕይወት የምንኖረው ከሆነ እግዚአብሔር ስለ እኛ ብሎ የተሸከመልንን ሸክምና ይቅር ያለንን እጅግ የከፋ ኃጢአት እንድናስብ ስለሚያደርግና ለእግዚአብሔርም ያለን ፍቅር እያደገ ስለሚሄድ ነው::

“ጽድቅንና ምሕረትን የሚከተል ሕይወትንና ጽድቅን ክብርንም ያገኛል።”
  — ምሳሌ 21፥21

የፈጸምኸውን ኃጢአት ሀብት አድርገህ አታስቀምጠው፤ ሰው ገንዘቡ ሊያደርገው የሚገባው ምርጥ ነገር ቢኖር ኃጢአቶቹን ለእግዚአብሔር በመናዘዝ ራሱን መውቀስ መቻሉ ነውና።"
ቅዱስ እንጦንስ

“ለድሀ የሚሰጥ አያጣም፤ ዓይኖቹን የሚጨፍን ግን እጅግ ይረገማል።”
  — ምሳሌ 28፥27

"ከንስሐ አባትህ ጋር ስትሆን ጥያቄህን እንጂ ውሳኔህን አታቅርብላቸው፤ በልብህ ካሰብከው ጋር እንዲስማሙ ሳይሆን በሀሳብህ ላይ ሀሳባቸውንና ምክራቸውን እንዲሰጡህ አድርግ።"
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሣዊ

በሚሞት ስጋችሁ ሐጢያት አይንገስ😇
“የምናስተውል ካለን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል”፤ ☦️በሚሞት ስጋችሁ ሐጢያት አይንገስ ብልቶቻችሁን የፅድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ ◌ (ሮሜ 6፥12-14) 📖ከሴት ጋር አለመገናኘት መልካም ነው ካልተቻለ ዝሙትን ለመከላከል በአንድ ይፅና ከዚህ ውጭ ጉዞ ወደ እሳት ነው ◌ (1ኛ ቆሮ 7፥1)📖 😇ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱ ያፈርሰዋል ቤተ መቅደሱም እናንተው ናችሁ ◌ (1ኛ ቆሮ 3፥17)📖 😇ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእረፍትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸፍኑ ◌ 📖(1 ኛ ጢሞ 2፥9) 😇የወንድ ልብስ የለበሰች ሴት በአምላክ ዘንድ የተጠላች ናት ◌📖 (ዘዳ 22፥5; ዘፀ 39፥28) 😇ፀጉሯን ሳትሸፍን የምትፀልይ ሴት እራሷን ያዋረደች ናት ◌ 📖(1ኛ ቆሮ 11፥5) 📖የወይን ጠጅ ከሚጠጣ ጋር አትቀመጥ ◌(ምሳ 23፥20) ☦️ዘፈን የሰነፎች ዜማ ነው ◌ (መክ 7፥5) 📖 በዛም አጋንንት ይዘፍናሉ ◌ (ኢሳ 13፥21)
አቤቱ ጌታሆይ ልቦና ስጠን✝

“እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።”
  — መዝሙር 126፥3

“ምሕረትህ ለመጽናናቴ ትሁነኝ፥ እንደ ቃልህም ለባሪያህ ይሁነው።”
  -- መዝ 119፥76

እኔም እልሀለው አንተ ቤጥሮስ ነህ በዚችም አለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሰራለው የገሀነም ደጆችም አይችሏትም 
        --- ማቴ 16:18

“በጎንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው?”
  — 1ኛ ጴጥሮስ 3፥13

አንድ ሰው በእግዚአብሔር ፊት ቆመና፦ "ጌታ ሆይ ተመልከት እጆቼ ንፁህ ናቸው ደም አላፈሰሱም የሰው ገንዘንብ አልቀሙም" አለው። እግዚአብሔርም ሲመልስለት፦ "ልጄ ሆይ አዎ እጆችህ ንፁህ ናቸው ግን ባዶ ናቸው" አለው ይባላል። ንፁህ እጅ ግን ባዶ እጅ፣ ያልገደለ ግን ያላዳነ እጅ፣ ያልሰረቀ ግን ያልመፀወተ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ የለውም። እውነተኛው መልካምነት ክፉ አለማድረግ ብቻ ሳይሆን መልካም ማድረግም ነው።🧡

“በልቡ ጠቢብ የሆነ ትእዛዝን ይቀበላል፤ በከንፈሩ የሚሰንፍ ግን ይወድቃል።”
  ምሳሌ 10፥8

“ምሕረትና እውነት ከአንተ አይራቁ፤ በአንገትህ እሰራቸው፤ በልብህ ጽላት ጻፋቸው።”
  — ምሳሌ 3፥3

“ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም።”
  — ማርቆስ 13፥33

“እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።”
  — 1ኛ ጴጥሮስ 5፥7

"ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች።"
መዝሙር ፲(10) ÷ ፯(7)

መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።”
  ማቴዎስ 10፥38