የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
Open in Telegram
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
514
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ትኩረቱን አንባቢ ትውልድን ለመቅረጽ ታዋቂ ሰዎች እና የንባብ ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉ ደራሲያን ልምድ የሚያካፍሉበት የታሪክ እና የንባብ ጉዞ በተለያዩ ከተሞች እየተካሔደ ይገኛል።
ዓመታዊው የተጓዥ ኪነ ጥበብ የታሪክ እና የንባብ መርሐ ግብር ሴቶችን እና
ህጻናትን ያካተተ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የሕፃናት፣ የሴቶች እና የእናቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ እንደሆነም ካገኘነው መረጃ ለመረዳት ችለናል።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት፣ቱሪዝም ሚኒስቴር እና ባይራ ትሬዲንግ በጋራ ባዘጋጁት መርሐ ግብር አንጋፋዎቹ ደራሲያን ዘነበ ዎላ ደራሲና ተዋናይ ሥዩም ተፈራ፣ ገጣሚያንና ጋዜጠኞች የንባብና የባህል ግንዛቤን ለህዝቡ ለማድረስ እንደሆነ ካገኘነው መረጃ ለመረዳት ችለናል።
በአንጋፋ ደራሲያንና አርቲስቶች እንዲሁም ጋዜጠኞች የተመራ የኪነ ጥበብ ልዑካን ቡድን ታሪካዊ የንባብ ተሞክሮ ጉዞውን በሆሳዕና ከተማ የሚገኘውን የካቲት 25/67 ት/ቤት የመጎብኘት እና ታላቋ የጥበብ ሰው ገጣሚ ፊርማዬ አለሙ የተማረችበትን ት/ቤት በእርሷ ስም ማስታወሻ እንዲሆን ለመነሻ ለት/ቤቱ ቤተመጻሕፍት ከ300 በላይ መጻሕፍት ድጋፍ እንደተደረገ እና ልዑኩ በሁለተኛነት ጉዞውን ወደ ንጉሥ ካዎ ጦና ምድር በማድረግ ልምድ የማካፈልና ተፈጥሯዊ ቦታዎችን በመጎብኘት በሙያቸው ብህራቸውን በማሳል አገራቸውን ከበፊቱ በተሻለ የሚያጎሉበት በሀገሪቱ እየተሰሩ የሚገኙ ልማቶችን ተመልክተው ላላየው የማኀበረሰብ ክፍል የሚያሳዩበትን ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩበት ሲሆን በሦሥተኛና የጉብኝታቸው ፍጻሜ በውቢቷ አርባ ምንጭ እንደሚያደርጉ እና እንደጎበኟቸው ሁለቱ አገራት የአርባ ምንጭንም ጸጋ ለማኀበረሰቡ የሚያስተዋውቁበትና ለተተኪው ትውልድ ተሞክሮ የሚያጋሩበት ጉዞም እንደሚሆን እውን ነው።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
+4
በተቋሙ ጉብኝት ተደረገ
ከናይጄሪያ እና ኡጋንዳ የተውጣጡ የጥናትና ምርምር ባለሙያዎች በባልቢስ ግሩፕ አማካኝነት የካቲት 25 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር)ን ጎብኝተዋል።
ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ከመረዳት ባለፈ የጽሑፍ ቅርሶችንና የመረጃ ሀብቶችን ጠብቆ ለማስተላለፍ እየተሰራ ያለውን ስራ በየስራ ክፍሎቹ በመገኘት ለመመልከት እና ግንዛቤ ለመውሰድ ችለዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
+1
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከየካቲት 22-25/2018 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ ባዘጋጀው የንባብ ሳምንት፣ ቡክፌር፣ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ሥልጠና እና የፖናል ውይይት መርሐ ግብር ላይ
ተሰንደው በአገልግሎቱ ከሚገኙት የጋሞና አካባቢው በርካታ ምስሎ ውስጥ የማህበረሰቡን ታሪክ እና ባህል የሚገልጹ ምስሎችም ለእይታ አቅርቧል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የካቲት 24/2018 ዓ/ም
ካራት ከተማ
=========
"የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል የንባብ ቀን ተካሔ።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ባህል ስፖርት ቢሮ እና ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመተባበር የተዘጋጀ የተዘጋጀው የንባብ ሳምንት፣ ቡክፌር፣ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ሥልጠና እና የፖናል ውይይት መርሐ ግብር አንዱ የሆነው የንባብ ሳምንት በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ተካሒዷል።
በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ በተካሄደውን የንባብ ሳምንት መድረክ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአገልግሎቱ ሥራ አመራር አቶ አብነት አበራ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ከተደራጀበት 1936 ዓ/ም ጀምሮ በንባብ፣ በመረጃ ማሰባሰብ እና ማደራጀት ላይ በርካታ ስራዎችን እየሰራ የቆየ ተቋም መሆኑን ጠቁመዋል።
ሥራ አመራሩ በቀጣይ የዞኑና የክልሉ መንግሥት የተለያዩ መንገዶችን ተጠቅመው መጻሕፍት የማሟላት ስራ በትኩረት መስራት እንዳለባቸውና የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ያመጣቸውን መጻሕፍት ተማሪዎች እና ማህበረሰቡ እንዲያነቡት እንዲሁም ዛሬ የሚደራጀው ቤተ መጻሕፍት ክፍት ሆኖ እንዲያገለግል ሊደረግ እንደሚገባም ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታርኩ ኦይቻ ንባብ የማይዳስሰው ታርክ እንደሌለና አሁን እየገጠመን ላለው የትምህርት ስብራት ሳንካ የንባብ ባህል ያለመዳበር በመሆኑ በቀጣይ የሚያነብ ትውልድ ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል ።
የኮንሶ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አሸናፊ በርሻ ለዞኑ በተደረገው ድጋፍ በዞኑና በተማሪዎች ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
አገልግሎቱ ለኮንሶ ዞን ትምህርት መምሪያ ለ4 አንደኛ ደረጃ እና ለ2 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተለያ ዩ ይዘት ያላቸው መጻሕፍቶችን ድጋፍ አድርጓል ።
በመርሐ ግብሩ ደራሲ ይታገሱ ጌትነት፣ደራሲ ዮሐንስ ገ/መድህን እና ደራሲ ገዛኸኝ ሀብቴ ተሞክሯቸውን ያካፈሉ ሲሆን በ6ኛ፣ በ8ኛ እና በ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ጥያቄና መልስ ውድድር ተካሒዶ ለተሳተፉ እና ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የምስክር ወረቀት እና መጻሕፍት ተበርክቶላቸዋል ።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የካቲት 23/2018 ዓ.ም
በአርባ ምንጭ ማረሚያ ተቋም
====================
መቶ ሺህ ብር የፈጁ መጻሕፍት በሥጦታ ተበረከቱ።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከየካቲት 22-25/2018 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ ባዘጋጀው የንባብ ሳምንት፣ ቡክፌር፣የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ ሥልጠና እና የፖናል ውይይት መርሐ ግብር ላይ ለአስራ አምስት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ቤተመጻሕፍት ቤት፣ለአንድ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት ቤት፣ለአርባ ምንጭ እና ለጊዶሌ ማረሚያ ተቋም በአጠቃላይ 4077 መጻሕፍት በበጀት 1,342,922 ብር የፈጁ መጻሕፍት በስጦታ አበርክቷል።
በመርሐ ግብሩን በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የከፈቱት የአርባ ምንጭ ተቋም ኃላፊ ኮማንደር አለሙ ኬንቶ 130ኛውን የዓደዋ ድል በዓልን በማስመልከት ዛሬ በቅኝ ሳንገዛ አንገታችንን ሳንደፋ በነጻነት እንድንኖር ምክንያት የሆነን አባቶቻችን በከፈሉት ጀግንነት ነው።
ሰላማችንን ለማስፈን ከፊታችን ያለውን ሀገራዊ ምርጫ በዲሞክራሲ መንገድ እውን ለማድረግ የሁላችንን ድምጽ ይጠይቃል።
ማረሚያ ተቋሙ በዋናነት ሰብዓዊ መብት ላይ ትኩረት በመስጠት እንደሚሰራና የሰብዓዊ መብት መከበር ዜጎች ብቁና ምቹ እንዲሁም ሰላማዊ ኑሮ እንዲኖሩ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
ታራሚዎች ታርመውና ታንጸው ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ በቆይታቸው ያገኙትን የሙያ ሰልጠና ተግባራዊ በማድረግ ማህበረሰባቸውን ራሳቸው ላይ ለውጥ የሚያመጡ ሊሆኑ እንደሚገባ እና ይህንኑ ለውጥ ለማምጣት ማረሚያ ተቋሙ ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር አጠናክሮ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊው አቶ አባተ ካሳው ለታራሚው መልዕክት ሲያስተላልፉ ዘመዶቻችሁ ሊጠይቋችሁ ሲመጡ ጥሩ የሚሉትን ምግብ ሰርተው ሳህን ቋጥረውላችሁ ይመጣሉ እኛ ደግሞ ለአእምሯችሁ ምግብ ሊሆኑ የሚችሉ መጻሕፍትን ይዘንላችሁ መጥተናል እናንተ በእርምት ጊዜያችሁ ሰዓታችሁን የሚሻማ ነገር ስለማይኖር ወጥታችሁ ከማህበረሰቡ ጋር ስትቀላቀሉ እኩል እንድትራመዱና እራሳችሁን ተወቃሽ ሳታደርጉ የፈለጋችሁት ደረጃ ለመድረስ በማንበብ ራሳችሁን እንድትለውጡ ብለዋል።
በንባብ ቀኑ ላይ ንባብን በማስመልከት ደራሲ ይታገሱ ጌትነት እና ደራሲ ገዛኸኝ ሀበቴ የንባብ ተሞክሯቸውን ሲያጋሩ፤ በታራሚዎች መልዕክት አዘል ግጥሞች ቀርበው ለግጥም አቅራቢዎች በአገልግሎቱ የሥራ አመራር በአቶ አብነት አበራ የመጽሐፍ ሰጦታ ሲበረከት ከአገልግሎቱ ለማረሚያ ተቋሙ የተበረከቱ የተለያዩ ይዘት ያላቸው ሁለት መቶ ሰባ መጽሐፍት የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ለማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ለኩማንደር አለሙ ኬንቶ አስረክበዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የነፃነት ቀንዲል ነጸብራቅ የአንድነት ተምሳሌት-አድዋ! 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል ተሰንደው ለእይታ ከቀረቡ ምሰሎች በጥቂቱ--
በየዓመቱ የካቲት 23 የሚከበረውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓልን ምክንያት በማድረግ በተቋሙ የሚገኙ የዓድዋ መዛግብቶችንንና የጀግኖቻችንን ፎቶ ግራፍ የያዙ ምሰሎችን ሰንዶ በማቅረብ በአርባ ምንጭ ከተማ ከየካቲት 22-25/2018 ዓ.ም በተዘጋጀው የንባብ ሳምንት፣ ቡክፌር፣የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ ሥልጠና እና የፖናል ውይይት መርሐ ግብር ላይ ለእይታ በዚህ መልክ አቅርቧል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት እንኳን ለ130ኛው የዓድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይመኛል።
ዓድዋ-የጥቁር ሕዝቦች የድል አክሊል!
የዓድዋ ጦርነት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን ትተው፣ በአንድነት የተሰለፉበትና ድል ያደረጉበት የወል እውነት፣ የወል ክብር፣ የወል ታሪካችን ነው።
ዓድዋ በመልካምነት የተባበሩ ልቦች፣ በፍቅር ጉልበት የበረቱ ክንዶች፣ በኅብረት የተሰለፉ ጀግኖች ድል ያስመዘገቡበት የጽኑ መንፈስና የከፍታችን ተምሳሌት ነው።
በመሆኑም ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን በክብር ጠብቀው ያሻገሩልንን ይቺን ታላቅ ሀገር ሰላሟንና ክብራን አሰጠብቆ ለተተኪው ትውልድ ማሻገር የሁሉንም ወገን ኃላፊነትን ይጠይቃልና ሰላሟን እናስጠብቅ መልክታችን ነው።
ታላቅ ክብር በደማቸው ጠብቀው ላሻገሩልን ኢትዮጵያውያን ጀግኖቻችን!!!
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
