ch
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

前往频道在 Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

显示更多
672
订阅者
无数据24 小时
+37 天
-130 天
帖子存档
✨✨እንኳን አደረሳችሁ ✨✨ ✝✝ኅዳር_ሚካኤል ✝✝ #አንተኑ_ሚካኤል አንተኑ ሚካኤል መና መና ዘአውረድከ/፪/ ወአንተኑ ለእስራኤል መና ዘአውረድከ/፪/ የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
       ✨✨እንኳን አደረሳችሁ ✨✨      ✝✝ኅዳር_ሚካኤል ✝✝ #አንተኑ_ሚካኤል አንተኑ ሚካኤል መና መና ዘአውረድከ/፪/ ወአንተኑ ለእስራኤል መና ዘአውረድከ/፪/   የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ እውነት እላችኋለሁ፥ከሁሉ ከሚያንሱ ከነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል። ማቴ 25:40 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ እውነት እላችኋለሁ፥ከሁሉ ከሚያንሱ ከነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል። ማቴ 25:40 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን🙏 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ውድ የፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት አባላት እንዲሁም የሰንበት ት/ቤቱ የቴሌግራም ቻናል ተከታታዮች ከላይ በምስሉ ላይ የምትመለከቱዋት እህታችን በአሰላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ፈለገ ሊቃውንት ሰ/ት/ቤት ለረጅም ጊዜያት ያገለገለች እና በማገልገል ላይ ያለች እንዲሁም ሰ/ት/ቤቱን ወክላ በሰበካ ጉባኤ ውስጥ የምትሳተፍ ብርቱ አገልጋይ ነች ። እናም ወዳጆቻችን በአሁኑ ሰዓት ይህች ትጉ እና ብርቱ እህታችን በከፍተኛ ልብ ህመም እየተሰቃየች ትገኛለች ። ለህክምናም ከአቅም በላይ የሆነ ገንዘብ ስለተጠየቀ ሁላችንም ያቅማችንን  በማገዝ እህታችንን አለንልሽ እንድንላት እናም ድና ወደምትናፍቀው አገልግሎትዋ እንድትመለስ እና ቤተሰብዋን እንድትመራ እንድናግዛት ስንል በአምላካችን በመድኃኔዓለም ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።       እህታችንን ለመርዳት ከላይ በምስሉ ላይ በተቀመጡት የባንክ አካውንቶች መጠቀም ትችላላችሁ። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ከምንም በላይ ግን ለጸሎት በቆማችሁ ጊዜ በጸሎታችሁ አስቡዋት 🙏 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ✨✨✨✨✨✨✨✨ ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ✨✨✨✨✨✨✨✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2

💐💐💐💐🍇🍇🍇🍇💐💐💐💐 ጸሎተ ሃይማኖት ዘአዘዙነ ፫ቱ ፻፲ቱ ፰ቱ ሊቃነ ጳጳሳት ዘጉባኤ ኒቅያ፤ እም ድኅረ አውገዝዎ በመንፈስ ቅዱስ ለከሐዲ አርዮስ ዘይቤ “ወልድ ፍጡር በትስብእቱ” ሎቱ ስብሐት፤ በዘመነ ቈስጠንጢኖስ ንጉሠ ጽድቅ። “ነአምን በአሐዱ አምላክ እግዚአብሔር አብ አሐዜ ኵሉ ዓለም፤ ገባሬ ሰማያት ወምድር፤ ዘያስተርኢ ወዘኢያስተርኢ፤ ወነአምን በአሐዱ እግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ አብ ዋሕድ፤ ዘኅልው ምስሌሁ እምቅድመ ይትፈጠር ዓለም፤ ብርሃን ዘእም ብርሃን፥ አምላክ ዘእም አምላክ ዘበአማን፥ ዘተወልደ ወአኮ ዘተገብረ፤ ዘእሩይ ምስለ አብ በመለኰቱ፤ ዘቦቱ ኵሉ ኮነ ወዘእንበሌሁሰ አልቦ ዘኮነ፥ በሰማይኒ ወበምድርኒ፤ ዘበእንቲአነ ለሰብዕ፥ ወበእንተ መድኃኒትነ፤ ወረደ እም ሰማያት፥ ተሰብዓ ወተሰገወ፥ እም መንፈስ ቅዱስ ወእም ማርያም እም ቅድስት ድንግል፤ ኮነ ብዕሴ፥ ወተሰቅለ በእንቲአነ፥ በመዋዕለ ጲላጦስ ጰንጠናዊ፤ ኀመ፥ ወሞተ፥ ወተቀብረ፥ ወተንሥአ እም ሙታን አመ ሣልስት ዕለት በከመ ጽሑፍ ውስተ ቅዱሳት መጻሕፍት፤ ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፤ ወነበረ በየማነ አቡሁ፤ ዳግመ ይመጽዕ በስብሐት፥ ይኴንን ሕያዋነ ወሙታነ ወአልቦ ማኅለቅት ለመንግሥቱ።” ተረፈ ሃይማኖተ አበው ዘተነግረ በ፻ቱ ወ፶ ሊቃነ ጳጳሳት ዘጉባኤ ቊስጥንጥንያ። እምድኅረ አውገዝዎሙ ለመናፍቅ መቅዶንዮስ ዘይቤ “መንፈስ ቅዱስ ሕፁፅ በመለኰቱ” ሎቱ ስብሐት። ወአዘዙነ ዝንቱ ኵሎሙ ሊቃነ ጳጳሳት። ወይብሉ “አዲ፦ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ እግዚእ ማሕየዊ ዘሠረፀ እም አብ፤ ንሥግድ ሎቱ ወንሰብሖ፤ ምስለ አብ ወወልድ ዘነበበነ በነብያት፤ ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንተ ላዕለ ኵሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት፤ ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢአት፤ ወንሴፎ ትንሣኤ ሙታን፥ ወሕይወተ ዘይመጽዕ ለዓለመ ለዓለም። አሜን።” 💐💐💐💐 ትርጉም 💐💐💐💐 ሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ሊቃነ ጳጳሳት ከሐዲ አርዮስን በጉባኤ ኒቅያ ክብር ይግባውና ጌታችንን 'ወልድ ፍጡር' ብሎ በካደ ጊዜ በደገኛው ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘመን ይሕንን የሃይማኖት ሥርዓት ሠሩልን። “ሁሉን በፈጠረ አንድ አምላክ በሆነ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን፤ ሰማይንና ምድርን በፈጠረ፥ የሚታየውንም የማይታየውንም፤ ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ ጋር በነበረ አንድ የአብ ልጅ በሚሆን በጌታችንና በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስም እናምናለን፤ ከብርሃን የተገኘ እውነተኛ ብርሃን፥ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ እውነተኛ አምላክ፤ የተወለደ እንጂ የተፈጠረ ያይደለ፤ በመለኰቱ ከአብ ጋር የተካከለ፤ ሁሉ በእርሱ እና ስለ እርሱ የሆነ፥ ከሆነውም ደግሞ አንዳች እንኳ ያለእርሱ የሆነ የሌለ፤ በሰማይም ከሆነው፥ በምድርም ከሆነው፤ እኛን ሰዎችን ስለመውደድ መድኃኒትን ይሆነን ዘንድ ከሰማይ የወረደው፥ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ፥ ደግሞም ስለእኛ ተሰቀለ፤ በጰንጠናዊው በጲላጦስ ዘመን ፍጹም መከራን ተቀበለ፤ ሞተ፥ ተቀበረ፥ በሦስተኛውም ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ፤ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ፥ ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በአባቱ በአብ ቀኝ ተቀመጠ፤ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ በምሥጋናና በክብር ይመጣል፤ ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም።” በጉባኤ ቊስጥንጥንያ መናፍቁን መቅዶንዮስ ክብር ይግባውና መንፈስ ቅዱስን 'በመለኰቱ ሕፁፅ' ነው ባለ ጊዜ እኒህ መቶ አምሳው ሊቃነ ጳጳሳት አውግዘው ከለዩት በኋላ በሃይማኖተ አበው ላይ ይህንን ጨምረዋል። “ዳግመኛም በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እናምናለን፤ እርሱ ጌታ የሆነ ሕይወትንም የሚሰጥ ነውና፤ ከአብና ከወልድ ጋር በአንድነት እንሠግድለታለን፥ እናመሰግነዋለንም፤ ከአብና ከወልድ ጋር በነብያት ቃል ተናግሮናልና፤ ሐዋርያት አባቶቻችን በሰበሰቧትና አንድ ባደረጓት በቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን፤ ስለ ኃጢአት ሥርየት በተሰጠችን በአንዲት ጥምቀትም እናምናለን፤ የሙታንንም ትንሣኤ ተስፋ እናደርጋለን፤ ለዘለዓለም በሚሆነው በሚመጣው ሕይወት አሜን።” 💐💐💐💐✝✝✝✝💐💐💐💐 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2

✨✨✨🌻🌻🌻 እውነተኛ ወዳጅ ወዳጅ መኾኑ የሚታወቀው ጓደኛውን መገሠጽ ሲችል ነው፡፡ ኹላችንም በየጊዜው ኃጢአት እንሠራለን፡፡ አብዛኞቻችን ደግሞ ኃጢአታችንን እንዳላየነው ኾነን ለማለፍ እንጥራለን፡፡ ለራሳችን ይቅርታ እንቸራለን፡፡ ወይም ምንም እንዳላጠፋ ሰው ለመምሰል እንሞክራለን፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሰዓት እውነታውን በትክክል እናይ ዘንድ ዓይናችንን የሚከፍት እውነተኛ ወዳጅ ያስፈልገናል፡፡ ✨✨🌻 አንተ ሆይ! እስኪ ራስህን መርምር፡፡ ጓደኛህ እውነታውን እንዲያይ ታደርጋለህ? ጓደኛህ ኃጢአት ሠርቶ ሲያበቃ ለራሱ ይቅርታ ሲያደርግ ይቅርታው ያደረገው ይቅርታ ትክክለኛ እንዳልኾነ እንዲያውቅ ታደርጓለህን? እንዲህ እውነታውን ስትነግረው ምናልባት ጓደኛህ አለአግባብ ሊቈጣህ ይችላል፡፡ ታዲያ ሲቈጣህ ለመታገሥ ዝግጁ ነህን? ወይስ ከዚህ በተቃራኒ የጓደኛህን ኃጢአት አይተህ እንዳላየህ ነው የምትኾነው? ጓደኛ ስንመርጥ ከእኛ ጋር እውነተኛ ወዳጅ ሊኾን የሚገባውን መኾን አለበት፤ ስንቈጣው እንኳን ቁጣችንን ታግሦ ስናጠፋ የሚያርመን ሊኾን ይገባል፡፡ እንደዚህ ካልኾነ ጓደኝነት ጥልቀት አይኖረውምና፤ ጓደኞች ነን መባባላችን ጥቅም የለውምና፡፡ ✨✨🌻 ልናውቀው የሚገባን ነገር ግን አለ፡፡ ጓደኛችን በሚያጠፋበት ሰዓት ተግሣጽ አስመስለን እንዲሁ ክብሩን በሚነካ መልኩ ልንናገረው አይገባንም፡፡ ተግሣጻችን ኹልጊዜ እውነቱን ብቻ እንጂ የተጋነነና ሌላውን መልካምነቱን የሚክድ መኾን የለበትም፡፡ ጥፋቱን ስንነግረው ኹልጊዜ በቀና ልብ እንደምንነግረው እርግጠኛ እንዲኾን ማድረግ አለብን፡፡ ይህን የምናደርገው ከፍቅራችን የተነሣ እንጂ ከቅናት ወይም ከንቀት እንዳልኾነ እንዲያውቅ ማድረግ አለብን፡፡ እውነተኛ ወዳጅነት ማለት ይህ ነውና፡፡ 📝ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 📚አምስቱ የንስሐ መንገዶች 📚ገጽ 100 ✨✨✨🌻🌻🌻 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2

+ የአንቺን መዓዛ ወደደ + አበባ በእሾህ መሃል እንደሚገኝ እመቤታችንም በእሾሆች በአይሁድ መካከል ያፈራች አበባ ነች፡፡ ሰሎሞን በመኃልይ 2፡2፤ “በእሾህ መካከል እንዳለ የሱፍ አበባ፥ እንዲሁ ወዳጄ በቈነጃጅት መካከል ናት፡፡"  እንዳለ። እመቤታችን በመከራና በኃጢአት በተሞላው ጨለማው ሕይወታችን መሃል የምታበራልን ነቢያት ከሩቅ አይተው የተጽናኑባት ማኅቶት፣ በሙሽሪት ቤተ-ክርስትያን ራስ ላይ የተቀጸለች አክሊል፣ ክረምት ሲያልፍ ተራሮችን በአበባ የሚያስጌጡ ሥሉስ ቅዱስ በኃጢአት ክረምት የጨቀየውን ልባችንን ያስጌጡባት ጽጌ ረዳ ነችና በአበባ እንመስላታለን። እናታችን ሔዋንስ እሾህ በሌለበት በገነት መካከል ተተከላ ሳለ መልካም ፍሬ ማፍራት አቅቷት ከገነት ተነቅላ ተጣለች፡፡ እመቤታችን ግን ኃጢአት በሞላበት በእሾኻማው ምድር መካከል ከገነት ዕጽዋት ሁሉ የምትበልጥ መልካም አበባ ሆና ተገኘች፡፡ አዳም በሔዋን ምክንያት የዕጸ ሕይወትን ፍሬ አጣ፣ በድንግል ማርያም ግን ከዕጸ ሕይወት የሚበልጥ አማናዊ ፍሬ ሕይወት ኢየሱስ ክርስቶስን አገኘ። ስለዚህም በማኅሌተ ጽጌ የእመቤታችንና የልጇን የኢየሱስ ክርስቶስን ስደት ስናስብ አበባ በመያዝ ቅድስት ቤተ-ክርስትያንን እየዞርን "ቀይና ነጭ አበባ ልጅሽን ታቅፈሽ ነይ" እያልን እንጠራታለን። አውግስጢን ስለዚህ " እግዚአብሔር ከሰማይ የወረደበት መሰላል የእመቤታችን ትኅትና ነው።" እንዳለ እመቤታችን ከአበቦች ሁሉ ልዩ መዓዛ ያላት አበባ ነችና መዓዛዋ ሰማያዊውያኑ ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ በፊቱ ሰማያዊ ዕጣን የሚያቀርቡለትን ጌታ በበረት ያስተኛ፣ ምድራዊውን የሰውን ባሕርይ በሰማያውያኑ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ያስቀመጠ ልዩ መዓዛ ነው፡፡ ንብ በአበባ መዓዛ እንደምትሳብ ንጉሥ በመዓዛ ድንግልናዋ ተሳበ፡፡ ንብ ከአበባ ቀስማ ማርን እንደምትሰራ እግዚአብሔር ወልድ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ተዋሓደ፡፡ ከአበባ ማር እንዲገኝ ለሚጠሩት ጥዑም ስም የሆነው፤ ዳዊትና ሰሎሞን በመዝሙር 119:103፤ “ቃልህ ለጕሮሮዬ ጣፋጭ ነው፤ ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ፡፡" "ወልድ እኁየ ቃልከ አዳም" እያሉ እየተቀባበሉ ያመሰገኑት የእግዚአብሔር ቃል ከእርሷ ሥጋ ሆኗልና ማርያም ፍሬ ሕይወትን ያፈራች ልዩ አበባ፣ ጥዑም መድኃኒት የተቀሰመባት አበባ፣ ኅብስተ ሕይወት ጵርስፎራን ያፈራች ልምልምት ተክል  ነች፡፡ ስለዚህም አባ ሕርያቆስ እንዲህ አለ: "በአማን ነጸረ እግዚአብሔር አብ እምሰማይ ምሥራቀ ወምዕራበ ሰሜነ ወደቡበ ወውስተ ኵሉ አጽናፍ፡፡ አስተንፈሰ ወአፄነወ፤ ወኢረከበ ዘከማኪ፤ ወሠምረ መዓዛ ዚአኪ፤ ወአፈቀረ ሥነኪ፤ ወፈነወ ኀቤኪ ወልዶ ዘያፈቅር፡፡ እግዚአብሔር አብ በሰማይ ሁኖ ምሥራቅንና ምዕራብን ሰሜንንና ደቡብን ዳርቻዎችንም ሁሉ በእውነት ተመለከተ፡፡ ተነፈሰ አሻተተም እንደ አንቺ ያለ አላገኘም፡ የአንቺን መዓዛ ወደደ ደም ግባትሽንም ወደደ የሚወደውን ልጁንም ወደአንቺ ሰደደ፡፡"                                 ~ቅዳሴ ማርያም የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2

🌹🌹🌹🌹🌼🌼🌼🌼🌹🌹🌹🌹 እመቤቴ ማርያም ሆይ እስከመቼ ድረስ በባዕዳን አገር ትኖሪያለሽ? ወደ አገርሽ ገሊላ አሁን ተመለሺ እንጂ ናዝራዊ ከሚሰኝ ሕፃን ልጅሽ ጋር ተመለሺ ዖዝያን ንጉሥ
🌹🌹🌹🌹🌼🌼🌼🌼🌹🌹🌹🌹
እመቤቴ ማርያም ሆይ እስከመቼ ድረስ በባዕዳን አገር ትኖሪያለሽ? ወደ አገርሽ ገሊላ አሁን ተመለሺ እንጂ ናዝራዊ ከሚሰኝ ሕፃን ልጅሽ ጋር ተመለሺ ዖዝያን ንጉሥ ስለ ቅዱሳን ክብር እንደተናገረው፥ አንድም በንጉሥ ዖዝያን ዘመን ስለ ቅዱሳን ክብር እንደተነገረው የልጅሽ የብቻ አባቱ ከሰማይ ሆኖ ከግብፅ ምድር እንደሚጠራው፥ እንደጠራው እንድትኖር ማርያም ወደ አባቷ አገር ወደ እሥራኤል ተመለሰች በምድረ ግብፅ በስደት አርባ ሁለት ወራትን ከኖረች በኋላ፥ ኖራ የጢሮስ ልጆች ስጦታውን አቅርበው ይሰግዱላታል፥ ይስገዱላት፥ እንደሰገዱላት እኛም እንዲሁ ስጦታዋ የሆነ ምስጋናዋን አቀረብንላት በእመቤታችን ከግብፅ ምድር መመለስም ልቦናችን ሐሴት አደረገች።
          የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2

"የአበባው ወቅት ባለቀ ጊዜ በማያልቅ ምስጋናሽ እያመሰገንኩሽ ከሥዕልሽ ፊት መቆምን አላፍርም። ማርያም! ተአምርሽ እንደሚያስረዳው ስምሽን መጥራት የወደቀውን ያነሳል በደለኛውንም ጻድቅ ያደርጋል።" — ማኅሌተ ጽጌ
የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2

የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በአርሲ ዞን በምእመናን ላይ በደረሰው እልቂት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገለጸ ! ሕዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በአርሲ ዞን በምእመናን ላይ በደረሰው እልቂት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገለጸ። የጉባኤው ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ፕሮፌሰር ጄሪ ፒሊ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በላኩት ደብዳቤ በአርሲ በኦርቶዶክሳውያን ላይ በደረሰው ግድያ ማዘናቸውን ገልጸዋል። Read more: https://www.oikoumene.org/news/wcc-extends-condolences-in-wake-of-attack-in-ethiopia የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2

በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ አባታዊ  ቡራኬና መመሪያ ሰጪነት የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በምሥራቅ አርሲ በተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ እና ጭፍጨፋ ተጎድቶ በሕይወት የተረፈውን ሕጻን ጎበኙ። ++++++++++++++ ህዳር 4 ቀን  2018 ዓ/ም(ብሕንሳ ሚዲያ ሆሣዕና ) ++++++++++++++ በምስራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክሳዊያን ላይ በደረሰው ጅምላ ጭፍጨፋ እናትቱን  (መላ ቤተሰቡን) በሞት ያጣውን ፣በተአምር ተርፎ በወላይታ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል የሕክምና እርዳታ እየተደረገለት የሚገኘውን ሕጻን ታምራት አውግቸዉ በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሀዲያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ በጳጳስ አባታዊ ቡራኬና መመሪያ ሰጪነት በሀገረስብከቱ ዋና ጸሐፊ ክቡር መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ወርቁ ተክሌ የተመራ ልዑካንን በመላክ እስከ ሆስፒታል ድረስ በመሄድ ጎብኝተዋል። በብፁዕነታቸው መመሪያ ሰጪነት የተላከው ልዑክ በአደጋው ቤተሰቦቻቸውን ያጡ ወገኖችን አጽናንተዉ ውድ ሕይወታቸውን ለተነጠቁትም እረፍተ ነፍስን ተመኝተዋል። በተጨማሪም በብፁዕነታቸው መመሪያ ሰጪነት  ለተጎጂው ሕጻን ጸሎት አድርሰው 50,250/ሃምሳ ሺህ ሁለት መቶ ሃምሳ ብር/ ገንዘብ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን  ክቡር መጋቤ ጥበብ ቀሲስ ወርቁ ተክሌ በሀገረስብከታችን የሚገኙ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። +++++++++++++++++ በአንቀጸ ሰማዕታት “ወእለሂ ይሰድድዎሙ በእንተ ሃይማኖት ወይጒይዩ እምሀገር ውስተ ሀገር በእንተ ትእዛዘ እግዚእነ ተወከፍዎሙ ወአዕርፍዎሙ። ወርብኅዎሙ፣ ወአክብርዎሙ ከመ ሰማዕታት/ ስለሃይማኖት የሚያሳድዷቸውን፣ ስለ ጌታችን ትእዛዝ ከአገር ወደ አገር የሚሸሹትን ተቀበሏቸው አሳርፏቸውም፣ ጥቀሟቸውም፣ እንደ ሰማዕታትም አድርጋችሁ አክብሯቸው/(ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 20 ቁ 749)” እንዳሉት ስለክርስቶስ መከራን የሚቀበሉትን እንደሰማዕታት አድርገን እንድናከብራቸው ታዝ ዘናል። እነርሱን የሚረዳ፣ የሚያከብር ብጹዕ ነውና። ስለዚህ እኛ ሰማዕት መሆን ባንችል እንኳን እነርሱን አክብረን መክበር ይጠበቅብናል። ++++++++++++++++ ድጋፍ ለማድረግ በህጻን ታምራት አውግቸው አጎት በአቶ ደበበ ተስፋዬ በተከፈተ አካውንት ድጋፍ ማድረግ ይችላሉ። የኢንባ1000073851867 አዋሽ ባንክ 01320191203800 አቢሲኒያ 42171182 ላይ ድጋፍ ያድርጉ። የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel2

"እጆቹ የነጹ፥ ልቡም ንጹሕ የሆነ፥ ነፍሱን ለከንቱ ያላነሣ፥ ለባልንጀራውም በሽንገላ ያልማለ። እርሱ ከእግዚአብሔር ዘንድ በረከትን ከመድኃኒቱ አምላክም ምሕረትን ይቀበላል።" መዝ. 23 (24)፥4-5

✨🌿🌹✨🌿🌹✨🌿🌹 "ተመየጢ እግዝእትየ ማርያም ሀገረኪ ናዝሬተ። ወኢትጐንድዪ በግብጽ ከመ ዘአልብኪ ቤተ። ዘያመጽእ አልቦ በላዕሌኪ ሁከተ። ለወልድኪ ዘየኃሥሦ ይእዜሰ ሞተ። በከመ ነገሮ መልአክ
✨🌿🌹✨🌿🌹✨🌿🌹
"ተመየጢ እግዝእትየ ማርያም ሀገረኪ ናዝሬተ። ወኢትጐንድዪ በግብጽ ከመ ዘአልብኪ ቤተ። ዘያመጽእ አልቦ በላዕሌኪ ሁከተ። ለወልድኪ ዘየኃሥሦ ይእዜሰ ሞተ። በከመ ነገሮ መልአክ ለዮሴፍ ብሥራተ።"
ትርጉም፦ "እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ መልአከ እግዚአብሔር ለአረጋዊ ጻድቅ ቅዱስ ዮሴፍ እንደነገረው በአንቺ ላይ መከራን የሚያመጣው ጠፍቷልና ልጅሽን የሚፈልገውም ጨካኝ ኄሮድስ እነሆ ሞቷልና ቤት እንደሌለውም በግብፅ አትዘግይ። ወደ ሀገርሽ ናዝሬትም ተመለሺ።" ሰቆቃወ ድንግል ✨🌿🌹✨🌿🌹✨🌿🌹✨🌿🌹

“የእግዚአብሔር ቃል የመላእክት ምግብ ነው፡፡ ይኽም ነፍስን የሚመግብ ነው፡፡ እግዚአብሔርን የተጠማች ነፍስ ምግቧ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሔር ቃል ነፍሱን የሚጠግን (የሚመግብ) ከኾ
“የእግዚአብሔር ቃል የመላእክት ምግብ ነው፡፡ ይኽም ነፍስን የሚመግብ ነው፡፡ እግዚአብሔርን የተጠማች ነፍስ ምግቧ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ሰው በእግዚአብሔር ቃል ነፍሱን የሚጠግን (የሚመግብ) ከኾነ በጎነትን በመረዳት ይሞላል፡፡ ክፋትንም ይጸየፋል፡፡”      ሊቁ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ⚜️⚜️⚜️ ⚜️⚜️⚜️ ⚜️⚜️⚜️

መንፈሳዊ ትምህርቱ ተጀምሯል! በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት የሚሠጠው አዲሱ ስርአተ ትምህርት ለመማር የተመዘገባችሉ ትምህርቱ የተጀመረ ስለሆነ ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ
+1
መንፈሳዊ ትምህርቱ ተጀምሯል! በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት የሚሠጠው አዲሱ ስርአተ ትምህርት ለመማር የተመዘገባችሉ ትምህርቱ የተጀመረ ስለሆነ ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ጥዋት ከ12:00-12:45 ድረስ እየተገኛችሁ ትምህርቱን እንድትከታተሉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን። ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት

እኛስ ነፍሳችን ከሥጋችን አንድ ሆና እንድትኖር ፈጽመን እናውቃለን ግን ነፍሱን ፈፅሞ ያየ ማን ነው? ከሥጋ ጋር የተዋሐደች ነፍሱን ልይ ብሎ በዓይነ ሥጋ ያያትስ ማነው? ይህንን ባልን ጊዜ የነፍስን ከሥጋ ተዋህዶ መኖርን አይምሰላችሁ የምታውቅ ለባዊት ነፍስ ከሥጋችን ጋር አንድ ሆና እንዳለች አውቀን እናምናለን እንጂ ተግቶ ተፈጥሮዋን የመረመረ ከሥጋውም ተዋህዳ ያለች ነፍሱን ያየ ማን ነው? አኗኗራስ እንደምን እንደሆነ ያወቀ ማነው? ነገር ግን ነፍስ ተዋህዳን እንዳለች ይህን ብቻ እናውቃለን በባሕርያችን ያለወቅን ምሥጢሩንም ያልተረዳን ወልድ ከአብ እንደምን እንደተወለደ እናውቅ ዘንድ እንዴት ይቻለናል? እንዲሁ እንደምን ይሆናል? ሳንል ቃል ከአብ እንደተወለደ ዐውቀን እንመን እንጂ። "ሃይማኖተ አበው ዘጎርጎርዮስ "

"ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይሆናል?" ~ ሉቃስ ፩ ፥ ፵፫
+8
"ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይሆናል?"                   ~ ሉቃስ ፩ ፥ ፵፫

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሥርዓተ ትምህርት መሠረት ያስተማራቸው ከ11,800 በላይ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ብፁዕ አቡነ ቀሌምጦስ የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ት
+6
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሥርዓተ ትምህርት መሠረት ያስተማራቸው ከ11,800 በላይ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት  ብፁዕ አቡነ ቀሌምጦስ የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት  ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀድያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ከፍተኛ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በርካታ ታዳሚዎች በተገኙበት ለ5ኛ ጊዜ በሚሊኒየም አደራሽ እያስመረቀ ይገኛል።

"ኅብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወፀዓድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር፡፡ ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር፡፡ ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ ሥሙር፡፡ አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር፡፡ ከመ በሕፅንኪ ያሰምክ
"ኅብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወፀዓድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር፡፡ ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር፡፡ ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ ሥሙር፡፡ አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር፡፡ ከመ በሕፅንኪ ያሰምክ ፍቁር፡፡" ትርጉም፦ "የሰማይና የምድር ንግሥት ማርያም ሆይ የብር ዝጕርጕር፣ የነጭና የቀይ ድብልቅ መልክ እንዳለው ጌጥ ንጹሕ የሆነ፣ (ሐሰት የሌለበት) ተአምርሽ፣ በወርቅ አምሳል የተዘጋጀ ሆኖ ያማረና የተወደደ ማኅሌተ ጽጌ የተባለ ምስጋና እነሆ ተፈጸመ፣ የተወደደ ልጅሽ በእቅፍሽ ውስጥ እንዳለ ይህንን የማኅሌተ ጽጌ ምስጋናን ተቀብለሽ ወደእሱ አድርሺ።" (ማኅሌተ ጽጌ)