የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
Open in Telegram
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
514
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የማይቀርበት መድረክ በክብር ተጋብዘዋል!!!
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከኢትዮጵያ ልጆች ሚዲያ ጋር በመተባበር በልጆች ሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ ዓለም አቀፍ አበርክቶ ያለውና አፍሪካዊ ተረቶችን በማሰባሰብ በአምስት ቋንቋዎች በርካታ የልጆች መጻሕፍትን በማዘጋጀት የሚታወቀው ጋናዊ የልጆች መጻሕፍት ደራሲ እና ተዋናይ ሚስተር ፓትሪክ አባዳይ (Mr.Patrick Addai) በመጋበዝ
ለኢትዮጵያ የህፃናት መጽሐፍ ጸሃፊዎች እና ተራኪዎች የተዘጋጀ ሙያዊ ልምድ ልውውጥ እና የይዘት ፈጠራ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ሐሙስ ታህሣሥ 9/2018 ዓ.ም ከ8፡00 -10፡00 ሰዓት በተቋሙ ቅጥር ጊቢ ኀሩይ ወልደ ሥላሴ አዳራሽ ስልጠናው ስለሚሰጥ በዘርፉ የምትሰሩ ድርጅቶች እና ፍላጎቱ ያላችሁ እንድትሳተፉ በክብር ተጋብዛችኋል፡፡
አዘጋጆች፡-
- የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት
-የኢትዮጵያ ልጆች ሚዲያ
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ለሚመለከተው በሙሉ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በየዓመቱ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በሚዘጋጀው ሀገር ዓቀፍ የግእዝ ጉባዔ ላይ ዘርፉን የሚያጎለብቱ እና ለትውልዱ የሚጠቅሙ መነሻ ጽሑፎችን አወዳድሮ ለዝግጅቱ ማቅረብ ይፈልጋል፡፡
ዘንድሮ ለዘጠነኛ ግዜ ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከሚያዚያ 15 - 17 ቀን 2018 ዓ.ም በሚያዘጋጀው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የግእዝ ጉባዔ ዓውደ ጥናት ላይ ለጉባዔው መወያያነት የሚበቁ ጽሑፎችን በተቀመጠው መስፈርትና የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ለውድድር ክፍት ስላደረገ በዘርፉ ልምዱ ያላችሁ እንድትሳተፉ እናሳውቃለን፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እና ከድሬዳዋ ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ከታህሳስ 2/2018 ዓ.ም ጀምሮ በድሬዳዋ ከተማ ባዘጋጀው የንባብ ቀን፤ስልጠና እና የፓናል ውይይት በድሬ ቲቪ ከተላለፈ የተወሰደ
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
በእምርታ የህዝብ ቤተ-መጻሕፍት የውይይትና የጉብኝት መርሐግብር ተከናወነ።
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ፣ የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እና ድሬዳዋ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በአዘጋጅነት በተሳተፉበት የንባብ ቀን፣ ፓናል ውይይትና ስልጠና በእምርታ የህዝብ ቤተ-መጻሕፍት የውይይትና የጉብኝት መርሐግብር ተከናውኗል ።
በውይይቱ ላይ ገለፃ ያደረጉትና ድሬዳዋ ባህልና ቱሪዝም ቢሮን ወክለው የተገኙት የድሬዳዋ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ዘርፍ ቡድን መሪ አቶ ቴዎድሮስ ታዬ በንግግራቸው ሙሉ በሙሉ ግንባታውን ጨርሶ ለአገልግሎት እየተዘጋጀ ለሚገኘው ባለ 3 ወለል የህዝብ ቤተ መጻሕፍት ከኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የሚገኘው የስልጠና ፣ የአገልግሎትና የግብዓት ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የአብያተ መጻሕፍት መረጃ ሀብቶች አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ስለሺ ሽፈራው በበኩላቸው ይህ የመጻሕፍት ድጋፍ የመጨረሻ አለመሆኑን ገልጸው ሀገር የምትሰራው በትውልድ ቅብብሎሽ እንደመሆኑ ለዚህ ዘመኑን ለዋጀ ለእምርታ የህዝብ ቤተ መጻሕፍት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ በአገልግሎቱ በኩል ያለውን ዝግጁነት ገልፀዋል ።
በጉብኝቱ ላይ የእምርታ የህዝብ ቤተ-መጻሕፍት የዓይነ ስውራን ቤተ - መጻሕፍት፣ የቡድን ንባብ ቤተ-መጻሕፍት፣ የውይይትና የስብሰባ አዳራሾች ፣ የኮምፒውተርና የኢንተርኔት አገልግሎትን ጨምሮ ለህዝብ ግልጋሎትን ለመስጠት በዝግጅት ላይ እንዳለ ተጠቁሟል፡ ፡
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ለእምርታ የህዝብ ቤተ-መጻሕፍት ያበረከተውን 192,570 ብር በጀት ያለው 668 መጻሕፍትን የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ለድሬዳዋ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ዘርፍ ቡድን መሪ አቶ ቴዎድሮስ ታዬ አስረክበዋል ።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የንባብ ክበባት ምስረታ በድሬዳዋ ሳብያን 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተካሔደ ።
ታህሳስ 2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ቃል በድሬዳዋ ሳቢያን 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት የንባብ ክበባት ምስረታ ተካሔደ።
በዕለቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የሳቢያን 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር በፍቃዱ ወልደሰማያት የተገኘው ድጋፍ ከፍተኛ ዋጋ የሚሰጠው በመሆኑ ተማሪዎች የሚተላለፈውን መልዕክት በትኩረት እንዲከታተሉና እንዲተገብሩ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው በንግግራቸው እንደ ተማሪ ትምህርታችሁን ማንበብና አጥንቶ መፈተን አንዱ ስራችሁ ቢሆንም ከዚህ በተጨማሪ ለህይወት ክህሎት፣ ለመመራመር ፣ ሰፊ ዕውቀትን ለማግኘት የምታነቡትን ሌሎች የመጽሐፍ ዓይነቶች ከአሁን ጀምራችሁ አንዱ የህይወታችሁ መንገድ አድርጉ ሲሉ መክረዋል፡:
በንባብ ክበባት ምስረታው የደራሲዎች ተሞክሮ በደራሲ ሊዲያ ተስፋዬ እና በደራሲና ጋዜጠኛ ኢሳያስ ሆርዶፍ የቀረበ ሲሆን የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ - መጻሕፍት አገልግሎት ለድሬዳዋ ሳቢያን 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያበረከተውን 83,189 ብር ያወጡ 220 መጻሕፍትን የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መ ጻሕፍት የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ለሳቢያን 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር በፍቃዱ ወልደሰማያት አበርክተዋል ።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
በድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ቤት ማረሚያ ቤቶች እንደ ስያሜያቸው የመማሪያ ማዕከል እንዲሆኑ የሚያግዝ የንባብ ቀን ተካሔደ::
ታህሳስ 2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
" የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እና ከድሬደዋ ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የንባብ ቀን፣ ስልጠና እና የፓናል ውይይት በድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ቤት እየተካሔደ ይገኛል።
የመርሐ ግብሩን ዓላማ አስመልክተው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በአዲስ አበባ ቢገኝም እዛ መጥተው መገልገል የማይችሉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ለመድረስ እንደዚሁም ማረሚያ ቤት እንደ ስያሜው ታራሚዎች ከማማረር ወደ መማር የሚያድጉበት ለማድረግ ዓላማ አድርገን መጥተናል፤ ስለዚህ ታራሚዎች ከሚሰሩት የተለያዩ ሙያዊ ስራዎች ባሻገር መጻሕፍትን እንደ መዝናኛ፣ ከውጭው ዓለም ጋር እንደ መገናኛ ድልድይ ለመጠቀም ፣ እውቀትን ለማግኘት እና ለትውልድ ማበርከት የምትፈልጉትን ሀሳብ ፅፎ ለመሰነድ ወደ ቤተ-መጻሕፍት አዘውትሩ ብለዋል።
አክለውም ተቋሙ ከመጽሐፍት ድጋፍ ባለፈ የቤተ-መጽሐፍት ሙያ ስልጠና እና የተቀናጀ የመረጃ አያያዝ ላይ ከ 8 አስርት አመታት በላይ እየሰራ የሚገኝ አንጋፍ ተቋም በመሆኑ በጋራ ለመስራት ያለውን ዝግጁነት ገልፀዋል።
በንባብ ዙሪያ ታራሚዎችን የሚያንፅ መልዕክት ያስተላለፉት ደራሲ ሊዲያ ተስፋዬ በኑሯችን ትኩረትን የሚወስዱ እና እይታን ለመሰብሰብ የሚያታክቱ ብዙ ውጣ ውረዶች አሉ። እናንተ ግን ትኩረታችሁን ለመሰብሰብ የተሻለ እድል አላችሁ፤ በመሆኑም በእነዚህ የመፅሐፍት ስጦታ አጋዥነት ቆይታችሁ የምታነቡበት፣ እይታችሁን የምታሰፉበት፣ ለምን ብላችሁ የምትጠይቁበት ፣ የዛሬና የነገን ህይወታችሁን ቅርፅ የምታስይዙበት ሊሆን ይገባዋል ብለዋል፡ ፡
ተሞክሯቸውን ያካፈሉት ጋዜጠኛና ደራሲ ኢሳያስ ሆርዶፍ በበኩላቸው ብዝሐ ቋንቋዎች ኢትዮጵያ የምትታወቅበትና ውበታችንን የሚያጕላ በመሆኑ ታራሚዎች ቋንቋዎችን እንዲማሩና በተለያዩ ቋንቋዎች ፅሑፍ እንዲፅፉ አበረታትተዋል።
በፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የማረምና ማነፅ ተሀድሶ ክፍል ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር ሉባባ ጀማል በማረሚያ ቤት ያሉ ወገኖቻችን የኛ ወገኖች ናቸው ብላችሁ ከሩቅ ስለመጣችሁ እናመሰግናለን ብለው ማረሚያ ቤቱ ለሚሰራው ዘርፈ ብዙ ስራ መጻሕፍት ዋና አጋዦች ናቸው ብለዋል።
በንባብ ቀኑ ማራኪ ስነ-ጽሑፍና ግጥም ያቀረቡ ታሪሚዎች የመጻሕፍት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ለድሬደዋ ሁሉ አቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ቤት ያበረከተውን 233,110 ብር በጀት ያላቸው 500 መጻሕፍት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጽሐፍት አገልግሎት የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ለረዳት ኮሚሽነር ሉባባ ጀማልና ለረዳት ኮሚሽነር ሙላት ጫን ያለው አስረክበዋል ።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ታህሳስ 1/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ዓለም አቀፍ በዓላት በፓናል ውይይት ተከበሩ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ተቋም አመራሮችና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የህጻናት፣የጸረ- ጾታዊ ጥቃት እና የኤች አይ ቪ/ኤድስ/ ቀንን "የህፃናት ጥበቃና የመጫወት መብት ለሁሉም ህፃናት"፣“ፆታዊ ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለትውልድ ግንባታ”፣"ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤች አይ ቪ ኤድስ ምላሽን በዘላቂነት እናረጋግጥ" በሚሉ መሪ ቃሎች በጋራ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡
በዝግጅቱ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ቀናቶቹ ትላልቅ ማህበራዊ ጉዳዩችን ያያዙ በመሆናቸው ቀኑ ሲታሰብ ከዚህ በተሻለ አስተማሪ ክዋኔዎች እና መልዕክት አዘል ግንዛቤ በሚያስጨብጡ ተግባራቶች ተካተው ትኩረት ኖሮት መዘጋጀት እንደሚያስፈልግ የዛሬው ጅማሮ የሚያሳይ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
ዝግጅቱን በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ በጋራ አዘጋጅተውታል፡፡
በዓላቱን ሊገልጹ የሚችሉ የመወያያ መነሻ ጽሑፍ በዶ/ር ታምራት ዘላለም ለውይይት ቀርቦ ሃሳብ፣ አስተያየት ተሰጥቶበት ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እና ከድሬዳዋ ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የንባብ ቀን፤ስልጠና እና የፓናል ውይይት ከታህሳስ 2/2018 ዓ.ም ጀምሮ በድሬዳዋ ለማካሔድ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች፣ ከባህል ስፖርት ሚኒስቴር እና ከሌሎች የተጠሪ ተቋማት ጋር የጸረ ሙስና ቀንን ዛሬ ኀዳር 30/2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር አክብረዋል፡፡ ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ከአስራ አንደኛው የወር ወንበር "ወደ ውኃ ፍሰት የተለወጠው የሥነ ሕንጻ ጥበብ" (Liquid Architecture) በሚል ርእስ ሥነ ጥበባዊ ወግ በአርክቴክት እና ሙዚቀኛ ምሕረቱ ዩሴፍ የቀረበ የምስልና የድምጽ መረጃ
የዘመን ጉዳይ ንባብን ቀነስ አድርጎታል ቢሆንም ንባብን ለማጠናከር እና አንባቢ ትውልድን ለመፍጠር በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ ባለሙያዎችን ወደ ተቋማችን በመጋበዝ ንባብን የሚያሳድግ ተግባር ተጠናክሮ ይሰራል።(የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት)
ኀዳር 27/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዛሬ ቅዳሜ ኅዳር 27 /2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ 11ኛውን የወር ወንበር አካሔደ።
በአስራ አንደኛው የወር ወንበር " ወደ ውኃ ፍሰት የተለወጠው የሥነ ሕንጻ ጥበብ" (Liquid Architecture) በሚል ርእስ ሥነ ጥበባዊ ወግ በአርክቴክት እና ሙዚቀኛ ምሕረቱ ዩሴፍ የውይይት መነሻ ጽሑፍ ቀርቧል።
መነሻ ጽሑፉ አርክቴክቸርንና ሙዚቃን ሁለቱን ትልልቅ ጥበብን ያነሳ ሲሆን የሚያገናኛቸውንም በስፋት ያስረዳ ነበር።
አርክቴክቸርም ሙዚቃም የሳይንስ ሙያን ጠቅሎ እንደሚይዝ እና የሁለቱ አረዳድ ልዩነቱንም ተነስቷል።
አርክቴክቸርን ልምድ ለማድረግ ከፈለግን የግዴታ በተቀመጠው ህንጻ ውስጥ መራመድ መቻል ሲኖርብን ሙዚቃን ግን ስንመለከተው የግዴታ ሙዚቃውን ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ማጫወት እንደሚጠበቅም በአርክቴክት እና ሙዚቀኛ ምሕረቱ የመነሻ ጽሑፍ ተዘርዝሮ በመቅረብ ግንዛቤ አስጨብጧል።
በሀገራችን ያሉ ህንጻዎች ኢትዮጵያዊ ይዘት የሌላቸው መሆን፣ሙዚቃንና አርክቴክቸርን አዋህዶ መቀጠል የተጀመረበት ጊዜ በመምጣቱ መደሰታቸውንና በውስጥ ላይ ሀሳቡ ኖሮ ሳይገለጽ ለረዠም ዘመናት ተይዞ የነበረ ነገር አሁን በዚህ መልክ መገለጹ ከዚህ በፊት በሙያው የተዋረዱ ሰዎች መከበሪያቸው ዘመን እንደሆነም ከታዳሚዎች ተነስቷል።
በዘርፉ የሚታየውን ክፍተት ለመሸፈን የተደረገውን ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት ሙዚቃንና አርክቴክቸርን በዚህ መልክ ተያያዥነታቸውን አዋህዶ ለቀረበ የመነሻ የመወያያ ጽሑፍ አቅራቢው ምስጋናቸውን ተሰጥቷል።
በ11ኛው የወር ወንበር የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ፣ ሙዚቀኛ ዳዊት ይፍሩ፣የዘርፉ ባለሙያዎች፣ደራሲ ገዛኸኝ ሀብቴ ተገኝተውበታል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ነገ ቅዳሜ ኅዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ በ11ኛው የወር ወንበር እጅግ ድንቅ የኾነ ሥነ ጥበባዊ ወግ በማቅረብ በዘርፉ ለሚገኙ ባለሙያዎች ባላቸው እውቀት ላይ ተጨማሪ እውቀት በመጨመር በዘርፉ ከራስ አልፎ ሀገራቸውን ተጠቃሚ የሚያደርጉበትን አቅም ለማጎልበት፤በዘርፉ የጠለቀ እውቀት ለሌላቸው ግንዛቤ በመፍጠር ብቁ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ታዳሚውን በክብር እየጠበቀ ይገኛል፡፡
ይኸው ዝግጅት በአርክቴክት እና ሙዚቀኛ ምሕረቱ ዮሴፍ “ወደ ውኃ ፍሰት የተለወጠው የሥነ ሕንጻ ጥበብ”(Liquid Architecture) በሚል ርእስ ድንቅ በሆነ ብቃት በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ አዳራሽ ይካሔዳል።
ሁላችሁም በአክብሮት ተጋብዛችኃል!
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ወርዓዊ የመጻሕፍት ዳሰሳ በኀዳር ወር የመጨረሻ ሳምንቱ "ቀይ ባህር ሲቀላ " በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መጽሐፍ በመ/ር መሰረት አበጀ በብቃት ይዳሰሳል።
መርሐ ግብሩ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ኀዳር 27/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ በኃሩይ ወልደ ስላሴ አዳራሽ ይካሔዳል በፕሮግራሙ እንድትታደሙ በአክብሮት ተጋብዛችኃል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ቅዳሜ ኅዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 10:00-12:00 በወመዘክር፤
“ወደ ውኃ ፍሰት የተለወጠው የሥነ ሕንጻ ጥበብ”(Liquid Architecture) በሚል ርእስ አርክቴክት እና ሙዚቀኛ ምሕረቱ ዮሴፍ፥ እጅግ ድንቅ የኾነ ሥነ ጥበባዊ ወግ ይዞልን በ11ኛው የወር ወንበር ይጠብቀናል።
"Architecture is a frozen music" የሚለውን ታዋቂውን የቩልፍ ጋንግ ገተን ተጠቃሽ አባባል፥ በሌላ አንጻር ሊያሣየን የወደደ ይመስላል። ይህንን ጥልቅ ሥነ ጥበባዊ ወግ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት፥ በብላታ መርስዔ ኀዘን አዳራሽ ትታደሙ ዘንድ በታላቅ አክብሮት ተጋብዛችኋል
