Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
前往频道在 Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
显示更多4 480
订阅者
-124 小时
+147 天
+3130 天
帖子存档
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎችን አስመልክቶ ምን አለ? ከፕሬዚዳንቱ ንግግር ይስሙ ...
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረትስ ምን ምላሽ ሰጠ? ከሕብረቱ ተወካዮች ያድምጡ
ኡስታዞችስ ምን አሉ? ኡስታዝ ካሚል ጣሃ ያሉትን ይከታተሉ
ሁሉም በዚህ አጭር ቪድዮ ውስጥ ተካቷል ... ለሌሎችም Share መደረግ እንዳይዘነጋ
ሙስሊሙ ተማሪ ጥያቄ አለው ... የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የዚህ ትውልድ አደራ ነውም ብሏል ! ! !
@aaumsu
"በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የእስልምና እምነት ተከታይ ተማሪዎች ላይ አድሎ ይፈፀማል በማለት የስም ማጥፋት ዘመቻ ላይ ተሳታፊ ሆኗል በሚል ክስ የቀረበብህ ስለሆነ ... !" - የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች ከሰጠው የክስ መጥሪያ ወረቀት
ዩኒቨርሲቲያችን ሙስሊም ተማሪዎችን የሚያገል መመሪያውን እንዲያስተካክል አሁንም ጥሪያችን ነው:: በግልፅ በመመሪያ በተቀመጠ ድንጋጌ ሙስሊም ኒቃቢስቶችን አግልሎ ሲያበቃ አድሎ ፈፅመሃል መባሉ የስም ማጥፋት ዘመቻ ነው ብሎ የሙስሊም ተማሪዎችን ተወካዮች መክሰስ አግባብነት የለውም:: ሙስሊም ተማሪዎች እንዲስተካከል እየጠየቁት ያለው የስነ-ስርዓት መመሪያው ክፍል በአንቀፅ 6.6 ላይ እንደሚከተለው ተቀምጧል::
"በዩኒቨርሲቲው ከሚከናወኑ የመማር ማስተማር ተግባራትና ከሚሰጡ አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ማንነትን ለመለየት ሲባል በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ፊትን ሙሉ በሙሉ የሚሸፍኑ አለባበሶችን መልበስ የተከለከለ ነው።"
ይህ በግልፅ ኒቃቢስት ተማሪዎችን ወደ ዩኒቨርሲቲው እንዳይገቡ የሚከለክል ድንጋጌ ነው:: ይህ መሆኑ ዛሬ በዩኒቨርሲቲው እየተማሩ ካሉት ባሻገር ሕልማቸውን በAAU ለመማር ያደረጉ ኒቃቢስቶችን ሕልም የሚያጨናግፍ ነው:: የአንድን ሕዝብ መገለጫ ማንነት የሚያገል ነው::
ስለሆነም አሁንም ቢሆን ይህንን ድንጋጌ በማሻሻል ለሙስሊም ተማሪዎች ደህንነት እውቅና የሚሰጥ እና ከለላ የሚያበጅ ድንጋጌ ይወጣ ዘንድ እንጠይቃለን::
የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የዚህ ትውልድ አደራ ነው ... አይሻገርም !
@aaumsu
+2
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከኢትዮጵያ ሙስሊም የሕግ ባለሙያዎች ማህበር ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ !
•••••••••••••••••••••••••••••••••••
ህዳር 26 / 2018 ዓ.ል
•••••••••••••••••••••••••••••••••••
ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚደርስባቸውን ሰብዓዊ የመብት ጥሰት ለመከላከል እና በሰላማዊ መንገድ መብታቸውን እንዲጠይቁ ለማድረግ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ለማስጠበቅ እና ያላቸውን አዎንታዊ አስተዋፅዖ ለማሰደግ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ሙስሊም የሕግ ባለሙያዎች ጋር ተፈራርሟል:: ስምምነቱን በሕብረቱ ፕሬዚዳንት ሙሐመድአሚን ካሳው እና በማህበሩ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙህዲን ጀማል መካከል የተፈረመ ሲሆን ወደፊት በሚሰሩ ዝርዝር ተግባራትም ውይይት ተደርጎል::
አላህ ለመልካም ለውጥ እና ለተሻለ ሁኔታ ሰበብ ያደርገው ዘንድ ዱዓችን ነው ! ! !
ውድ ወደ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባችሁ የሪሜዳል ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ!!
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ፦
Assalaamhwaalayiku worahmatullahi wobarakaatuhu፦
ወደ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ የተመደባች የremedial) ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ እንደሚታወቀው በ2018 ዓ.ል ወደ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ የተመደቡ የሪሜዳል ሙስሊም ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ታህሳስ 02 እና 03 2018 አ.ል እንደሆነ ይታወቃል።
Nagaa fi nageenya insiniif haa ta'u!!
yaa barattoota Muslimaa gara yuuniversiti dabra Maarqoositti dirqamaa fi beekumsa dabalataa(remedial) itti fufsiifatan! Akukuma beekanu,barattoonni remedial 2018 wagga tti yuuniversiitii dabra maarqoositi dirqaman,guyyaa isaan mana barumsaa seenan Tasassa 02 fi 03 2018 ta'uu beekama.
ስለሆነም ይህን በማስመልከት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ እናንተን ሙስሊም ወንድምና እህቶቹን ተቀብሎ ማንኛውንም ዲናዊም ሆነ አካዳሚክ መረጃዎችን ለመስጠት እንዲሁም ስለሌሎች ሊያጋጥሟችሁ የሚችሉ አዲስ ነገሮች በሙሉ የሚያስፈልጓችሁን ድጋፍና ትብብር ለማድረግ ሙሉ ዝግጅታቸውን አድርገው የናንተን መምጣት ብቻ በጉጉት እየጠበቁ ይገኛሉ።
Kannaf,kanarra ka'uudhaan, Gamaaleen Muslimaa Yuuniversiitii Dabra Maarkoos(jama'a) oggaantotaafi obboloota Muslimaa keessan fudhachuuf,beekumsa amantii,fi aadaa hunda isiniif kennuuf,fi haala haaraa kan muraasni isin tuqu danda'u irratti isin gargaaruuf,akkasumas deeggarsa isiniifi barbaachisu hunda kenyaaf dirqamaa qopheessee,seenaa keessan qofa eeggachaa jira.
ስለዚህ ስለሚያስፈልጋችሁ ማንኛውም አይነት ጥያቄም ይሁን ትብብር ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ስልኮች ደውላችሁ ሙሉ መረጃ ማግኘት እና ያለምንም እንግድነት ስሜት ውድ ጀመዐችንን መቀላቀል ትችላላችሁ ስንል ትብብራችንን እንገልጻለን።
አላህ እኛንም እናንተንም ሰላም አድርጎ
በሰላም እንዲያቀላቅለን እንጠይቀዋለን።
Kanaaf,yoo deeggarsa dandeessaa ykn gaaffii barbaachisa qabaatan, lakkoofsa bilbilaa aramaan qadii tuqiidhaan odeeffannoo guutuu argschuu fi gamaalee kenya jaalatamoo( jama'a) tii walqunnamtii mijeessuu dandeessuudhaan,deeggarsa keenya ifa baasna.
✅ወንድም አህመድ፦
📞0973780733
✅ወንድም ኑረድን፦
📞0968192873
✅ወንድም ጅብሪል፦
📞 0929628329
✅ወንድም አልይ፦
📞 0905951202
✅ወንድም አብዱል ሀሚድ፦
📞0935873486
*️⃣ መልካም ጉዞ። አላህ ከእናንተ ጋር ይሁን!!!
*️⃣ Waa'ee keengaas,waa'ee keessaniifis naggan akku nu walsimu Rabbi hajedhu!!!
Imala gaarii rabbiin isin woliin haa ta'u.
*️⃣ የእህቶችን አድራሻ ለማግኘት፦
📞 0968192873
https://t.me/EHEMSU
AMBO UNIVERSITY MUSLIM STUDENTS JEMA'A
Aselamualeykum werhmetullahi weberekatu
በ 2018 ዐ.ል ወደ አምቦ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ሬሜዲያል(የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ተማሪዎች መግቢያ ህዳር 29 እና 30 መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል::
የ አምቦ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ (AUMSJ)እናንተን ሙስሊም ወንድም እና እህቶችን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ያለ ሲሆን ከመምጣታችሁ በፊትም ይሁን በ መግቢያችሁ ቀን የሚያስፈልጋችሁን ማንኛውም መረጃ ለማግኘት ከታች በተዘረዘሩት የስልክ ቁጥሮች መደወል ትችላላችሁ::
Yuunvarsitiin Amboo akka beeksisetti, barattoonni sagantaa sirreeffama (remedial program) bara 2018 A.L.I Yuunvarsitii Ambootti ramadamtan, guyyaan gara mooraa seentan Sadaasa29 fi 30 ta'uu ibsee jira.
Jama'aan Barattoota Muslimaa Yuunvarsitii Amboo (AUMSJ) obboleewwan keenya Muslimoota dhiiraa fi dubartoota isin simachuuf qophii irra jira.
Odeeffanno barbaachisaa ta'e kamuu argachuuf lakkoofsota bilbilaa gadiitti tarreeffamanitti bilbiluun nu qunnamuu dandeessu.
## For Natural science( Hachalu Hundesa Campus)
1.Zaakir (Hachalu Campus)
+251913044612
2.Muhammad Arab (Hachalu Campus)
0904190352
## For social science (main campus)
📞 Saadaam Abdusamad– +251926630411
📞 Muusaa Ibraahim – 0917544231
📞 Jamaal Aliyyii – +251918934445
የእህቶችን ስልክ ለማግኘት +251926630411 በመደወል ማግኘት ትችላላችሁ::
Ambo University Muslim Students’ Jema’a
https://t.me/EHEMSU
የAAU ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት አመራሮች እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት በሀሩን ሚዲያ ስለ ሙስሊም ተማሪዎች መብት ፕሮግራም ካቀረቡ ቡሃላ በAAU የፀጥታ አካላት የዲሲፕሊን ጥፋት ሰርታችሗል በሚል ቃላቸውን እንደሰጡ ተገለፀ !
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ህዳር 24 / 2018 ዓ.ል
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በዛሬው እለት ባወጣው መግለጫ እንደገለፀው የዩኒቨርሲቲው ጀመዓ ፕሬዚዳንት መሕፉዝ ነጋሽ: ምክትል ፕሬዚዳንት አብዱልሐሚድ አሕመድ እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፕሬዚዳንት ሙሐመድአሚን ካሳው ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ በሀሩን ሚዲያ ፕሮግራም ካዘጋጁ ቡሃላ የሕብረቱን ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዚዳንት: በሕብረቱ የ6ኪሎ ጀመዓ አሚር የሆነውን አብዱረሒም አሚን እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፕሬዚዳንት የሆነውን ሙሐመድአሚን ካሳው የዩኒቨርሲቲው የፀጥታ አካላት ጠርተው "በሀሩን ሚዲያ ቀርቦ የዩኒቨርሲቲውን ስም በማጥፋት እውቅና ሳይኖራቸው የሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች ነን በማለት: አገባብነት በሌለው መልኩ ጥያቄዎችን በመጠየቅ ወዘተ... ::" በሚሉ ጉዳዮች እንደተከሰሱ በመግለፅ ቃላቸውን ተቀብለዋል::
ሕብረቱ መሠል አካሄዶች ሙስሊም ተማሪዎች ከአመት በላይ ሲጠይቁት የነበረውን የመብት ጥያቄ ችላ ያለ እና የሙስሊም ተማሪዎችን ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት የሚገድብ እንደሆነ በመጥቀስ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል::
@MohammadamminKassaw
"በጅህልና ከመቀጣት በላይ ቅጣት የለም:: በጅሕልና ሊቀጡን ያሰቡትን ሰዎች ግን ልቀን ከትልቅ ደረጃ ደርሰን እናሳያቸዋለን::" - የጉንችሬዋ እህት
"በዚህ ምክንያት (በሒጃብ ክልከላ) ተባረናልም ተፈናቅለናልም (ከትምህርት)::" - ሸሕ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ
"በጅልባብ ምክንያት ማዕከላዊ እስር ቤት የታሰሩ ሴት ተማሪዎች ነበሩ:: በሒጃብ ክልከላ ምክንያት ተማሪዎች በገፍ ታስረው: ተባረው ተሳደው ነበር::" - ሙሐመድአሚን ካሳው
:- ሙሉውን አዳምጡት ... ለሌሎችም ማጋራት እንዳይዘነጋ ! ! !
@MohammadamminKassaw
"ማንም ሒጃብን ለበሰ ተብሎ መከልከል የለበትም:: ኒቃብ is a different story (ኒቃብ ሒጃብ አይደለም እንደማለታቸው ነው) ::" - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
"ይሄ ሒጃብ ነው ያ ኒቃብ ነው እንዴት ይላሉ? ማን ነው የለየላችሁ?" - ሸህ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ
" የትምህርት አካላት ኒቃብ እና ሒጃብን ለመለያየት ሲሞክሩ ሴኩላሪዝምን ሙሉ ለሙሉ እየደፈጠጡ ነው::" - ሙሐመድአሚን ካሳው
ዝርዝር ማብራሪያውን ከቪድዮው ይመልከቱ ... ለሌሎችም ያሰራጩ ! ! !
@MohammadamminKassaw
በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት ... ከድሮ እስከ ዘንድሮ ... በሙሐመድአሚን ካሳው ! ! !
@MohammadamminKassaw
ኒቃቢስቶቹ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ደምቀዋል
ትግሉ ለዚህ ነበር
የታገሉት ለዚህ ነበር
የምንታገለውም ለዚህ ነው
ኒቃብን ለአመታት ከልክሎ በሙስሊም ተማሪዎች ትግል ክልከላውን በገታው ጅማ ዩኒቨርሲቲ "በጋራ ጎበዞቹን እንሸልም!" - ፕሮግራም ላይ ኒቃቢስቶቹ በጋራ ደምቀው ተሸልመዋል::
ዶክተር አይሻ ደኬቦ ... 3.89 በማስመዝገብ ከኮሌጇ ሰቃይ ሆናለኅ ... ደግሞ የአግሪ ካምፓስ ጀመዓ አሚራ ናት::
ሌላኛዋ ... ዶክተር ደሜ ቶላ ... 3.45 በማምጣት ተሸላሚ ሆናለች ... ይህችኛዋ ደግሞ የጀመዓው ሶሻል ሴክተር አሚራ ነች::
Congrats... 😍
በዚህ ውስጥ ለሁሉም ሰው ድንቅ ተምሳሌትነት አለ !
የእነዚህ እንቁ ልጆች ኒቃብ የመልበስ መብት በሕግ እስኪፀና እና ከለላ እስኪሰጣቸው ድረስ መታገል የሁሉም ሀገር ወዳድ ሀላፊነት ነው ! ! !
@MohammadamminKassaw
ከሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ጥያቄ እና መፍትሔዎች ጋር ተያይዞ በሐሩን ሚዲያ የተዘጋጀው ፕሮግራም ተለቋል ... በተከታዩ ሊንክ ገብተው ይከታተሉ::
https://youtu.be/fnbO4WjfM7E?si=Bbk3fvBoq5Bhutyi
በሙስሊም ተማሪዎች ሶላት እና ሒጃብን ሰበብ አድርጎ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ተዳስሷል ... የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት ሙሐመድአሚን ካሳው እንዲሁም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት መህፉት ነጋሽ እና ምክትል ፕሬዚዳንት አብዱልሐሚድ አሕመድ ሰፊ ማብራሪያዎችን አስቀምጠዋል ! ! !
ምሽት 2:00 በሀሩን ሚዲያ እንገናኝ ! ! !
በመጅሊሱ የተቋቋመው ግብረ ሀይል ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ዘላቂ መፍትሄ ለመምጣት ውይይት ማካሄድ ጀመረ
በትምህርት ተቋማት ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት እየተፈጠሩ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎችን በአለባበስ ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው የማፈናቀል ተግባር በቋሚነት እልባት ያገኝ ዘንድ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ግብረ ሀይል በማቋቋም እየተንቀሳቀሰ ይገኛል::
ይህ ግብረ ሀይልም ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የመጀመሪያውን ጥልቅ ውይይት ያካሄደ ሲሆን ችግሩን በዘላቂነት መፍትሄ እንዲያገኝ ሊሰሩ በሚገባቸው ስራዎች ላይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል::
@MohammadamminKassaw
+9
የስነ- ስርዓት መመሪያው የሙስሊም ተማሪዎችን ሐይማኖታዊ መብት ይጥሳል:: ይህንንም ተከትሎ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው ፎርም ላይ እያስገቡ ነው:: ያላስገባችሁ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScC1ecfQ0ZhBB3etPOWhBUILxTtFQO9r5hMcrDmxYW9CLn2nA/formResponse ላይ አስገቡ::
ሰዓቱ መብቶቻችንን ቆጥረን የምንረከብበት ነውና በመመሪያው ላይ ያላችሁን ቅሬታ በዝርዝር በመግለፅ ቅሬታችሁን አስገቡ:: ይህ በዚህ እንቅስቃሴ ትንሹ ሀላፊነታችን ነው:: የላካችሁትን አስተያየትም Screenshot በማድረግ @MOHAMMADAMMINM ላኩልኝ::
መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም ! ! !
+9
ሙስሊም ተማሪዎች ስለመብቶቻቸው መጠየቃቸውን ይዘዋል
ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው ረቂቅ መመሪያ ላይ ያላቸውን ቅሬታ ሚኒስቴሩ ባስቀመጠው ፎርም ላይ እያስገቡ ነው:: ያላስገባችሁ አስገቡ:: ማስገቢያ ፎርሙ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScC1ecfQ0ZhBB3etPOWhBUILxTtFQO9r5hMcrDmxYW9CLn2nA/formResponse ነው:: የላካችሁትን አስተያየትም Screenshot በማድረግ @MOHAMMADAMMINM ላኩልኝ::
ይህ ስለመብት ጥያቄዎቻችን ልናደርገው የሚገባው ትንሹ ሀላፊነት ነው!!!
@MohammadamminKassaw
ሐቅ ነው ... ሆኖም ግን የአፄው ስርዓት እንዳለፈው ሁሉ ይህም ያልፋል ... ከፍትሕ ጋር ! ! !
@MohammadamminKassaw
+9
የትምህርት ሚኒስቴር ለአስተያየት ክፍት ባደረገው የስነ-ስርዓት ረቂቅ መመሪያ ላይ ከሙስሊም ተማሪዎች እየተሰጡ ያሉ ቅሬታዎች ናቸው::
ጥያቄ አለን !
ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ ጥያቄ አለን ... ጥያቄያችን ደግሞ የሙስሊም ተማሪዎች የዘመናት ጥያቄ የሆነውን የመብት ጥያቄ በመመሪያው ውስጥ እውቅና ሰጥቶ ከለላ እንዲያደርግለትም ነው::
ተማሪዎች:- https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScC1ecfQ0ZhBB3etPOWhBUILxTtFQO9r5hMcrDmxYW9CLn2nA/formResponse በመግባት በመመሪያው ዙሪያ ያላችሁን ጥያቄ አስገቡ:: የላካችሁትን አስተያየትም Screenshot በማድረግ @MOHAMMADAMMINM ላኩልኝ::
ይህ ስለ መብት ጥያቄዎቻችን የምናደርገው ትንሹ ሀላፊነት ነው:: የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች ደግሞ የዚህ ትውልድ አማና ናቸው::
@MohammadamminKassaw
+6
ከተለያየ አካባቢ ያሉ ተማሪዎች ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን ረቂቅ መመሪያ በመቃወም ቅሬታቸውን እያስገቡ ነው:: ይህ በዚህ አጀንዳ ዙሪያ ሁሉም ተማሪ ሊያደርገው የሚገባ ትንሹ ሀላፊነት ነው:: ሚኒስቴሩ ቅሬታችሁን አስገቡ ባለበት ፎርም በኩል ገብተን በመመሪያው ላይ ያለንን ጥያቄ እናንሳ:: ሶላት ኒቃብ እና መሠል የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄዎች እውቅና እንዲሰጣቸው እና ተያይዞ ለሚመጣ የመብት ጥሰት ከለላ እንዲሰጥ እንጠይቅ::
ፎርሙ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScC1ecfQ0ZhBB3etPOWhBUILxTtFQO9r5hMcrDmxYW9CLn2nA/formResponse ነው:: የላካችሁትን አስተያየት Screenshot በማድረግ @MOHAMMADAMMINM ላኩልኝ::
መብት በመጠየቅ በመታገል በመጠየቅ እንጂ እንዲሁ አይገኝም ... የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች ደግሞ የዚህ ትውልድ ሀላፊነቶች ናቸው ! ! !
@MohammadamminKassaw
