ch
Feedback
Education For Generation - EFG

Education For Generation - EFG

前往频道在 Telegram

╱◥██████◣ │∩│🪟▤│🪟│ ▓▆▇█▓🚪▓█▇ Education for generation (EFG) "ትምህርት ለትውልድ!! https://t.me/EFG2018T ዛሬ የምንዘራው እውቀት የነገዋን ኢትዮጵያ ፍሬ ያበቅላል።" መ/ር በላይ ክብረት ከሰሜን ሸዋ ዞን ለትምህርት ጥራት እንተጋለን !! @EFG77777

显示更多
4 597
订阅者
+324 小时
+387
+18030
帖子存档
+8
ለጓደኞቻችሁ ይን ሀገራዊ ራዕይ ያለውን ተወዳጅ ቻናል ሼር አድርጉላቸው Join us for more 👉 ተወዳጁን የቴሌግራም ቻናል በዚህ ሊንክ ይቀላቀሉን ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ 🍁 JOIN: Channel https://t.me/EFG2018T 🍁 JOIN : Group https://t.me/EFG2018 "ትምህርት ለትውልድ!! ዛሬ የምንዘራው እውቀት የነገዋን ኢትዮጵያ ፍሬ ያበቅላል!! መ/ር በላይ ክብረት (ከሰሜን ሸዋ ዞን አሳግርት ወረዳ )

100 ኢትዮጵያውያን ነፃ የውጭ የትምህርት ዕድል ማግኘታቸውን የእስራኤል ኤምባሲ ገለጸ የኢትዮጵያና እስራኤል የትብብር መስኮች ውስጥ አንዱ በሆነው የትምህርት ዕድል፣ በዚህ ዓመት 100 ተማሪዎች በመንግስት ለመንግስት በሚደረገው ግንኙነት ወደ እስራኤል ለትምህርት ማቅናታቸውን የእስራኤል ኤምባሲ ለአሐዱ ገልጿል። በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብረሃም ንጉሴ፤ ተማሪዎቹ በተለያየ መስክ ሙያ ሰልጥነውና ልምድን ቀስመው የሚመለሱባቸው ሁኔታዎች መኖራቸውን ገልጸዋል። ከእነዚህም መካከል በመንግስት ለመንግስት በሚደረገው ግንኙነት፣ በእስራኤል የውጭ ግንኙነት ማዕቀፍ ውስጥ የሚሰጠው የትምህርት ዕድል አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። በግብርና፣ ቴክኖሎጂ፣ ህክምና እንዲሁም በሰላምና ፀጥታ ዘርፎች የረጅም እና የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆናቸውን የገለጹት አምባሳደሩ፤ ስልጠናው የሴቶች የአመራር ክህሎት እና የህፃናት ዕድገትንም የሚያካትት መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪም በግሉ ዘርፍ በሚደረግ ግንኙነት ባለሙያዎችን በተለያየ መንገድ በማሰልጠን ወደ ስራ የሚያስገቡበት ሁኔታ መኖሩን አንስተዋል። ለአብነትም "Save a Child's Heart" የተባለው ድርጅት በእስራኤል ሀገር ለአምስት ዓመታት ለአምስት የህክምና ባለሙያዎች የትምህርት ዕድል በመስጠት፣ አሁን ላይ በኢትዮጵያ በስፔሻሊስትነት ደረጃ እየሰሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

New Ethiopian music Belay kibiret 2018 ተስፋ አትቁረጥ ልቤ Tesfa Atkuret Libe.mp3

Track 12 ተስፋ አትቁረጥ ልቤ የምታምነው ጠፋ በዚህ ዘመን ውለታ የሚቆጥር ማንንም አላየን ልብህን ቢሰብሩት በክፉ ክህደት ብቻህን ብትቀርም በከባድ ጭንቀት ሰው እንደ ነፋስ ወዲያ ወዲህ ይላል የ
Track 12 ተስፋ አትቁረጥ ልቤ የምታምነው ጠፋ በዚህ ዘመን ውለታ የሚቆጥር ማንንም አላየን ልብህን ቢሰብሩት በክፉ ክህደት ብቻህን ብትቀርም በከባድ ጭንቀት ሰው እንደ ነፋስ ወዲያ ወዲህ ይላል የገባው ቃል ኪዳን በአንድ ጀምበር ይፈርሳል ተስፋ አትቁረጥ ልቤ (ተስፋ አትቁረጥ) ይህ ሁሉ ያልፋል በጊዜው (ያልፋል በጊዜው) ከፈጣሪ በቀር የሚታመን የለም ጽናቱን ለነፍስህ ዛሬውኑ ለግሰው ተስፋ አትቁረጥ ልቤ (አትቁረጥ) ወዳጅ ነኝ ይሉሃል ለጥቅም ሲያልሙ አንተን ጥለው መሄድ በፍጹም አይሳለሙ በሰው ላይ አትደገፍ የሸንበቆ በትሩ እውነቱን አጥፍተው በሀሰት ቢዘምሩ ዓይኖችህን ወደ ላይ ብቻ አንሳና በርታ በትዕግስት በጽኑ ምስጋና ተስፋ አትቁረጥ ልቤ (ተስፋ አትቁረጥ) ይህ ሁሉ ያልፋል በጊዜው (ያልፋል በጊዜው) ከፈጣሪ በቀር የሚታመን የለም ጽናቱን ለነፍስህ ዛሬውኑ ለግሰው ተስፋ አትቁረጥ ልቤ (አትቁረጥ) ሰው ይለወጣል ወቅቱን ጠብቆ ፈጣሪ ግን ያውቅሃል ከውስጥህ ዘልቆ አይዞህ አትፍራ አንተ ብቻህን አይደለህም እውነቱ ሲገለጥ መቼም አትሸነፍም (ጽና ልቤ... ጽና)ተTraስፋስፋ አትቁረጥ ልቤ (ተስፋ አትቁረጥ) ይህ ሁሉ ያልፋል በጊዜው (ያልፋል በጊዜው) ከፈጣሪ በቀር የሚታመን የለም ጽናቱን ለነፍስህ ዛሬውኑ ለግሰው ተስፋ አትቁረጥ ልቤ (አትቁረጥ) (ጽና... ጽና) አይዞህ ልቤ ተስፋ አትቁረጥ የታመነው እሱ ነው (ጌታ ብቻ) (ተስፋ አትቁረጥ) በፈጣሪህ ታመን (ተስፋ... ተስፋ) ጽና ልቤ... ጽና... (ጽና...) ድ/መ/ር፦ በላይ ክብረት ሰላም ለኢትዮጵያ

ማሳሰቢያ ልምድ መለዋወጣችን መልካም ሆኖ ሳለ ለመምህራን በሙሉ በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ 2015 ተዘጋጅቶ የነበረው ስርአተ ትምህርት ተንደገና በአዲስ ተከልሶ የተዘጋጀ መሆኑ ይታወቃል ። ነገር ግን አንዳንድ የቴሌግራም ገፆች ላይ የሚለቀቁ አመታዊ እቅዶች ከአሁኑ መፅሐፍ ጋር የማይዛመድ ስለሆነ ይዘቱ ትኩረት ሰጥታችሁ ስሩ ። በነፃ አገኘን ብላችሁ ግብአት አታበላሹ ። ነገ በባለሙያዎች ሲታይ ተጠያቂ እንዳትሆኑ ። ሌሎችም ክልል የምትገኙ መምህራን ።

Share አመታዊ እቅድ እጣ የወጣለት እድለኛ ነው በዚህ መሰረት አቅዶች ታቅደው ተዘጋጅተዋል plan 2019.pdf

+5
የክበባት ማቋቋሚያ ጋይድ ላይን.docx1.10 MB

+1
የመምህራን_ልማትና_አስተዳደር_ምርመምህራን_ተግባርና_ሃላፊነት.docx0.24 KB

የፈተና ኮሚቴ.docx0.23 KB

ይህን ፎቶግራፍ በመከተል በዚህ ቴሌግራም ላይ ያሉ ከዚህ ቀደምት የተለቀቁ መረጃዎችን በሙሉ መመልከት ትችላላችሁ
ይህን ፎቶግራፍ በመከተል በዚህ ቴሌግራም ላይ ያሉ ከዚህ ቀደምት የተለቀቁ መረጃዎችን በሙሉ መመልከት ትችላላችሁ

2019 ዓ ም ካሌንደር በpdf

Education For Generation - EFG 📣 ለክቡራን መምህራን እና የትምህርት አመራሮች ታላቅ የምስራች! 📣 ቀን: 02/10/2018 ዓ.ም. "Education For Generation" ለሁሉም ክልሎች የሚሆኑ፣ በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት መሠረት በጥራት የተዘጋጁ አመታዊ የትምህርት እቅዶችን በዎርድ (Editable Word) እጅግ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቦልዎታል። እቅዶቹን እንደ ፍላጎትዎ በቀላሉ ማስተካከል (Edit) ይችላሉ! 📚 የምናቀርባቸው ዋና ዋና አገልግሎቶች፦ ክፍል1 ለሁሉም ክልሎች እና ከተሞች 1️⃣ አመታዊ የትምህርት እቅዶች (Annual Plans)፦ 40 ብር ብቻየKG (ኬጂ) ደረጃ የትምህርት እቅዶች • ከ1ኛ - 8ኛ ክፍል፦ አማርኛ፣ English፣ ሒሳብ፣ አካባቢ ሳይንስ፣ General Science፣ ግብረገብ፣ ዜግነት፣ CTE፣ IT፣ ስነ-ጥበባት፣ ህብረተሰብ፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ያካተተ • ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል፦ አማርኛ፣ English፣ Mathematics፣ Geography፣ History፣ Agriculture፣ Biology፣ Physics፣ Chemistry፣ IT፣ Citizenship እና ሌሎችንም ያካተተ 2️⃣ የዲፓርትመንት እና የአደረጃጀት እቅዶች ዋጋ 100 ብር ብቻ በየክፍሉ ለሚገኙ የትምህርት ክፍሎች ሁሉ የተዘጋጀ 3️⃣ የቤተ-ሙከራ (Laboratory) እቅዶች ዋጋ __ ብር ብቻ፦ ከ7ኛ - 12ኛ ክፍል ለተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርቶች 4️⃣ የክበባት እቅዶች ዋጋቸው 50 ብር ብቻ፦ ለሁሉም ዓይነት ትምህርታዊና ማህበራዊ ክበባት 5️⃣ የሲፕ (SIP) እቅዶችሮስተር ከነካርዱ መስሪያየግል ትምህርት ቤት መመስረቻ ፕሮፖዛል 0904128750 ይደውሉልን 6. ድርጊታዊ ጥናትና ምርምር እና ከነፕሮፖዛሉ 0904128750 ይደውሉልን ክፍል2 ኦሮሚያ ክልል 𝐁𝐚𝐚𝐟𝐚𝐭𝐚 𝐊𝐚𝐫𝐨𝐨𝐫𝐚 𝐁𝐚𝐫𝐧𝐨𝐨𝐭𝐚 𝐰𝐚𝐠𝐠𝐚𝐚 አመታዊ ዕቅድ  የአንዱ ዋጋ 40 ብር ብቻ ነው። 💬 በግል ቴሌግራም ለማግኘት፡ @EFG77777 🔗 የዕውቀት ምንጭ የሆነውን ተወዳጁን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፦ 👉 https://t.me/EFG2018T 0904128750 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 1-8: ➛A,Oromoo / አ/ኦሮሞ 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 1-6: ➛ S/Naannoo/ አ/ሳይንስ 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 1-8: ➛ F.J.Q  /  ጤ.ሰ.ማ 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 1-8: ➛ Og-Aartii / ስነ-ጥበብ 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 3-8: ➛ Amaariffaa / አማረኛ 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 1-6: ➛ Safuu / ግብረ-ገብ 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 7-8: ➛ C.T.E 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 7-8: ➛ I.C.T 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 1-8: ➛ Gadaa 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 7-8: ➛ Hawaasaa / ሕብረተሰብ 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 7-8: ➛ G,Science 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 1-6: ➛ Herregaa  / ሒሳብ 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 7-8: ➛ Citizenship 𝐆𝐫𝐚𝐝𝐞 1-8: ➛ Ingiliffaa / English ✨ ዋጋችን እጅግ በጣም አነስተኛ እና ተመጣጣኝ ነው! ይደውሉልን! ⚠️ እጅግ በጣም ጠቃሚ የጥንቃቄ መልዕክት፦ ከመምህር በላይ ክብረት (0904128750) የጥሪ መስመር ውጭ ሌላ ምንም ዓይነት አገልግሎት የማንሰጥ መሆኑን ተረድተው፣ ማንነታቸውን በስልክ ሳያረጋግጡ ምንም አይነት የገንዘብ ክፍያ እንዳይፈጽሙ በጥብቅ እናሳስባለን። ታማኝነት እና ጥራት 100% መለያችን ነው! 💳 የመክፈያ የባንክ አካውንት፦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ: 1000265462239 • የሂሳብ ባለቤት: መ/ር በላይ ክብረት ኃ/ጊዮርጊስ 📞 ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን፦ • 📱 ስልክ፡ 0904128750 • 💬 በግል ቴሌግራም ለማግኘት፡ @EFG77777 🔗 የዕውቀት ምንጭ የሆነውን ተወዳጁን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፦ 👉 https://t.me/EFG2018T ትምህርት ለትውልድ: ጥራታችን 100% ተቀባይነት ያለው ደረጃውን የጠበቀ እቅድ እና ስራ መምህራን የመሰከሩለት አሁንም ምስክር ናቸው ታማኝነት 100%

Education For Generation - EFG: 📢 ማስታወቂያ 📚 Education For Generation Telegram Channel 📚 ትምህርት ለትውልድ የቴሌግራም ቻናል የተለያዩ የት/ቤት ክበቦች እና የትምህርት አደረጃጀዶች አመታዊ እቅዶች ይፈልጋሉ? እነዚህ ከታች የተዘረዘሩት እቅዶች ሁሉ በቻናላችን አሉ። 1. የትምህርት አመታዊ እቅዶች (ከኬጂ - 12ኛ ክፍል በሁሉም ክልሎች ፣ክፍሎች እና የትምህርት አይነቶች) 2. የበጎ አድራጎት እና የቀይ መስቀል ክበብ 3. የሚኒሚዲያ ክበብ 4. የሰብአዊ መብት ክበብ 5. የስካውት ክበብ 6. የስፖርት ክበብ 7. የተማሪዎች መማክርት ክበብ 8. የነገው መምህር ክበብ 9. የንባብ ክበብ 10. የእንግሊዝኛ ቋንቋ ልማት ክበብ 11. የግብረገብነት ፀረ ሙስና ክበብ 12. የግብርና፣ የእርሻ እና የእርባታ ክበብ 13. የስርአተ ምግብ ክበብ 14. የአካባቢ እንክብካቤ ክበብ 15. የመንገድ ደህንነት ክበብ 16. የልዩ ፍላጎት ክበብ 17. የጤናና ፀረ ኤች አይቪ ኤድስና ስነ ተዋልዶ ክበብ 18. የአገራችንን እንወቅ ክበብ 19. የስርአተ ፆታ ክበብ 20. የሳይንስና ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ክበብ 21. የሰላም ክበብ 22. መሰረታዊ የመምህራን ማህበር እቅድ 23. የወሳኝ ኩነት ክበብ እቅድ 24. የእጅ ስራ ክበብ 25. የትምህርት ቤት የክረምት ስራ እቅዶች 26. የቅርንጫፍ ማዕከል አመታዊ እቅድ 27. የቤተ-መፅሐፍት ክበብ 28. የስርአተ ትምህርት አመታዊ እቅድ 29. የፈተናና ምዘና አመታዊ እቅድ 30. የማኔጅመንት አመታዊ እቅድ 31. የአይሲቲ (ICT) አመታዊ እቅድ 32. የሴቶች ክበብ 33. የህፃናት ኮንቬክሽን ክበብ 34. የተማሪዎች ፓርላማ ክበብ 35. የትራኮማ ክበብ 36. የት/ቤት ወተመህ እቅድ 37. የቀተስቦ አመታዊ እቅድ 38. የትምህርት ክፍል እቅድ 39. የሴክሽን ወተመህ እቅድ 40. የግል ትምህርት ቤት መመስረቻ ፅሑፍ ፕሮፖዛል 41. ድርጊታዊ ጥናትና ምርምር (ከነ ፕሮፖዛል ርዕስ ይንገሩን እናስተናግዳለን) 42. የህፃናት ፖርላማ ክበብ 43. ቋንቋ ክበብ 44. የ SIP እቅዶች 45. የትምህርት ቤት መልካም አስተዳደር እቅድ 46. የዋን ዋሽ ክበብ አመታዊ እቅድ ➕ ሌሎችም ብዙ እቅዶች አሉ። ሙሉ መረጃዎችን ከቻናሉ ተቀላቅላችሁ በመደወል ውሰዱ። ለጓደኞቻችሁ ይህን ሀገራዊ ራዕይ ያለውን ተወዳጅ ቻናል ሼር አድርጉላቸው። 👉 ተወዳጁን የቴሌግራም ቻናል በዚህ ሊንክ ይቀላቀሉን 🔗 https://t.me/EFG2018T ☎️ ለተጨማሪ መረጃ ይደውሉ፦ 0904128750 (መምህር በላይ ክብረት)

ሪፎርሙ ለትምህርት ዘርፉ መሰረታዊ ችግሮች መፍትሄ ይዞ የሚመጣ መልካም አጋጣሚ ነው" - አቶ ጥላሁን ወርቅነህ ==== ሰኔ 26/2018 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) በትምህርት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ብዝሀነትና አካታችነት አስመልክቶ ከቢሮ ሰራተኞች ጋር የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው። በሪፎርሙ ዙሪያ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወርቅነህ እንደገለጹት ሪፎርም ተፈጥሯዊ ሂደት ከመሆኑም በላይ ለትምህርት ተቋማችን ትልቅና መልካም እድል ነው ብለዋል። ኃላፊው አክለውም በትምህርት ዘርፉ ለዓመታት የቆዩ መሰረታዊ ችግሮችን የሚፈታ መሆኑን አክለው ገልፀዋል። የዘርፉን አሰራር በማዘመንና ጥራትን በማረጋገጥ የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት ወሳኝ ሚና እንዳለውም በመድረኩ ተገለጿል። በትምህርት ተቋማት የሚስተዋሉ መሰረታዊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የትምህርት ስራችንን ለማሻሻል የሚያስችሉ ልዩ ልዩ መመሪያዎችና አሰራሮች በተግባር ላይ እንደሚውሉም ተመላክቷል። ይህ የሪፎርም ትግበራ ተቋማዊ አሰራርን ግልጽ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ በማድረግ ለትምህርት ማህበረሰቡ እና ለመላው ህብረተሰብ የሚሰጠውን አገልግሎት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። #የአማራ_ክልል_ትምህርት_ቢሮ #የትምህርት_ሪፎርም

የሥልጣኔ አከርካሪ የሆነው መምህርነት የሰው ልጅ ሥልጣኔ ግንባታ ከሕንጻዎች እና ከቴክኖሎጂ ግኝቶች በላይ በመምህር እና ተማሪ መካከል በሚፈጠር የዕውቀት ፍሰት ውስጥ ሥር የሰደደ ነው። አስተማሪዎች በታሪክ መድረክ ላይ መረጃን የሚያስተላልፉ ብቻ ሳይሆኑ የሰውን ልጅ አቅም የሚቀርጹ የሕይወት አርክቴክቶች ናቸው። ከጥንታዊው ዘመን የፍልስፍና መድረኮች አንስቶ እስከ አሁን ባለው የዲጂታል ዓለም እምብርት ድረስ መምህርነት የሰው ልጅን አእምሮ ከድንቁርና ጨለማ ወደ ማስተዋል ብርሃን የሚያሸጋግር ዘላለማዊ ድልድይ ሆኖ ቆይቷል። የአርስቶትልና የአሌክሳንደር ግንኙነት እንደሚያሳየው የመምህርነት ኃይል የጂኦግራፊን ወይም የውጊያ ስልትን ማስተማር ብቻ ሳይሆን የተማሪውን ነፍስ በመንካት ለታላቅነት የሚያበቃ የሞራል እና የራዕይ ብርሃን መፍጠር ነው። በመረጃ በተጥለቀለቀው የዘመናችን ዓለም የመምህርነት ሚና ከመረጃ አቅራቢነት ወደ መረጃ አጣሪነት እና የሕይወት ኮምፓስነት ተቀይሯል። የዩኔስኮ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የዓለማችን የወደፊት እጣ ፈንታ በአብዛኛው የሚወሰነው በእነዚህ በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ መምህራን እጅ ነው። ውጤታማ መምህር የሚባለው መረጃን በተማሪው አእምሮ ውስጥ የሚቀብር ሳይሆን ያንን መረጃ ለሕይወት ስኬት እንዴት እንደሚጠቀምበት የሚያስተምርና የመፍጠር አቅምን የሚከፍት ነው። የጥናት ውጤቶች እንደሚያሳዩት አንድ ተማሪ በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት ውስጥ የሚኖረው የሕይወት ስኬት ከሰባ በመቶ በላይ ጥገኛ የሆነው በአስተማሪው የጥራት ደረጃ ላይ ነው። ይህ የሚያመለክተው የመምህርነት ሚና በዘመናዊው ማህበረሰብ ውስጥ የሰውን ልጅ አቅም የሚያንቀሳቅስ ማዕከላዊ ሞተር መሆኑን ነው። የመምህርነት ጥበብ በውስጡ ጥልቅ የሆኑ ፓራዶክሶችን የያዘ ነው። እጅግ የተዋጣለት መምህር የመጨረሻው ግብ ተማሪው መምህሩን አያስፈልገኝም እስኪል ድረስ ማብቃት ነው። ይህ "የመጥፋት ፓራዶክስ" እንደሚነግረን የመምህሩ ስኬት የሚለካው በመገኘቱ ሳይሆን ተማሪው በራሱ እግር መቆም ሲችል ነው። በተመሳሳይ ሁኔታ መምህሩ ሁሉን አዋቂ መስሎ ሲታይ የተማሪው የማወቅ ፍላጎት ይሞታል ነገር ግን መምህሩ "እኔም አላውቅም አብረን እንፈልገው" ሲል የተማሪው የመፍጠር አቅም ይነቃቃል። እውነተኛ የትምህርት ጥበብ የሚያብበው በጋራ ፍለጋ እንጂ በብቸኛ የዕውቀት የበላይነት አይደለም። የመምህርነት ተጽዕኖ በጊዜ ሂደት የሚንሰራፋው እንደ ታላቅ የጂኦሜትሪክ ሰንሰለት ነው። አንድ መምህር አንድን ተማሪ በአስተሳሰብ ሲቀይር ያ ተማሪ ወደፊት የሌሎች መቶዎችን ሕይወት የመቀየር ኃይል ይኖረዋል። ይህ የሰንሰለት ምላሽ በታላላቅ የሳይንስ ሰዎች የሕይወት ታሪክ ውስጥ በግልጽ ይስተዋላል። የአስተማሪነት ኃይል የሚመነጨው መረጃን ከማስተላለፍ፣ ተማሪውን ከማነሳሳት እና የራስን የትምክህት ስሜት በመግራት የሚገኝ የሥልጣኔ ቀመር ነው። የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች መሣሪያዎች ናቸው። ነገር ግን በመምህር እና ተማሪ መካከል የሚፈጠር የዕውቀት ብልጭታ ከማንኛውም የቴክኖሎጂ አቅም በላይ የሆነ የሰው ልጅ የህልውና ኃይል አለው። መምህራን ወደፊት ዓለምን የሚመሩትን አዲስ ትውልድ ቀራጮች ናቸው። መምህርነት ከክፍል ውስጥ ገደብ ወጥቶ ወደ ምናባዊው ዓለም እና ወደ ሰው ልጅ ንቃተ-ህሊና ጥልቀት እየተሸጋገረ ነው። የዓለም የወደፊት ብሩህነት የተመሰረተው በመምህራን እጅ ላይ ሲሆን እነርሱ ለሰው ልጅ ሥልጣኔ አከርካሪ የሆኑ የዕውቀት ኮምፓሶች ናቸው። የሰው ልጅ የህልውና ትልቁ ስኬት እነዚህ መምህራን በየቀኑ በሚያደርጉት ጥረት በአንድ ተማሪ ሕይወት ውስጥ የሚፈጥሩት የማይጠፋ የአእምሮ እና የስነ-ምግባር አሻራ ነው። መምህርነት ማለት ለዘመናት የሚቀጥል የሰው ልጅ የልህቀት ጉዞ ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር የጥበብ ሰንሰለት ነው። ✍ ዛዲግ አብርሀ (የአፍሌክስ ፕሬዝደንት) https://t.me/EFG2018T

ትምህርት ለትውልድ (Knowledge for Generations).mp32.78 MB

አንድ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ራስ-ገዝ ለመሆን በሁሉም ፕሮግራሞች ለሦስት ተከታታይ ዓመታት 80 በመቶ ተማሪዎቹን በመውጫ ፈተና ማሳለፉን እንደ አንድ አካዳሚክ መመዘኛ ነጥብ የሚይዝ መመሪያ ትምህርት ሚኒስቴር አውጥቷል።ማንኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን በመመዘኛ ነጥቦቹ 60 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅበታል የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካሉባቸው የአደረጃጀት እና የአሰራር ውሱንነቶች ወጥተው፣ ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ የሚያስችላቸውን “የመንግስት ዩኒቨርሲቲ የራስ-ገዝነት የሽግግር መምረጫ መመሪያ ቁጥር 1143/2018” አውጥቷል። ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያውን ማውጣት ያስፈለገበትን ምክንያት ሲያስረዳ፤ እስካሁን በነበረው አሰራር ዩኒቨርሲቲዎች በቂ ተቋማዊ ነፃነት ባለመኖሩ ምክንያት የመማር ማስተማር፣ የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት ተልዕኮዎቻቸውን በአግባቡ ለመወጣት እንቅፋት ሆኖባቸው መቆየቱን ገልጿል። በመሆኑም ተቋማቱ ከመንግስት ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው በሰው ኃይል፣ በሀብት አጠቃቀም እና በአካዳሚክ ጉዳዮች ላይ ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ ማስቻል አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ገልጿል። ይህ መመሪያ በራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ አዋጅ ቁጥር 1294/2015 አንቀጽ 5 እና 45 መሠረት የተዘጋጀ ነው። እንደ መመሪያው ገለጻ፣ አንድ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር በአራት ዋና ዋና አምዶች ላይ ተመስርቶ ግምገማ ይደረግበታል። እነዚህም አስተዳደር (30%)፣ ፋይናንስ (20%)፣ የሰው ኃይል (15%) እና አካዳሚክ (35%) ጉዳዮች ናቸው። የሽግግር ሂደቱም በተጨባጭ መረጃ፣ በላቀ ብቃት፣ በውጤታማነት፣ በአካታችነት፣ በግልጽነት እና በተጠያቂነት መርሆዎች ላይ ተመስርቶ የሚከናወን ይሆናል። ዩኒቨርሲቲዎች ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ለመሸጋገር በዝግጅት ምዕራፍ ወቅት ቢያንስ 60 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በመመሪያው ላይ በዝርዝር የተቀመጡ እና ተቋማቱ ሊያሟሏቸው የሚገቡ መመዘኛዎች መስፈርቶች መካከል:- • ተቋማቱ ቢያንስ 15 በመቶ የሚሆኑ የመማሪያ ክፍሎቻቸውን ወደ “ስማርት ክላስሩም” የቀየሩ • 80 በመቶ እና ከዚያ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎቻቸው ብሄራዊ የመውጫ ፈተናን ያለፉ •ቢያንስ 5 በመቶ የሚሆኑ የትምህርት ፕሮግራሞቻቸው ዓለም አቀፍ እውቅና (Accreditation) ማግኘታቸው እና የዲጂታል ቤተ-መጽሐፍት አገልግሎታቸው ከ70 በመቶ በላይ መድረስ አለበት • አንድ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት የሂሳብ ምርመራ (Audit) ያስደረገና የኦዲት ግኝቱም “ንጹህ” (Unqualified) ወይም አስተያየት ያልተሰጠበት መሆን ይኖርበታል። • ተቋሙ ካለው አጠቃላይ በጀት ውስጥ ቢያንስ 15 በመቶውን ከውስጥ ገቢና ከውጭ የገቢ ምንጮች መሸፈን ይጠበቅበታል። • ለገቢ ምንጭነትም ቢያንስ አምስት እና ከዚያ በላይ የገቢ ማመንጫ ዘርፎችን ወደ ስራ ማስገባት እንደ ግዴታ ተቀምጧል። • የዩኒቨርሲቲው መምህራን የትምህርት ደረጃ ስብጥር 0፡ 60፡ 40 (የመጀመሪያ ዲግሪ 0%፣ ሁለተኛ ዲግሪ 60% እና ሦስተኛ ዲግሪ 40%) መድረስ እንዳለበት ተደንግጓል። • በተጨማሪም የአካዳሚክ ማዕረግ ስብጥሩ ሌክቸረር 46%፣ ረዳት ፕሮፌሰር 31%፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር 20% እና ፕሮፌሰር እና ከዚያ በላይ 3% መሆኑ መረጋገጥ ይኖርበታል። • ተቋማቱ በምርምር ዘርፍ ያላቸውን ጥንካሬ ለማሳየትም ቢያንስ አምስት እና ከዚያ በላይ የሆኑ የአእምሯዊ ንብረት መብት (IP) ባለቤት መሆን እንዳለባቸው በመመሪያው ተመላክቷል። • ተቋማዊ አገልግሎትንና የተገልጋይ እርካታን በተመለከተም፣ ዩኒቨርሲቲዎች በመምህራን፣ በሠራተኞችና በተማሪዎች ዘንድ ቢያንስ 75 በመቶ የእርካታ ደረጃ ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል። • ከአካባቢው ማህበረሰብና ከኢንዱስትሪ ተዋንያን ጋር ባላቸው ግንኙነት ደግሞ የ70 በመቶ የእርካታ ደረጃን በጥናት ማሳየት ይኖርባቸዋል። • በቴክኒክ ረገድም ካሏቸው ቤተ-ሙከራዎች (Laboratories) ውስጥ 10 በመቶ የሚሆኑት፣ ከወርክሾፖቻቸው ደግሞ 5 በመቶው በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የተደራጁ መሆናቸው በሽግግር ግምገማው ወቅት ትልቅ ዋጋ ይሰጠዋል። የሽግግር ሂደቱ በሁለት ደረጃዎች የሚከናወን ሲሆን፣ መጀመሪያ ዩኒቨርሲቲው በራሱ ኮሚቴ አማካኝነት የውስጥ ግለ-ግምገማ (Self-assessment) ያካሂዳል ይህ ግምገማ በዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ ጸድቆ ለትምህርት ሚኒስቴር ይቀርባል። ሚኒስቴሩ የቀረበለትን ሪፖርት መነሻ በማድረግ በገለልተኛ ባለሙያዎች የታገዘ የመስክ ምልከታና ማረጋገጫ ከሰጠ በኋላ፣ መስፈርቱን አሟልተው ለተገኙ ተቋማት ወደ ራስ-ገዝነት እንዲሸጋገሩ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል። ወደ ራስ-ገዝነት የተሸጋገረ ዩኒቨርሲቲ የሽግግር ጊዜው ለሁለት ተከታታይ ዓመታት የሚቆይ ሲሆን፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ ተቋማዊና አካዳሚክ ነፃነቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል አቅም ይገነባል። ይሁን እንጂ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ መግባት ካልቻለ፣ ሚኒስቴሩ ተጨማሪ ጊዜ ሊሰጠው ወይም ከቦርዱ ጋር በመመካከር ሌሎች ውሳኔዎችን ሊያስተላልፍ እንደሚችል መመሪያው ደንግጓል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር ተመዝግቦ የጸደቀ መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል። join https://t.me/EFG2018T

የመምህራን ዝውውር አፈጻጸም መመሪያ.pdf12.04 MB

የ1ኛ ደረጃ መርሱ ዝውውር.pdf7.91 KB