የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
Open in Telegram
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
514
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት እና በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክት አዘጋጅነት ከሐምሌ 23 እስከ 26/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ታላቅ የዕውቀት ድግስ ተዘጋጅቷል፡፡
በዝግጅቱ፡-የምርምር ተቋማት፣የዕውቀት ማዕከላት፣በርካታ አንጋፋና ወጣት ደራሲያን፣አሳታሚዎች፣የመጻሕፍት መደብሮች በስፋት ይሳተፋሉ።
የመጻሕፍት ዋጋ ላይ ልዩ ቅናሽ ይደረጋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
የማይቀርበት የዕውቀት ድግስ እየተሰናዳላችሁ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት እና በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክት አዘጋጅነት ከሐምሌ 23 እስከ 26/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ታላቅ የዕውቀት ድግስ ተዘጋጅቷል፡፡
በዝግጅቱ፡-የምርምር ተቋማት፣የዕውቀት ማዕከላት፣በርካታ አንጋፋና ወጣት ደራሲያን፣አሳታሚዎች፣የመጻሕፍት መደብሮች በስፋት ይሳተፋሉ።
የመጻሕፍት ዋጋ ላይ ልዩ ቅናሽ ይደረጋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
57ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 57ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር ጋር በተፈረሙ ሶስት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው ለዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ የእድገት ልማት ፖሊሲ ማስፈፀሚያ የሚውል የአራት መቶ ሰላሳ ሰባት ሚሊዮን አራት መቶ ሺ (437,400,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡ ሁለተኛው የማህበረሰብ ተኮር የመሬት አያያዝ ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል የአንድ መቶ አርባ አምስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ (145,500,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡ ሶስተኛው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የመስኖ ልማት ለዘላቂ ምርታማነት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሀምሳ አራት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሺ (54,600,000) ኤስ.ዲ.አር የብድር ስምምነት ነው፡፡ ምክር ቤቱም ሶስቱ የብድር ስምምነቶች ከሀገራችን የብድር ፖሊሲ ጋር የሚጣጣሙ መሆናቸውን በማረጋገጥ የብድር ስምምነት ማጽደቂያ ረቂቅ አዋጆቹ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት እና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተቋማት ለሚሰጧቸው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚከፈሉ የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመወሰን በቀረቡ ረቂቅ ደንቦች ላይ ተወያይቷል፡፡ ተቋማቱ ለሚሰጧቸው አገልግሎቶች በውስጥ ገቢ የሚሸፈኑ ወጪዎችን ከአገልግሎት ተጠቃሚዎች በሚሰበሰበው የአገልግሎት ክፍያ ለመሸፈን እንዲችሉ የአገልግሎት ተጠቃሚውን አቅም ባገናዘበ መልኩ አገልግሎት በጥራት መስጠት የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት እንዲያስችሉ ረቂቅ ደንቦቹ ተዘጋጅተው ለምክር ቤቱ ቀርበዋል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቦቹ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውሉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
3. ከዚያም ምክር ቤቱ ውይይቱን ያደረገው ለኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ ማቋቋሚያ ስምምነት የአባልነት ማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክን በአባልነት መቀላቀሏ ለሀገራዊ የልማት ፋይናንስ፣ ለመሠረተ ልማት ድጋፍ እና ለማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት አማራጭ የገንዘብ ምንጮችን ለማግኘት የሚያስችላትና ከደቡብ ደቡብ የፋይናንስ ሥርዓቶች ጋር የሚኖራትን ትስስር የሚያጠናክር መሆኑ ስለታመነበት የባንኩን የመመስረቻ ስምምነት ለማጽደቅ ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየበት አጀንዳ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ረቂቅ ፖሊሲ ነው፡፡ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ለሀገራችን ዕድገት ወሳኝ ሚና የሚጫወት እንደመሆኑ በ2006 ዓ.ም የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ፖሊሲ ወጥቶ ላለፉት አመታት ሲተገበር ቆይቷል፡፡ በዚህም በኢንዱስትሪው አንዳንድ ለውጦች የተመዘገቡ ቢሆንም አለማችን ከደረሰችበት የቴክኖሎጂ እድገት፣ የከተሞች መስፋፋት፣ የመሰረተ ልማቶች ፍላጎት ማደግ አንጻር ሰፊ ክፍተት የነበረበት በመሆኑ የዘርፉን ምርታማነትንና ተወዳዳሪነትን በማሳደግ፣ በስራ ላይ ያሉ የህግ ማዕቀፎችን በማጣጣምና በማዋሃድ እንዲሁም የዘርፉን የመልማት አቅም አሟጦ በመጠቀም የበለጸገች ኢትዮጵያን ዕውን ማድረግ እንዲያስችል ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያያበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ከዛሬ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
5. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የከተማ ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ በ1997 ዓ.ም ወጥቶ ላለፉት ሁለት አስርት አመታት በስራ ላይ በቆየው የከተማ ልማት ፖሊሲ በከተሞች የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት፣ ከተሞች በኢኮኖሚ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ፣ አገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ እንዲሆን፣ የገጠርና ከተማ እንዲሁም የከተማ ከተማ ትስስር እንዲጠናከር፣ መሰረተ ልማትና የተለያዩ ማምረቻና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲስፋፉ በተደረገው ጥረት ውጤቶች የተመዘገቡ ቢሆንም ክፍተቶችም የነበሩበት ስለሆነ የነባሩን ፖሊሲ ክፍተቶች ለማረም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከተሞች አካባቢ እየታዩ ያሉ አበረታች ለውጦችን ለማጽናት እና የበለጠ ለማጎልበት የከተማ ልማት ፖሊሲ በአዲስ መልክ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያያበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ከዛሬ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
///
ባለንበት ወቅት ዲጂታላይዜሽን ለኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ በመሆኑ ዘርፉን ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት)
ሰኔ 18/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂካዊ ግብ ለማሳካት እጅግ ዘመናዊ የዲጂታይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን፣ ሶፍትዌሮችንና የሀርድዌር ሥርዓቶችን ያካተተው ለተቋሙ የተለገሰው በለጋሹ የዓለም ባንክ (World Bank) የስራ ኃላፊዎች ተጎበኘ፡፡
በጎብኝቱ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት እና ከዓለም ባንክ (World Bank) Tim Kelly – Task Team Leader (TTL), Lead Digital Development Specialist፣Victor Kyalo – Co-Task Team Leader (Co-TTL), Senior Digital Development Specialist፣ Binyam Mesfin Shiferaw – Digital Specialist እንዲሁም የተቋሙ የማኔጅመንት አባላት ተገኝተውበታል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በርካታ የመንግሥትና የግል ተቋማት የቴክኖሎጂ ድጋፍ ጥያቄ አቅርበውለት እንደነበር እና በዚሁ በሰኔ ወር ለኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ያስረከበውን 792,422 (ሰባት መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ አራት መቶ ሀያ ሁለት) የአሜሪካ ዶላር ወይም በወቅታዊ ምንዛሬ 126,787,520 (መቶ ሀያ ስድስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰማኒያ ሰባት ሺህ አምስት መቶ ሀያ) የኢትዮጵያ ብር ወጪ የተደረገበት እና ሀገራችን ያሏትን ታሪካዊ ሀብቶች ወደ መላው ዓለም በዲጂታል መረብ የምታገናኝበትን የቴክኖሎጂ ሽግግር የለገሰው የዓለም ባንክ (World Bank) የበላይ አመራሮች ተጎብኝቷል፡፡
በነበረው የጎብኝት ሥነሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ተቋሙ መጻሕፍት፣መጽሔቶች፣ ጋዜጦች፣መጣጥፎች፣ቀረጸ ድምጾችና ምስሎች፣ ማኑስክሪፕቶች፣የነገስታት ደብዳቤዎች፣የፋይናንስ መረጃዎች፣ ማስታወሻዎች፣ ፎቶ ግራፎች፣ ካርታዎች ፣የተለያዩ የብር ኖቶች፣ የጠረፍ ስምምነቶች ፣ቆየት ያሉ የፍርድ ቤት መዝገቦች፣ ካሴቶችና ሸክላዎች፣ በግዕዝ የተጻፉ የነገስታት ታሪኮች ተሰንደው የሚገኙበት ትልቅ ሀገራዊ ተቋም እንደሆነም አስረድተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አካታች የሆነ የዲጂታላይዜሽን ስትራቴጂ ተጠቃሚ መሆኗን አንስተው ቴክኖሎጂ ቅንጦት ሳይሆን መሰረታዊ ፍላጎት መሆኑን በመገንዘብ ያሉንን የሀገር ሀብቶች እና የተዘረጋው ቴክኖሎጂ በብቃት በመጠቀም ተቋሙ ውስጥ ያሉትን የጽሑፍ ሀብቶች በሙሉ አቅም ወደ ዲጂታል ለመቀየር የሚያስችል ቋሚ መሰረተ ልማት እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
Tim Kelly – Task Team Leader (TTL), Lead Digital Development Specialist የዓለም ባንክ (World Bank) ለተለያዩ ዓላማዎች የሚሆኑ በርካታ ይፋዊ አንድሮይድ አፕሊኬሽኖች ያሉት ሲሆን በአጠቃላይ የዓለም ባንክ ዋና ዓላማ ድህነትን መቀነስ፣ የኢኮኖሚ እድገትን ማፋጠን እና በዓለም ዙሪያ ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ዋና ዋና ስልቶች ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡
ይህንን ዓላማ ለማሳካት ባንኩ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ሀገራት የሥራ ዕድሎችን እንዲፈጥሩ እና የግል ዘርፍ ኢንቨስትመንትን እንዲያበረታቱ መደገፍ፤የሰው ኃይል ልማት በሕዝብ ጤና፣ ጥራት ባለው ትምህርት እና የሙያ ሥልጠና ላይ ኢንቨስት ማድረግ፤አቅም መገንባት (Resilience) ሀገራት ከተፈጥሮ አደጋዎች፣ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ችግሮች ጋር ለመላመድ ያላቸውን አቅም ማጠናከር፤ፋይናንሳዊ ድጋፍ አባል ሀገራት የልማት ፕሮጀክቶቻቸውን ድጋፍ እንደሚያደርግ እና እንደዚ ያለ ሀገራዊ ተቋም ላይ ደግሞ ለትውልድ ተሸጋሪ ስራዎች የሚደራጁበትን በጎ ስራ በጋራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ለተደረገው ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እጅግ ዘመናዊ የዲጂታይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን፣ ሶፍትዌሮችንና የሀርድዌር ሥርዓቶችን ያካተተ፣ ከእነዚህም መካከል ለጥንታዊ መጻሕፍት ልዩ ጥንቃቄ የሚያደርጉ ዘመናዊ የመጻሕፍት ስካነሮች፣ የሰነድና የካርታ መዛግብት ስካነሮች እንዲሁም የተደራጁ የኮምፒውተር አውታረ-መረብ መሰረተ-ልማቶች መተግበሪያ ለተቋሙ በመበርከቱ እና ተቋሙም የዚህ በጎ እድል ተጠቃሚ በመሆኖ መደሰታቸውን ለእንግዶቹ አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም Tim Kelly – Task Team Leader (TTL), Lead Digital Development Specialist በተለይም በዚህ ሀገራዊ መረጃ ማደራጀት ላይ እና በሌሎችም ተግባራት ዙሪያ አብረው እንደሚሰሩ ተናግረው የተቋሙን አገልግሎት መስጫ ክፍሎች በመጎብኘት ተጠናቋል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
የተቋም አቅምን ከፍ ለማድረግ ተቋማዊ ህብር ወይም organizational harmony ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ሰኔ 15 / 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
በአራተኛው "እንገናኝ እንሰናኝ!" የሰኞ ንጋት የሠራተኞች መድረክ በተቋማዊ ህብር እና የጋራ ዓላማ ላይ አትኩሮት የሠጠ ውይይት ተካሔደ፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በየሁለት ሳምንቱ ሰኞ ንጋት "እንገናኝ እንሰናኝ!" በሚል ስያሜ ምቹ የስራ አካባቢን እና መልካም የስራ ባልደረቦች ግንኙነትን በመፍጠር ተቋማዊና ሀገራዊ ራዕይ እና ተልዕኮን ለማሳካት በማለም የተጀመረው የማነቃቂያ መድረክ መርሐ ግብር ተካሒዷል።
በመድረኩ ሀሳባቸውን ለማካፈል የተገኙት እንግዳ የአሻም ሬድዮ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ፣የጥበብ እና የዲስኩር መድረኮች አዘጋጅ፣የፎክሎርና የሥነ-ጽሑፍ እንዲሁም የሥነ መለኮት አጥኚና ተመራማሪ በተጨማሪም የምስክር ጌታነው ሚዲያና ፕሮሞሽን ባለቤት አቶ ምስክር ጌታነው ናቸው።
አቶ ምስክር ተቋሙንና በተቋሙ አገልግሎት የሚሰጡትን ሁሉ እንደ አንድ ዜጋ ለማመስገን እድሉን በማግኘታቸው መደሰታቸውን በመግለጽ ይህን ታሪካዊ ተቋም አቅሙን ከፍ ለማድረግ ተቋማዊ ህብር ወይም organizational harmony ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል።
በማብራሪያቸውም ተቋሙ ሊደርስበት ላሰበው ግብ ሁሉም የተቋሙ ባልደረባ እኩል ግንዛቤ እና የጋራ ዓላማ (unity of purpose) ሊኖረው እንደሚገባ እና ሁሉም የተቋሙ ባልደረባ በሚና ቢለያይም በአስፈላጊነት ግን እኩል መሆኑን (mutual respect) በመረዳት የእኔ መኖር ለተቋሙ አስፈላጊ እንደሆነ ሁሉ የሌላውም መኖር አስፈላጊ ነው የሚለውን መርህ መከተል እንደሚገባ ከተጨባጭ ነባራዊ ዕለት ተዕለት ሁኔታዎች ጋር በማያያዝ አስረድተዋል።
የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰርፀ ፍሬ ስብሐት በበኩላቸው የአቶ ምስክርን ሀሳብ በማጠናከር ህብር ፈጥሮ በአንድ ተቋም ውስጥ መስራት እንደ ግለሰብ፣እንደ ተቋም፣እንደ ሀገር ውጤታማ እንደሚያደርግ አስገንዝበዋል።
በማጠቃለያ ንግግራቸውም ያልተገባ ግላዊ ህልም ብዙ እንደሚያሳጣ እና ብዙ ዋጋ እንደሚያስከፍል አስረድተዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
በየሁለት ሳምንቱ ሰኞ ንጋት የሚካሔደው "እንገናኝ እንሰናኝ!" የሰራተኞች መድረክ ለአራተኛ ጊዜ በተቋሙ ቅጥር ጊቢ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም ይካሔዳል።
በሰላም ያገናኘን!
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
ይህን ያውቁ ኖሯል?
📚 የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ልብወለድ
«ጦቢያ» (1900 ዓ.ም)
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከጥንት እስከ ዛሬ የኢትዮጵያ ደራሲያን የሥነ-ጽሑፍ ሥራዎች በክብር ተሰንደው ይገኛሉ።
የቤተመጽሐፍታችን የቆዩ ልብወለዶችን ስናስተዋውቅ፣ በኢትዮጵያ የሥነ-ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው የሆነውን ድንቅ መጽሐፍ በመጋበዝ ነው፡፡
ርዕስ :- ጦቢያ
ደራሲ፦ አፈወርቅ ገብረኢየሱስ
የታተመበት ዘመን፦ 1900 ዓ.ም
ታሪኩ በአጭሩ፦ «ጦቢያ» የተባለችው ቆንጆ ልጅ እና ወንድሟ «ዋህድ» በክርስቲያኖችና በአረማውያን ጦርነት ምክንያት የገጠማቸውን መከራ፣ ቤተሰባዊ ፍቅርና ይቅር ባይነትን የሚተርክ ጥልቅ ታሪክ ነው።
ተናፋቂ እና ጥንታዊ ሥራዎችን በጋራ እንጠብቅ!
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ከብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል ጋር የቤተክርስትያንዋ የጽሑፍ ቅርሶች እንዲሁም የድምጽና የምስል ሀብቶች ጠብቆ ለትውልድ ከማሻገር አንጻር ጥልቅ ውይይት አደረጉ።
ሰኔ 10/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎትም ወደ ካቴድራሉ ሲያቀና ዓላማ ያደረገው እንደ ሀገር የተሰጠውን ስልጣንና ኃላፊነት ተግባራዊ በማድረግ የቤተክርስትያኗ መዛግብቶች ካሉበት ተሰብስበው በተቋሙ በቤተክርስቲያኗ ስም ስያሜ ቦታ ተሰጥቷቸው ለተመራማሪዎች፣ ለአንባቢያን ተደራጅተው እንዲቀመጡ በማድረግ እና ሰንዶ ለመጪው ትውልድ በማቆየት እንዲሻገሩ ለማስቻል እንዲሁም ከታሪክ ተጠያቂነት ለመዳን እንደሆነ አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ለብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ በስፋት አስረድተዋል።
የይፋዊ ውይይቱ ዋነኛ ዓላማንም አቶ ሠርፀ ለብፁነታቸው ሲያስረዱ ሦሥት ትላልቅ ጉዳዮችን ዓላማ ያደረገ እንደሆነ አንደኛው የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት
ቤተክርስቲያንን ታሪካዊ መዛግብት፣ መጻሕፍት፣ ፎቶግራፎች፣ ኦዲዮ ቪዥዋል ቅርሶች እና የኀትመት ውጤቶች በጋራ በመለየት ወደ ብሔራዊ ቤተመዛግብት በማምጣት ዘላቂ ጥበቃ እንዲደረግባቸው ማድረግ
በሁለተኛነት በቤተክርስቲያኒቱ የሥነ-መለኮት ዩኒቨርሲቲዎች እና በቅድስት መንበረ ቫቲካን ባለው የኢትዮጵያ ገዳም የሥነ መለኮት የሚካሔዱ የምርምር ሥራዎችን ለተመራማሪዎች እንዲደርሱ በማድረግ በብሔራዊ የዕውቀት ክምችት ማበልጸግ እና በ3ኛነት ኃላፊው ያቀረቡት ተቋሙ ካለው የረዥም ጊዜ ልምድ በመነሳት ለቤተክርስትያኑቱ የቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት ክፍል የቴክኒክ ድጋፍ እና ሥልጠና ለመስጠት ዝግጁ መኾኑን አስረድተዋል።
ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል፣ ከኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በጽሕፈት ቤታቸው በነበራቸው የውይይት ጊዜ፣ የቤተክርስቲያኒቱን ጥልቀት ያለው ታሪክ በሰፊው አስረድተዋል። በተለይም፥ "የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ታሪካዊ ጉዞ እና የካቶሊክ ሃይማኖት በኢትዮጵያ ያለው ታሪክ ጥልቅ፣ ውስብስብ እና የኢትዮጵያን የፖለቲካና የባህል ታሪክ በቅርበት የተሳሰረ ነው። ፖርቹጊዞች የፕሪስተር ጆንን ሀገር ከመፈለግ ጉዟቸው፣ በተለይም ከፍራንሲስኮ አልቫሬዝ ጀምሮ በትልቅ ፍላጎት እና አድናቆት የታየች ሀገር ናት። የካቶሊክ ሃይማኖት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በተለይም በ16ኛው እና በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከፖርቱጋልና ከስፔይን በመጡ ጄዝዊት ሚሽነሪዎች አማካኝነት ነበር።"ይላሉ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ።
በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የክሪስቶቫዎ ዳጋማ የጦር ሠራዊት መምጣት እና ከጦር ኃይሉ ጋር አብረው የገቡት የካቶሊክ ሚሽነሪዎች (ጄዝዊት)፣ እንደ ፔድሮ ፓኤዝ ያሉ ሚሽነሪዎች በጎርጎራ፣ በደንቀዝ እና በሌሎች የጎንደር አካባቢዎች አብያተ ክርስቲያናትን በመገንባት፣ የሕንፃ ጥበብን በማስተዋወቅ ትልቅ ተጽዕኖ ፈጥረው ነበር።"
"የካቶሊክ ሃይማኖት የአዲግራት እና የዓድዋ አካባቢ እንደ ፍሬሞና በመሳሰሉ ቦታዎች የካቶሊክ እምነት የትምህርት እና የሃይማኖት ማዕከል ኾነው አገልግለዋል። በተለይም በአሊተና እና በኢሮብ አካባቢዎች የካቶሊክ እምነት ከባህላዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ጎን ለጎን ተቀባይነትን በማግኘት፣ የራሱ የኾነ አሻራ ዐሳረፈ። የኤርትራው ከረንም የካቶሊክ ሚሽነሪዎች በጤና እና በትምህርት መስክ የገቡበት ትልቅ ማዕከል ነበር። በዘመኑ የነበረው የኅትመት ውጤቶች፣ እንደ እምኩሉ የካቶሊክ ማተሚያ ቤት ያሉ ተቋማት፣ ሃይማኖታዊ መጻሕፍትን በማሳተም ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።"
"በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሐረር ከተማ በአባ እንድርያስ ጃሮሶ አማካኝነት የተነሳሳው የካቶሊክ ሃይማኖት መንፈሳዊ መነቃቃት፣ ካቶሊካዊነት ከሰሜን ወደ ምስራቅ ኢትዮጵያ እንዲስፋፋ አድርጓል።"
"ኾኖም የካቶሊክ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ፈታኝ ወቅቶችን አሳልፋለች። የጣሊያን ወረራ (1928-1933 ዓ.ም.) አንዱ ወሳኝ ወቅት ነበር። ጣሊያኖች የካቶሊክ እምነትን ለፖለቲካ ዓላማቸው በመጠቀም፣ ከሌሎች አገራት የመጡ ሚሽነሪዎችን በማባረር፣ የራሳቸውን ጣሊያናዊ ሚሽነሪዎች ብቻ እንዲሰብኩ በማድረጋቸው በቤተክርስቲያኗ ላይ ጥላ ሆኖ ቀርቷል። በዚህ ሒደት ውስጥ፣ በተለይም የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አማኞች በሕዝብ ዘንድ ጥርጣሬ ውስጥ እንዲወድቁ የተደረገበት እና የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እንደ "ወራሪ" መሣሪያ እንድትታይ የተደረገበት አስቸጋሪ ጊዜ ነበር።"
"የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ የትምህርት ታሪክ ውስጥ ያላት አስተዋጽዖ ተወዳዳሪ የለውም። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (የቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ) ሲቋቋም የካቶሊክ ሚሽነሪዎች፣ በተለይም አሜሪካዊያኑ የኢየሱሳውያን አባቶች (Jesuits) የነበራቸው ሚና የመሠረተ ድንጋይ ዓይነት ነበር። የልደታ ካቴድራል እና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት አካባቢ የተገነቡ ትምህርት ቤቶች ለሀገሪቱ የሰው ኃይል ግንባታ ትልቅ ድርሻ አበርክተዋል። የጤና ተቋማት፣ ሆስፒታሎች እና የሰብአዊ ተራድዖ ሥራዎች ቤተክርስቲያኗ እንደ ማኅበረሰብ ግንባታ ማዕከል እንድትታይ አድርገዋታል።"
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ታሪክ የኢትዮጵያ ታሪክ አካል ኾኖ በምርምር እና በጽሑፍ ተጠብቆ እንዲቆይ ማድረግ ብሔራዊ ግዴታ ነው። የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን መሪ የኾኑት ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል ይህንን ጉዳይ በሰፊው ያንፀባርቃሉ። ብፁዕ ካርዲናል እንደሚሉት፣ በዘመናት ውስጥ የተፈጠሩት የቤተክርስቲያኗ ታሪካዊ ሠነዶች፣ መጻሕፍት፣ የካርታ መረጃዎች፣ የሕክምና እና የትምህርት ተቋማት መዛግብት የኢትዮጵያ ሀብት ናቸው።
እርሳቸው እንደሚያስረዱት፣ እነዚህን አያሌ የታሪክ ማስረጃዎች በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ውስጥ ተሰብስበው እና ተደራጅተው መቀመጣቸው የኢትዮጵያ ታሪክ ሙሉ እንዲኾን ያደርጋል። ይህ የትውልድ ቅርስ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንን ሃይማኖታዊ ትግል ብቻ ሳይኾን፣ ለሀገር ግንባታ ያበረከተችውን አወንታዊ አስተዋጽዖ ለቀጣዩ ትውልድ በግልጽ ለማሳየት ያስችላል ብለዋል።
በመጨረሻም አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ብፁዕነታቸው የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎትን እንዲጎበኙ በመጋበዝ እና የካቴድራሉን የአገልግሎት ክፍሎችን በመጎብኘት ተጠናቋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
ትዊተር:https//@wemezekr
ቲክቶክ፡https፡/tiktok.com/@wemezekrnals
ኢ-ሜይል፡- https://www.nala@nala.gov.et/
