ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
前往频道在 Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
显示更多2 935
订阅者
-124 小时
+3307 天
+38330 天
帖子存档
አድርገው ማቆማቸው እስኪታወቅ ድረስ በቀላሉ አማራን ጨፍልቀው ወደ ኤርትራ መሻገርና የየራሳቸውን ግብ ማሳካት እንደሚችሉ እርግጠኞች ነበሩ።ባልጠበቁት ሁኔታ ህወሃት የራሱን ስትራቴጅካዊ ስሌት ይዞ አማራን አልወጋም፥ ኤርትራ ላይም አልዘምትም ሲል ቀመሩ ተዛባ። የአማራው የህልውና ትግልም በመካከል በፍጥነት ሌላ ደረጃ ላይ ደረሰ።ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ በአንድ እጁ እየተዋጋ በሌላኛው እጁ የራሱን ትግሉን የሚመራ ተቋም ፈጠረ።ይህ ሲሆን የጨዋታው መልክ ሙሉ በሙሉ ተቀየረ ማለት ነው።
አብይ ግን እድሎች ከተገኙ አሁንም እዛው ጨዋታ ውስጥ መሆኑን እና ተስፋ አለመቁረጡን የሚያሳየው በተለይ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ አማራውን ለመነጠል የሚያደርገው ሩጫ ነው። በዚህ መሃል አንዳንድ አውቀው የተኙ ወይንም በአሞሌ ጨው ራሳቸውን የሸጡ የኛን ወገኖች ሳይ "ሌላው ሁሉ ይቅር ይህ ሁሉ ሩጫና ግርግር አማራን ብቻውን አቁሞ ለማጥፋት በመመኜት የሚደረግ መሆኑን እንዴት ማወቅ ተሳናቸው ?" እላለሁ።ለዚህ እፍኝ እድሜስ ስንት አመት አሞሌ ይላሳል?
በእኔ እምነት፦
የፕሪቶሪያ አፈራራሚዎች ዋና ግብ ፀረ-አማራ ብለው ያሰቧቸውን ሃይሎች አስተባብሮ እየተነሳ ያለው አዲሱ የአማራ አቢዮት መንፈስ ላይ ማዝመት ነበር።ለጊዜው አልተሳካም።
እነዚህ ሃይሎች የአማራ ልዩ ሃይል እንዲፈርስ ለአብይ ቀጭን ትእዛዝ ሰጠዋል።ልዩ ሃይሉ ፈረሰ። ያም ሆኖ ያሰቡት ሳይሳካ እንዴውም የፈረሰው ልዩ ሃይል ለትግሉ ልዩ ግብአት ሆነ።
ትንሽ ገፋ እና ደፈር አድርጌ ከደመደምሁ... የፕሪቶሪያው ስምምነት በራሱ "የአማራ ትንሳኤ" ፍርሃትና ድንጋጤ ውጤት ነው።አማራው ባይነሳ ኖሮ የፕሪቶሪያ ስምምነትም አይፈጠርም ነበር።ለዚህ ነው አንዳንድ ወገኖች የአማራው የህልውና ትግል የዘመናት ፍጅትና መጎሳቆል ውጤት መሆኑን ረስተው በፕሪቶሪያው ስምምነት ምክንያት የተፈጠረ ኩርፊያ የወለደው ሊያስመስሉት ሲሞክሩ ሲታይ አስቂኝና አስተዛዛቢ የሚሆነው።ፕሪቶሪያ የአማራን ትግል አልወለደም፥ የአማራ መነሳት ፕሪቶሪያን ወለደ እንጅ።
ቆላም ነፈሰ ደጋ ጨዋታውን በደንብ ተጫውተናል። ።ስርአቱንም እንደተደገመበት ሰይጣን አፍዝዘን አስቀምጠነዋል። እጣፋንታውንም በምንወስደው ቀጣይ ሙሉ ለሙሉ ገፍቶ የመጣል እርምጃ ላይ እንዲወሰን አድርገነዋል።
የዚህ ትብብር ስኬትና ውድቀት ግን የሚቀጥሉት ብዙ መቶ አመታት የእርስበርስ እልቂት ወይም ሰላምና ልማት ማለት ነው።
በዚህ አጋጣሚ፦ ባለሃብት ነን የምትሉና ይህን ትግል ለማፍረስ በድለላ የተሰማራችሁ ወገኖች ተው።!---ከፀሃይ በታች የምትሰሩት እያንዳንዱ ስራ ይታወቃል።እንኳን ከህዝብ ከጎረቤት ተጣልቶ መኖር ይቸግራልና አስቡበት።አርፋችሁ ስራችሁን ስሩ።
በዚሁ የፖለቲካ ድለላ ውስጥ የተሰማራችሁ አንዳንድ የሃይማኖት አባት ነን የምትሉ የየቤተ እምነቱ ሰዎችም ከዚህ ድርጊታችሁ ተቆጠቡ።ሌላው ቢቀር ቤተ እምነታችሁን ለሚያፈርስ ሃይል አካፋ አቀባይ አትሁኑ።ለምድርም ለሰማይም የማይሆን ነገር አትስሩ። በ80 አመታችሁ የሰላሳ አመት ጆሮ ጠቢን አትፍሩ።በውድቀታችሁ የጣላችሁትን ዘመንና ህዝብ ልናቃና ስንደክም ደንቃራ አትሁኑ።ትንሽ እንኳን እፈሩ።
ለውዱ የአማራ ህዝብ!
የአለምን መከራ ተሸክመሃል፥ እንድታልቅ ፍጅት ታውጆብሃል።ከዘመናት ሞት-ቀመስ እንቅልፍ በኋላ ተነስተሃል። ጠላትህ አቁስለህ የምትተወው አውሬ አይደለምና ሳትቀብረው እንዳትቀመጥ።ጠላት አንድነትህን በወንዝ ለመክፈል፥ በጎጥ ለመተልተል፥እየሰራ በመሆኑ በደምህ የገነባኸውን ቤት የሙጥኝ በል። እንደወትሮው ሁሉ በተለይ ደግሞ ከቅርብ ግዜ ወዲህ አብይ የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር እየሰራ በመሆኑ መዋደድህ የበለጠ መጠንከር ይኖርበታል። በየቀኑ የሚከፈለውን ዋጋ ባውቅም በነፃ ነፃ አይወጣምና አይዞህ በርታ!
ለመላው የኢትዮጲያ ህዝብ‼️
ይህ እብድ ሰውዬና ቡድኑ በስልጣን ላይ እስካሉ ድረስ የማይጎሳቆል፥ የማይራብ፥ የማይታረዝና ህልውናው አደጋ ውስጥ የማይገባ ኢትዮጲያዊ አይኖርም። በኢትዮጲያ ምድር ላይ ቆሞ መራመድ እስከቻለ ድረስ መሬቱንም ህዝቡንም በግራም ሳይቀር እየለካ ከመሸጥና ከማጥፋት አይመለስም። ስለዚህ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ይነሳ።
ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ‼️
ዛሬ ከአብይ ጎን ቁሞ የሚገኝ ብሄራዊ ጥቅም ነገ ከቀጠናው የሚመነጭ ትልቅ ብሄራዊ ኪሳራን ያመጣባችኋልና ከእውነት፥ ከፍትህና ከነፃነት ሃይሎች ጎን ቁሙ። በተለይ አንዳድ ሃገራት አብይን መደገፍ አቁሙ።አብይ አማራን ሲፈጅ፥
የትግራይን፥ የኦሮሞን፥ የጋምቤላን፥ የሲዳማን፥ የጉምዝን፥ የቤኒሻንጉልን፥ የአፋርን፥ የሶማሊን፥ የጉራጌን በአጠቃላይ የሃገሪቱ ህዝብ ላይ እሳት ለኩሶ እያቃጠለ ቆሞ መመልከት ነገ አለም ቢጮህ የማይፈታው ቀጠናዊና አለም አቀፋዊ ምስቅልቅል ይፈጥራልና አስቡበት።ፍትህና ነፃነት ደንበር የላቸውም። እንደ ፀሃይ ለሁሉም መሆን አለባቸው።
ለሚሊሻ፥መደበኛና አድማ ብተና ፖሊስ አባላት።---በራሳችሁ ፀብ ውስጥ የጠላት ዱላም ገላጋይም መሆን ታሪክ የማይረሳው ክህደት ነው። ወደ ወገኖቻችሁ ኑ።ያለበለዚያ እጣ ፋንታችሁ አንደኛው ተራራ ስር ወይ አንዱ ጎዳና ላይ ደመ-ከልብ መሆን ነው።አሁንም ቢረፍድም አልመሸምና ወደ ወገኖቻችሁ ኑ።በኛ በኩል እንደ ወንድምና እንደ አባት እንቀበላችኋለን።
ድል ለአማራ ህዝብ!
ክፋት ለማንም፥ በጎነት ለሁሉም
አዲስ ትውልድ፥ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
በጣም አመሰግናለሁ!!
02/11/2018 ዓ.ም
#ከአርበኛ_ዘመነ_ካሴ በመተከል ቀጠና #መተከል_ኮርስ ወስደው በተመረቁ ተማራቂ የፋኖ ሰራዊት አባላት የምረቃ ፕሮግራም ላይ የተላለፈ መልዕክት‼️
#እንዴት_ሰነበታችሁ‼️❓
እንኳን ለዚህ ቀን አበቃችሁ‼️እንኳን ደስ አላችሁ!
ከፊታችሁ በመቆሜ ታላቅ ክብር ይሰማኛል‼️።
ታሪክ የራሱ ነፍስና የራሱ ረቂቅ የስሌት ቀመር አለው። ከነመፈጠራቸው የማይተዋወቁ ሁለት ሰዎችን በራሱ ልብ መርምሮ፥ በራሱ ቀመር አንጥሮ ከየጥጉ ጎትቶ አምጥቶ ለአንድ ወርቃማ አላማ ሲል ያገናኛቸዋል። እናም ለብዙሃኑ እውነትና ነፃነት እንደጧፍ ያበሩ ዘንድ በፍቅር ያሰልፋቸዋል። ይበራሉ።በድቅድቅ ጨለማ መሃል የተስፋ ብርሃን የነፃነት ወጋገን ይሆናሉ።ይህ አስበው የማይዘልቁት የታሪክ ጥልቅ ምስጢር ነው።ታሪክ እኔንና እናተንም በዚህ ዘመን በዚሁ ስሌት ለአንድ ወርቃማ የትውልድ ፕሮጀክት አገናኝቶናል።ዛሬ እየታገልን ነው፥ነገ እናሸንፋለን።የአማራን ቀን እናመጣለን።
በድጋሜ እንኳን ደስ ያላችሁ‼️
ህልውናችን እስካልተረጋገጠ ድረስ የዛሬ አምሳ አመት በዚህ ቦታ ላይ ሌላ አማራ ቆሞ፥ ሁልጊዜም ስለመሰልጠንና ስለመዘጋጀት አስፈላጊነት ሊናገር ይችላል።መደራጀታችን፥ መሰልጠናችን፥ መታጠቃችንና ለህልውናችን መታገላችን የሚቆመው ህልውናችን የተረጋገጠ እለት ብቻ ነው።ይህ የዛሬው የእናንተ ምርቃት የአማራ ህዝብ ትግልና የሃገሪቱ እጣፋንታ ተገፍቶ አንድ ጫፍ ላይ የቆመበት ምእራፍ ላይ የሚደረግ ነው። ስራ የሚጠይቅ የድል ታዛ ላይ የቆመ እጅግ አጓጊ ምእራፍ ነው ።
ውድ ጓዶቼ በዚህ አጋጣሚ አደራ ልላችሁ የምፈልገው ብዙ ጉዳይ አለ፦
ዛሬ ለመመረቅ ላለፉት በርካታ ወራት ብዙ ወጣችኋል፥ብዙ ወርዳችኋል፥ ብዙ ላብ አፍሳችኋል። በአካልና በመንፈስ ጠንክራችኋል፥ የትግላችን ሀሁ እና ግብ ተገንዝባችኋል።በዚህ ሙሉ ቁመናችሁ መከላከያ የሚባል የአብይ አህመድ ታጣቂ ጋር ፊት ለፊት ትገጥማላችሁ።
ትግል ግን ሌላም መልክ አለው። ከራስ ጋር የሚደረግ ትግልና አብሮ ሲኖር ከጓድ ጋር የሚደረግ ትግል እጅግ ከባድና ፈታኞቹ የትግል መልኮች እንደሆኑ ልትገነዘቡ ይገባል። ወደ አብይ አህመድ መተኮስና አብይን ማሸነፍ ቀላል ነው፥ ከባዱ ወደ ራስና ጓደኛ ድክመቶች ማነጣጠር ነው።
አብይ በታንክና በድሮን ያልቻለውን ጦርነት በገንዘብ፥ በሽማግሌና በወሬ ሊያሸንፍ እየሞከረ ነው።አንዳንዴ ከሽህ የአብይ ታንከኛ አንድ ወሬኛ ትግላችን ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላልና ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል።እንግሊዞች "ስራ ለፈቱ እጆች ሰይጣን ስራ ይፈጥርላቸዋል" ይላሉ።ብዙ ጊዜ የወሬና ሃሜት ምንጩ መቦዘን ስለሆነ እያንዳንዱን ደቂቃ ስለትግላችን በመድከምና በማሰብ እናሳልፍ።
ታጋይ ወንድሞቼ ❗ ይህ በእናንተ ላብ፥በወንሞቻችሁ ደም እና በህዝባችን ሲቃ የተገዛ ትግል ነው። የአቢዮቱ ዘበኞች እናንተ ናችሁ።ስለዚህ ከፋፋይ፥ ለግልና ለቡድን ፍላጎት ብቻ የሚሰሩ መንፈሰ ደካሞች ቢገጥሟችሁ ናቋቸው፥ ታገሏቸው።ይህ ትግል የህልውና አደጋ ለገጠመው የአማራ ህዝብ የህልውና ጉዳይ ነው። የሚሳሱለት አይኖች፥ ሌት ተቀን የሚጠብቁት እጆች ይፈልጋል።እና አደራ!!
ክፋትን፥ ምቀኝነትን፥ ቅናትንና ተንኮልን ተፀየፉ። ማንም የግለሰብም ይሁን የቡድን ጠላት አማራ ላይ ይነሳ መግጠምና መጣል እንችላለን። እነዚህ የመፈስ ደዌዎች ከተጠናዎቱን ግን ከጠላት ቀድመው እኛኑ ይጥሉናል።ፖለቲካችን ችላ ያለው ፥ያልተሄደበት መንገድ ቅንነት ነው።አለም ደጋግሞ የሚወድቀውም በዚህ ምክንያት ነው። በተንኮልና በክፋት በቦካ ፖለቲካ አለም የራሱን እጅ እየበላ ለጊዜው ይረካ ይሆናል እንጅ የትም አይደርስም። ይህ የመሳሪያም የቅንነትም አቢዮት ነውና ክፋትንና ተንኮልን ራቁ።የወንድምን ስኬት ውደዱ።ለሌሎች መኖርን ልመዱ።ራስ ወዳድ እንዳትሆኑ። ህዝባችን እያለቀ ራስ ወዳድ እንደመሆን ትልቅ ወንጀል የለም።ከፍ ባላችሁ ቁጥር የበለጠ ትሁት ሁኑ።
ይህን የምላችሁ የአለም ፖለቲካ እንዴት እንደሚሰራና እንደሚሰራ የማላውቅ ቂል ሆኜ አይደለም፥
ይልቁንም በመደበኛ ፖለቲካው ውስጥ ያለው መደበኛ የቅጥፈት መንገድ ውጤቱ ውድቀት እንደሆነ የአለም ተሞክሮ በተለይ ደግሞ የራሳችን ልምድ ስለሚነግረኝ እንጅ።
ይህ ትግል የህዝብ ትግል ነው። ይህ ትግል ለአማራ ህዝብ የሚደረግ ትግል ነው። መነሻችንም መድረሻችንም ህዝባችን ነው። ምድራዊዩ እግዜራችን ህዝብ ነው። ይህን እግዜር አይኑን መጠንቆል ያስቀስፋል። በስህተት እንኳን ህዝብን የሚያስቀይም ነገር አንዳትሰሩ። ክልክል ነው። ህዝብ እንኳን መብቱን ሰብል የለበሰ የእርሻ መሬቱን ስትረግጥበት፥ የቤት አጥሩን ስትደገፍበት አይወድም። ህዝብ "ፈጣሪያችን" ነውና እንቅስቃሲያችን ያያል፥ እስትንፋሳችን ይለካል።ጥንቃቄ እናድርግ።
የአማራ ህዝብ የራሱ የሆነ ንፁህ ተቋም እንዲኖረው ብዙ ቀደምቶች ብዙ ደክመዋል።ታስረዋል፥ አካላቸውም ቅስማቸውም ተሰብሯል፥ህይወታቸውንም ሰጠዋል። በቀጠለ ጥረትና ብዙ ድካም በዚህ በኛ ዘመን ተሳክቷል። የአማራ ህዝብ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄን ፈጥሯል።ይህ ተቋም መድህናችን ሆኖ ወደምንፈልገው ግብ ያደርሰን ዘንድ በየዘርፉ የተሳሉ ፖሊሲዎች አሉት።የተቋማችን የመጀሪያውና ቋሚው ፖሊሲያችን ራስን መቻል ነው። ሁሉን አቀፍ ራስ በቅነትን በየቀኑ ማሳደግ ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ ድርጅታዊ ውስጣዊ አንድነታችን እናጠናክራለን። ራሱን ያልቻለ አንገት የሚያቅፈው የለውም።ስለዚህ የእዞች ውስጣዊ አንድነት፥ የድርጅታችን አፋብን ጠንካራ ውስጣዊ አንድነት እጅግ አስፈላጊ ነው።የህዝባችን አንድነት የመተንፈስ ያክል ፍፁም አስፈላጊ ነው።የተበተነ ህዝብ ነጥሎ የሚበላውን ጠላት ከየአቅጣጫው ይጋብዛልና።
ሁለተኛውና ተያያዥ ፖሊሲያችን ከራስ መቻል ላይ የመነጨ ከሌሎች ጋር የሚደረግ የተመረጠ በጎ ትብብር ነው። የተሰላና የተጠና ትብብር ሁልጊዜ አስፈላጊ ነው። ጥቅምህን በሚስጢር ኪስህ ይዘህ ፥ የሌላን ወገን ጥቅም ሳትነካ፥ የራስህን ሳታስነካ መተባበር ሁሌም ልክ ነው። ስለዚህ በአጭርም በረጅምም እንተባበራለን።የቀጠናው ሃይሎችም ጋር ቀጠናዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከጥቅማችን አኳያ እናብራለን። ፋኖ ልብ አለውም አላለውም የግዙፉና የውስብስቡ የምስራቅ አፍሪካ መልክአፖለቲካ አካል ሆኗል። ወይ ዋኝቶ ይወጣል ያለበለዚያ ግብግቡ በሚያስነሳው ማእበል ውስጥ ይሰጥማል።ግዙፉ ቁመናችን በስሌትና በጥበብ ታግዞ፥ የምላጭ ጠርዝ ላይ የመቆም ያክል ተጠንቅቆ ሌሎችን ሳይደፍቅ አሸናፊ ይሆናል።
ከዚህ አኳያ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚስተዋለው ግርግር አማራን ብቻውን ለማቆም ነው።‼️
በእርግጥ ማንም ሃይል መተማመኛው የራሱ አቅም ነው።የማይሸሽ፥ የማይለወጥና የማይነቅዝ የራስ አስተማማኝ አቅም ነው።ይህም ሆኖ አማራ በአለም ፊት ቆሞ ብቻውን ገለባብጦ ተራራውን ሜዳ ፥ሜዳውን ተራራ እንዳላደረገ ሁሉ የአማራ ትግል "ተነጥሎ" የቆመ እለት ይከስማል የተባለ ይመስል ይህ ሁሉ ግርግር ፋኖን ብቻውን ለማቆም ነው።
ከሶስት አመታት በፊት ሁሉም የጨዋታው ተሰላፊ የየራሱን ስሌት ይዞ በፕሪቶሪያ መድረክ ቢጫዎትም "በስምምነቱ" ውስጥ የነበረው የብዙዎች ተሰላፊዎች "ድብቅ" የጋራ ግብ ግን መቀጣጠል ጀምሮ የነበረውን የአማራ የአቢዮት እሳት በጋራ የማጥፋት እቅድ ነበር ብዬ አምናለሁ ። በዚህ " አደገኛውን ሰደድ የማጥፋት ተልእኮ" ውስጥ ህወሃትና ብልፅግና በደስታ አብረው እንደሚሰለፉ የፕሮቶሪያ ስምምነት "ሽማግሌዎቹም" እርግጠኞች ነበሩ ማለት ይቻላል። ምናልባት የትግራይ ሃይሎች ታሪካዊ ውሳኔ ወስነው ራሳቸውን ግሉል
የአፋብን/ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክፍለ ጦር በሺዎች የሚሆኑ አዲስ የፋኖ አባላትን በመተከል ቀጠና በድምቀት አስመረቀ!
ሐምሌ 2/11/2018 ዓ.ም
በአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ውስጥ ትልቅ ሚና እየተጫወተ የሚገኘው የአፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክፍለ ጦር በሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ የፋኖ አባላትን "መተከል ኮርስ" ብሎ በመሰየም በመተከል ቀጠና በዛሬው ዕለት በደማቅ ወታደራዊ ስነስርዓት አስመርቋል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ የአፋብን ሊቀ መንበር አርበኛ ዘመነ ካሴ፣ የቴዎድሮስ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በዕለቱ አርበኛ ዘመነ ካሴ ለአዲስ ተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ይህ የምርቃት ፕሮግራም የአፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ ያለውን የማደራጀትና የማሰልጠን አቅም ማሳያ ከመሆኑም ባለፈ፣ ለህልውና ትግሉ አዲስ ጉልበት ይሰጣል።
ድል ለአማራ ህዝብ!
ክፋት ለማንም፥ በጎነት ለሁሉም
አዲስ ትውልድ፥ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
#_ሁለት_የፖሊስ_አመራር_እና _ሚሊሻው ወደ 54ኛ ክፍለ ጦር ፋኖን ተቀላቀሉ።
^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^
....ሐምሌ02/2018 ዓ.ም
የአብይ አህመድ ስርዓትና የፀጥታ መዋቅር እየፈረሰ ነው። ለብዙ ወራት ለመውጣት አቅደን ነበር ያሉት ወደ ፋኖ የተቀላቀሉት ፖሊሶች የቆየንበትን የትግል ዘመን በታሪካችን ህዝብ የበደልንበትና የበዳዮች ተባባሪ የሆንበትን ህዝባችንና ይቅር ይበለን በማለት ከድጎፅዮን ከተማ
1ኛ.ሳጅን ልመንህ አንዷለም... የትራፊክ ፖሊስ ምክትል
2ኛ. ምክትል ሳጅን ተሾመ ፈንታ....ፓለስ
3ኛ.ልንገረው ስለሽ .....ሚሊሻ ሲሆኑ ወደ 201ኛ 54ኛ ክ/ጦርን ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ተቀላቅለዋል።
አብይ የአማራ ልዩ ኃይልን በሴራ እንደበተነው እናውቅ ነበር እኛንም ከፋኖ ጋር ትሰራላችሁ በማለት አያምኑንም በየጊዜው ቁጥጥርና ጭቆና ይበዛብን ነበር ያሉት ፖሊሶቹ ዛሬ የነፃነት አየር ከፋኖ ጋር ተንፍሰናል ሲሉም ደስታቸውን ገልፀዋል።
ብልጦች ህይወታቸውን እያተረፉ ነው።
አማራነት ያሸንፋል።
አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
አስደናቂው የ55ተኛ ክ/ጦር ተጋድሎ
ሀምሌ 2/2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴዎድሮስ እዝ 105ተኛ ኮር 55ተኛ ክ/ጦር በዛሬው እለት ከለሊቱ 11:30 በዳንግላ ወረዳ ጫራ ከተማ ላይ በወሰደው አስደናቂ የማጥቃት እርምጃ አገዛዙን ጥምር ጦር አንድ ሬጅመንት ሙሉ በሙሉ በመደምሰስ ከስራ ውጭ አድርጓታል ።
በውጊያው የ55ተኛ ክ/ጦር 3ተኛ እና 4ተኛ ሻለቆች ከክፍለጦራችን ቃኝእና መሀንዲስ እና ከዳንግላ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት አመራሮች ጋር በመናበብ ታአምራዊ ውጊያ በማድረግ በmላት ላይ ሰብአዊ ቁሳዊ እና ሞራላዊ ጉዳት አድርሷል ።
በዚህ አውደ ውጊያ
1 ዲሽቃ
1 የዲሽቃ ተቀያሪ አፈሙዝ
3 ብሬን
2 m14
1ፋል
52 ክላሽንኮፍ
6 አብራራው
13 sks
450 የዲሽቃ ጥይት
250 የብሬን ተተኳሽ
1300 የክላሽ ተተኳሽ
የሟ,ች እና የቁsለኛ ቁጥር በርካታ ስለሆነ ቆጠራ ላይ ነን
ድሉ ይቀጥላል
ምስጌ ዘድንግል
ማሳሰቢያ በፎቶው ላይ የሚታዩ መሳሪያዎች በአንድ ግንባር ብቻ የተማረኩ እንጅ ሙሉ የምርኮ መሳሪያ የሚያሳይ አደለም
አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በየቦቅላ ከተማ ድል ተቀዳጅቷል!!
~~~~~~~
በዛሬው ዕለት ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር በ206 ኮር ቀጠና የቦቅላ ከተማ ከሌሎች ክፍለ ጦር ጋር ባካሄደው ውጊያ በርካታ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ መማረክ ችሏል።
ድርጅት በመጠበቅና ከሌሎች ክ/ጦሮች ጋር በመቀናጀት ሁሌም ድል በማድረግ የሚታወቀው 64ኛ ክ/ጦር በ206 ኮር በሚያስተዳድረው ቀጠና ጎዛም ወረዳ የቦቅላ ከተማ ሰፍሮ በሚገኘው የአገዛዙ የጠላት ኃይል ላይ ከ24ኛ እና 34ኛ ክ/ጦር ጋር በመቀናጀት ባአካሄደው ውጊያ #አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በተሰጠው የውጊያ ቀጠና ብቻ በርካታ የጠላት ሀይል በመደምሰስና በማቁሰል የአገዛዙ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን መማረክ ችሏል። ክ/ጦሩ በአካሄደው ውጊያ ያገኘው ድል:-
➤2 ጥቁር ክላሽ
➤2 ኮሪያ ክላሽ
➤አንድ 10 ቁጥር ክላሽ
➤ጠ/ድምር= 5 ክላሽ ማርኳል። በአውደ ውጊያ የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች ዛሬም እንደ ልማዳቸው ፉከራ በተቀላቀለበት ወኔቸው የጠላት ኃይልን ሲያደባዩት ውለዋል። በእጃቸው ላይ ቁስል አስርው ውጊያው የመሩት ወታደራዊ አመራር እና በአንድ ክላሽ አራት ክላሽ የማርኩ የክፍለ ጦሩ ምሽግ ሰባሪ ጀግኖችን ጀብድ ይዘን እንመለሳለን።
ለአናሸንፍ የጀመርነው ትግል የለም! አማራነት ወይም ሞት!!
ድል ለአማራ ሕዝብ🔥🔥🔥 ድል ለአማራ ፋኖ💪💪💪
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
🎯 የትውልዱ መልክና ግርማ!
(አዲሱ ደረበ)
በማኅበራዊና ፖለቲካዊ ሳይንስ እሳቤ ውስጥ፣ የታሪክን አቅጣጫ የሚቀይሩና የሕዝቦችን የህልውና መስመር አድሰው የሚጽፉ ትውልድ አሻጋሪ መሪዎች በዘፈቀደ አይፈጠሩም። እሳቤያቸው ከዘመኑ የቀደመ፣ ፅናታቸው ከብረት የጠነከረና ልባቸው እንደ ውቅያኖስ የሰፋ መሪዎች የክፍለ-ዘመናት እምቅ የጭቆና ብሶትና የሕዝብ መቅበዝበዝ የወለዳቸው የታሪክ ስጦታዎች ናቸው።
እነዚህ መሪዎች የሕዝባቸውን የትግል ሰንሰለት አስተሳስረው ወደ ድል ማማ የሚያሻግሩ፣ በፖለቲካዊ ብስለት፣ በወታደራዊ ሳይንስ፣ በጂኦ-ስትራቴጂካዊ ግንዛቤና በጥልቅ ታሪካዊ መረዳት የተገነቡ ሁለንተናዊ መሐንዲሶች ናቸው። በአማራ ሕዝብ የህልውና ትግል ውስጥ፣ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሊቀመንበር የሆነው ራስ-አርበኛ ዘመነ ካሴ የዚህ ሳይንሳዊ ሀቅ ሕያው ማሳያ ነው።
ራስ-አርበኛ ዘመነ ካሴ ተራ የትግል አጋጣሚ የፈጠረው መሪ አይደለም። ሙሉ ወጣትነቱን፣ ዕድሜውን፣ አቅሙንና መላው ቤተሰቡን ለአማራነት እውነት ያሰለፈ፣ በትግል እቶን እሳት ውስጥ ተፈትኖ የወጣ ጥንቅቅ ያለ ምሁርና አብዮተኛ ነው። አማራነት እንደ ወንጀል ተቆጥሮ ሕዝባችን በአገር በቀል ፋሽስቶች የታሪክ ፍርደኛ ተደርጎ ከተፈረጀበት አስከፊ ዘመን መባቻ ጀምሮ፣ ራስ ዘመነ ካሴ ከኤርትራ በረሃዎች አንስቶ እስከ አሁኑ አብዮታዊ ትግል ድረስ አማራነትን ሰብኳል። እልፍ የተኛንና የተሸማቀቀን ሕዝብ በጥልቅ የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና ቀስቅሶ አነቃቅቷል። የእሱ አስተዋይና ስልታዊ የአብዮት ጥሪዎች፣ አያሌ የቁርጥ ቀን ወጣቶችን የነፃነት ትጥቅና ሞራል አስታጥቀው የትግሉ ግንባር ቀደም ተሰላፊ አድርገዋቸዋል።
በአብዮታዊ ትግል ውስጥ የላቁ መሪዎች የሚለኩባቸው መሠረታዊ መለኪያዎች አሉ፤ እነሱም ጽናት፣ ቻይነት፣ ስልታዊ ምሁርነትና ተራማጅ አመራርነት ናቸው። ዘመነ ካሴ በዙሪያው ባሉ ታጋዮችና ሕዝቡ ዘንድ “አባ መቻል” የሚባለው ዝም ብሎ አይደለም፣ አእምሮው፣ ልቡና ትክሻው በእጅጉ ሰፊ በመሆኑ ነው። መከራን፣ እንግልትን፣ ክህደትን፣ የስም ማጥፋት ዘመቻዎችንና የትግል ስንክሳሮችን ሁሉ ያለ ምንም ድካም ተሸክሞ ያሻግራል። እርሱ ያችን አይነ-ግቡ ሳቅ እየሳቀ፣ የጠላትን ሰይፍና የውስጥ ደካሞችን ሴራ ሁሉ በትዕግሥት አክሽፎ ያልፋል። የከፋው አይመስል፤ የደከመው አይመስል፤ የራበው አይመስል!
ሊጥሉት፣ ሊያወርዱትና ስሙን ሊያጠፉ የሞከሩ የውስጥና የውጭ አተሎች ሁሉ ወርደው ተፈጠፈጡ እንጂ፣ ራስ-አርበኛ ዘመነ ካሴን የነቀነቀውና ከዓላማው ያናወጠው አንድም ኃይል የለም። በእሱ ቦታ ብሆን ብዬ አሰብኩት እኮ! እውነት ለመናገር፣ ለአንድ ወር እንኳ በዚህ ከፍታ መታገልና፣ ያንን ሁሉ ማዕበል ተቋቁሞ ሕዝብን ማታገል አይቻልም፤ ኧረ ፍጹም አይታሰብም!
በዓለም ታሪክ ውስጥ የሕዝባቸውን ሕልውና ያስጠበቁና ከጥፋት የታደጉ ታላላቅ አብዮተኞች በሙሉ የዘመነ ካሴን ዓይነት መዋቅራዊና ስነ-ልቦናዊ ግርማ ነበራቸው። ዘሜን በታሪክ መድረክ ከታዩት እንደነ ጆርጅ ዋሽንግተን፣ ጋሪባልዲ፣ ፊደል ካስትሮ እና ማኦ ዜዱንግ ካሉ ግዙፍ የአብዮት መሪዎች ጎን አሰልፈን ስንመለከተው የትግላችንን መዳረሻ እናውቃለን።
ሀገራቸው ልትበታተን ስትቃረብ ወታደራዊና ጂኦ-ፖለቲካዊ ስልትን በመጠቀም የቱርክን ሕልውና እንደታደገው እንደ ሙስጠፋ ከማል አታቱርክ፣ ወይንም የአፓርታይድን ስቃይና እሥራት በትዕግሥትና በቻይነት አሸንፎ ሕዝቡን ወደ አንድነት እንደመራው እንደ ኔልሰን ማንዴላ ሁሉ፣ ዘሜም በጥልቅ ስልታዊ ምሁርነቱ የውስጥ ቁስሎችን እያከመ ትግሉን ወደፊት ያስኬዳል። ሙሉ ሕይወታቸውንና ወጣትነታቸውን ለሕዝባቸው ነፃነት እንደገበሩት እንደነ ሆ ቺ ሚን እና ቼ ጉቬራ ሁሉ፣ የዘሜም የኤርትራ በረሃዎችና የአማራ ተራሮች ስንክሳር ይህንኑ አብዮታዊ ታማኝነትና የትውልድ መሪነት በተግባር ያሳያል።
እንደ ዘመነ ካሴ ዓይነት ትውልድ አሻጋሪ መሪዎች በአመቺ ሕይወት ውስጥ አይበቅሉም፤ በትግል እቶን፣ በከፋ መከራ፣ በሕዝብ ዕንባና በጠላት የጭካኔ ቀንበር ውስጥ ተፈትነውና ተቅንብበው ነው የሚወጡት። እንዲህ ዓይነት መሪዎች አንዴ ከተፈጠሩ በኋላ፣ ሕዝቡ እንደ ዓይን ብሌኑ ሊጠብቃቸውና ሊንከባከባቸው ይገባል። ምክንያቱም የጠላት ዋነኛ ስትራቴጂ የሕዝብን ኮምፓስና መሪ ማጥፋት በመሆኑ ነው። የእንዲህ ዓይነት መሪዎች መኖር የትግሉን ዕድሜ ያሳጥራል፣ መስዋዕትነትን ይቀንሳል፣ ድልን ያረጋግጣል።
ራስ-አርበኛ ዘመነ ካሴ ሆይ! አንተ ስላለኸንና ትግሉን በሳይንሳዊ፣ በተራማጅና በበሰለ አመራርነትህ ስለምትመራው የታደልን ነን። ያቺን የአሸናፊነት ሳቅህን እየሳቅህ፣ መከራውን ሁሉ በትከሻህ ተሸክመህ፣ የአማራን ሕዝብ ዘላለማዊ ህልውና እና ነፃነት በተግባር እንደምታረጋግጥ ሙሉ እምነት አለኝ። ታሪክ ያከበረህ መሪ ነህ፤ ትውልድም በአክብሮት ይጠብቅሃል!
ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯
+1
የቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 55ኛ ክፍለ ጦር አንበሶች በዛሬው ዕለት ባደረጉት ፈጣን የፀረ ማጥቃት እንቅስቃሴ ዲሽቃን ጨምሮ ብሬንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን ማርከዋል። ይህ በዘፈቀደ የተገኘ ድል አይደለም። ዲሽቃን ለማንሳት በተደረገ ውጊያ የአንድን እብድ ስልጣን ለመጠበቅ ሲሉ የሚረግፋ ‘ጭቃ የሆኑ የኢትዮጵያ ልጆች’ ተንቀሳቃሽ ምስል ማየት ቢዘገንንም በፍሊት የተረጩ እንጅ በአልሞ ተኳሽ ብቻ የተመቱ አይመስሉም። በሌላ ግንባር 206ኛ ኮር 24ኛና 34ኛ ክፍለ ጦር እንዲሁም 201ኛ ኮር 64ኛ ክፍለ ጦር የቦቅላ ላይ የቡድንና ነፍስ ወከፍ መሳሪያ ምርኮን የተገኘበት ውጊያ አድርጓል።
፤
ቴዎድሮስ ዕዝ ሳምንት ባልሞላ ተከታታይ ጊዜ ጎህ በቀደደ ቁጥር የቡድን መሳሪያ ምርኮ የምስራችን እያሰማን ነው። የጠላትን ስስ ቦታ ለይቶ መምታት፣ የተመታው ሀይል እንዳይፀና ማድረግና ተከታትሎ መደምሰስ የፋኖ ሰራዊታችን ያዳበረው ጉልበት እየሆነ መጥቷል። የሌሊት ውጊያን ልምምድን መተግበር ወራቶችንም ፈጅቶም ቢሆን አሁን ውጤት እየተገኘባቸው ነው።
፤
ሞትን ለናቁ ቴዎድሮስን መሳይ የቴዎድሮስ ልጆች ሁሉ አክብሮታችን እጅግ ላቅ ያለ ነው።✌🏿
+2
በአገዛዙ ከባድ መሳሪያ ድብደባ የአርሶ አደር እንስሳት ተገደሉ!!
በመቅደላ ወረዳ አሶል ቀበሌ በተሰነዘረው የሞርተር ጥቃት በአካባቢው በሚገኙ የአርሶ አደሮች ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ታውቋል።
ከስፍራው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ በ11ኛ ዕዝ ዋና አዛዥ ጀነራል አድማሱ ትዕዛዝ በተሰነዘረው በዚህ የከባድ መሳሪያ ጥቃት የአርሶ አደር አቶ ስጋት አለሙ ንብረት የሆኑ እንስሳት ላይ ጉዳት ደርሷል። በዚህም መሰረት፡-
አንድ ላም
አንድ አህያ እና
አንድ ወይፈን በጥቃቱ ሰለቫ ሁነዋል።
ይህ ጥቃት በአማራ ህዝብ ላይ ለዓመታት ሲፈጸም የቆየው ግድያ፣ መፈናቀልና የሀብት ንብረት ማውደም ቀጣይ አካል መሆኑን የአካባቢው ምንጮች ገልፅዋል ። በማንነቱ ላይ ያነጣጠረውና ህዝብን የማፅዳት እንዲሁም ንብረትን የማውደም፣ የመዝረፍና የማረድ ተግባር ዛሬም በተጠናከረ መልኩ እየቀጠለ እንደሚገኝ ማሳያ ነው ተብሏል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩነኒኬሽን መምሪያ!
ሀምሌ 2/2018 ዓ.ም
ሰበር ዜና!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ 24ኛ ክፍለጦርና እና 35ኛ ክፍለጦር በጋራ ታላቅ ጀብድ በመፈፀም ድል ተቀዳጁ።
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ከ104ኛ ኮር 24 ክፍለጦር እና ከ101ኛ ኮር 35 ክፍለጦር አገዛዙ ከመርሳ የገበሬዎችን 50 ግመል በማስገደድና በመሰብሰብ ሬሽን ፣ ተተኳሽ ፣ እና መሳሪያ በመጫን ወደ አበጋር ሜዳና ፀዶት ሚካል አጂቦ የመጣውን የስርዐቱን ዙፉን ጠባቂ ሰራዊት ገሚሱን ሙትና ገሚሱን ቁስለኛ በማድረግ ወደ አሰበውና ወደ አቀደው ቦታ ሳይደርስ የያዘውን ቁሳቁስ እያንጠባጠበ ወደ መርሳ ከተማ እንድመለስ አድርገውታል።
በዚህ አውደ ውጊያ ትላንት ሀምሌ 02/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 5:30 ጀምሮ ከማህበረሰቡ 50 ግመሎችን በማስገደድ ሰብስቦ የተለያዩ የሊጀስቲክ አቅርቦትና መሳሪያ በመጫን ከመርሳ ወደ አበጋር ሜዳ:ፀዶት ሚካኤል 24ኛ እና 35ኛ ክፍለጦርን አፍናለሁ ብሎ የሚያስበው የስርዐቱ ግትልትል ጦር ከ35ኛ ክፍለጦር በክፍለጦሩ ቃኝና ከ24ኛ ክፍለጦር በአንደኛ ሻለቃ ቃኝ ወደ መግደያ ቦታ ስቦ በማስገባት ሲቀጠቅጡት ይዞት ስንቀሳቀስ የነበረውን ሬሸን እና ሎጀስቲክ እያንጠባጠበ ወደ መርሳ ከተማ እንድፈረጥጥ ሆኗል።
በዚህ የተበሳጨው የጥላት ሀይል ሲፈረጥጥ መንገድ ላይ ያገኘውን ሰለሞን ደስየ የተባለ የአምሮ በሽተኛ መንገድ ላይ ነፃ እርምጃ ወስዶበት ፈርጥጧል።
በሌላ አውደ ውጊያ በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ኤጀርሳ ቀበሌ በአካባቢው በአህመድ እድሪስ የምትመራውን ና የባለሸርጡ አካል የሆነችውን የአባት አርበኞች ስብስብ ወደ ኤጀርሳ የተንቀሳቀሰውን የብአደን ምንጣፍ ጎታች ሚሊሻና አድማ ብተና ሙትና ቁስለኛ አድርገው መልሰውታል። በዚህም 5 የሚሊሻያ ና አድማ ብተና ሱደመሰስ 7ቱን ደግሞ ቁስለኛ አድርገው ወደ መጣበት ቢስቲማ መልሰውታል ሲል የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ35ኛ ክፍለጦር ቃል አቀባይ ፉኖ ደምሌ መኮነን መረጃውን ልኮልናል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ሀምሌ 02 /2018 ዓ.ም
ኮንስታብል እሱባለው ሀብታሙ ከነ ሙሉ ትጥቁ በመካነሰላም ግንባር ፋኖን ተቀላቀለ!!
በየቀኑ በቡድንም በተናጠልም የጠላት ኃይል ወደ ፋኖ እየገባ ነው:: በዚህም መሰረት የአድማ ብተና አባሉ ኮንስታብል እሱባለው ሀብታሙ ከጠላት ጋር በማበር የራሴን ህዝብ ከዚህ በላይ ልበድል አልፈልግም በማለት የአፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ እዝ 105 ኛ ኮር 29ኛ ክፍለ ጦር ሰራዊትን በዛሬው እለት ተቀላቅሏል:: የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ም/ኃላፊ አርበኛ አበራ አቢ ከጓዶቹ ጋር ሆኖ ኮንስታብሉን ተቀብሎታል::
የአማራን ህዝብ ላይ በምድርም በሰማይም እየተኮሰ ካለው የአብይ አህመድ መንግስት ጋር የተሰለፉ የፀጥታ ኃይል አባላት እየፈፀሙ ያሉት የግፍ ግፍ አንገሽግሾት ወደ ፋኖ መምጣቱን የገለፀው ኮንስታብሉ መከላከያ ሰራዊት አድማ ብተና እና ፓሊስ እንድሁም ሚሊሻን እንደት እየተጠቀመበት እንደሆነም አብራርቷል:: እንደ ኮንስታብሉ ገለፃ የአማራ ክልል የፀጥታ ሀይል አባላት ለመከላከያ ጥይት ማብረጃ ሆነዋል:: ከፊት ግቡ እየተባልን እንገደዳለን ሲልም ነው ኮንስታብሉ የነበረውን ሁኔታ በማስታወስ የገለፀው::
አማራ ሆኜ በአማራ ላይ ስተኩስ የነበረው ሴራው ስላልገባኝ ነበር አሁን ህዝቤን ለመካስ መጥቻለሁ ሲልም ኮንስታብል እሱባለው ተናግሯል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩነኒኬሽን መምሪያ
ሀምሌ 2/2018 ዓ.ም
